ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 697 подписчиков, занимая 8 062 место в категории Технологии и приложения и 2 174 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 697 подписчиков.

Согласно последним данным от 01 сентября, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 139, а за последние 24 часа — 1, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 28.75%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.42% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 513 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 578 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 10.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 02 сентября, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 697
Подписчики
+124 часа
+277 дней
+13930 дней
Архив постов
‹‹የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የማንሰራራት ዘመን ምሳሌ ነው›› ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ...///… በሁሉም ኢትዮጵያዊያን ትብብር እና ተሳትፎ የተገነባው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት መጠናቀቅ የማንሰራራት ዘመን ማሳያ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለፁ፡፡ ተቋሙ በሰው ኃይል ልማት፣ በፋይናንስ፣ በኃይል ማመንጨት፣ በማስተላለፊያ፣ በማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን፣ ግንባታና የጥገና እንዲሁም የሪፎርም ሥራዎች አፈፃፀምን ገምግሟል። የበጀት ዓመቱን አፈፃፀም ያቀረቡት በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዱዓለም ሲዓ እንደገለፁት ተቋም የሚቀየረው የሠራተኛውን አቅም በማሳደግ በሚሰሩ ዘርፈ ብዙ ሥራዎች ነው፡፡ በበጀት ዓመቱ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን የተናገሩት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው በሁሉም ዘርፍ የነበረው አፈፃፀም እንዲሁም የኦፕሬሽን ሥራዎች እና የኃይል ሽያጭ የተሻለ እንደነበር ገልፀዋል። እንደ ኢንጂነር አንዱዓለም ገለፃ ለዓመታት ሳይከለስ የቆየውን የኤሌክትሪክ ታሪፍ የማሻሻል ሥራን በማከናወን ተቋሙ የተሻለ ገቢ እንዲኖረው ተደርጓል፡፡ በበጀት ዓመቱ በፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ የነበሩ ችግሮችን በመፍታት በታቀደላቸው ጊዜ ተጠናቀው ወደ አገልግሎት እንዲገቡ ማድረግ መቻሉን ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው አስረድተዋል። ፕሮጀክቶቹ ከጅማሬ አንስቶ፣ በትግበራ ሂደት እና በማጠቃለያ ወቅት ያላቸውን አፈፃፀም እንዲሁም አጠቃላይ መረጃዎቻቸውን መመዝገብ የሚያስችል መተግበሪያ ተዘጋጅቶ አገልግሎት ላይ መዋሉን ጠቅሰዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ አንድ አጠቃላይ የኃይል መቋረጥ በግሪድ ሥርዓቱ ላይ ማጋጠሙ፣ በግዥ የአሰራር ሥርዓቶች የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች ላይ ክፍተት መታየቱ፣ የመቆጣጠሪያ ሥርዓቶችን የማዘመንና ወጥነት ያለው ሥራ አለመሰራቱ እና በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሠራሮችን በተሟላ ሁኔታ መተግበር አለመቻሉ በበጀት ዓመቱ የታዩ ክፍተቶች መሆናቸው በመድረኩ ተነስቷል፡፡ በውይይቱ ላይ የማጠቃለያ ሀሳብ የሰጡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ የታየውን ትብብር እና በጋራ የመልማት ቁርጠኝነት በሌሎች ፕሮጀክቶች መድገም እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡ የፕሮጀክቱ መጠናቀቅ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ማሳያ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጠቅሰዋል። የህብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ አስተማማኝ በሆነ መልኩ ለማሟላት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ግንባታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ዋና ሥራ አስፈፃሚው በማረጋገጥ የኃይል አቅርቦትን ተደራሽ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልገሎት ጋር በጋራ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ሙስናን በመዋጋት የተቋሙን መልካም ሥምና ዝና በማስጠበቅ ረገድ ሁሉም የሥራ አመራር እና ሠራተኛ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣም አሳስበዋል፡፡ በውይይቱ ላይ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በሚመለከታቸው የዘርፍ ሥራ አስፈፃሚዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

ተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም መገምገም ጀመረ .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራሮችና ሠራተኞች የተቋሙን የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም በተቋሙ የስብሰባ አዳራሽ መገምገም ጀምረዋል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የግምገማ መርሃ-ግብሩን ሲያስጀምሩ እንደተናገሩት በጀት ዓመቱ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት መጠናቀቅ ለዓለም ህዝብ የተበሰረበት ነው። የግድቡ መጠናቀቅ የሁሉም የተቋሙ የሥራ አመራሮች እና ሠራተኞች እንዲሁም የመንግሥት ቁርጠኝነት የታየበት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በተቋሙ የ12 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም እና ተቋሙን በቀጣይ ማሻሻል በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ይደረጋል። በ2018 በጀት ዓመት የበለጠ ውጤት ለማምጣት በሚቻልባቸው የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። በአፈፃፀም ውይይቱ ላይ ሁሉም አመራሮችና ሠራተኞች ለተቋሙ ውጤታማነት ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ዋና ሥራ አስፈፃሚው አሳስበዋል። ግምገማው በተቋሙ የስትራቴጂክ ዕቅድ የትኩረት መስኮች በሆኑት የአስተዳደርና የኦፕሬሽን ልህቀት፣ የማይበገርና አስተማማኝ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች፣ የፈጠራና የዲጂታል ሽግግር እንዲሁም በሰው ሃብት ልማት ላይ ባለፉት 12 ወራት በተከናወኑ አበይት ተግባራት ላይ ያተኩራል። በአፈፃፀም ግምገማው ላይ የተቋሙን የ12 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ጠንካራና ደካማ ጎኖች፣ የተገኙ መልካም አጋጣሚዎች እና ያጋጠሙ ችግሮች እንዲሁም በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ ውይይት ይካሔዳል ተብሎም ይጠበቃል። የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ከመጀመሩ አስቀድሞ ተቋሙ በጀት ዓመቱ በህይወት ላጣቸው ሠራተኞች የህሊና ፀሎት ተደርጓል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አምስት አመታት የኤሌክትሪክ አቅርቦት ሽፋንን 100% ለማዳርስ ትሰራለች …///… ኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ አጋርነት በማጠናከር 54 በመቶ የሆነውን የኤሌክትሪክ ተደራሽነት በ2022 ዓ.ም 100% ለማድረስ እየሰራች መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር የሀገሪቱን የኃይል ዘርፉ ኢንቨስትመንት ማሻሻል እና ማዘመን ላይ ያተኮረ ወርክሾፕ በዛሬው ዕለት አካሂደዋል፡፡ በዘርፉ የፕሮግራም ሁለት ዳይሬክተር አቶ ደስታለም ኃይሉ በወርክሾፑ ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ በኃይል አማራጭ ላይ እየስራች ያለውን መጠነ ሰፊ ስራ ጠቅሰው የኃይል ተደራሽነት ዋስትናን ለማረጋገጥ ከሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራች እንደምትገኝ ገልፀዋል፡፡  በውይይት መድረኩ በዓለም ባንክ እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተወካዮች፣ የስራ ተቋራጮች እና ተበዳሪዎች ፕሮጀክቶችን በጨረታ አሸንፈው የብድር አገልግሎት በሚያገኙባቸው ጉዳዮች ላይ  ለመወያያ የሚሆኑ ሰነዶች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡  በዓለም ባንክ የፕሮክዩርመንት ባለሙያ አቶ አማረ አሰፋ ባቀረቡት ሰነድ ባንኩ በኢነርጂ፤ በትምህርት፤ በፆታ፤ በአየር ንብረት ዘርፎች እና መሰል ጉዳዮች ላይ ለተበዳሪዎች የራሱን ፕሮግራም ቀርፆ እንደሚሰራ ገልፀው ተበዳሪዎች ስለባንኩ ማወቅ ያለባቸዉን ጉዳዮች በዝርዝር አስረድተዋል፡፡ እንደ አቶ አማረ ገለፃ ባንኩ በዓለም ላይ በ327 ቢሊዮን ዶላር 1,819 ፕሮጀክቶችን እያስፈፀመ መሆኑን ገልፀው ከእነዚህ ፕሮጀክቶች 41 በመቶዉ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ላይ እንደሚገኙ አስታውሰው ተበዳሪዎች የፋይናንስ አቅርቦትን ከባንኩ ለማግኘት የሚችሉበትን የአሠራርና የተቋሙን ህገ-ደንቦች አብራርተዋል፡፡ በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በፕራይም አንድ ሊያስገነባቸዉ ያሰባቸዉን ስድስት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ጨምሮ ተቋሙ በማከፋፈያ ጣቢዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ እየሰራቸው ያለውን የማዘመን እና የማስፋፋት ስራዎችን አስመልክቶ በተወካዩ አቶ ታደሰ ብሩ ቀርቧል፡፡  መድረኩ በዋናነት ፕሮጀክቶች በታለመላቸዉ ጊዜ እና ጥራት ተጠናቀው አገልግሎት ላይ እንዲዉሉ የግዥ ሂደት ላይ መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች፤ አቅራቢዎች እና ፍላጎቱ ያላቸው ተቋማት በቀረበው ሰነድ ላይ ሀሳባቸውን እንዲሰጡ እና የገበያ ዕድሉን ለማስፋት ያለመ መሆኑን በመድረኩ ተመላክቷል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ጣቢያው ከ520 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል …///….. የመልካ ዋከና የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት 527 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማምረቱን የጣ
+5
ጣቢያው ከ520 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል …///….. የመልካ ዋከና የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት 527 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማምረቱን የጣቢያ የኦፕሬሽን ክፍል ሥራ አስኪያጅ ተናገሩ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ተክሉ ጎንፋ እንደተናገሩት ጣቢያው በበጀት ዓመቱ 488 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት አቅዶ 527 ጊጋ ዋት ሰዓት አመንጭቷል። ይህም ከዕቅዱ የ39 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ7 በመቶ ብልጫ ያለው ሲሆን በበጀት ዓመቱ በጣቢያው የተከናወኑ የፍተሻና ጥገና ሥራዎች የተርባይኖችን የማመንጨት አቅም ማሳደግ መቻሉን  ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ከሚያዚያ 1980 ዓ.ም ጀምሮ ኃይል በማምረት ላይ የሚገኘው የመልካ ዋከና የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 153 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም አለው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም

ማከፋፈያ ጣቢያው በአካባቢዉ የነበረውን የኃይል አቅርቦት ችግር አቃሏል ..…///…. የቱለፋ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሸ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በቡልጋ ከተማ እና አካባቢው ለበርካታ ዓመታት ፈተና ሆኖ የቆየውን የኃይል አቀርቦት ችግር ማቃለሉን የቡልጋ ከተማ የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት አስታወቀ። የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ሸዋየ ማሞ እንደተናገሩት በቡልጋ ከተማ እና አካባቢው ከ256 በላይ ባለሃብቶች በአምራች ኢንደስተሪዎች እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዘርፍ መሰማራታቸውንና ከእነዚህ ውስጥ ከ40 በላይ የሚሆኑት ወደ ምርት ገብተዋል፡፡  በቡልጋ ከተማ እና አካባቢዉ ለሚገኙና ወደ ምርት ለገቡት አምራች ኢንዱስትሪዎች የኃይል አቅርቦት ተደራሽ በማድረግ ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን አብራርተዋል። በ2012 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሥራ የገባው የቱለፋ ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው ያለውን የኃይል አቅርቦት ችግር እያቃለለ ቢመጣም ቀሪዎቹን ፋብሪካዎች ወደ ምርት ለማስገባት ከተማዉ ተጨማሪ የኃይል አቅርቦት እንደሚያስፈልገው ገልፀዋል።  ከተማ አስተዳደሩ እያከናወናቸው ያሉ ሥራዎችና ወደ ከተማዋ እየመጡ ያሉ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎችን አሁን ላይ ባለው የቱለፋ ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ ብቻ ለማስተናገድ የሚቻል አለመሆኑን አብራርተዋል፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በከተማዋ ያለውን ከፍተኛ የኃይል ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ ሥራ ቀድሞ እንዲያከናውን የጠየቁት አቶ ሸዋየ ለዚህም ከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግና ከተቋሙ ጋር ተባብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የከተማ መስተዳደሩ ለኢንቨስትመንት ያለውን ተመራጭነት ግምት ውስጥ በማስገባት መመስረቱን የገለፁት ኃላፊው በርካታ የአገር ውስጥ እና የውጭ ኢንቨስተሮች በተለያዩ ዘርፎች በስፋት እየተስማሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

💡የግንባታ ማሽነሪዎችን በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ሥር ማንቀሳቀስ የሚኖረው ጉዳት 📌 የኤሌክትሪክ ዥረት (current) የብረት ይዘት ያላቸው ኤሌክትሪክ አስተላላፊ ቁሶች ላይ በቀላሉ ስለሚተላለፍ እና ከኤሌክትሪክ ጋር በቀጥታ ስለሚገናኝ በማሽነሪዎቹም ሆነ በሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል፡፡ በማሽነሪዎቹ እንቅስቃሴ የተነሳ አየሩን ኤሌክትሪክ አስተላላፊ ሊያደርገው ይችላል፡፡ 📌 ከከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ጋር መቀራረብ ከፍተኛ የኤሌክትሮ ማግኔቲክ እንቅስቃሴ እንዲፈጠር ያደርጋል፡፡ ይህም የኮሙዩኒኬሽን፣ የመቆጣጠሪያ እና የማንቂያ መሳሪያዎች በአግባቡ እንዳይሰሩ በማድረግ ማሽኖች ያልተጠበቀ ባህርይ እንዲያሳዩና እንዲጎዱ ሊያደርግ ይችላል፡፡ 📌 ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች በከፍተኛ ሙቀት፣ በንፋስ እና ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዙ ምክንያቶች ሊረግቡ ስለሚችሉ ከመስመሮቹ ጋር ድንገተኛ መነካካት በመፍጠር አደጋ ሊያስከትሉ ይችላሉ፡፡ 📌 የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እንደ መካከለኛ እና ዝቅተኛ የስርጭት መስመሮች ኃይል በማያስተላልፍ ጎማ ወይም ኢንሱሌተር ስለማይሸፈኑ ኤሌክትሪክ በቀላሉ ወደማሽነሪዎቹ ሊተላለፍ ይችላል፡፡ አደጋ ተከስቶ ማሽነሪውን ለመንቀሳቀስ ቢፈለግ እንኳ የማሽነሪው ጎማዎች እንዲቃጠሉ ስለሚያደርግ በጥቅሉ የማሽነሪዎች ሙሉ ቃጠሎ እና የሰው ህልፈት እንዲከሰት ምክንያት ይሆናል፡፡ 📌 በከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የሚደርስ ጉዳት ኃይል እንዲቋረጥ ከማድረግ ባለፈ የታወቆች መውደቅ በአቅራቢያቸው የሚገኙ ህንፃዎች እንዲጎዱ ሊያደርግ ይችላል፡፡ 📌 ስለሆነም ወደ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮቹ ቀርቦ ማሽነሪዎችን አለማንቀሳቀስ፣ የግድ ከሥራቸው የሚሰራ ነገር ሲኖር ኃይል መቋረጡን ማረጋገጥ፣ የቅርበትን/የርቀትን መጠን የሚያሳይ ምልክት ማስቀመጥ፣ ማሽነሪዎችን በቀጥታ በሰውነት ላለመንካት መጠንቀቅ እና የአስቸኳይ ጊዜ የጥንቃቄ ርምጃዎችን መተግበር ያስፈልጋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 6 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ለኃይል መቋረጥ ምክንያት የሆኑ ነገሮች፡- ‎•  የኃይል መዋዠቅ (voltage fluctuation)፤ ‎•  ከፍተኛ የኃይል ጭነት (overload)፤ ‎•  በኃይል መስመሩ ሥር እና አካባቢው የሚኖሩ ዛፎች፤ ‎•  ንፋስ የቀላቀለ ዝናብ፤ ‎•  ያረጀ እና የተጎዳ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር፤ ‎•  የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆት፤ ‎•  መንገድ መቋረጫ ላይ ጭነት የጫኑ መኪኖች መስመሩን ሲነኩት፤ ‎ ‎ ‎ችግሩን ለመከላከል እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች፡- ‎ ‎•  መንገድ የሚሻገሩ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን ከፍታ በመጨመር፤ ‎•  በመስመሩ ስር ያሉ ዛፎችን በመቁረጥና የአፈር ክምችት በማስወገድ፤ ‎•  ያረጁ መስመሮችን በአዲስ የመተካት (reconductor) ሥራ በመስራት፤ ‎•  ከፍተኛ የኃይል ጭነት ያለባቸው መስመሮች በማጥናት ሌላ አጋዥ መስመሮችን በመዘርጋት፤ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን ከፍታ ለመጨመር ጥናት እየተከናወነ ነው፤ …..///…. ትልልቅ ዕቃዎች በተሽከርካሪ ተጭነው የሚያልፉባቸውና መንገድ የሚሻገሩ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን ከፍታ ለመጨመር ጥናት እየተከናወነ መሆኑን የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ማስተባበሪያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ መንግስቱ እንደገለፁት ተቋሙ በሚያስተዳድራቸው ከ132 እስከ 500 ኪሎ ቮልት የቮልቴጅ መጠን ያላቸው ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ከመሬት ሊኖራቸው የሚገባ ከፍታ (minimum clearance) እንደቮልቴጅ መጠናቸው የተለያየ ነው፡፡ በዚህም መሰረት ለባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ቢያንስ 6 ነጥብ 1 ሜትር፣ ለባለ 230 ኪሎ ቮልት 7 ሜትር፣ ለባለ 400 ኪሎ ቮልት 8 ነጥብ 84 ሜትር እንዲሁም ለባለ 500 ኪሎ ቮልት 9 ነጥብ 45 ሜትር ከመሬት ከፍታ ሊኖራቸው እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ ሆኖም በግንባታ ግዜ ስታንዳርዱን ጠብቆ ባለመዘርጋት፣ በሙቀት ምክንያት ኮንዳክተር ረዝሞ ሲረግብ፣ መንገድም ይሁን ቤት ሲሰራ አዲስ አፈር በመስመሩ ስር ሲራገፍ እና መሰል ምክንያቶች ከፍታው በሚጠበቀው ልክ ያለመሆን ችግሮች እንደሚስተዋሉ ተናግረዋል፡፡ ይህም በተሸከርካሪዎች ተጭነው በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ስር የሚያቋርጡ ከፍታ ያላቸው ብረት ነክ ዕቃዎች ዓለም አቀፍ አሰራሮችን በጠበቀ መልኩ እንዲያልፉ እንቅፋት የሚፈጥር ከመሆኑ ባሻገር ለኃይል መቆራረጥና ለአዳጋ የሚዳርግ ነው ብለዋል፡፡ በመስመሩ ስር ያሉ ዛፎችን በመቁረጥና የአፈር ክምችት በማስወገድ፣ ያረጁ መስመሮችን በአዲስ በመተካት፣ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን ቁመት በመጨመር፣ ዓመታዊ ክትትል በማድረግ እና ችግሩን በጊዜያዊነት ለመከላከል እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል። አሁን ላይ ከጣናነሽ ጀልባ የየብስ ጉዞ ጋር በማያያዝ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ከመሬት ያላቸውን ከፍታ በዘመናዊ መሳሪያ በመለካት መረጃዎችን የማደራጀት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የገለፁት አቶ ተስፋዬ መንገድ የሚሻገሩ መስመር ላይ ያሉ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን ከፍታ ለመጨመር ጥናት እየተከናወነ ነው ብለዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ዘርፉ እንደአዲስ ከተደራጀ በኋላ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም ላይ መሻሻል እየታየ ነው፤ ‎......///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እያካሄደ ባለው ተቋማዊ ለውጥ ዘርፉ እንደአዲስ ከተደራጀ በኋላ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም ላይ መሻሻሎች መታየታቸውን የኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ። ‎ ‎ዘርፉ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን ከሚመለከታቸው የመምሪያና የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ጋር ገምግሟል፡፡ መድረኩ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ አበይት ተግባራትን፣ የተመዘገቡ ውጤቶችን፣ የነበሩ ክፍተቶችን እና ሥራዎች ሲመሩበት የነበረውን አግባብ በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ ለመስጠት ያለመ ነው፡፡ ‎ ‎የዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ውድነህ የማነ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ ከዲዛይን ጀምሮ እስከ ፕሮጀክት ትግበራ እና አፈፃፀም ድረስ አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡ ዘርፉ እንደ አዲስ በአምስት መምሪያዎችንና በሁለት  ቢሮዎች መደራጀቱን ገልፀው ይህም ከዲዛይን ጀምሮ የሚታዩ ችግሮችን በቅርበት በመፍታት እንዲሁም የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎችን በማጠናከር የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ማሻሻል መቻሉን ተናግረዋል፡፡ በተቋሙ የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት እና በውጭ የሥራ ተቋራጮች የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው በጀት፣ ጊዜና ጥራት እንዲጠናቀቁ የሚያስችሉ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች በመስራት የኦፕሬሽን ሥራዎች እንዲቀላጠፉ በማድረግ ተቋማዊ ለውጡን እያገዘ ነው ብለዋል፡፡ ቀደም ሲል የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት መምሪያ በርካታ ፕሮጀክቶችን ሲያከናውን የቆየ ቢሆንም በፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ ክፍተቶች ይስተዋሉበት እንደነበር አቶ ውድነህ አስታውሰዋል፡፡ ሆኖም ዘርፉ ባካሔደው የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች በተለያዩ ምክንያቶች ግንባታቸው ሲጓተቱ የነበሩ ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም በማሻሻል መምሪያው ያከናውናቸው ከነበሩ ፕሮጀክቶች ውስጥ ከ90 በመቶ በላይ መጠናቀቃቸውንም አብራርተዋል፡፡ በተጨማሪም ከአላማጣ - ኮምቦልቻ- ለገጣፎ ኃይል ሳይቋረጥ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ሽቦ ዝርጋታን በኮንስትራክሸን ማኔጅመንት ወይም ራስ ኃይል መምሪያ ማከናወን መቻሉንም ጠቁመዋል፡፡ ዘርፉ ወደፊት የተሟላ ሥራ ተቋራጭ ለመሆን ካቀደው ዕቅድ አንፃር ትርፋማ መሆን አለበት ያሉት አቶ ውድነህ በ2017 በጀት ዓመት በፕሮጀክት አፈፃፀም ላይ የተመዘገበውን ስኬት በማጎልበትና ተቋማዊ አቅሙን በማሳደግ ፕሮጀክቶች ትርፋማ የሚሆኑበትን መንገድ ለመፍጠር ይሰራል ብለዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ የነበሩ ክፍተቶችን በማረም እንዲሁም የታዩ ጠንካራ አፈፃፀሞችን በማጠናከር ዘርፉ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከአገር ውጭ በሚገኙ ፕሮጀክቶች ላይ ተሳታፊ ለመሆን የያዘውን ግብ ለማሳካት አመራሩና ሠራተኛው በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ተቋሙ ከ7 ሺ በላይ ለሚሆኑ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች የህክምና አገልግሎት ሰጥቷል፤ ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መካከለኛ ክሊኒክ በ2017 በጀት ዓመት 7 ሺ 330 ለሚሆኑ የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች የህክምና አገልግሎት መስጠቱን የተቋሙ የጤና አገልግሎት ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ረዳት ሥራ አስኪያጅ አቶ አድማሱ ተኽልቁ እንደገለጹት የተቋሙን የሥራ መሪዎችና ሠራተኞችን ጤንነት ለማስጠበቅ ከበሽታ መከላከልና ህክምና አገልግሎት ጋር የተያያዙ ሥራዎችን በጀት ዓመቱ አከናውኗል፡፡ በበጀት ዓመቱ በክሊኒኩ 5 ሺ 132 ወንድ እና 2 ሺ 198 ሴት ሠራተኞች የህክምና አገልግሎቱን ማግኘታቸውን እና ከእነዚህም ውስጥ በላቦራቶሪ አገልግሎት 2 ሺ 485 ያህል ወንድ እና ሴት ሠራተኞች መስተናገዳቸውን አስታውቀዋል፡፡ ተቋሙ በ2017 በጀት ዓመት ግልጽ ጨረታ በማውጣትና በማወዳደር ከ 21 የህክምና ተቋሞች ጋር አዲሰ የህክምና አገልግሎት ሰምምነት በመፈራረም ከክሊኒኩ በላይ የሆኑ የጤና ችግሮች ሲያጋጥሙ ሠራተኛኞች ተልከው እንዲገለገሉ መደረጉን አስረድተዋል። በዚህም ከክሊኒኩ አቅም በላይ የሆኑ 5 ሺ 825 ሠራተኞች ወደ ተለያዩ የህክምና ተቋማት መላካቸውን እና 7 ሺ 56 ሠራተኞች ደግሞ በከነማ ፋርማሲ አገልግሎት ማግኘታቸውን ገልፀዋል። ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት የክሊኒክ መድኃኒቶችን ከመድኃኒት ፈንድ ኤጀንሲ ግዥ በማከናወን እና ቦታው ድረስ በመሄድ የባለሙያ ድጋፍ መደረጉን የጠቆሙት አቶ አድማሱ ለወላይታ ሶዶ ቁጥር 1 እና 2 ኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያዎች የወባ መከላከል እና መቆጣጠር የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናና ህክምና መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡ ኃላፊው አክለውም በዋናው መ/ቤት ክሊኒክ የመድኃኒት መጋዘን ውስጥ የተቀመጡ መድኃኒቶች የመጠቀሚያ ጊዚያቸው ሳያልፍ ለኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲከፋፈል ተደርጓል ብለዋል፡፡ በሰሜን ሪጅን ለስምንት እንዲሁም በምሰራቅ 2 ሪጅን ለአምስት ማከፋፈያ ጣቢያ ሠራተኞች በአቅራቢያቸው ከሚገኙ የጤና ተቋማት ጋር ስምምነት በመፍጠር የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉን አስገንዝበዋል፡፡ እንደ አቶ አድማሱ ገለፃ በበጀት ለአጠቃላይ ህክምና ከ68 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

የኃይል ተደራሽነትን የሚያጎለብቱ ሥራዎች ማከናወኑን ሪጅኑ ገለፀ ‎.....///….. የኃይል ተደራሽነትን ይበልጥ የሚያጎለብቱ የሲቪል እና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ማከናወኑን የሰሜን ምስራቅ ሪጅን አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንደተናገሩት በሪጅኑ ውስጥ ለሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች የማስፋፊያ፣የአቅም ማሳደግና የጥገና ሥራዎች ተከናውኗል፡፡ የከሚሴ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አቅምን ለማሳደግ 50 ኤም ቪ ኤ ፓወር ትራንስፎርመር ተከላ እንዲሁም በኮምቦልቻ 2 እና በጋሸና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የጂ አይ ኤስ ገጠማ ሥራ የተከናወነ መሆኑንም ነው ዳይሬክተሩ ያስታወቁት፡፡ የኃይል መቋረጥን ከመቀነስ አንፃር በስርቆት እና በተለያዩ ምክንያቶች ጉዳት የደረሰባቸውን ከ13 በላይ የኃይል ማስተላለፊያ ምሶሶዎች (ታዎሮች) ጥገና በማከናወን ወደ አገልግሎት እንዲመለሱ ማድረግ ተችሏል፡፡ አቶ በድሩ እንደገለፁት በአራት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሠራተኞች መኖሪያ ቤት፣ የጥበቃ ማማ እና የስቶር ግንባታ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡ የስራ ከባቢን ለሠራተኞች ምቹ ከማድረግ አንፃር ከፍተኛ የውሃ ችግር የነበረባቸው አራት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ውሃ እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡ የመፈፀም አቅምን ለማጎልበት የሚረዱ በመሰረታዊ ኮምፒውተር፣ በዘመናዊ የአሰራር ስርዓት እና የስራ ደህንነት ላይ ያተኮረ ስልጠና ለ143 ሠራተኞች ተሰጥቷል፡፡ የሰሜን ምስራቅ ሪጅን በአጠቃላይ ስምንት ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በስሩ ይገኛሉ፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም