ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 525 подписчиков, занимая 8 336 место в категории Технологии и приложения и 2 179 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 525 подписчиков.

Согласно последним данным от 07 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 5, а за последние 24 часа — -2, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 28.59%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.03% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 440 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 489 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 10.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 08 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 525
Подписчики
-224 часа
-57 дней
+530 день
Архив постов
የአሰላ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ …………………………///////…………………… 100 ሜጋ ዋት እንዲያመነጭ ታስቦ በአርሲ ዞን ሂጦሳ ወረዳ ኢተያ የሚገነባው
+2
የአሰላ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ …………………………///////…………………… 100 ሜጋ ዋት እንዲያመነጭ ታስቦ በአርሲ ዞን ሂጦሳ ወረዳ ኢተያ የሚገነባውን የአሰላ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ለማስጀመር የሚያስችል ስምምነት ተፈርሟል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በስምምነት ሰነዱ ላይ ፊርማቸውን ካኖሩ በኋላ እንደገለፁት የአሰላ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ ከተገነቡት የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች መካከል አነስተኛ ቁጥር ያላቸው ተርባይኖችን በመጠቀም ከፍተኛ ኤነርጂ የሚያመርት መሆኑ የተለየ ያደርገዋል፡፡ እንደ አቶ አሸብር ገለፃ በፕሮጀክቱ እያንዳንዳቸው 3 ነጥብ 45 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው 29 ተርባይኖች ይተከላሉ፡፡ ለንፋስ ኃይል ማመንጫው የሚውለውን ገንዘብ የዴንማርክ መንግስት በስጦታና በብድር እንደሚሸፍን፣ ለ20 ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና እንደሚሰጥና ለአምስት ዓመት የኦፕሬሽንና የጥገና ስራ እንደሚሰራ ስምምነት ላይ መደረሱን ስራ አስፈፃሚው ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱን በተቋራጭነት የዴንማርክና ስፔን ጥምር ኩባንያ የሆነው ሲመንስ ጋሜሳ ሪኒውኤብል ኢነርጂ ሲገነባው የዴንማርኩ ኮዊ ደግሞ በአማካሪነት እንዲሰራ ተመርጧል፡፡ የፊርማ ስነስርዓቱ ተዋዋይ ወገኖች በአካል ሳይገናኙ በቨርቹዋል የተከናወነ ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ከአዲስ አበባ ፤ የዴንማርክና ስፔን ጥምር ኩባንያ የሆነው ሲመንስ ጋሜሳ ሪኒውኤብል ኢነርጂ ደግሞ ከአውሮፓ በመሆን ስካን በተደረገው የስምምነት ሰነድ ላይ ፊርማቸውን አኑረዋል፡፡ በ145 ሚሊየን ዩሮ የሚገነባውን የአሰላ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ለማጠናቀቅ 25 ወራት ተይዘውለታል፡፡

የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ሠራተኞች ለአካባቢው ነዋሪዎች ድጋፍ አደረጉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሰራተኞች የኮረና ቫይርስ ወረርሽኝን ለመግታት የሚደረ
+4
የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ሠራተኞች ለአካባቢው ነዋሪዎች ድጋፍ አደረጉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሰራተኞች የኮረና ቫይርስ ወረርሽኝን ለመግታት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ በኃይል ማመንጫው አካባቢ ለሚኖሩ 30 አቅመ ደካማ አባወራዎች የምግብና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ፡፡ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው የኦፕሬሽን ክፍል ኃላፊ ወ/ሮ አይናለም ወ/ሚካኤል እንደተናገሩት የኃይል ማመንጫው 59 ሠራተኞች ገንዘብ በማዋጣት ለ30 አቅመ ደካማ አባወራዎች ወይም ለ120 የቤተሰብ አባላት የሚሆን 15 ሺህ ብር የሚገመት የምግብ እና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርገዋል፡፡ በመልካ አዳማ ቀበሌ ቀጣና አሮጌ አዳማ ውስጥ ለሚገኙት አባወራዎች ለእያንዳንዱ ቤተሰብ 5 ኪሎ ዱቄት፣1 ሊትር ዘይት፣3 እሽግ ፓስታ፣ 4 ኪሎ መኮሮኒ፣አንድ ኪሎ ጨው፣1 ሊትር ፈሳሽ ሳሙና እና 6 ላይፍ ቦይ ሳሙና ድጋፍ መደረጉን ኃላፊዋ ገልጸዋል፡፡ ሚያዚያ 22 ቀን 2012 ዓ.ም.

ከሌሎች ምንጮች……. የአሜሪካው ሲዲሲ ተጨማሪ ይፋ ያደረጋቸው 6 የኮሮናቫይረስ ምልክቶች ***************************** በኮሮናቫይረስ የተያዘ ሰው 6 ተጨማሪ ምልክቶች ሊኖሩት እንደሚ
ከሌሎች ምንጮች……. የአሜሪካው ሲዲሲ ተጨማሪ ይፋ ያደረጋቸው 6 የኮሮናቫይረስ ምልክቶች ***************************** በኮሮናቫይረስ የተያዘ ሰው 6 ተጨማሪ ምልክቶች ሊኖሩት እንደሚችል የአሜሪካው የበሽታ መከላከልና መቆጣጠሪያ ማዕከል (ሲዲሲ) ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህም መሰረት አንድ በኮሮናቫይረስ የተያዘ ሰው ከዚህ ቀደም ከታወቁትና በዓለም ጤና ድርጅት ከተገለፁት ምልክትች በተጨማሪ • በተደጋጋሚ ብርድ ብርድ ማለት • ማንቀጥቀጥ • የጡንቻ ህመም • የጉሮሮ መቁሰል • ራስ ምታት • ድንገተኛ የመቅመስና የማሽተት ፍላጎት ማጣት ሊያሳይ ይችላል ብሏል፡፡ በከሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው ከ2 እስከ 14 ባሉት ቀናት መካከል እነዚህን ምልክቶች ሊያሳይ እንደሚችል የአሜሪካው የበሽታ መከላከልና መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታውቀዋል፡፡ ኢቢሲ ሲ.ኤን.ቢ.ሲን ጠቅሶ እንደዘገበው

ለአምቦ ከተማና አካባቢው ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሊተከል ነው ………………/////……………….. የአምቦ ከተማና የአካባቢውን የኃይል አቅርቦት ችግር በጊዜያዊነት የሚፈታ ተንቀሳቃሽ የኃይል ማ
+2
ለአምቦ ከተማና አካባቢው ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሊተከል ነው ………………/////……………….. የአምቦ ከተማና የአካባቢውን የኃይል አቅርቦት ችግር በጊዜያዊነት የሚፈታ ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሊተከል መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስፈፃሚው አቶ ሐብታሙ ውቤ እንዳስታወቁት በጉደር ከተማ በጊዜያዊነት የሚተከለው የማከፋፈያ ጣቢያ ችግሩን በዘላቂነት የሚፈታ ማከፋፈያ ጣቢያ እስኪገነባ ድረስ የሚቆይ ነው፡፡ ቀደም ሲል ሆርማት ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ተገንብቶ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ነባሩ የማከፋፈያ ጣቢያ በርካታ የኃይል ፈላጊዎችን ደንበኞችን ሲያስተናግድ ቆይቷል፡፡ እንደ አቶ ሀብታሙ ገለፃ ጣቢያው በሙሉ አቅሙ ኃይል በመሸከሙ በአምቦ ከተማና በአካባቢዋ ከፍተኛ የኃይል መቆራረጥ ከማስከተሉም ሌላ እንደ ኢትዮ ቴሌኮም ያሉ ደንበኞችም አገልግሎት በአግባቡ እንዳይሰጡ አድርጓቸዋል፡፡ በመሆኑም በሁለት ወራት ውስጥ ተተክሎ አገልግሎት እንደሚሰጥ የሚጠበቀው ጊዜያዊ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የኃይል መቆራረጥን በማስቀረት ለአምቦና አካባቢዋ ትልቅ እፎይታን ይፈጥራል ብለዋል፡፡ ተንቀሳቃሽ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው በዛሬው ዕለት አምቦ ከተማ ደርሷል፡፡ በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ተመሳሳይ የኃይል መቆራረጥ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ጊዜያዊና ዘላቂ መፍትሔዎች በመተግበር ላይ መሆናቸውን አቶ ሐብታሙ ገልፀዋል፡፡ ሚያዚያ 21 ቀን 2012 ዓ.ም.

Ethiopian Electric Power ከሌሎች ምንጮች…. የሕዳሴው ግድብ በመጪው ክረምት ውሃ መያዝ የሚችልበት የግንባታ ደረጃ ላይ መድረሱ ተገለጸ *********************************** ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ውሃ መያዝ የሚችልበት የግንባታ ደረጃ ላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በዓባይ ወንዝ ላይ እየተገነባ ያለው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለት ተርባይኖች በቀጣዩ ዓመት ኃይል እንዲያመነጩ ለማድረግ በመጪው ክረምት ግድቡ ውሃ መያዝ ይጀምራል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለኢዜአ እንዳሉት በአሁን ጊዜ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ የዓለም ብሎም የኢትዮጵያ ስጋት ቢሆንም የግድቡ ግንባታ ለአፍታም አልተቋረጠም። የግንባታ ሥራው የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ባወጣው የጥንቃቄ መመሪያ መሰረት እየተከናወነ ነው ብለዋል። የግድቡ ሁለት ተርባይኖች ኃይል ማመንጨት የሚያስችላቸውን ውሃ በመጪው ክረምት ለመያዝ የሚቻልበት የግንባታ ደረጃ ላይ ለማድረስ በፍጥነት እየተከናወነ ነው”። ግድቡ ኃይል እንዲያመነጭ ከታሰበው ጊዜ በላይ ከተራዘመ አገሪቷ በየዓመቱ ማግኘት ያለባትን ገቢ እንድታጣ ከማድረግ ባለፈ ለተጨማሪ የግንባታ ወጪ ትጋለጣለች ያሉት አቶ ሞገስ፤ አላስፈላጊ ወጪን ለማስቀረትም በዕቅዱ መሰረት የውሃ ሙሌት ሥራው ”ከዘንድሮ ክረምት አያልፍም” ብለዋል። የግድቡ ግንባታው እየተከናወነ ውሃው መያዝ የሚችለውን ያህል መያዝ ካልቻለ ተጨማሪ አንድ ዓመት ሃይል ሳያመነጭ ሊያልፍ ይችላል ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ክረምት ላይ ውሃ መያዝ ከቻለ ግን ከሚቀጥለው ዓመት አጋማሽ በኋላ ሁለቱ ኃይል ቀድመው የሚያመነጩ ዩኒቶችን በመፈተሽ ስራ እንዲጀምሩ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ በአሁን ጊዜ የግድቡ የብረታ ብረት ሥራ 26 በመቶ ላይ ደርሷል።“ይህ አሀዝ የዛሬ ሁለት ዓመት ከነበረው ጋር ተመሳሳይ ቢሆንም በዓለምአቀፍ ጥራትና ግብዓት እንደ አዲስ እርማት ተደርጎለት በአዲስ የሚተኩት ግብዐቶች ተቀይረው ግንባታው እየተከናወነ በመሆኑ የተፈጠረ ነው” ብለዋል። የደን ምንጣሮን ጨምሮ ለግድቡ ውሃ ሙሌት አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል። የብሔራዊ ኤክስፐርቶች ፓናል ሰብሳቢና የሦስትዮሽ ድርድር ኮሚቴ አባል ኢንጂነር ጌዲዮን አስፋው በበኩላቸው እ.ኤ.አ በ2015 ኢትዮጵያ፣ ግብጽና ሱዳን በመሪዎቻቸው አማካኝነት ካርቱም ላይ በተፈራረሙት የመርህ ስምምነት በሕዳሴው ግድብ ውሃ አሞላል ላይ የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል ነው ያሉት። ይሁንና ግብጽ ግድቡ ውሃ መያዝ የሚያስችለው ደረጃ ላይ መድረሱን እርግጠኛ በመሆኗ የተለያዩ ምክንያቶችን በመፍጠር የመርህ ስምምነቱን ለመጣስ ሙከራ በማድረግ ላይ ናት ያሉት ኢንጂነር ጌዲዮን፤ ግብጽና ሱዳን የኢትዮጵያንና ሌሎች የዓባይ ተፋሰስ አገሮችን መብትና ጥቅም በጣሰ መልኩ የወንዙን ውሃ በብቸኝነት ሲጠቀሙ እንደነበርም አታውሰዋል። ግድቡ 65 ሜትር ቁመት ላይ ሲደርስ የመጀመሪያ ዙር ውሃ ለመሙላት ዕቅድ መያዙን ገልጸው ይህም በተያዘው ዕቅድ መሰረት በዘንድሮ የዝናብ ወቅት እንደሚከናወን ተናግረዋል። ”ከግድቡ መሰረት ወደ 65 ሜትር የውሃ ቁመት ከፍ ይላል የሚይዘው ውሃ አራት ነጥብ ዘጠኝ ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ይሆናል።በሁለተኛው ዓመት ላይ ተጨማሪ 13 ነጥብ አምስት ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ ግድቡ ይይዛል። በዚህ ጊዜ የውሃው ቁመት 595 ላይ ወይም ከግድቡ መሰረት 95 ሜትር ከፍ ብሎ ይገኛል ማለት ነው። በዚያን ወቅት ተጨማሪዎቹ 11 አሸንዳዎች ውሃ ማስተላለፍ ይጀምራሉ” ብለዋል ኢንጂነር ጌዲዮን። እንደ ኢንጂነር ጌድዮን ገለጻ የውሃ ሙሌት ስርዓቱ በየዓመቱ ደረጃ በደረጃ የሚከናወን ይሆናል። ይህም የግድቡ ተርባይኖች ሙሉ ለሙሉ ኃይል ማመንጨት የሚችሉበት ቁመት ላይ እስኪደርሱ ውሃው ከአምስት እስከ ስድስት ዓመት ይሞላል ብለዋል። እንደ ኢዜአ ዘገባ የግድቡን ውሃ ሙሌት በሁለት ዓመት ማከናወን ቢቻልም የግድቡን ደህንነትና የታችኞቹ ተፋሰስ አገሮች ላይ ጉልህ ጉዳት ላለማድረስ ደረጃ በደረጃ የመሙላት እቅድ መያዙንም ኢንጅነር ጌድዮን ገልጸዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ አፈፃፀም በአሁኑ ወቅት 73 በመቶ መድረሱን ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ከኢቢሲ የተገኘ የኢዜአ ዘገባ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተግባርና ኃላፊነት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ለማቋቋም በወጣው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 381/2008 እንደተሻሻለው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተግባርና ኃላፊነት እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፡፡  የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ሥራዎች የአዋጭነት ጥናት፣ የንድፍ እና ቅየሳ ሥራዎችን ማከናወን፣ እንደአስፈላጊነቱ እነዚህኑ ሥራዎች በአማካሪዎች ማሰራት፤  የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ መስመሮችና ጣቢያዎች የግንባታና የማሻሻያ ሥራዎች ማከናወን፤ እንደአስፈላጊነቱ እነዚህኑ በሥራ ተቋራጭ ማሰራት፤  የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ እና 132 ኪ.ቮ እና ከዛ በላይ መጠን ያላቸውን ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን እንዲሁም የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎችን ማከናወን፤  እንደአስፈላጊነቱ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮችን ሊዝ ማድረግ፤  የኤሌክትሪክ ኃይል በጅምላ መሸጥ፤  የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር የሚያወጣውን መመሪያና የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት በማድረግ ቦንድ መሸጥና በዋስትና ማስያዝ እና ከአገር ውስጥና ከውጭ የገንዘብ ምንጮች ጋር የብድር ውል መደራደርና መፈራረም፤  ዓላማውን ከግብ ለማድረስ የሚረዱ ሌሎች ተዛማጅ ሥራዎችን መሥራት የሚሉት ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌትሪክ ኃይል የኢትዮጵያ ኤሌክሪክ ኃይል ከምስረታው ጀምሮ በተለያዩ ስያሜዎች አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ከጀርመን መንግስት በ1890 ዓ.ም. ለአፄ ምኒልክ በተበረከተ የናፍጣ ጄኔሬተር
የኢትዮጵያ ኤሌትሪክ ኃይል የኢትዮጵያ ኤሌክሪክ ኃይል ከምስረታው ጀምሮ በተለያዩ ስያሜዎች አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ከጀርመን መንግስት በ1890 ዓ.ም. ለአፄ ምኒልክ በተበረከተ የናፍጣ ጄኔሬተር በቤተ መንግስት አገልግሎት መስጠት የጀመረው ይህ ተቋም ቀስ በቀስ አገልግሎቱ እየተስፋፋ ሲመጣና ተጠቃሚ የሚሆኑ ከተሞች ቁጥር እያደገ ሲመጣ በ1940 ዓ.ም. የኃይል ዘርፉን የሚያተዳድር ተቋም የሸዋ መብራት ኃይል በሚል ስያሜ ራሱን ችሎ ተቋቋመ፡፡ ከዓመታት በኋላም ይህ ተቋም እንደገና በ1948 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ መብራት ኃይል ባለስልጣን ወይም በእንግሊዝኛ ምህፃሩ (EELPA) ተብሎ ህጋዊ ሰውነት በማግኘት በቻርተር ተቋቋመ፡፡ መንግስት ለኃይል ዘርፉ በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት በ1989 ዓ.ም. ተቋሙን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮፖሬሽን በሚል ስያሜ እንደ አዲሰ እንዲቋቋም አደረገ፡፡ የኮፖሬሽኑ እንቅስቃሴ እየሰፋ በመሄዱ፣ ዘርፉም እያደገ በመምጣቱ መንግስት የኃይል ልማት ዘርፉን ይበልጥ ለማሳደግ፣ ለማዘመንንና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆን ለማስቻል ተቋሙን ወደ ሁለት ተቋም እንዲከፈል አደረገ፡፡ እነዚህ ተቋማት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ናቸው፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለደንበኞች የኤሌክትሪክ አገልግሎት የመስጠት፤ የኤሌክትሪክ ጥገና አገልግሎት ተግባራትን የማከናወን፤ የተገለገሉበትን የኤሌክትሪክ ፍጆታ ስሌት የማንበብ፣ ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሒሳብን የማስከፈልና ከኤሌክትሪክ ሥርጭት ተያያዥነት ያላቸው ስራዎች ሲሰራ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ደግሞ ከኃይል ማመንጨትና የመነጨውን ኃይል ከማስተላለፍ ጋር የተያያዙ ተግባራትን ያከናውናል፡፡

የአላማጣ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ተጠገነ ******************** በአላማጣ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በትራንፎርመር ላይ የደረሰው ብልሽት ተጠግኖ ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኃ
የአላማጣ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ተጠገነ ******************** በአላማጣ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በትራንፎርመር ላይ የደረሰው ብልሽት ተጠግኖ ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኃይል ማግኘት ጀመሩ፡፡ በማከፋፈያ ጣቢያው ትራንስፎርመር ላይ የደረሰው ችግር በአላማጣ፣ ላሊበላ፣ ሰቆጣ እና ማይጨው ከተሞችና አካባቢያቸው ለቀናት የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲቋረጥ አድርጎ ቆየቷል፡፡ ችግሩን ለመቅረፍ የጥገና ባለሙያዎቻችን በሶስት ፈረቃ ለሃያ አራት ሰዓታት ጥረት ሲያደረጉ የቆዩ ሲሆን የአላማጣ ከተማ ወዲያውኑ መብራት እንዲያገኝ ተደርጓል፡፡ የላሊበላ፣ ሰቆጣና ማይጨው እንዲሁም በአቅራቢያዎቹ የሚገኙ ከተሞች ደግሞ ዛሬ ኤሌክትሪክ አግኝተዋል፡፡ የገጠመንን ችግር ከግምት ውስጥ በማስገባት በትዕግስት ለጠበቃችሁን ደንበኞቻችን የኢትየጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምስጋናውን ያቀርባል፡፡ የተጠገነው ትራንፎርመር እስከ ሰማኒያ በመቶ ኃይል የመሸከም አቅም ያለው በመሆኑ የኃይል ጭነት በሚበዛባቸው ሠዓታት ከተሞቹ በፈረቃ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ ስለሚደረግ የአካባቢው ነዋሪዎች ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ እናሳስባለን፡፡ ችግሩን ሙሉ በሙሉ ለመቅረፍ እስከ ሁለት ሳምንት ጊዜ ሊወስድ ይችላል። ሚያዝያ 18 ቀን 2012 ዓ.ም

ተቋሙ ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ግብዓቶችን በስጦታ አገኘ ..............//////......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከቻይናው ሲኖ ሃይድሮ - ፓወር ቻይና ለኮሮና መከላከል የሚያግዙ
+2
ተቋሙ ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ግብዓቶችን በስጦታ አገኘ ..............//////......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከቻይናው ሲኖ ሃይድሮ - ፓወር ቻይና ለኮሮና መከላከል የሚያግዙ ግብዐቶች በስጦታ ተበረከተለት። ስጦታውን ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ያበረከቱት የሲኖ ሃይድሮ ተወካይ ሚስተር ቲያን ሆንግጁን እና የፕሮጀክት ሥራ አስኪያጁ ዩ ሚንጉሂ ናቸው። ድርጅቱ ያበረከተው ስጦታ ሶስት ሺህ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብልና አርባ ሊትር የእጅ ንፅህና መጠበቂያ ሳኒታይዘር ነው። ስጦታውን ከተረከቡ በኋላ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ድርጅቱ ያበረከተው ስጦታ ለሁለቱ ተቋማት አጋርነት ማሳያ ነው። ስጦታው በዓለማችን እና በሀገራችን የተከሰተውን የኮሮና ወረርሽኝ በተቋም ደረጃ ለመከላከል የሚያግዝ በመሆኑ ምስጋናም አቅርበዋል። የሲኖ ሃይድሮ - ፓወር ቻይና ተወካዮችም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር የረጅም ጊዜ ግንኙነት እንዳላቸው ጠቅሰው ሁለተኛ ዙር የመከላከያ ግብዐቶችን ለመለገስም ቃል ገብተዋል። ሲኖ ሃይድሮ - ፓወር ቻይና ከተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግንባታ ጀምሮ ለረጅም ዓመታት የተለያዩ የኃይል ማመንጫ ግንባታዎች ውስጥ በመሳተፍ መልካም ግንኙነት ያለው ተቋም ነው። ሚያዚያ 17 ቀን 2012 ዓ/ም

ኮሮና ለመግታት፣ ግድቡንም ለማጠናቀቅ የሚተጋው የህዳሴ ሠራዊት ******************************** ኢ.ፕ. ድ. ወረሃ ሚያዝያ ለወትሮው በኢትዮጵያ ሞቃታማው ጊዜ ተደርጎ ይቆጠራል።የሕዳሴው ግድብ በሚገነባበት አካባቢ ያለው ተፈጥሯዊ አቀማመጥ ደግሞ የሙቀቱን ሁኔታ ቃጠሎ ያደርገዋል፤ ላብ በጆሮ ግንድ ብቻ ሳይሆን በሠራ አካላት እንዲንቀረቆር ያስገድዳል። እነዚህን ሁኔታዎች ተቋቁመው በሕዳሴው ግድብ ግንባታ የተሰማሩና ዓመታትን ያስቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ቁጥራቸው ቀላል አይደለም።አሁን ላይ እነዚህ ዜጎች እንደወርቅ በሙቀት ብቻ አይፈተኑም፤ የኮሮና ወረርሽኝን በመዋጋትም ጭምር እንጂ።ከእነዚህ ነባራዊ ሁኔታዎች በመነሳት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል ምን እየተሠራ ነው? ስንል የፕሮጀክቱን ኃላፊዎች ጠየቅን፡፡ የሕዳሴው ግድብ ሥራአስኪያጂ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ እንዳሉት፤ በአገሪቱ ላይ ያንዣበበው የወረርሽኝ ስጋት በእነሱም ዘንድ መኖሩን ገልጸዋል።ዋናው የኮሮና ቫይረስ ማሸነፊያ መንገድ ጥንቃቄ በማድረግ መከላከል መሆኑን አስታውሰው፣በቅንጅት ሰፊ ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛሉ ብለዋል።ማንኛውም አካል መግባትና መውጣት የሚችለው በለይቶ ማቆያ ለ14 ቀናት በመቆየት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ባለሙያዎችንና ለመከላከል የሚያስፈልጉ ግብዓቶች በክልሉ ጤና ቢሮ በኩል እንደሚቀርቡላቸውና የሠራተኞች ጤና እንዲጠበቅ አስፈላጊው ተግባር እየተከናወነ ስለመሆኑም ተናግረዋል። የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ፍሬሕይወት አበበ በበኩላቸው፤የሕዳሴው ግድብ ፕሮጀክት ሠራተኞች ከኮሮና ወረርሽኝ መጠበቅ እንዲችሉ ከፌዴራል እስከ ክልልና ሕዳሴው ግድብ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ድረስ በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።ይሄን ጉዳይ የሚመራ ራሱን የቻለ ግብረኃይል የተቋቋመ ሲሆን በቅርበት እየተገኘ ምቹ ሁኔታዎችን ይፈጥራል፤ ለመከላከል የሚያግዙ አስፈላጊ ተግባራትንም ያከናውናል፡፡ ለተጨማሪ https://www.press.et/Ama/?p=30979

የታላቁ ኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም 73 በመቶ ደረሰ .............///////............. የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም 73 በመቶ መድረሱን የግድቡ
የታላቁ ኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም 73 በመቶ ደረሰ .............///////............. የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም 73 በመቶ መድረሱን የግድቡ ግንባታ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ እንደገለፁት የፕሮጀክቱ የሲቪል ስራዎች አፈፃፀም 87 በመቶ፣ የብረታ ብረት ስራዎች አፈፃፀም ደግሞ 26 በመቶ ደርሷል። ቅድሚያ ኃይል ያመነጫሉ ተብሎ የታቀዱት ሁለት ዩኒቶች የብረታ ብረት ስራም በአብዛኛው የተጠናቀቀ ሲሆን የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸምም 73 በመቶ መድረሱን ገልፀዋል፡፡ ግድቡ በሚቀጥለው ዓመት መጨረሻ ላይ ኃይል ማመንጨት እንዲችል በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የገለጹት ኢንጂነር ክፍሌ፣ የውሃ ሙሊቱ በመጪው ክረምት ለመጀመር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ተናግረዋል። ሚያዚያ 16 ቀን 2012 ዓ/ም

ለመላው #የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለታላቁ ረመዳን ፆም በሠላም አደረሳችሁ!!! መልካም #የፆምና #የሶላት ወር ይሁንልላችሁ! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
ለመላው #የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለታላቁ ረመዳን ፆም በሠላም አደረሳችሁ!!! መልካም #የፆምና #የሶላት ወር ይሁንልላችሁ! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

በአላማጣ፣ ማይጨው፣ ላሊበላ፣ ቆቦ፣ ሰቆጣና በአካባቢው የሚገኙ ከተሞች ኃይል ተቋርጧል፡፡ በአላማጣ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በትራንፎርመር ላይ ባጋጠመ ችግር ከማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል የሚያገኙ የአላማ
በአላማጣ፣ ማይጨው፣ ላሊበላ፣ ቆቦ፣ ሰቆጣና በአካባቢው የሚገኙ ከተሞች ኃይል ተቋርጧል፡፡ በአላማጣ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በትራንፎርመር ላይ ባጋጠመ ችግር ከማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል የሚያገኙ የአላማጣ፣ ማይጨው፣ ላሊበላ፣ ቆቦ፣ ሰቆጣና በአካባቢው የሚገኙ ከተሞች ኃይል ተቋርጦባቸዋል፡፡ በትራንስፎርመሩ ላይ የገጠመውን ብልሽት ለማስተካከል በሰሜን ሪጅን የሚገኙ የጥገና ሠራተኞቻችን ርብርብ በማድረግ ላይ ቢሆኑም ብልሽቱን በፍጥነት በመጠገን ኃይል እንዲሰጥ ማድረግ አልተቻለም፡፡ በመሆኑም ለትራንስፎርመሩ አስፈላጊ ዕቃዎችን በመቀየር ወደስራ ለማስገባት በርካታ ቀናት የሚፈልግ በመሆኑ ጊዜያዊ መፍትሔ ለመስጠት ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ በዚህ መሰረት የአላማጣ ከተማና አካባቢው ኃይል እንዲያገኝ 15 ኪሎ ቮልት ትራንስፎርመር የመተካት ስራ ተጀምሯል፡፡ በተመሳሳይም የላሊበላ፣ ሰቆጣና ማይጨው ከተሞች ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ በማከፋፈያ ጣቢያው የማስፋፊያ ስራ ለመስራት የተዘጋጀ ትራንስፎርመር በመትከል ችግሩን ለመቅረፍ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው፡፡ ኃይል የተቋረጠባቸውን አካባቢዎች ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ በአማካይ አምስት ቀን የሚፈልግ በመሆኑ ህብረተሰቡን ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ በመጠየቅ ችግሩ እስኪቀረፍ በትዕግስት እንዲጠብቀን ጥሪ እናቀርባለን፡፡ ሚያዝያ 14 ቀን 2012 ዓ.ም

የህክምና ባለሙያ ነዎት? ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ከሆነ ዕድሉን እንዲጠቀሙበት ተጋብዘዋል፡፡ የህክምና ባለሙያ ካልሆኑ ደግሞ ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት ዕድሉን እንዲጠቀሙበት ይጋብዟቸው፡፡ መልካም ዕድል ተመኝተናል፡፡

የቡታጅራ - ቡኢ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ሥራ ጀመረ ....................///.................... በደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል በጉራጌ
+6
የቡታጅራ - ቡኢ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ሥራ ጀመረ ....................///.................... በደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል በጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ቡኢ ከተማ የተገነባው የባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር በዛሬው ዕለት ኃይል መስጠት ጀመረ፡፡ ከአዲስ አበባ በ100 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው የቡኢ ከተማ የተገነባው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መካከል በተደረገ ሥምምነት መሠረት በጥር ወር 2009 ነበር ግንባታው ተጀመረው፡፡ በፍተሻ እና ሙከራ ሥራ ላይ ቆይቶ ዛሬ በይፋ ስራ የጀመረው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው 132 ኪሎ ቮልት ኃይል የመሸከም አቅም አለው፡፡ ጣቢያው 25 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች የተተከሉለት ሲሆን አራት ባለ 15 ኪሎ ቮልት እና አራት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮችም አሉት፡፡ በማከፋፈያ ጣቢያው የመቆጣጠሪያ ክፍሎች፣ የመኖሪያ ቤቶች እና የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ግንባታም ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ተደርጓል፡፡ ከቡታጅራ ነባር ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተነስቶ ቡኢ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ 30 ኪ.ሜ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋባታ ሥራም ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን 78 ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችም ተተክለዋል፡፡ ለተጨማሪ https://www.facebook.com/Ethioelectric/posts/517011005640404

የክርስትና እምነት ተከታይ የተቋማችን ሠራተኞች እንኳን ለትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ!! መልካም በዓል!!! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

ተቋሙ ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ የሚያግዙ ቁሳቁሶች ድጋፍ አገኘ ............/////............. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከዶንግፋንግ ኤሌክትሪክ ኢንተርናሽናል ኮርፖሬሽን የኮሮና
+3
ተቋሙ ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ የሚያግዙ ቁሳቁሶች ድጋፍ አገኘ ............/////............. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከዶንግፋንግ ኤሌክትሪክ ኢንተርናሽናል ኮርፖሬሽን የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚያስችሉ ግብዓቶችን ድጋፍ አገኘ። ኮርፖሬሽኑ የዓለማችንና የሃገራችን የጤና ስጋት የሆነውን የኮሮና ወረርሽኝ ለመከላከል የሚያግዙ አስር ሺህ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብሎችንና ሃያ የሙቀት መለኪያ መሳሪያዎች (thermometers) በዛሬው ዕለት ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስረክቧል። በኢትዮጵያ የኩባንያው ዋና ሥራ አስኪያጅ ዣንግ ሻቦ እንደተናገሩት ድርጅታቸው 120 ሜጋ ዋት እንዲያመነጭ ታስቦ እየተገነባ የሚገኘውንና የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በመገንባት ላይ ነው። ኩባንያቸው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ጥብቅ የስራ ግንኙነት ያለው በመሆኑ ተቋሙ ወረርሽኙን ለመከላከል በሚያደርገው ጥረት የድርሻቸውን ለመወጣት ድጋፍ ማድረጉን ገልፀዋል። ስጦታዎቹን የተረከቡት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በበኩላቸው የኤሌክትሪክ ኃይል ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት የሚያረክተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው የኮሮና ወረርሽኝን በመከላከል ረገድ እንደተቋም በከፍተኛ ትኩረትና ጥንቃቄ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዛሬው ዕለት ከዶንግፋንግ ኤሌክትሪክ ኩባንያ የተገኘው የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል (mask) እና የሙቀት መለኪያ መሳሪያዎቹ ተቋሙ የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያደርገውን ጥረት ስለሚያግዝ ኩባንያውን በተቋሙ ስም አመስግነዋል። ለተጨማሪ https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=516428439031994&id=320447995296707

የያቤሎ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ሥራ ጀመረ ....................///............ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በቦረና ዞን ያቤሎ ወረዳ የተገነባው የ
+2
የያቤሎ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ሥራ ጀመረ ....................///............ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በቦረና ዞን ያቤሎ ወረዳ የተገነባው የባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት የፍተሻ እና ሙከራ ሥራ ተጠናቆ በዛሬው ዕለት ኃይል መስጠት ጀመረ፡፡ የኃይል ማከፋፈያ እና ማስተላለፊያ ጣቢያው በጥር ወር 2009 በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መካከል በተደረገ የኮንትራት ሥምምነት መሠረት የተገነባ ፕሮጀክት ነው፡፡ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው 132 ኪ.ቮ ኃይል የመሸከም አቅም ያለው ሲሆን አንድ ባለ 20/25 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመርም ተተክሎለታል፡፡ በማከፋፈያ ጣቢያው የመቆጣጠሪያ ክፍሎች፣ የመኖሪያ ቤቶች እና የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ግንባታም ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ተደርጓል፡፡ አዲሱን ባለ 132 ኪ.ቮ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ከሃገረ-ማርያም - ቦኩሉ ጉማ ከተማ ድረስ ተገንብቶ አገልግሎት እየሰጠ ከሚገኘው ባለ 132 ኪ.ቮ ነባር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር (existing line) ላይ በመውሰድ (tapping) ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ጋር ለማገናኘት 2 ነጥብ 5 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የተዘረጋ ሲሆን 8 ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችም ተተክለዋል፡፡ ለተጨማሪ https://www.facebook.com/Ethioelectric/posts/515702975771207

ጣቢያው ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች መሠረታዊ የፍጆታ ዕቃዎችን ለማገዝ ዝግጅት አድርጓል ……../////……. የጊቤ 1 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የተለያዩ
ጣቢያው ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች መሠረታዊ የፍጆታ ዕቃዎችን ለማገዝ ዝግጅት አድርጓል ……../////……. የጊቤ 1 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የተለያዩ ሥራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ የጣቢያው የአስተዳደር እና ጠቅላላ አገልግሎት ኃላፊ አቶ የበጋሸት ስርጉ ገለፁ፡፡ በጣቢያው ከሚገኙ 208 ሠራተኞች ውስጥ 46 የሚሆኑትን እረፍት እንዲወጡ በማድረግ በኃይል ማመንጫ ቤት እና በቢሮ አካባቢ የሚታየውን ርቀትን ጠብቆ የመንቀሳቀስ ሂደትን ለማገዝ ጥሩ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ የበጋእሸት ገለፃ በጣቢያው ውስጥ ያሉ የመዝናኛ ቦታዎችን ሙሉ በሙሉ በመዝጋት ሠራተኛው ከሥራ ውጭ ቤቱ እንዲያሳልፍ የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች እየተከናወነ ይገኛልም ብለዋል፡፡ በተጨማሪም በጣቢያው የተቋቋመው ግብረ ኃይል ቤት ለቤት በመሄድ ለሰራተኞቹ በቫይረሱ ዙሪያ በቂ የሆነ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ማካሔዱን ተናግረዋል፡፡ የሠራተኛውን እንቅስቀሴ ከመግታት አኳያም የገቢያ ሳምንት ሲደርስ ለሠራተኛው የሚሆኑ መሠረታዊ የፍጆታ ዕቃዎችን የሚገዛ ኮሚቴ በማዋቀር ግዥዎች እየተፈፀሙ መሆኑን ነው አቶ የበጋሸት ያስታወቁት፡፡ ከጣቢያው ለሥራም ሆነ ለሌላ ተግባራት የሚወጡ ሠራተኞች ወደ ጣቢያው ሲመለሱ ለ14 ቀናት ራሳቸውን እንዲያገሉ እየተደረገ ነው ያሉት ኃላፊው ይህ ተግባር ግን በአንዳንድ ሠራተኞች ተፈፃሚ እየተደረገ ባለመሆኑ የቅጣት እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ እንገኛለን ብለዋል፡፡ የጣቢያው ሰራተኞች 52,500 ብር በበጎ ፈቃደኝነት በማዋጣት በሶኮሩ ወረዳ በገንገላታ እና ዳካ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ውስጥ ለሚኖሩ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች መሠረታዊ የፍጆታ ዕቃዎችን ገዝቶ ለማከፋፈል ዝግጅት እያደረጉ እንደሚገኙ አቶ የበጋእሸት አብራርተዋል

የቀብሪ ደሃር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተመረቀ ............///........ በቀብሪ ደሃር የተገነባው የባለ 132/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በይፋ ተመርቆ ስራ ጀመረ። የኃይል ማ
+6
የቀብሪ ደሃር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተመረቀ ............///........ በቀብሪ ደሃር የተገነባው የባለ 132/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በይፋ ተመርቆ ስራ ጀመረ። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያውን የመረቁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻና የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ ናቸው። ዋና ስራ አስፈፃሚው እንደተናገሩት የኃይል ዘርፍ ለኢኮኖሚ ዕድገት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ በመላው ሀገሪቱ ኤሌክትሪክን ለማስፋፋት ተቋሙ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ላይ ይገኛል። በቀብሪደሃር የተገነባው የማከፋፈያ ጣቢያና ወደ ጎዴ የተዘረጋው የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመር የክልሉን ኢኮኖሚያዊ እድገት ለማፋጠን ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። አካባቢውን ከጨለማ ለማውጣት የተሳተፉ ባለሙያዎችን በማመስገን ለአካባቢውና ለክልሉ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል። የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ በበኩላቸው የውሃ፣ የስልክ፣ የጤናና ሌሎች መሰረተልማቶችን ለማስፋፋት መብራት አስፈላጊ በመሆኑ ከሁሉም መሰረተ ልማት ቅድሚያ ትኩረት ይሰጠዋል ብለዋል። በሶማሌ ክልል ለውጥ ከመጣ በኋላ ቀብሪደሀር መብራት በማግኘት ሁለተኛዋ ከተማ እንደሆነች ተናግረዋል። በቀጣይም እንደ ዋርዴር ያሉት ከተሞች ትኩረት ተሰጥቷቸው ኃይል እንዲያገኙ እንደሚደረግ ገልፀዋል። የማከፋፈያ ጣቢያ በአጭር ጊዜ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ያልተለመደ ነው ያሉት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ፕሮጀክቱ ከታች እስከላይ ባለው መዋቅር ትብብር ስላልተለየው በፍጥነት ሊጠናቀቅ መቻሉ አንስተዋል። ለተጨማሪ https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=514390629235775&id=3204479952967