en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 697 subscribers, ranking 8 049 in the Technologies & Applications category and 2 173 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 697 subscribers.

According to the latest data from 02 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 141 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 28.59%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.37% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 487 views. Within the first day, a publication typically gains 2 569 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 03 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 697
Subscribers
No data24 hours
+147 days
+14130 days
Posts Archive
ተቋማዊ ለውጡን በብቃት መምራት የሚችል አመራር ለመፍጠር እየተሰራ ነው …….///…… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተጀመረውን ተቋማዊ ለውጥ በአግባቡ መምራት የሚችል የሥራ መሪ ለመፍጠር እየተሰራ መ
+3
ተቋማዊ ለውጡን በብቃት መምራት የሚችል አመራር ለመፍጠር እየተሰራ ነው …….///…… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተጀመረውን ተቋማዊ ለውጥ በአግባቡ መምራት የሚችል የሥራ መሪ ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን የኢትዮ ፓወር አካዳሚ የአመራር ልማት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ተናኘ መኮንን ገለጹ። ሥራ አስኪያጇ እንደተናገሩት ተቋማዊ ለውጡን በአግባቡ ተረድቶ መምራት የሚችል አመራር ለመፍጠር የለውጥ ምንነትንና ተያያዥ ጉዳዮችን ማዕከል ያደረጉ ተከታታይ ስልጠናዎች እየተሰጡ ይገኛሉ። ቀደም ሲል በ14 ዙሮች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ስልጠና መሰጠቱን ያስታወሱት ወ/ሮ ተናኘ ዛሬን ጨምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ተመሳሳይ የአቅም ግንባታ ሥልጠና መጀመሩን አስታውቀዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋማዊ-ለውጡን-በብቃት-መምራት-የሚችል-አ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

ፕሮጀክቱን ወደ ኦፕሬሽን በማስገባት ሀገራዊ የኃይል ስብጥርን ማስፋት እንደሚገባ ተገለፀ ……..///…….. የአሉቶ ላንጋኖ የእንፋሎት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በማጠናቀቅ ለኦፕሬሽን ማብቃት እንደሚገ
+5
ፕሮጀክቱን ወደ ኦፕሬሽን በማስገባት ሀገራዊ የኃይል ስብጥርን ማስፋት እንደሚገባ ተገለፀ ……..///…….. የአሉቶ ላንጋኖ የእንፋሎት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በማጠናቀቅ ለኦፕሬሽን ማብቃት እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወልደኪዳን የተመራ የሥራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ቡድን በአሉቶ ላንጋኖ የእንፋሎት ጉድጓድ (Wellhead) ፕሮጀክት እና በነባሩ የአሉቶ ጂኦተርማል የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የመስክ ምልከታ አድርጓል። የመስክ ምልከታው የ5 የእንፋሎት ጉድጓድ ቁፋሮና የነባሩን ጣቢያ የመልሶ ጥገና ሂደት በመገምገም ቀጣይ የሥራ መመሪያዎችን ለማስተላለፍ ያለመ ነው። ጉብኝቱ ነባር የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ውጤታማነት እና ደህንነት ለማሳደግ ዘርፉ የጀመረው ተሃድሶ አካል መሆኑም ተገልጿል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ፕሮጀክቱን-ወደ-ኦፕሬሽን-በማስገባት-ሀገ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

የጉዞ አበል የአሰራር ሂደትን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለመቀየር እየተሰራ ነው .........///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በወረቀት እየተሰራ ያለውን የጉዞ አበል የአሰራር ሂደት ወደ ዲጂ
+6
የጉዞ አበል የአሰራር ሂደትን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለመቀየር እየተሰራ ነው .........///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በወረቀት እየተሰራ ያለውን የጉዞ አበል የአሰራር ሂደት ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለመቀየር እየተሰራ መሆኑን በተቋሙ የፋይናንስ ሥራ አስፈጻሚ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስፈጻሚው አቶ አለማየሁ መንግስቱ እንዳስታወቁት ተቋሙ የጉዞ አበልን ጨምሮ  የተለያዩ የአሰራር ሂደቶችን ዲጂታላይዝድ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል፡፡ በተቋሙ እየተተገበረ ያለውን የጉዞ አበል አሰራር ወደ ዲጂታል ሥርዓት የመቀየሩ ሥራ በሦስት ምዕራፎች ተከፋፍሎ የሚተገበር ሲሆን በመጀመሪያው ምዕራፍ በኮርፖሬት ዘርፎችና በዋና ሥራ አስፈጻሚ ስር ባሉ የሥራ ክፍሎች፣ በሁለተኛው ምዕራፍ በቢዝነስ ዘርፎች እንዲሁም በሦስተኛው ምዕራፍ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችና በሪጂኖች ላይ ተግባራዊ እንደሚደረግ አስረድተዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የጉዞ-አበል-የአሰራር-ሂደትን-ወደ-ዲጂታል&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠግኖ ከሁለት ዓመታት በኋላ ለአገልግሎት ዝግጁ ተደረገ ........///........ የበለስ-ጃዊ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ከሁለት ዓመታት በ
+4
የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠግኖ ከሁለት ዓመታት በኋላ ለአገልግሎት ዝግጁ ተደረገ ........///........ የበለስ-ጃዊ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ከሁለት ዓመታት በኋላ ተጠግኖ ዳግም ኤሌክትሪክ ለመስጠት ዝግጁ መደረጉን የሰሜን ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ። በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ በላይነህ ልጅዓለም እንዳስታወቁት ከሁለት ዓመት በፊት በበለስ ባለ 400/132/ 33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ የትራንስፎርመር ችግር ምክንያት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ከአገልግሎት ውጪ ሆኖ ቆይቷል፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ለረጅም ጊዜ ከአገልግሎት ውጪ ሆኖ በመቆየቱ ምክንያትም በአማራ ክልል አዊ ብሔረሰብ ዞን ጃዊ ከተማ አካባቢ ለከፍተኛ ስርቆትና ውድመት ተዳርጎ እንደነበርም አስረድተዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-ማስተላለፊያ-መስመሩ-ተጠግኖ-ከሁ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ.ም

በማከፋፈያ ጣቢያው ተጨማሪ የኃይል ትራንስፎርመር ለመትከል ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል …….///…… ለድሬዳዋ ቁጥር 3 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አንድ ተጨማሪ የኃይል ትራንስፎርመር ለመትከል የቅድመ ዝግጅት
+5
በማከፋፈያ ጣቢያው ተጨማሪ የኃይል ትራንስፎርመር ለመትከል ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል …….///…… ለድሬዳዋ ቁጥር 3 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አንድ ተጨማሪ የኃይል ትራንስፎርመር ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቃቸውን የምስራቅ አንድ ሪጅን ገለፀ። የሪጅኑ ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ በየነ እንዳስታወቁት በምስራቅ ኢትዮጵያ ያለውን ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ለማርካት ተጨማሪ የኃይል ትራንስፎርመር ለመትከል የሚያስችሉ ሥራዎች ተከናውነዋል። 125 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለውን የኃይል ትራንስፎርመር የማጓጓዝ ሥራ በቅርቡ እንደሚጀመር የገለፁት አቶ ቴዎድሮስ የተከላ ሥራው በሪጅኑ ባለሙያዎች በራስ አቅም እንደሚከናወን ተናግረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በማከፋፈያ-ጣቢያው-ተጨማሪ-የኃይል-ትራን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ.ም

በጣቢያው እየተከናወነ ያለው የጂ አይ ኤስ ተከላ 90 በመቶ ተጠናቋል …….///…….. በድሬዳዋ ቁጥር 2 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ እየተከናወነ የሚገኘው የጂ አይ ኤስ (GIS) ተከላ ሥራ 90 በ
+3
በጣቢያው እየተከናወነ ያለው የጂ አይ ኤስ ተከላ 90 በመቶ ተጠናቋል …….///…….. በድሬዳዋ ቁጥር 2 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ እየተከናወነ የሚገኘው የጂ አይ ኤስ (GIS) ተከላ ሥራ 90 በመቶ መጠናቀቁን የምስራቅ አንድ ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ በየነ እንደገለጹት በአሁኑ ወቅት የተከላ ሥራው ተጠናቆ የኬብል አቅርቦት በመጠባበቅ ላይ ይገኛል። አስፈላጊው የኬብል አቅርቦት እንደተሟላም በአጭር ጊዜ ውስጥ የዝርጋታ ሥራው ተጠናቆ የጂ አይ ኤስ ሥርዓቱ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር አስረድተዋል። በጣቢያው የጂ አይ ኤስ (GIS) ቴክኖሎጂ ተከላ መከናወኑ ማከፋፈያ ጣቢያውን ከማዘመኑ ባለፈ፣ በአደጋ ጊዜ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በአፋጣኝ ለመከላከልና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለመፍጠር እንደሚያስችል ተገልጿል። በተጨማሪም ባለ 15 ኪሎ ቮልት አቅም ያላቸው አዳዲስ አምስት ወጪ መስመሮች መዘርጋታቸውን የገለጹት አቶ ቴዎድሮስ፤ እነዚህ መስመሮች ወደ አገልግሎት ሲገቡ የድሬዳዋንና የአካባቢውን የኃይል አቅርቦት እንደሚያሳድጉት አረጋግጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ.ም

የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራው የኃይል መሰረተ ልማት ጥበቃ ሥራዎችን ያጠናክራል- ተቋማቱ …….///…… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በጋራ በሶዶ ኮንቨርተር ጣቢያ ዙ
+6
የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራው የኃይል መሰረተ ልማት ጥበቃ ሥራዎችን ያጠናክራል- ተቋማቱ …….///…… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በጋራ በሶዶ ኮንቨርተር ጣቢያ ዙሪያ ለሚገኙ 12 ቀበሌዎች የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ የተከናወነው ሥራ የእኔነት ስሜት በመፍጠር የኃይል መሰረተ ልማት ጥበቃ ሥራዎችን እንደሚያጠናክር የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሀብታሙ ግርማ እንደገለፁት ጣቢያው ከተሰጠው ሀገራዊና ቀጣናዊ ተልዕኮ በተጨማሪ በአካባቢው የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ተቋሙ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በቅንጅት በመስራት በጣቢያው ዙሪያ ለሚገኙ ቀበሌዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ በማድረግ በማህበረሰቡ ሲነሳ የነበረውን የኃይል አቅርቦት ጥያቄዎች መመለስ መቻሉን አስታውሰዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የማህበራዊ-ኃላፊነት-ሥራው-የኃይል-መሰረ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ.ም

አዲስ ሳምንት፣ አዲስ ተነሳሽነት! ......///...... አዲሱን ሳምንት በአዲስ መንፈስ በመጀመር፣ ለሀገራችን የኤሌክትሪክ ፍላጎት መሟላት የበኩላችንን ድርሻ እንወጣ። ስኬታማ የስራ ጊዜ ይሁንልን
አዲስ ሳምንት፣ አዲስ ተነሳሽነት! ......///...... አዲሱን ሳምንት በአዲስ መንፈስ በመጀመር፣ ለሀገራችን የኤሌክትሪክ ፍላጎት መሟላት የበኩላችንን ድርሻ እንወጣ። ስኬታማ የስራ ጊዜ ይሁንልን። መልካም የስራ ሳምንት! Facebook | Telegram | Twitter | YouTube | TikTok | Website | LinkedIn

እያንዳንዷ ሴት ህልሟን በነፃነት የምትኖርበት ዓለም መፍጠር የጋራ ኃላፈነታችን ነው - ኢንጂነር ምትኩ ንጉሴ ......///...... የደቡብ 1 ሪጅን ሠራተኞች እና አመራሮች 50 ኛውን ዓለም ዓቀፍ
+3
እያንዳንዷ ሴት ህልሟን በነፃነት የምትኖርበት ዓለም መፍጠር የጋራ ኃላፈነታችን ነው - ኢንጂነር ምትኩ ንጉሴ ......///...... የደቡብ 1 ሪጅን ሠራተኞች እና አመራሮች 50 ኛውን ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀን በዓል አከበሩ። በበዓል አከባበሩ ላይ ኢንጂነር  ምትኩ ንጉሴ እንደተናገሩት ማርች 8 በዓለም ዙሪያ ያሉ ሴቶች ስኬት ፅናት እዲሁም ለእኩልነት የሚደረግ ቀጣይ ትግል የሚታወስበት ቀን በመሆኑ ከካላንደር በላይ የሆነ ኹነት ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=እያንዳንዷ-ሴት-ህልሟን-በነፃነት-የምትኖ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ.ም

ለተከበራችሁ የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፤ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እላለሁ። ረመዳን የራስን ፍላጎት በመግታት ለላቀ ዓላማ የመገዛት፣ የመረዳዳትና የጽናት
ለተከበራችሁ የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፤ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እላለሁ። ረመዳን የራስን ፍላጎት በመግታት ለላቀ ዓላማ የመገዛት፣ የመረዳዳትና የጽናት ወር ነው። ይህ መንፈስ ደግሞ እኛ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ ለምንከተለው “ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ለሚለው ተልዕኳችን ዋነኛ ስንቅ ነው። ተቋማችን በታዳሽ የኃይል ምንጮች ላይ የተመሰረቱ ግዙፍ የኃይል ማመንጫዎችን፣ የማከፋፈያ ጣቢያዎችንና የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን በመገንባት የሀገራችንን የብልጽግና ጉዞ ለማፋጠን ቀን ከሌሊት እየደከመ ይገኛል። ይህ ጉዞ ያለ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ድጋፍ፣ እንዲሁም ያለ ተቋማችን ሠራተኞች ጥረት፣ መስዋዕትነትና ብርቱ ተጋድሎ ሊሳካ የሚችል እንዳልሆነ አምናለሁ፡፡ በመሆኑም ዛሬም እንደ ትናንቱ፣ በብርሃን ጉዟችን ላይ የሚገጥሙንን ፈተናዎች በጋራ በማለፍ፣ ለሀገራችን የኢንዱስትሪና የማኅበራዊ እድገት የጀርባ አጥንት የሆነውን ኃይል ለማቅረብ ሁላችንም በጋራ እንድንተጋ ጥሪዬን አቀርባለሁ። በተመደባችሁበት ፈታኝ የሥራ ሁኔታ እና ቦታ ውስጥ የምትከፍሉት ዋጋ ለሚሊዮኖች ተስፋ የሚሰጥ የሀገር ኩራት እንደሆነ አምናለሁ። ታላቁ የኢድ አል-ፈጥር በዓል የሠላም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሁም አንድነታችን ይበልጥ የሚጠነክርበት እንዲሆን ከልብ እመኛለሁ። ኢድ ሙባረክ! አሸብር ባልቻ(ኢንጂነር) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ

ማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ለሐዋሳ ከተማ ዕድገት አስተዋፅኦ እያደረጉ ነው ……..///……… በሐዋሳ ከተማ የሚገኙት ሁለቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለከተማዋ ሁሉን አቀፍ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከ
+6
ማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ለሐዋሳ ከተማ ዕድገት አስተዋፅኦ እያደረጉ ነው ……..///……… በሐዋሳ ከተማ የሚገኙት ሁለቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለከተማዋ ሁሉን አቀፍ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከቱ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። በከተማዋ መሬት አስተዳደርና ኢንቨስትመንት መምሪያ የኢንቨስትመንት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አበራ አዴላ እንደገለፁት በከተማው ያለው የኃይል አቅርቦት ከጊዜ ወደጊዜ እየተሻሻለ በመምጣቱ ለኢንቨስትመንት ፍሰቱ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው። የኃይል አቅርቦቱ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ከሚኖረው ሚና ባለፈ ለከተማ ውበት፣ የማህበረሰቡን የአኗኗር ዘይቤ ለመቀየር እና ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚኖረው ድርሻ የጎላ ነው ብለዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ማከፋፈያ-ጣቢያዎቹ-ለሐዋሳ-ከተማ-ዕድገት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 9 ቀን 2018 ዓ.ም

በስርቆት ምክንያት ኃይል የተቋረጠበት መስመር ወደ አገልግሎት ተመልሷል ……..///……. በስርቆት ምክንያት ኃይል የተቋረጠበት የይርጋለም ቁጥር 2 - ሐዋሳ ቁጥር 2 ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዳግም ወደ አገልግሎት መመለሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ 1 ሪጅን አስታወቀ፡፡ በሪጂኑ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሞሲሳ ገልቻ እንደገለፁት በማስተላለፊያ መስመሩ ላይ በተፈፀመበት ስርቆት ምክንያት አንድ የኃይል ማተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ በመውደቁ ከመጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት 12 ሰዓት አካባቢ ጀምሮ መስመሩ ኃይል ማስተላለፍ አቋርጧል፡፡ የወደቀውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የብረት ምሰሶ በጊዜያዊነት በባለ 132 ኪሎ ቮልት የብረት ምሰሶ በመተካት ተቋርጦ የነበረው መስመር ዳግም ወደ አገልግሎት መመለስ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ በዚህም በመስመሩ መቋረጥ ምክንያት በከፊል ኃይል ሲያገኙ የነበሩ ደንበኞች ሙሉ በሙሉ እንዲያገኙ መደረጉን በመግለጽ ኃይል በከፊል ተቋረጦ በነበረበት ወቅት በትዕግስት ለጠበቁ ደንበኞች ምስጋና አቅርበዋል፡፡ የወደቀውን ምሰሶውን ወደነበረበት በመመለስ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አቶ ሞሲሳ ገልፀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 9 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+2

የውጤት ማስታወቂያ ........///............ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የስራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥር 08 እና ጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ
+1
የውጤት ማስታወቂያ ........///............ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የስራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥር 08 እና ጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱ አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው 1. በቧንቧ ጥገና ሠራተኛ ተ.ቁ. 1 በተሰጠው የጽሁፍና የተግባር ፈተና ብልጫ ያመጡ ስለሆነ 2. በኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ አድራጊ ተ.ቁ. 1-2 በተሰጠው የጽሁፍ ፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከመጋቢት 08 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ ብረታብረት ፊት ለፊት በሚገኘው ዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናዉን በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 9 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለአካባቢው የኃይል አቅርቦት ጥያቄ ምላሽ ሰጥቷል ………///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በወላይታ ሶዶ ኮ
+6
ተቋሙ ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለአካባቢው የኃይል አቅርቦት ጥያቄ ምላሽ ሰጥቷል ………///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ጣቢያ ዙሪያ ለሚገኙ ነዋሪዎች የኃይል አቅርቦት ጥያቄ ምላሽ መስጠቱን በተቋሙ የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሀብታሙ ግርማ እንደገለፁት ተቋሙ በሶዶ ከተማ የሚገኙ 12 ቀበሌዎችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ የሰራው ሥራ የአካባቢው ነዋሪዎችን እርካታ አሳድጓል፡፡ ቀበሌዎቹን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ ከተመደበው ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ውስጥ 60 በመቶውን ወይም 150 ሚሊዮን ብሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሲሸፍን የተቀረውን 40 በመቶ ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መሸፈኑን ገልፀዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-ከ150-ሚሊዮን-ብር-በላይ-ወጪ-በማድረግ-ለ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 8 ቀን 2018 ዓ.ም

የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ለማሻሻል የሚያስችል የኢነርጂ ትግበራ ሞዴል ለማዘጋጀት እየተሰራ ነው …….///……. የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ለማሻሻል የሚያስችል የኢነርጂ ትግበራ ሞዴል
+8
የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ለማሻሻል የሚያስችል የኢነርጂ ትግበራ ሞዴል ለማዘጋጀት እየተሰራ ነው …….///……. የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ለማሻሻል የሚያስችል የኢነርጂ ትግበራ ሞዴል ለማዘጋጀት እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ ተቋሙ ከዴንማርክ የኢነርጂ ኤጀንሲ እና ኢነርጂኔት የኤሌክትሪክ ኃይልና የጋዝ አቅርቦት ኩባንያ ጋር በመተባበር በፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ የሚስተዋሉ መዘግየቶችን ለመቅረፍ የሚያስችል አውደ ጥናት አካሂዷል፡፡ አውደ ጥናቱ በዴንማርክ - ኢትዮጵያ የኢነርጂ ትብብር (Danish-Ethiopian Energy Partnership) ማዕቀፍ ስር የተዘጋጀ ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎች እና ባለሙያዎች ከፕሮጀክት ትግበራ ሞዴል ጋር ተያይዞ ዓለም አቀፍ ልምዶችንና ተሞክሮዎችን እንዲቀስሙ ያለመ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የፕሮጀክቶችን-አፈፃፀም-ለማሻሻል-የሚያ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 8 ቀን 2018 ዓ.ም

የተቋሙን ተሽከርካሪዎች በራስ አቅም በመጠገን ከ31 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን ተችሏል ‎…....///....... ‎በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስምንት ወራት የተቋሙን ተሽከርካሪዎች በራስ አቅ
+4
የተቋሙን ተሽከርካሪዎች በራስ አቅም በመጠገን ከ31 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን ተችሏል ‎…....///....... ‎በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስምንት ወራት የተቋሙን ተሽከርካሪዎች በራስ አቅም በመጠገን ከ31 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን መቻሉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሽከርካሪ ጥገና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ። ‎ ‎የቢሮው ሥራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ ብሩክ እንዳለ እንደገለጹት ቢሮው በበጀት ዓመቱ ስምንት ወራት በተቋሙ ጋራዥ ለ1 ሺህ 227 ተሽከርካሪዎች የቀላል፣ መካከለኛ እና ከባድ የጥገና ሥራዎች አከናውኗል፡፡ ‎ ‎በተቋሙ ጋራዥ በራስ አቅም ጥገናዎችን ማከናወኑ ተሽከርካሪዎች በጥገና የሚቆዩበትን ጊዜ በማሳጠር፣ የተሽከርካሪዎችን የጥገና ታሪክ በቀላሉ በመመዝገብ እና በመከታተል የተሽከርካሪዎችን ዝግጁነት ማሳደጉን የገለጹት አቶ ብሩክ በተከናወነው ጥገናም 31 ነጥብ 58 ሚሊዮን ብር ማዳን መቻሉን ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-ተሽከርካሪዎች-በራስ-አቅም-በመ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 8 ቀን 2018 ዓ.ም

የጊቤ ግድቦች ኢትዮጵያ የውሃ ሀብቷን በአግባቡ መጠቀም የመጀመሯ ማሳያ ናቸው - ዛዲግ አብርሃ ‎....///.... ‎በኦሞ ጊቤ ተፋሰስ ላይ የተገነቡት የግልገል ጊቤ 1 እና 2 እንዲሁም የጊቤ 3 የ
+3
የጊቤ ግድቦች ኢትዮጵያ የውሃ ሀብቷን በአግባቡ መጠቀም የመጀመሯ ማሳያ ናቸው - ዛዲግ አብርሃ ‎....///.... ‎በኦሞ ጊቤ ተፋሰስ ላይ የተገነቡት የግልገል ጊቤ 1 እና 2 እንዲሁም የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድቦች ኢትዮጵያ የውሃ ሀብቷን በአግባቡ መጠቀም የመጀመሯ ማሳያ መሆናቸውን የአፍሪካ አመራረረ ሥራ አመራር አካዳሚ ፕሬዝዳንት ዛዲግ አብርሃ ገለጹ። ‎ ‎እንደ ፕሬዝዳንቱ ገለጻ ይህ የግቤ ሰንሰለት የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይልና የኢኮኖሚ ከፍታ ማሳያ ከመሆኑም በተጨማሪ የቀጠናው የኃይል ማማ እንድትሆን አስችሏታል። ‎ ‎ እ.ኤ.አ በ2004 ሥራ የጀመረው የግልገል ግቤ 1፣ 184 ሜጋ ዋት በማመንጨት በወቅቱ የነበረውን የኃይል እጥረት በመቅረፍ ለሀገሪቱ የኢንዱስትሪ መነሳሳት መሠረት እንደነበር አስታውሰዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የጊቤ-ግድቦች-ኢትዮጵያ-የውሃ-ሀብቷን-በአ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም

ጣቢያዉ ከ200 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል ለደንበኞች እያቀረበ ነው …….///…. የሐዋሳ ቁጥር 2 ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው ለሚገኙ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች፣ ለቴክኖሎጂ ድርጅቶች
+5
ጣቢያዉ ከ200 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል ለደንበኞች እያቀረበ ነው …….///…. የሐዋሳ ቁጥር 2 ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው ለሚገኙ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች፣ ለቴክኖሎጂ ድርጅቶች እና ለማህበረሰቡ ከ200 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ የጣቢያው ኃላፊ ገለፁ። ኃላፊው አቶ ዳንኤል አንጄሎ እንደገለፁት በ2011 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረው የማከፋፈያ ጣቢያው እያንዳንዳቸው 125 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል የመሸከም አቅም ያላቸው ሁለት አውቶ ትራንስፎርመሮች እና ሁለት ፓወር ትራንስፎርመሮች አሉት፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው 28 ሜጋ ዋት ለከተማው ነዋሪዎች፣ 40 ሜጋ ዋት ለኢንዱስትሪዎች እንዲሁም 135 ሜጋ ዋት ለቴክኖሎጂ ተቋማት በመስጠት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ጣቢያዉ-ከ200-ሜጋ-ዋት-በላይ-ኃይል-ለደንበኞች&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 5 ቀን 2018 ዓ.ም

መምሪያው የሴቶችን የአመራርነት እና ውሳኔ ሰጭነት ሚና ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው ….…///……. የሴቶችን የአመራርነትና እና ውሳኔ ሰጪነት ሚና በማሳደግ ሴቶች በዘርፉ ላይ የላቀ ተሳትፎ እንዲ
+8
መምሪያው የሴቶችን የአመራርነት እና ውሳኔ ሰጭነት ሚና ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው ….…///……. የሴቶችን የአመራርነትና እና ውሳኔ ሰጪነት ሚና በማሳደግ ሴቶች በዘርፉ ላይ የላቀ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ለማስቻል በትኩረት እየሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መመሪያ አስታወቀ፡፡ በኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ከ60 በላይ ለሚሆኑ የተቋሙ ሴት አመራሮች በሁለት ዙር ሲሰጥ የቆየው የአመራርነት ሥልጠና ተጠናቋል፡፡ በሥልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ የመምሪያው ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ እንደገለጹት የተቋሙ ሴት አመራሮች ሥራዎችን በብቃት ቢያከናውኑም ራሳቸውን ወደ ፊት በማምጣት እና ሥራዎቻቸውን በማሳየት ረገድ ግን ውስንነቶች አሉባቸው፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=መምሪያው-የሴቶችን-የአመራርነት-እና-ውሳ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 5 ቀን 2018 ዓ.ም