es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 518 suscriptores, ocupando la posición 8 333 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 176 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 518 suscriptores.

Según los últimos datos del 09 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -5, y en las últimas 24 horas de -12, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 28.93%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.57% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 489 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 416 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 11.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 10 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 518
Suscriptores
-1224 horas
-277 días
-530 días
Archivo de publicaciones
በገባነው ቃል መሰረት ፈተናዎችን አልፈን የቅድመ ማመንጨት ሂደቱን እውን እናደርጋለን - ዶ/ር አብርሃም በላይ። የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በመጪው ክረምት ውሃ ለመያዝ በሚያስችለው ደረጃ ላይ ይገ
+2
በገባነው ቃል መሰረት ፈተናዎችን አልፈን የቅድመ ማመንጨት ሂደቱን እውን እናደርጋለን - ዶ/ር አብርሃም በላይ። የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በመጪው ክረምት ውሃ ለመያዝ በሚያስችለው ደረጃ ላይ ይገኛል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር አብርሃም በላይ፣ የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ አባል አምባሳደር ግርማ ብሩና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር በላይ በፕሮጀክቱ ስፍራ በመገኘት የግንባታውን ሂደት ገምግመዋል።። ከግንባታው ተቋራጮች ጋር በግንባታው ሂደት ዙሪያ በዝርዝር ተወያይተው ግድቡን በመጎብኘት ግንባታው ውሃ ለመያዝ በሚያስችል ደረጃ ላይ እንደደረሰ አረጋግጠዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር አብርሃም በላይ ግንባታው በብዙ ፈተናዎች የታጀበ ቢሆንም ለህዝባችን በገባነው ቃል መሰረት ፈተናዎችን አልፈን የቅድመ ማመንጨት ሂደቱን እውን እናደርጋለን ብለዋል። የተቋሙ የስራ አመራር ቦርድና ማኔጅመንት የግንባታ ሂደቱን በየወሩ በቦታው እየተገኘ የሚገመግም ሲሆን የኮሮና ቫይረስ በሀገራችን መከሰቱ ይፋ ከተደረገ በኋላ የአሁኑ የመጀመሪያው ነው። ሚያዚያ 24 ቀን 2012 ዓ/ም

ተቋሙ የአፍና አፍንጫ መከላከያ ጭምብል በስጦታ አገኘ ...............////////.......... የቻይና ኤሌክትሪክ ዕቃዎች አቅራቢ (CET) ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሃያ ሺህ የአፍና
+1
ተቋሙ የአፍና አፍንጫ መከላከያ ጭምብል በስጦታ አገኘ ...............////////.......... የቻይና ኤሌክትሪክ ዕቃዎች አቅራቢ (CET) ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሃያ ሺህ የአፍና አፍንጫ መከላከያ ጭምብል በስጦታ አበረከተ። የአፍና አፍንጫ መከላከያ ጭምብሉ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል አስተዋጽኦ እንደሚኖረው በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ ተገልጿል። ከዚህ ቀደም ሲል ከተቋማችን ጋር የተለያዩ ስራዎችን የሰሩ ሁለት ተቋማት የኮረና መከላከያ ግብዓቶች መለገሳቸውን መዘገባችን ይታወሳል። ሚያዚያ 23 ቀን 2012 ዓ/ም

የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ እና ማስተላለፊያ መስመር ለመገንባት ስምምነት ተፈረመ ……………….//////………….. ለጊምቢ ቱሉ ካፒ የወርቅ ማዕድን የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል ባለ
+2
የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ እና ማስተላለፊያ መስመር ለመገንባት ስምምነት ተፈረመ ……………….//////………….. ለጊምቢ ቱሉ ካፒ የወርቅ ማዕድን የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያና ማስተላለፊያ መስመር ለመገንባት ስምምነት ተፈርሟል፡፡ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የሲኖ ሃይድሮ ኩባንያ ተወካይ ሚስተር ቲያን ሆንጉአን ተፈራርመዋል፡፡ መንግስት ለዚህ ፕሮጀክት ልዩ ትኩረት በመስጠት የፕሮጀክቱን አጠቃላይ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት እንዲሸፈን ማድረጉን ኢንጂነር አሸብር ተናግረዋል፡፡ የወርቅ ማዕድኑ ከሚያስገኘው የውጭ ምንዛሬ አንፃር የፕሮጀክቱ ግንባታ በተያዘለት የጊዜ መርሃ ግብር ጥራቱን ጠብቆ መጠናቀቅ እንዳለበትም ዋና ስራ አስፈፃሚው አሳስበዋል፡፡ የስራ ተቋራጩ ተወካይ ሚስተር ቲያን በበኩላቸው የፕሮጀክቱን አስፈላጊነት ስለተገነዘብን ፕሮጀክቱን በተያዘለት የጊዜ ገደብ እና ጥራት ለማጠናቀቅ በትኩረት እንሰራለን ብለዋል፡፡ ለፕሮጀክቱ ግንባታ 5 ነጥብ 6 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር እና 121 ሚሊየን ብር ተበጅቶለታል፡፡ ፕሮጀክቱ አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና 40 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታን ያጠቃልላል፡፡ አጠቃላይ ግንባታውም በ13 ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ሚያዚያ 22 ቀን 2012 ዓ.ም

የአሰላ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ …………………………///////…………………… 100 ሜጋ ዋት እንዲያመነጭ ታስቦ በአርሲ ዞን ሂጦሳ ወረዳ ኢተያ የሚገነባው
+2
የአሰላ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ …………………………///////…………………… 100 ሜጋ ዋት እንዲያመነጭ ታስቦ በአርሲ ዞን ሂጦሳ ወረዳ ኢተያ የሚገነባውን የአሰላ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ለማስጀመር የሚያስችል ስምምነት ተፈርሟል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በስምምነት ሰነዱ ላይ ፊርማቸውን ካኖሩ በኋላ እንደገለፁት የአሰላ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ ከተገነቡት የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች መካከል አነስተኛ ቁጥር ያላቸው ተርባይኖችን በመጠቀም ከፍተኛ ኤነርጂ የሚያመርት መሆኑ የተለየ ያደርገዋል፡፡ እንደ አቶ አሸብር ገለፃ በፕሮጀክቱ እያንዳንዳቸው 3 ነጥብ 45 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው 29 ተርባይኖች ይተከላሉ፡፡ ለንፋስ ኃይል ማመንጫው የሚውለውን ገንዘብ የዴንማርክ መንግስት በስጦታና በብድር እንደሚሸፍን፣ ለ20 ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና እንደሚሰጥና ለአምስት ዓመት የኦፕሬሽንና የጥገና ስራ እንደሚሰራ ስምምነት ላይ መደረሱን ስራ አስፈፃሚው ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱን በተቋራጭነት የዴንማርክና ስፔን ጥምር ኩባንያ የሆነው ሲመንስ ጋሜሳ ሪኒውኤብል ኢነርጂ ሲገነባው የዴንማርኩ ኮዊ ደግሞ በአማካሪነት እንዲሰራ ተመርጧል፡፡ የፊርማ ስነስርዓቱ ተዋዋይ ወገኖች በአካል ሳይገናኙ በቨርቹዋል የተከናወነ ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ከአዲስ አበባ ፤ የዴንማርክና ስፔን ጥምር ኩባንያ የሆነው ሲመንስ ጋሜሳ ሪኒውኤብል ኢነርጂ ደግሞ ከአውሮፓ በመሆን ስካን በተደረገው የስምምነት ሰነድ ላይ ፊርማቸውን አኑረዋል፡፡ በ145 ሚሊየን ዩሮ የሚገነባውን የአሰላ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ለማጠናቀቅ 25 ወራት ተይዘውለታል፡፡

የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ሠራተኞች ለአካባቢው ነዋሪዎች ድጋፍ አደረጉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሰራተኞች የኮረና ቫይርስ ወረርሽኝን ለመግታት የሚደረ
+4
የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ሠራተኞች ለአካባቢው ነዋሪዎች ድጋፍ አደረጉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሰራተኞች የኮረና ቫይርስ ወረርሽኝን ለመግታት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ በኃይል ማመንጫው አካባቢ ለሚኖሩ 30 አቅመ ደካማ አባወራዎች የምግብና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ፡፡ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው የኦፕሬሽን ክፍል ኃላፊ ወ/ሮ አይናለም ወ/ሚካኤል እንደተናገሩት የኃይል ማመንጫው 59 ሠራተኞች ገንዘብ በማዋጣት ለ30 አቅመ ደካማ አባወራዎች ወይም ለ120 የቤተሰብ አባላት የሚሆን 15 ሺህ ብር የሚገመት የምግብ እና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርገዋል፡፡ በመልካ አዳማ ቀበሌ ቀጣና አሮጌ አዳማ ውስጥ ለሚገኙት አባወራዎች ለእያንዳንዱ ቤተሰብ 5 ኪሎ ዱቄት፣1 ሊትር ዘይት፣3 እሽግ ፓስታ፣ 4 ኪሎ መኮሮኒ፣አንድ ኪሎ ጨው፣1 ሊትር ፈሳሽ ሳሙና እና 6 ላይፍ ቦይ ሳሙና ድጋፍ መደረጉን ኃላፊዋ ገልጸዋል፡፡ ሚያዚያ 22 ቀን 2012 ዓ.ም.

ከሌሎች ምንጮች……. የአሜሪካው ሲዲሲ ተጨማሪ ይፋ ያደረጋቸው 6 የኮሮናቫይረስ ምልክቶች ***************************** በኮሮናቫይረስ የተያዘ ሰው 6 ተጨማሪ ምልክቶች ሊኖሩት እንደሚ
ከሌሎች ምንጮች……. የአሜሪካው ሲዲሲ ተጨማሪ ይፋ ያደረጋቸው 6 የኮሮናቫይረስ ምልክቶች ***************************** በኮሮናቫይረስ የተያዘ ሰው 6 ተጨማሪ ምልክቶች ሊኖሩት እንደሚችል የአሜሪካው የበሽታ መከላከልና መቆጣጠሪያ ማዕከል (ሲዲሲ) ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህም መሰረት አንድ በኮሮናቫይረስ የተያዘ ሰው ከዚህ ቀደም ከታወቁትና በዓለም ጤና ድርጅት ከተገለፁት ምልክትች በተጨማሪ • በተደጋጋሚ ብርድ ብርድ ማለት • ማንቀጥቀጥ • የጡንቻ ህመም • የጉሮሮ መቁሰል • ራስ ምታት • ድንገተኛ የመቅመስና የማሽተት ፍላጎት ማጣት ሊያሳይ ይችላል ብሏል፡፡ በከሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው ከ2 እስከ 14 ባሉት ቀናት መካከል እነዚህን ምልክቶች ሊያሳይ እንደሚችል የአሜሪካው የበሽታ መከላከልና መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታውቀዋል፡፡ ኢቢሲ ሲ.ኤን.ቢ.ሲን ጠቅሶ እንደዘገበው

ለአምቦ ከተማና አካባቢው ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሊተከል ነው ………………/////……………….. የአምቦ ከተማና የአካባቢውን የኃይል አቅርቦት ችግር በጊዜያዊነት የሚፈታ ተንቀሳቃሽ የኃይል ማ
+2
ለአምቦ ከተማና አካባቢው ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሊተከል ነው ………………/////……………….. የአምቦ ከተማና የአካባቢውን የኃይል አቅርቦት ችግር በጊዜያዊነት የሚፈታ ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሊተከል መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስፈፃሚው አቶ ሐብታሙ ውቤ እንዳስታወቁት በጉደር ከተማ በጊዜያዊነት የሚተከለው የማከፋፈያ ጣቢያ ችግሩን በዘላቂነት የሚፈታ ማከፋፈያ ጣቢያ እስኪገነባ ድረስ የሚቆይ ነው፡፡ ቀደም ሲል ሆርማት ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ተገንብቶ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ነባሩ የማከፋፈያ ጣቢያ በርካታ የኃይል ፈላጊዎችን ደንበኞችን ሲያስተናግድ ቆይቷል፡፡ እንደ አቶ ሀብታሙ ገለፃ ጣቢያው በሙሉ አቅሙ ኃይል በመሸከሙ በአምቦ ከተማና በአካባቢዋ ከፍተኛ የኃይል መቆራረጥ ከማስከተሉም ሌላ እንደ ኢትዮ ቴሌኮም ያሉ ደንበኞችም አገልግሎት በአግባቡ እንዳይሰጡ አድርጓቸዋል፡፡ በመሆኑም በሁለት ወራት ውስጥ ተተክሎ አገልግሎት እንደሚሰጥ የሚጠበቀው ጊዜያዊ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የኃይል መቆራረጥን በማስቀረት ለአምቦና አካባቢዋ ትልቅ እፎይታን ይፈጥራል ብለዋል፡፡ ተንቀሳቃሽ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው በዛሬው ዕለት አምቦ ከተማ ደርሷል፡፡ በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ተመሳሳይ የኃይል መቆራረጥ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ጊዜያዊና ዘላቂ መፍትሔዎች በመተግበር ላይ መሆናቸውን አቶ ሐብታሙ ገልፀዋል፡፡ ሚያዚያ 21 ቀን 2012 ዓ.ም.

Ethiopian Electric Power ከሌሎች ምንጮች…. የሕዳሴው ግድብ በመጪው ክረምት ውሃ መያዝ የሚችልበት የግንባታ ደረጃ ላይ መድረሱ ተገለጸ *********************************** ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ውሃ መያዝ የሚችልበት የግንባታ ደረጃ ላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በዓባይ ወንዝ ላይ እየተገነባ ያለው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለት ተርባይኖች በቀጣዩ ዓመት ኃይል እንዲያመነጩ ለማድረግ በመጪው ክረምት ግድቡ ውሃ መያዝ ይጀምራል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለኢዜአ እንዳሉት በአሁን ጊዜ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ የዓለም ብሎም የኢትዮጵያ ስጋት ቢሆንም የግድቡ ግንባታ ለአፍታም አልተቋረጠም። የግንባታ ሥራው የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ባወጣው የጥንቃቄ መመሪያ መሰረት እየተከናወነ ነው ብለዋል። የግድቡ ሁለት ተርባይኖች ኃይል ማመንጨት የሚያስችላቸውን ውሃ በመጪው ክረምት ለመያዝ የሚቻልበት የግንባታ ደረጃ ላይ ለማድረስ በፍጥነት እየተከናወነ ነው”። ግድቡ ኃይል እንዲያመነጭ ከታሰበው ጊዜ በላይ ከተራዘመ አገሪቷ በየዓመቱ ማግኘት ያለባትን ገቢ እንድታጣ ከማድረግ ባለፈ ለተጨማሪ የግንባታ ወጪ ትጋለጣለች ያሉት አቶ ሞገስ፤ አላስፈላጊ ወጪን ለማስቀረትም በዕቅዱ መሰረት የውሃ ሙሌት ሥራው ”ከዘንድሮ ክረምት አያልፍም” ብለዋል። የግድቡ ግንባታው እየተከናወነ ውሃው መያዝ የሚችለውን ያህል መያዝ ካልቻለ ተጨማሪ አንድ ዓመት ሃይል ሳያመነጭ ሊያልፍ ይችላል ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ክረምት ላይ ውሃ መያዝ ከቻለ ግን ከሚቀጥለው ዓመት አጋማሽ በኋላ ሁለቱ ኃይል ቀድመው የሚያመነጩ ዩኒቶችን በመፈተሽ ስራ እንዲጀምሩ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ በአሁን ጊዜ የግድቡ የብረታ ብረት ሥራ 26 በመቶ ላይ ደርሷል።“ይህ አሀዝ የዛሬ ሁለት ዓመት ከነበረው ጋር ተመሳሳይ ቢሆንም በዓለምአቀፍ ጥራትና ግብዓት እንደ አዲስ እርማት ተደርጎለት በአዲስ የሚተኩት ግብዐቶች ተቀይረው ግንባታው እየተከናወነ በመሆኑ የተፈጠረ ነው” ብለዋል። የደን ምንጣሮን ጨምሮ ለግድቡ ውሃ ሙሌት አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል። የብሔራዊ ኤክስፐርቶች ፓናል ሰብሳቢና የሦስትዮሽ ድርድር ኮሚቴ አባል ኢንጂነር ጌዲዮን አስፋው በበኩላቸው እ.ኤ.አ በ2015 ኢትዮጵያ፣ ግብጽና ሱዳን በመሪዎቻቸው አማካኝነት ካርቱም ላይ በተፈራረሙት የመርህ ስምምነት በሕዳሴው ግድብ ውሃ አሞላል ላይ የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል ነው ያሉት። ይሁንና ግብጽ ግድቡ ውሃ መያዝ የሚያስችለው ደረጃ ላይ መድረሱን እርግጠኛ በመሆኗ የተለያዩ ምክንያቶችን በመፍጠር የመርህ ስምምነቱን ለመጣስ ሙከራ በማድረግ ላይ ናት ያሉት ኢንጂነር ጌዲዮን፤ ግብጽና ሱዳን የኢትዮጵያንና ሌሎች የዓባይ ተፋሰስ አገሮችን መብትና ጥቅም በጣሰ መልኩ የወንዙን ውሃ በብቸኝነት ሲጠቀሙ እንደነበርም አታውሰዋል። ግድቡ 65 ሜትር ቁመት ላይ ሲደርስ የመጀመሪያ ዙር ውሃ ለመሙላት ዕቅድ መያዙን ገልጸው ይህም በተያዘው ዕቅድ መሰረት በዘንድሮ የዝናብ ወቅት እንደሚከናወን ተናግረዋል። ”ከግድቡ መሰረት ወደ 65 ሜትር የውሃ ቁመት ከፍ ይላል የሚይዘው ውሃ አራት ነጥብ ዘጠኝ ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ይሆናል።በሁለተኛው ዓመት ላይ ተጨማሪ 13 ነጥብ አምስት ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ ግድቡ ይይዛል። በዚህ ጊዜ የውሃው ቁመት 595 ላይ ወይም ከግድቡ መሰረት 95 ሜትር ከፍ ብሎ ይገኛል ማለት ነው። በዚያን ወቅት ተጨማሪዎቹ 11 አሸንዳዎች ውሃ ማስተላለፍ ይጀምራሉ” ብለዋል ኢንጂነር ጌዲዮን። እንደ ኢንጂነር ጌድዮን ገለጻ የውሃ ሙሌት ስርዓቱ በየዓመቱ ደረጃ በደረጃ የሚከናወን ይሆናል። ይህም የግድቡ ተርባይኖች ሙሉ ለሙሉ ኃይል ማመንጨት የሚችሉበት ቁመት ላይ እስኪደርሱ ውሃው ከአምስት እስከ ስድስት ዓመት ይሞላል ብለዋል። እንደ ኢዜአ ዘገባ የግድቡን ውሃ ሙሌት በሁለት ዓመት ማከናወን ቢቻልም የግድቡን ደህንነትና የታችኞቹ ተፋሰስ አገሮች ላይ ጉልህ ጉዳት ላለማድረስ ደረጃ በደረጃ የመሙላት እቅድ መያዙንም ኢንጅነር ጌድዮን ገልጸዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ አፈፃፀም በአሁኑ ወቅት 73 በመቶ መድረሱን ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ከኢቢሲ የተገኘ የኢዜአ ዘገባ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተግባርና ኃላፊነት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ለማቋቋም በወጣው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 381/2008 እንደተሻሻለው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተግባርና ኃላፊነት እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፡፡  የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ሥራዎች የአዋጭነት ጥናት፣ የንድፍ እና ቅየሳ ሥራዎችን ማከናወን፣ እንደአስፈላጊነቱ እነዚህኑ ሥራዎች በአማካሪዎች ማሰራት፤  የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ መስመሮችና ጣቢያዎች የግንባታና የማሻሻያ ሥራዎች ማከናወን፤ እንደአስፈላጊነቱ እነዚህኑ በሥራ ተቋራጭ ማሰራት፤  የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ እና 132 ኪ.ቮ እና ከዛ በላይ መጠን ያላቸውን ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን እንዲሁም የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎችን ማከናወን፤  እንደአስፈላጊነቱ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮችን ሊዝ ማድረግ፤  የኤሌክትሪክ ኃይል በጅምላ መሸጥ፤  የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር የሚያወጣውን መመሪያና የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት በማድረግ ቦንድ መሸጥና በዋስትና ማስያዝ እና ከአገር ውስጥና ከውጭ የገንዘብ ምንጮች ጋር የብድር ውል መደራደርና መፈራረም፤  ዓላማውን ከግብ ለማድረስ የሚረዱ ሌሎች ተዛማጅ ሥራዎችን መሥራት የሚሉት ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌትሪክ ኃይል የኢትዮጵያ ኤሌክሪክ ኃይል ከምስረታው ጀምሮ በተለያዩ ስያሜዎች አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ከጀርመን መንግስት በ1890 ዓ.ም. ለአፄ ምኒልክ በተበረከተ የናፍጣ ጄኔሬተር
የኢትዮጵያ ኤሌትሪክ ኃይል የኢትዮጵያ ኤሌክሪክ ኃይል ከምስረታው ጀምሮ በተለያዩ ስያሜዎች አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ከጀርመን መንግስት በ1890 ዓ.ም. ለአፄ ምኒልክ በተበረከተ የናፍጣ ጄኔሬተር በቤተ መንግስት አገልግሎት መስጠት የጀመረው ይህ ተቋም ቀስ በቀስ አገልግሎቱ እየተስፋፋ ሲመጣና ተጠቃሚ የሚሆኑ ከተሞች ቁጥር እያደገ ሲመጣ በ1940 ዓ.ም. የኃይል ዘርፉን የሚያተዳድር ተቋም የሸዋ መብራት ኃይል በሚል ስያሜ ራሱን ችሎ ተቋቋመ፡፡ ከዓመታት በኋላም ይህ ተቋም እንደገና በ1948 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ መብራት ኃይል ባለስልጣን ወይም በእንግሊዝኛ ምህፃሩ (EELPA) ተብሎ ህጋዊ ሰውነት በማግኘት በቻርተር ተቋቋመ፡፡ መንግስት ለኃይል ዘርፉ በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት በ1989 ዓ.ም. ተቋሙን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮፖሬሽን በሚል ስያሜ እንደ አዲሰ እንዲቋቋም አደረገ፡፡ የኮፖሬሽኑ እንቅስቃሴ እየሰፋ በመሄዱ፣ ዘርፉም እያደገ በመምጣቱ መንግስት የኃይል ልማት ዘርፉን ይበልጥ ለማሳደግ፣ ለማዘመንንና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆን ለማስቻል ተቋሙን ወደ ሁለት ተቋም እንዲከፈል አደረገ፡፡ እነዚህ ተቋማት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ናቸው፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለደንበኞች የኤሌክትሪክ አገልግሎት የመስጠት፤ የኤሌክትሪክ ጥገና አገልግሎት ተግባራትን የማከናወን፤ የተገለገሉበትን የኤሌክትሪክ ፍጆታ ስሌት የማንበብ፣ ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሒሳብን የማስከፈልና ከኤሌክትሪክ ሥርጭት ተያያዥነት ያላቸው ስራዎች ሲሰራ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ደግሞ ከኃይል ማመንጨትና የመነጨውን ኃይል ከማስተላለፍ ጋር የተያያዙ ተግባራትን ያከናውናል፡፡

የአላማጣ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ተጠገነ ******************** በአላማጣ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በትራንፎርመር ላይ የደረሰው ብልሽት ተጠግኖ ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኃ
የአላማጣ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ተጠገነ ******************** በአላማጣ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በትራንፎርመር ላይ የደረሰው ብልሽት ተጠግኖ ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኃይል ማግኘት ጀመሩ፡፡ በማከፋፈያ ጣቢያው ትራንስፎርመር ላይ የደረሰው ችግር በአላማጣ፣ ላሊበላ፣ ሰቆጣ እና ማይጨው ከተሞችና አካባቢያቸው ለቀናት የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲቋረጥ አድርጎ ቆየቷል፡፡ ችግሩን ለመቅረፍ የጥገና ባለሙያዎቻችን በሶስት ፈረቃ ለሃያ አራት ሰዓታት ጥረት ሲያደረጉ የቆዩ ሲሆን የአላማጣ ከተማ ወዲያውኑ መብራት እንዲያገኝ ተደርጓል፡፡ የላሊበላ፣ ሰቆጣና ማይጨው እንዲሁም በአቅራቢያዎቹ የሚገኙ ከተሞች ደግሞ ዛሬ ኤሌክትሪክ አግኝተዋል፡፡ የገጠመንን ችግር ከግምት ውስጥ በማስገባት በትዕግስት ለጠበቃችሁን ደንበኞቻችን የኢትየጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምስጋናውን ያቀርባል፡፡ የተጠገነው ትራንፎርመር እስከ ሰማኒያ በመቶ ኃይል የመሸከም አቅም ያለው በመሆኑ የኃይል ጭነት በሚበዛባቸው ሠዓታት ከተሞቹ በፈረቃ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ ስለሚደረግ የአካባቢው ነዋሪዎች ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ እናሳስባለን፡፡ ችግሩን ሙሉ በሙሉ ለመቅረፍ እስከ ሁለት ሳምንት ጊዜ ሊወስድ ይችላል። ሚያዝያ 18 ቀን 2012 ዓ.ም

ተቋሙ ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ግብዓቶችን በስጦታ አገኘ ..............//////......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከቻይናው ሲኖ ሃይድሮ - ፓወር ቻይና ለኮሮና መከላከል የሚያግዙ
+2
ተቋሙ ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ግብዓቶችን በስጦታ አገኘ ..............//////......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከቻይናው ሲኖ ሃይድሮ - ፓወር ቻይና ለኮሮና መከላከል የሚያግዙ ግብዐቶች በስጦታ ተበረከተለት። ስጦታውን ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ያበረከቱት የሲኖ ሃይድሮ ተወካይ ሚስተር ቲያን ሆንግጁን እና የፕሮጀክት ሥራ አስኪያጁ ዩ ሚንጉሂ ናቸው። ድርጅቱ ያበረከተው ስጦታ ሶስት ሺህ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብልና አርባ ሊትር የእጅ ንፅህና መጠበቂያ ሳኒታይዘር ነው። ስጦታውን ከተረከቡ በኋላ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ድርጅቱ ያበረከተው ስጦታ ለሁለቱ ተቋማት አጋርነት ማሳያ ነው። ስጦታው በዓለማችን እና በሀገራችን የተከሰተውን የኮሮና ወረርሽኝ በተቋም ደረጃ ለመከላከል የሚያግዝ በመሆኑ ምስጋናም አቅርበዋል። የሲኖ ሃይድሮ - ፓወር ቻይና ተወካዮችም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር የረጅም ጊዜ ግንኙነት እንዳላቸው ጠቅሰው ሁለተኛ ዙር የመከላከያ ግብዐቶችን ለመለገስም ቃል ገብተዋል። ሲኖ ሃይድሮ - ፓወር ቻይና ከተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግንባታ ጀምሮ ለረጅም ዓመታት የተለያዩ የኃይል ማመንጫ ግንባታዎች ውስጥ በመሳተፍ መልካም ግንኙነት ያለው ተቋም ነው። ሚያዚያ 17 ቀን 2012 ዓ/ም

ኮሮና ለመግታት፣ ግድቡንም ለማጠናቀቅ የሚተጋው የህዳሴ ሠራዊት ******************************** ኢ.ፕ. ድ. ወረሃ ሚያዝያ ለወትሮው በኢትዮጵያ ሞቃታማው ጊዜ ተደርጎ ይቆጠራል።የሕዳሴው ግድብ በሚገነባበት አካባቢ ያለው ተፈጥሯዊ አቀማመጥ ደግሞ የሙቀቱን ሁኔታ ቃጠሎ ያደርገዋል፤ ላብ በጆሮ ግንድ ብቻ ሳይሆን በሠራ አካላት እንዲንቀረቆር ያስገድዳል። እነዚህን ሁኔታዎች ተቋቁመው በሕዳሴው ግድብ ግንባታ የተሰማሩና ዓመታትን ያስቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ቁጥራቸው ቀላል አይደለም።አሁን ላይ እነዚህ ዜጎች እንደወርቅ በሙቀት ብቻ አይፈተኑም፤ የኮሮና ወረርሽኝን በመዋጋትም ጭምር እንጂ።ከእነዚህ ነባራዊ ሁኔታዎች በመነሳት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል ምን እየተሠራ ነው? ስንል የፕሮጀክቱን ኃላፊዎች ጠየቅን፡፡ የሕዳሴው ግድብ ሥራአስኪያጂ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ እንዳሉት፤ በአገሪቱ ላይ ያንዣበበው የወረርሽኝ ስጋት በእነሱም ዘንድ መኖሩን ገልጸዋል።ዋናው የኮሮና ቫይረስ ማሸነፊያ መንገድ ጥንቃቄ በማድረግ መከላከል መሆኑን አስታውሰው፣በቅንጅት ሰፊ ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛሉ ብለዋል።ማንኛውም አካል መግባትና መውጣት የሚችለው በለይቶ ማቆያ ለ14 ቀናት በመቆየት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ባለሙያዎችንና ለመከላከል የሚያስፈልጉ ግብዓቶች በክልሉ ጤና ቢሮ በኩል እንደሚቀርቡላቸውና የሠራተኞች ጤና እንዲጠበቅ አስፈላጊው ተግባር እየተከናወነ ስለመሆኑም ተናግረዋል። የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ፍሬሕይወት አበበ በበኩላቸው፤የሕዳሴው ግድብ ፕሮጀክት ሠራተኞች ከኮሮና ወረርሽኝ መጠበቅ እንዲችሉ ከፌዴራል እስከ ክልልና ሕዳሴው ግድብ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ድረስ በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።ይሄን ጉዳይ የሚመራ ራሱን የቻለ ግብረኃይል የተቋቋመ ሲሆን በቅርበት እየተገኘ ምቹ ሁኔታዎችን ይፈጥራል፤ ለመከላከል የሚያግዙ አስፈላጊ ተግባራትንም ያከናውናል፡፡ ለተጨማሪ https://www.press.et/Ama/?p=30979

የታላቁ ኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም 73 በመቶ ደረሰ .............///////............. የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም 73 በመቶ መድረሱን የግድቡ
የታላቁ ኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም 73 በመቶ ደረሰ .............///////............. የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም 73 በመቶ መድረሱን የግድቡ ግንባታ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ እንደገለፁት የፕሮጀክቱ የሲቪል ስራዎች አፈፃፀም 87 በመቶ፣ የብረታ ብረት ስራዎች አፈፃፀም ደግሞ 26 በመቶ ደርሷል። ቅድሚያ ኃይል ያመነጫሉ ተብሎ የታቀዱት ሁለት ዩኒቶች የብረታ ብረት ስራም በአብዛኛው የተጠናቀቀ ሲሆን የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸምም 73 በመቶ መድረሱን ገልፀዋል፡፡ ግድቡ በሚቀጥለው ዓመት መጨረሻ ላይ ኃይል ማመንጨት እንዲችል በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የገለጹት ኢንጂነር ክፍሌ፣ የውሃ ሙሊቱ በመጪው ክረምት ለመጀመር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ተናግረዋል። ሚያዚያ 16 ቀን 2012 ዓ/ም

ለመላው #የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለታላቁ ረመዳን ፆም በሠላም አደረሳችሁ!!! መልካም #የፆምና #የሶላት ወር ይሁንልላችሁ! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
ለመላው #የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለታላቁ ረመዳን ፆም በሠላም አደረሳችሁ!!! መልካም #የፆምና #የሶላት ወር ይሁንልላችሁ! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

በአላማጣ፣ ማይጨው፣ ላሊበላ፣ ቆቦ፣ ሰቆጣና በአካባቢው የሚገኙ ከተሞች ኃይል ተቋርጧል፡፡ በአላማጣ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በትራንፎርመር ላይ ባጋጠመ ችግር ከማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል የሚያገኙ የአላማ
በአላማጣ፣ ማይጨው፣ ላሊበላ፣ ቆቦ፣ ሰቆጣና በአካባቢው የሚገኙ ከተሞች ኃይል ተቋርጧል፡፡ በአላማጣ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በትራንፎርመር ላይ ባጋጠመ ችግር ከማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል የሚያገኙ የአላማጣ፣ ማይጨው፣ ላሊበላ፣ ቆቦ፣ ሰቆጣና በአካባቢው የሚገኙ ከተሞች ኃይል ተቋርጦባቸዋል፡፡ በትራንስፎርመሩ ላይ የገጠመውን ብልሽት ለማስተካከል በሰሜን ሪጅን የሚገኙ የጥገና ሠራተኞቻችን ርብርብ በማድረግ ላይ ቢሆኑም ብልሽቱን በፍጥነት በመጠገን ኃይል እንዲሰጥ ማድረግ አልተቻለም፡፡ በመሆኑም ለትራንስፎርመሩ አስፈላጊ ዕቃዎችን በመቀየር ወደስራ ለማስገባት በርካታ ቀናት የሚፈልግ በመሆኑ ጊዜያዊ መፍትሔ ለመስጠት ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ በዚህ መሰረት የአላማጣ ከተማና አካባቢው ኃይል እንዲያገኝ 15 ኪሎ ቮልት ትራንስፎርመር የመተካት ስራ ተጀምሯል፡፡ በተመሳሳይም የላሊበላ፣ ሰቆጣና ማይጨው ከተሞች ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ በማከፋፈያ ጣቢያው የማስፋፊያ ስራ ለመስራት የተዘጋጀ ትራንስፎርመር በመትከል ችግሩን ለመቅረፍ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው፡፡ ኃይል የተቋረጠባቸውን አካባቢዎች ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ በአማካይ አምስት ቀን የሚፈልግ በመሆኑ ህብረተሰቡን ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ በመጠየቅ ችግሩ እስኪቀረፍ በትዕግስት እንዲጠብቀን ጥሪ እናቀርባለን፡፡ ሚያዝያ 14 ቀን 2012 ዓ.ም

የህክምና ባለሙያ ነዎት? ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ከሆነ ዕድሉን እንዲጠቀሙበት ተጋብዘዋል፡፡ የህክምና ባለሙያ ካልሆኑ ደግሞ ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት ዕድሉን እንዲጠቀሙበት ይጋብዟቸው፡፡ መልካም ዕድል ተመኝተናል፡፡

የቡታጅራ - ቡኢ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ሥራ ጀመረ ....................///.................... በደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል በጉራጌ
+6
የቡታጅራ - ቡኢ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ሥራ ጀመረ ....................///.................... በደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል በጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ቡኢ ከተማ የተገነባው የባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር በዛሬው ዕለት ኃይል መስጠት ጀመረ፡፡ ከአዲስ አበባ በ100 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው የቡኢ ከተማ የተገነባው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መካከል በተደረገ ሥምምነት መሠረት በጥር ወር 2009 ነበር ግንባታው ተጀመረው፡፡ በፍተሻ እና ሙከራ ሥራ ላይ ቆይቶ ዛሬ በይፋ ስራ የጀመረው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው 132 ኪሎ ቮልት ኃይል የመሸከም አቅም አለው፡፡ ጣቢያው 25 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች የተተከሉለት ሲሆን አራት ባለ 15 ኪሎ ቮልት እና አራት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮችም አሉት፡፡ በማከፋፈያ ጣቢያው የመቆጣጠሪያ ክፍሎች፣ የመኖሪያ ቤቶች እና የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ግንባታም ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ተደርጓል፡፡ ከቡታጅራ ነባር ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተነስቶ ቡኢ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ 30 ኪ.ሜ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋባታ ሥራም ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን 78 ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችም ተተክለዋል፡፡ ለተጨማሪ https://www.facebook.com/Ethioelectric/posts/517011005640404

የክርስትና እምነት ተከታይ የተቋማችን ሠራተኞች እንኳን ለትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ!! መልካም በዓል!!! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

ተቋሙ ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ የሚያግዙ ቁሳቁሶች ድጋፍ አገኘ ............/////............. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከዶንግፋንግ ኤሌክትሪክ ኢንተርናሽናል ኮርፖሬሽን የኮሮና
+3
ተቋሙ ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ የሚያግዙ ቁሳቁሶች ድጋፍ አገኘ ............/////............. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከዶንግፋንግ ኤሌክትሪክ ኢንተርናሽናል ኮርፖሬሽን የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚያስችሉ ግብዓቶችን ድጋፍ አገኘ። ኮርፖሬሽኑ የዓለማችንና የሃገራችን የጤና ስጋት የሆነውን የኮሮና ወረርሽኝ ለመከላከል የሚያግዙ አስር ሺህ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብሎችንና ሃያ የሙቀት መለኪያ መሳሪያዎች (thermometers) በዛሬው ዕለት ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስረክቧል። በኢትዮጵያ የኩባንያው ዋና ሥራ አስኪያጅ ዣንግ ሻቦ እንደተናገሩት ድርጅታቸው 120 ሜጋ ዋት እንዲያመነጭ ታስቦ እየተገነባ የሚገኘውንና የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በመገንባት ላይ ነው። ኩባንያቸው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ጥብቅ የስራ ግንኙነት ያለው በመሆኑ ተቋሙ ወረርሽኙን ለመከላከል በሚያደርገው ጥረት የድርሻቸውን ለመወጣት ድጋፍ ማድረጉን ገልፀዋል። ስጦታዎቹን የተረከቡት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በበኩላቸው የኤሌክትሪክ ኃይል ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት የሚያረክተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው የኮሮና ወረርሽኝን በመከላከል ረገድ እንደተቋም በከፍተኛ ትኩረትና ጥንቃቄ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዛሬው ዕለት ከዶንግፋንግ ኤሌክትሪክ ኩባንያ የተገኘው የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል (mask) እና የሙቀት መለኪያ መሳሪያዎቹ ተቋሙ የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያደርገውን ጥረት ስለሚያግዝ ኩባንያውን በተቋሙ ስም አመስግነዋል። ለተጨማሪ https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=516428439031994&id=320447995296707