ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 554 подписчиков, занимая 8 397 место в категории Технологии и приложения и 2 165 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 554 подписчиков.

Согласно последним данным от 21 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 10, а за последние 24 часа — 1, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.74%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 14.94% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 003 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 323 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 9.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 22 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 554
Подписчики
+124 часа
+87 дней
+1030 день
Архив постов
#photonews የኢፌዲሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት እና የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲዔታዎችን ጨምሮ በፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ ላይ ግንባር ቀደም ከነበሩ ቀደምት የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ልጆችና የልጅ ልጆች እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያደረጉት ጉብኝት በምስል!! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ህዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም

ግድቡ በኢትዮጵያ የቱሪዝም ሀብቶች ላይ ትልቅ እሴት የሚጨምር ነው -የቱሪዝም ሚኒስቴር …....///…….. ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ እስካሁን ከነበሯት የቱሪዝም ሀብቶች ላይ ትልቅ እሴት የሚጨምር መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስትር ዲኤታ አስታወቁ። ሚኒስትር ዲኤታው እንደገና አበበ (ዶ/ር ) እንዳስታወቁት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የሠንደቅ ዓላማ ፕሮጀክት እና ኢትዮጵያውያን ፅናታቸውን ያሳዩበት እንደ አፍሪካ ደግሞ ከአድዋ በኋላ ለፓን አፍሪካ ንቅናቄ ያዋጣነው ትልቅ ሀብት ነው። የህዳሴ ግድብ በቱሪዝም እሳቤ ውስጥ የሚመጡ ሁለት ነገሮችን ያሟላ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትር ዲኤታው  የመጀመሪያው  ተጨባጭ የሆነና በአካል የሚታይ ሲሆን  ሁለተኛው የሚነገርለት ታሪክ ያለው መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ሚኒስትር ዲኤታው ገለጻ  የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የፈጠረው ንጋት ሀይቅን ጨምሮ የሌሎች ደሴቶች አካላዊ ዕይታ ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ፍሰት ትልቅ ተስፋ ይዞ መጥቷል። በተጨማሪም ግድቡን  በራሳችን ሀብት እና ልጆች  በብዙ ጫና ውስጥ ሆነን ማጠናቀቃችን ኢትዮጵያዊያን መሥራት እንደምንችል ለዓለም ያሳየንበት በመሆኑ ትርክቱ በራሱ ትልቅ የቱሪዝም መስህብ መሆኑን አስረድተዋል። ግድቡ ከቱሪዝም ባሻገር ኢንቨስትመንትን በመሳብ  ለኢትዮጵያ ብዙ ሀብት ሊያመጣ የሚችል በመሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ይህን ታሳቢ ያደረገ የሮድ ማፕ ጥናት እያከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል። ቱሪዝሙን ለማሳደግ በህዳሴ ግድቡ ላይ ለሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች ሚኒስትር መስሪያ ቤታቸው ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥም ነው ያመለከቱት። አስጎብኚ ድርጅቶች ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ሂደው በማየትና በፓኬጃቸው ውስጥ በማካተት ለዓለም ህዝብ እንዲያስተዋውቁ መንግስት ምቹ ሁኔታዎችን እንደሚፈጥር ሚኒስትር ዲኤታው አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ በርካታ የቱሪዝም ሀብቶች ያሏት ሰፊ ሃገር በመሆኗ የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችም ግድቡን በመጎብኘት ሀሳብ እንዲወስዱና ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን የገነባችው ካላት የመልማት ፍላጎት እንጂ ሌሎችን ለመጉዳት አይደለም - የኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት …....///…..... ኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብን የገነባችው ካላት የመልማት ፍላጎት እና የኤሌክትሪክ ኃይልን ለህዝቦቿ ተደራሽ ለማድረግ እንጂ ሌሎችን ለመጉዳት አለመሆኑን መገንዘብ  እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ ገለጹ። በሚኒስትር ዲኤታው ተስፋሁን ጎበዛይ የተመራ እና በአፍሪካ ፖለቲካ እና የነጻነት ትግል ውስጥ ትልቅ ድርሻ የነበራቸው የአፍሪካ የቀድሞ መሪዎች ልጆችን ያካተተ የልዑካን ቡድን ትናንት በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጉብኝት አካሂዷል። ሚኒስትር ዴታው በጉብኝቱ ላይ እንደገለጹት የግድቡን እውነታ በቦታው ተገኝተው  ያላዩ  አካላት ግድቡን በሚመለከት የሚያነሷቸው ጥያቄዎች በመረጃ መዛባት የተቃኙ ስለነበሩ ይህን በማረም እውነታውን ማስረዳት ያስፈልጋል። ጉብኝቱ በፓን አፍሪካ እንቅስቃሴ እና በአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምስረታ እንዲሁም በአህጉሪቱ ታሪክና ፖለቲካ ትልቅ ስም ያላቸው መሪዎች ልጆች የተሳተፉበት መሆኑ አባቶቻቸው ሲመኙት የነበረውን አፍሪካ ትልልቅ ጉዳዮችን አቅዶ የመፈጸም እና ፕሮጀክቶችን ሰርቶ የማጠናቀቅ ህልም ምን እንደሚመስል ግድቡን አይተው እንዲረዱ ለማስቻል ያለመ መሆኑን ሚኒስትር ዲኤታው ገልጸዋል። በተጨማሪም  ጉብኝቱ ከአፍሪካ የመጡ የህዝብና የንግድ ሚዲያ ኃላፊዎችም  ግድቡን በተመለከተ ከአሁን በፊት በተለያዩ መንገዶች ሲሰሯቸው ከነበሩ ዘገባዎች በተሻለ ቦታው ላይ በመገኘት እውነታውን የበለጠ በዓይናቸው አይተው እንዲረዱና እንዲገልጹ ያስችላል ብለዋል። ስለሆነም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ውሃ ኤሌክትሪክ አመንጭቶ እንደሚፈስ፣ ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጥቅም እንጂ ጉዳት እንደሌለው እንዲሁም ኢትዮጵያ ይህን ግድብ የሠራቸው ካላት የመልማት ፍላጎት እና የኃይል ጥማት እንጂ ሌሎችን ለመጉዳት እንዳልሆነ ተገንዝበው በሚያገኙት አጋጣሚ ሁሉ እውነታውን እንዲያሳውቁ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ በፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ በተለያዩ ትውልዶች ገላጭ የሆኑ አስተዋፅኦዎችን ስታበረክት እንደነበር የጠቀሱት ሚኒስትር ዲኤታው ለዚህም አድዋ ጥቁር ማሸነፍ እንደሚችል ለአፍሪካውያን በማሳየት የፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ እንዲጀመር በር የከፈተ እንደነበር አስታውሰዋል። የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ እና በከተማ ልማትና በግብርና የተከናወኑና በመከናወን ላይ የሚገኙ ሥራዎችም  አፍሪካውያን መፈጸምና ማሳካት ይችላሉ የሚለውን የማስረጽ ሞዴል ተደርጎ እንደሚወሰድ አብራርተዋል። ኢትዮጵያ ያከናወነቻቸው ሥራዎችና የተገኙ ውጤቶችን በማስተዋወቅ አፍሪካውያን እንዲገነዘቡት ለማስቻል እንዲሁም በቀጣይ በጋራ በሚከናወኑ ጉዳዮች ላይም አብሮ ለመሥራት ጉብኝቱ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 28 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የአዲሱ ትውልድ ፓን አፍካኒዝም ነው - የቀድሞ የአፍሪካ የነጻነት ታጋዮች ልጆች .......///........ ኢትዮጵያ ገንብታ ያጠናቀቀችው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ቀደምት አፍሪካውያን አባቶቻችን ሲመኙት የነበረውን ርዕይ እውን ያደረገ፣ አፍሪካን ዳግም ወደ አንድነት የሚያመጣ የአዲሱ ትውልድ ፓን አፍሪካኒዝም መሆኑን የቀድሞ የአፍሪካ የነጻነት ታጋዮች ልጆች  ገለጹ። በአፍሪካ ታዋቂ የሆኑ የነጻነት ታጋዮችና ተፅዕኖ ፈጣሪ መሪዎች ልጆች ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት ጎብኝዎቹ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካውያን ትልቅ የመቻል ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። የቀድሞው የጋና የነጻነት ታጋይ የክዋሚ ንክሩማ ልጅ ሳሚያ ንኩርማ አፍሪካውያን በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካ እና በማህበራዊ ጉዳዮች አንድ ሆነው ማየት የአባታቸው የዘወትር ህልም እንደነበር አስታውሰዋል። ስለሆነም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አፍሪካውያን በሁሉም ዘርፎች ቢጀምሩም ማጠናቀቅ አይችሉም የሚለውን የተሳሳተ ትርክት መለወጥ የሚችል ከኢትዮጵያም አልፎ ለመላው ጥቁር ህዝቦች ኩራት መሆኑን አብራርተዋል። የቀድሞ የታንዛኒያ ፕሬዚዳንት ጁሊየስ ኔሬሬ ልጅ ማዳርካ ኔሬሬ በበኩላቸው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ በታንዛኒያ እና በኢትዮጵያ መካከል የተፈረመውን የኃይል ሽያጭ ስምምነት እውን በማድረግ በቀጣናው የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማስፋት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል። የህዳሴ ግድብ የኤሌክትሪክ ኃይል ከማመንጨት ባሻገር የፓን አፍሪካኒዝምን እሳቤ በአዲሱ ትውልድ ውስጥ ለማስረጽ እና  የፓን አፍሪካን አባቶችን ሌጋሲ ለማስቀጠል ትልቅ መነሳሳት እንደሚፈጥር ተናግረዋል። ከደቡብ አፍሪካ የመጡት እና የቀድሞው የአፍሪካ ናሽናል ኮንግረስ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ኦሊቨር ታምቦ ልጅ ኖማቴምባ ታምቦ ኢትዮጵያ ህዝቦቿን አስተባብራ በራሷ የፋይናንስ አቅም ይህን ታላቅ ግድብ ገንብታ ማጠናቀቋ የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰዋል። ይህ ጥንካሬና ፅናት ለሌሎች አፍሪካውያንም ትልቅ መነሳሳት ይፈጥራል የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያን ብዙ  ውስብስብ ችግሮችን በመፍታት ፅናታቸውን ለዓለም ህዝብ ያስመሰከሩበት እንደሆነ ማረጋገጣቸውን ጎብኝዎቹ መስክረዋል። ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ለፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ የነበራትን አስተዋጽኦ እንደሚያውቁ አስታውሰው በቀጣይም  አፍሪካን አንድ የማድረግ የአባቶቻቸውን ሌጋሲ እውን ለማድረግ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። በጉብኝቱ ታዋቂው የጋና የነጻነት ታጋይ ኩዋሚ ንኩሩማ ልጅ ሳሚያ ንኩሩማ እና የቀድሞ የታንዛኒያ የነጻነት ቀንዲልና  ፕሬዚዳንት የነበሩት የጁሊየስ ኔሬሬ ልጅ ማዳርካ ኔሬሬ ልጅን ጨምሮ የቀድሞ የሊቢያ መሪ መሃመድ ጋዳፊ፣ የቀድሞ የዛምቢያ ፕሬዚዳንት ኬኔት ካውንዳ፣ የፓትሪስ ሉምባ እና ሌሎች የአፍሪካ ተፅዕኖ ፈጣሪ መሪዎች ልጆች ተሳትፈዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 27 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

የሚዲያ ባለሙያዎች የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጎበኙ ...///..... በኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ የተመራ የሚዲያ ባለሙያዎች ልዑካን ቡድን በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ጎብኝት እያካሄዱ ነው። ሚኒስትር ዲኤታው አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ የጉብኝቱን  ዋና ዓላማ አስመልክተው እንደገለጹት ሚዲያዎች ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ማመንጫ ጣቢያ ነባራዊ እውነታን እንዲረዱና ትክክለኛ መረጃ እንዲያጋሩ ለማስቻል ነው። በጉብኝቱ ዲሴንደንት በሚል ማህበር የተቋቋሙ  የቀድሞ ታዋቂ የአፍሪካ መሪዎች ልጆች  በጉብኝቱ ላይ የተገኙ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትር ዲኤታው ይህም አባቶቻቸው ሲመኙት የነበረውን አፍሪካውያን ጀምሮ የመጨረስ ህልም በህዳሴ ግድቡ የተሳካ መሆኑን እንዲመለከቱ ታስቦ መሆኑን አስረድተዋል። ታዋቂው የጋና የነጻነት ታጋይ ክዋሚ ንኩርማ ልጅ ሳሚያ ንኩሩማን ጨምሮ የኬኔት ካውንዳ፣ የጁሌስ ኔሬሬ  እና ሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች መሪዎች ልጆች እንዲሁም የተለያዩ የሃገር ውስጥና የውጭ ሃገር ሚዲያዎች በጉብኝቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተጨማሪም ከቱሪዝም ሚኒስትር፣  እና ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኃይል የተውጣጡ አመራርና ሠራተኞች በጉብኝቱ ታድመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 27 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ለማሟላት የመንግሥት እና የግል አጋርነት ፕሮጀክቶችን ማጠናከር ይገባል ......///...... በኢትዮጵያ እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ለ
+6
እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ለማሟላት የመንግሥት እና የግል አጋርነት ፕሮጀክቶችን ማጠናከር ይገባል ......///...... በኢትዮጵያ እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ለማሟላት በመንግስት እና በግል አጋርነት የሚከናወኑ ፕሮጀክቶችን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። ተቋሙ በመንግሥት እና በግል አጋርነት የሚገነቡ የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶችን ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያግዝ የግንዛቤ ማስጨበጫ... ሙሉ ለማንበብ 👉 https://www.eep.com.et/?amh-news=እያደገ-የመጣውን-የኤሌክትሪክ-ኃይል-ፍላ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል መሰረተ ልማቱን መጠበቅ የብሔራዌ ደህንነት አጀንዳ ነው ……..///……... የኤሌክትሪክ ኃይል ግሪድ የሳይበር ጥቃት ተጋላጭ እንዳይሆን የተለያዩ የደህንነት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን በኢት
+1
የኃይል መሰረተ ልማቱን መጠበቅ የብሔራዌ ደህንነት አጀንዳ ነው ……..///……... የኤሌክትሪክ ኃይል ግሪድ የሳይበር ጥቃት ተጋላጭ እንዳይሆን የተለያዩ የደህንነት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሳይበር ደህንነት መምሪያ ዳይሬክተር ገለፁ፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ ጌትነት አድማሱ እንደተናገሩት የኤሌክትሪክ ኃይል ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት የሚኖረውን አስተዋጽኦ ከግምት ውስጥ በማስገባት የኦፕሬሽናል ቴክኖሎጂውን... ሙሉ ለማንበብ 👉 https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-መሰረተ-ልማቱን-መጠበቅ-የብሔራዌ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም

#vacancy የፈተና ውጤት ማስታወቂያ ......///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-1ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥቅምት 03 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂ
+2
#vacancy የፈተና ውጤት ማስታወቂያ ......///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-1ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥቅምት 03 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት ህዳር 17 ቀን 2018 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ በአሽከርካሪ እና ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ደንብና መመሪያ መሰረት 74 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጣችሁ ለተግባር ፈተና ያለፋችሁ ሲሆን ፤ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 16 ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች ታህሳስ 02 ቀን 2018 ዓ.ም እና 17 እስከ 32 ስማችሁ የተገለጸው ታህሳስ 03 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ተሽከርካሪ ጥገና አስተዳደር ቢሮ የተግባር ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

ሙስና ሀገራዊ ዕድገትን የሚገታ ካንሰር ነው ......///....... ሙስና ሀገራዊ ዕድገትን የሚገታ ካንሰር በመሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች በጋራ ሊታገሉት እንደሚገባ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ፡፡ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ- ሙስና ቀን "ትውልድን በሥነ ምግባር፣ ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪቃል በተቋሙ ሲከበር እንደተናገሩት የካንሰር በሽታ የሰውነት ህዋሶችን ቀስ በቀስ እያጠፋ ለሞት እንደሚዳርግ ሁሉ ሙስናም ቀስ በቀስ እየተስፋፋ እና ስር እየሰደደ ሀገርን አደጋ ላይ ይጥላል። ተቋሙ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የሚፈስበት እንደመሆኑ መጠን ተቋሙ ያስቀመጣቸው የአሰራር ስርዓቶች ሳይሸራረፉ እየተተገበሩ መሆኑን በየጊዜው ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል፡፡ ተቋሙ በሚያከናውናቸው ግዥዎች፣ በፕሮጀክት አፈፃፀም፣በንብረት ማስወገድ ላይ ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ ማከናወን እንደሚገባም ነው ያሳሰቡት፡፡ ሙስናን የመከላከል ተግባር ለሥነምግባር መከታተያና ፀረ ሙስና መምሪያ ብቻ የሚተው አለመሆኑን የጠቆሙት ኢንጂነር አሸብር ሁሉም የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። ዋና ሥራ አስፈፃሚው አክለውም ከተቋም ባሻገር በሥነ ምግባር የታነፁ ሀገር ወዳድ ዜጎችን ለማፍራት ቀን ከሌት መስራት ይገባል ብለዋል። ከሙስና መከላከያ ስልቶች መካከል የዲጂታል የአሰራር ስርዓት አንዱና ዋነኛው በመሆኑ ይህን አሰራር እውን ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አረጋግጠዋል። ሙስናንና ብልሹ አሠራርን የሚጠያፉ አርአያ የሆኑ አመራሮች እና ባለሙያዎች ለመፍጠር መስራት ይገባልም ብለዋል። የተቋሙ የኮርፖሬት ገቨርናንስ እና ኮምፐሊያንስ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ድጉማ ነዳ በበኩላቸው ሙስና የሀገርን ህልውና የሚፈታተን አደገኛ ወንጀል ስለሆነ በጋራ እና በተቀናጀ መንገድ መከላከል እንደሚገባ አስታውቀዋል፡፡ ሙስና ከአስተሳሰብ ይጀምራል ያሉት ሥራ አስፈፃሚው ስነ ምግባር የተላበሰና ህጋዊ የአሠራር ስርዓት የሚከተል የስራ መሪ እና ሠራተኛ መፍጠር እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል፡፡ ሙስና በባህሪው ውስብስብ ከመሆኑ አንፃር ሳይከሰት ቀድሞ መከላከል ተመራጭ እና አዋጭው ስልት መሆኑንም ነው የገለፁት። በመርሃግብሩ መገባደጃ ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚን ጨምሮ የተቋሙ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የሀብት ማስመዝገቢያ ሰነድ በመሙላት ለተቋሙ የስነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና መከታተያ መምሪያ በማስረከብ የአርአያነት ተግባር አከናውነዋል፡፡ በመጨረሻም ሁሉም የተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች ሙስናን ለመከላከል በተቋሙ የስነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና መከታተያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ደረጀ አጥናፌ አማካኝነት ቃለ መሃላ ፈፅመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በተቋም ደረጃ እየተከበረ ነው ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በተገኙበት ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን በዋ
+6
ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በተቋም ደረጃ እየተከበረ ነው ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በተገኙበት ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን በዋና መስሪያ ቤት የስብሰባ አዳራሽ እያከበረ ይገኛል። መርሃ ግብሩን በይፋ ያስጀመሩት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት ሁሉም የሥራ መሪና ሠራተኞች የዕለት ከዕለት ስራዎችን ሲያከናውኑ ሥነ ምግባርን በመላበስ እና ህጋዊ የአሰራር ሥርዓት በተከተለ መንገድ መሆን ይኖርበታል። የዘንድሮው የፀረ- ሙስና ቀን "ትውልድን በሥነ ምግባር፣ ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ እየተከበረ መሆኑንም ነው ዋና ሥራ አስፈፃሚው የገለፁት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም

የአካል ጉዳተኞች ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ይገኛል ........///................ የ2018 ዓ.ም የአካል ጉዳተኞች ቀን “አካል ጉዳተኝነትን የሚያካትት ማህበረሰብ መገንባት ለተሻለ ማህበራዊ ዕድገት!” Fostering disability inclusive societies for advancing social progress! በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ይገኛል፡፡ የተቋማችን የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢዳኤ ዕለቱን አስመልክቶ ለኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ባስተላለፉት መልዕክት በተቋማችን ውስጥ ለሚገኙ የአካል ጉዳተኛ ሠራተኞች በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ የዕኩል እድል ተሳታፊና ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ዳይሬክተሯ በመልዕክታቸውም አካታች ማህበረሰብ የመፍጠር አንዱ እና ዋነኛው መገለጫ የአካል ጉዳተኞችን የእንቅስቃሴ ችግሮች መቅረፍ በመሆኑ በተቋማችን ለሚገኙ የአካል ጉዳተኞች ሁለንተናዊ ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሉት የስራ ቦታዎች ለአካል ጉዳተኞች ምቹ መሆናቸውን የማረጋገጥ ስራና፤አካል ጉዳተኞች እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ እኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ የክትትልና ድጋፍ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውንም ነው የገለፁት፡፡ ተቋሙ በሚያከናውናቸው ፕሮግራሞች ፣ ፕሮጀክቶችና በሚያወጣቸው የተለያዩ ፖሊሲዎችና የአሰራር መመሪያዎች የአካል ጉዳታኞችን ታሳቢ እንዲያደርግ እየተሰራ ነውም ብለዋል፡፡ አካል ጉዳተኝነት ማለት ከውልደት ጀምሮ ወይም ከውልደት በኋላ በአደጋ ወይም በህመም የሚያጋጥሙ የአካል ወይም የአዕምሮ ጉዳቶች ናቸው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

በትራንስፎርመር ብልሽት ሳቢያ በከፊል ተቋርጦ የቆየው ኃይል ዳግም ተመልሷል .....///..... በኮምቦልቻ አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ካሉት ሁለት ትራንስፎርመሮች መካከል በአንደኛው ላይ ባጋጠመ ችግር ምክንያት በከፊል ተቋርጦ የቆየው ኃይል ዳግም መመለሱን የሰሜን ምስራቅ 1 ሪጅን አስታወቀ።   ‎በሪጅኑ የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንደገለፁት 40 ሜጋ ቮልት አምፒር ኃይል የመጫን አቅም ባለው ትራንስፎርመር ላይ ባጋጠመ የእሳት አደጋ ምክንያት ለአንድ ወር ያህል  በአካባቢው በከፊል ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ቆይቷል፡፡ በዚህም በትራንስፎርመሩ ታፕ ቼንጀር ላይ በደረሰው ጉዳት ምክንያት በደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች እና በአካባቢያቸው  በከፊል የኃይል ተቋርጦ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ ጉዳት የደረሰበትን ባለ 132/66/15 ኪሎ ቮልት ትራንስፎርመር ጠግኖ  ዳግም  አገልግሎት ለማስጀመር ከሪጅኑ እና ከማዕከል የተውጣጡ የጥገና ባለሙያዎች ርብርብ ሲያደርጉ መቆየታቸውንም ነው የገለፁት። በአካባቢው በከፊል ተቋርጦ የቆየውን የኤሌክትሪክ ኃይል በዛሬው ዕለት ሙሉ በሙሉ መመለስ ተችሏል ያሉት አቶ በድሩ በጥገና ሥራው ላይ ርብርብ ሲያደርጉ ለነበሩ የጥገና ባለሙያዎች በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም