EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 559 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 384,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 165 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 559 名订阅者。
根据 23 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 0,过去 24 小时变化为 -2,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.89%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.48% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 026 次浏览,首日通常累积 2 408 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 24 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 559
订阅者
-224 小时
-37 天
无数据30 天
帖子存档
15 570
+4
በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነን የተሰጠንን ኃላፊነት እየተወጣን ነው
……..///…….
ሴትነት እና የአየር ሁኔታ አስቸጋሪነት ሳይበግረን የተሰጠንን ተቋማዊ ኃላፊነት እየተወጣን ነው ሲሉ በሰሜን ምስራቅ ሪጅን 2 የሰመራ ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬሽን ሠራተኛ ወ/ሮ ነጃት እሸቱ ተናገሩ፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች በማንኛውም የአየር ሁኔታ እና መልክዐ ምድር የሚሰሩ በመሆናቸው ሰመራ ማከፋፈያ ጣቢያ ስመደብ በሙሉ ፍላጎት እና በልበ ሙሉነት ሥራዬን እንደምወጣ ቁርጠኛ ነበርኩ ብለዋል፡፡
አሁን በሚሰሩበት ማከፋፈያ ጣቢያ ሌሎች ሁለት እህቶቼ አብረውኝ ስለሚሰሩ ሴትነት ሳይበግረን በከፍተኛ የሥራ ሞራል እና መተሳሰብ ሥራቸውን እየፈፀሙ ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሰሜን ምስራቅ 2 ሪጅን አስር የአካባቢዉን ተወላጆች አወዳድሮ በማሰልጠን በኦፕሬተርነት እንዲያገለግሉ መድቧል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
+3
የእንጨት ምሰሶው በብረት ምሰሶ ተተክቶ መደበኛ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል
.........///.......
በስርቆት ምክንያት ወድቆ የነበረውና በእንጨት ምሰሶ ተተክቶ ጊዜያዊ አገልግሎት ሲሠጥ የነበረው የኮምቦልቻ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በብረት ምሰሶ ተተክቶ መደበኛ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ አንድ ሪጅን አስታወቀ።
የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንደገለፁት በኮምቦልቻ ከተማ አቅራቢያ በተፈፀመው ዝርፊያ ምክንያት ወድቆ የነበረው የብረት ምሰሶ ቀድሞ በነበረው ሁኔታ መልሶ እንዲተከል ተደርጓል።
በዝርፊያ ምክንያት ኃይል ተቋርጦ የነበረው መስመር ወደ መደበኛ አገልግሎት እንዲመለስ ላደረጉ የሪጅኑ የጥገና ባለሙያዎች አቶ በድሩ ምሰጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
የኮምቦልቻ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር የብረት ምሰሶ ሚያዝያ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ስርቆት ተፈፀሞበት እንደነበር መግለፃችን ይታወሳል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
ሪጅኑ በክልሉ መቋቋሙ የክልሉን የኃይል ጥያቄ ለመመለስ አስችሏል
……..///……..
ለአፋር ክልል በቅርበት አገልግሎት እንዲሰጥ የተቋቋመዉ የሰሜን ምስራቅ 2 ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ የክልሉን የኃይል ጥያቄን ለመመለስ ማስቻሉን የሪጅኑ ዳይሬክተር አስታወቁ፡፡
ዳይሬክተሩ አቶ ሀሰን መሀመድ እንዳስታወቁት በክልሉ የሚገኙት የሰመራ፣ አፍዴራ እና ዲቼቶ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ቀደም ሲል ተጠሪነታቸዉ በደሴ ለሚገኘው የሰሜን ምስራቅ 1 ሪጅን ነበር፡፡
ይህም የኤሌክትሪክ መቋረጥ ሲያጋጥም በአፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት አዳጋች እንደነበር አስታዉሰዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ 2 ሪጅን በሰመራ እንዲቋቋም መደረጉ የኤሌክትሪክ ብልሽት ሲያጋጥም አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት፣ የኃይል መቆራራጥን ለመቀነስ፣ በክልሉ የሚገኙ የተለያዩ አምራች እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሥራዎቻቸዉን እንዲያከናዉኑ ለማድረግ መደላደልን ፈጥሯል ብለዋል፡፡
ከተቋቋመ አንድ ዓመት ከስምንት ወራትን ያስቆጠረዉ ሪጅኑ የክልሉን ሰማንያ በመቶ አካባቢዎችን ተደራሽ በማድረግ የተሻለ የኃይል አቅርቦቱ እንዲኖር ማድረጉን አመልክተዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
በወልቂጤ ማከፋፈያ ጣቢያ በገጠመ ችግር የተነሳ ኃይል በወሊሶና አካባቢው የኃይል መቋረጥ አጋጥሟል
………///………
ከወልቂጤ ማከፋፈያ ጣቢያ በሚወጣ የስርጭት መስመር ላይ ባጋጠመ ችግር የተነሳ የጣቢያው ባለ 230/66/33 የፓወር ትራንስፎርመር ላይ ችግር ተከስቷል፡፡
በዚህ የተነሳ ከወልቂጤ በ33 ኪሎ ቮልት ኃይል የሚያገኙት አገና፣ ጉንችሬ፣ ጦላይ፣ እምድብር እና ዘቢዳር ቢራ ፋብሪካ እንዲሁም በ66 ኪሎ ቮልት ኃይል የሚያገኙት ወሊሶና አካባቢው፣ ቱሉቦሎና አካባቢው፣ ጦላይና አካባቢ ኃይል ተቋርጣል፡፡
በትራንስፎርመሩ ላይ የገጠመውን ችግር ለመለየት እና ለችግሩን መፍትሔ ለመስጠት የማዕከላዊ 3 ሪጅን የጥገና ባለሙያዎች ወደ ሥፍራው ተንቀሳቅሰዋል፡፡
በመሆኑም ችግሩ እስኪቀረፍ ድረስ ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም በትዕግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዝያ 24 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
የኤሌክትሪክ ኃይል ለክልሉ ዕድገት መነቃቃት መሰረት ጥሏል
……….///………
ኤሌክትሪክ ለአፋር ክልል ኢኮኖሚዊ ዕድገትና ማህበራዊ መነቃቃት መሰረት መጣሉን የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ ተናገሩ፡፡
የቢሮ ኃላፊዋ ወ/ሮ አይሻ መሀመድ እንደተናገሩት የኤሌክትሪክ ኃይል ለሰው ልጅ ከሚያስፈልጉ መሰረታዊ ግብዓቶች ውስጥ ወሳኝ በመሆኑ አፋሮች እንደ ዓይን ብሌናቸው የሚያዩት ነው፡፡
ባለሀብቶች በክልሉ ኢንቨስት ለማድረግ በቅድሚያ የሚጠይቁት የኃይል አቅርቦትን በመሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በክልሉ እያከናወነ ያለው የኃይል መሰረተ ልማት ሥራ ለባለሃብቶች መተማመኛቸው መሆኑን አንስተዋል፡፡
በክልሉ ያለው ሰላም የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማቶችን ደኅንነት ለማስጠበቅ ትልቅ ድርሻ ያለው በመሆኑ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት እንደሚሰሩ የቢሮ ኃላፊዋ አረጋግጠዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በክልሉ ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል ባለሀብቶችን እየሳበ መሆኑን የገለፁት ወ/ሮ አይሻ በቀጣይ እያደገ የሚሄደውን የኃይል ፍላጎቱ ለማሟላት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ፈጣን ምላሽ እንዲሚሰጥ እምነታቸውን ገልፀዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዝያ 25 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
የማከፋፈያ ጣቢያውን ብሬከሮች ወደ ጂ አይ ኤስ ብሬከሮች የመቀየር ሥራ እየተከናወነ ነው
…….///……..
በሻሸመኔ ባለ 132/33/15 ኪሎ ቮልት ማከፋፊያ ጣቢያ ረጅም ዓመት ያገለገሉ መቆጣጠሪያዎችን በዘመናዊ የጂ አይ ኤስ መቆጣጠሪያዎች የማዘመን ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ምሕረቱ ግዛው እንደገለጹት ጣቢያው ከ1966 ዓ.ም. ጀምሮ አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ መቆጣጠሪያዎችን በዘመናዊ የጂ አይ ኤስ ብሬከሮች በመቀየር የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ እየተሰራ ነው።
ማከፋፈያ ጣቢያው ካለው 60 ሜጋ ዋት የመጫን አቅም በአሁኑ ወቅት 50 ሜጋ ዋት እየጫነ መሆኑን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ በጣቢያው የተጀመረው የ15 ኪሎ ቮልት መቆጣጠሪያዎችን የማዘመን ሥራም ወደመጠናቀቁ ተቃርቧል ብለዋል።
የጣቢያ የኦፕሬሽን ሰራተኛ አቶ ሰጠኝ ተስፋዬ በበኩላቸው የቆዩ መቆጣጠሪያዎችን ዘመኑ በደረሰበት የመቆጣጠሪያ ቴክኖሎጂ መቀየራቸው ከኃይል መቋረጥ ጋር ተያይዘው የሚፈጠሩ ችግሮችን እንደሚፈታ ተናግረዋል።
መቆጣጠሪያዎችን የማዘመንና የመቀየር ሥራው በተቋሙ ሠራተኞች መከናወኑ የሠራተኞችን ክህሎትና ዕውቀት በማሳደግና ወጪን በመቀነስ ረገድ ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልፀዋል።
የሻሸመኔ ማከፋፈያ ጣቢያ 50 እና 25 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት ፓወር ትራንስፎርመሮች፣ አራት ገቢ መስመሮች እንዲሁም ዘጠኝ ባለ 15 እና ሦስት ባለ 33 ወጭ መስመሮች አሉት፡፡
ማከፋፈያ ጣቢያው ለመቱ፣ ለዋርካ፣ ለሮጲ፣ ለወንዶ ገነት፣ ለአርሲ ነገሌ፣ ለኮፈሌ ፣ ለሻሸመኔ ከተማ እና አካባቢዉ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እየሰጠ ይገኛል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የየኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዝያ 25 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
የጣቢያውን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች በትኩረት ሊሰሩ ይገባል
.......///…....
የአላማጣ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ የጣቢያው የኦፕሬሽንና ጥገና ባለሙያ ገለፁ።
ባለሙያው አቶ ሙሉጌታ አሰፋ እንደገለፁት ጣቢያው ለረጅም ዓመታት አገልግሎት እየሰጠ የቆዬ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት በኦፕሬሽን እና ጥገና ሥራዎች ላይ አሉታዊ ጫና እየተፈጠረ ይገኛል።
የጣቢያው የመቆጣጠሪያ ሥርዓት የአገልግሎት ዘመኑን ያጠናቀቀ በመሆኑ ለተደጋጋሚ የኃይል መቆራረጥና ብልሽት እየተዳረገ እንደሚገኝም ነው ያነሱት።
እንደ ባለሙያው ገለፃ የጣቢያውን አቅም ለማሳደግና ደህንነቱን አስተማማኝ አድርጎ ለማስቀጠል የዘመናዊ ስዊችጊር ቅየራ ሥራዎች ሊሰሩ ይገባል።
እስከ 140 ሜጋ ዋት ድረስ ኃይል የመሸከም አቅም ያለው የአላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ ለሰሜንና ሰሜን ምስራቅ አካባቢዎች ኤሌክትሪክ በማቅረብ በኩል ድርሻው የጎላ ነው።
የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ሁለት ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፔር አውቶ ትራንስፎርመሮች እና ሁለት ባለ 20 ሜጋ ቮልት አምፔር እንዲሁም አንድ ባለ 25 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው አምስት ትራንስፎርመሮች አሉት።
ጣቢያው ከባህር ዳር ኃይል ተቀብሎ በ230 ኪሎ ቮልት ለኮምቦልቻ፣ መኾኒና አሸጎዳ እንዲሁም በ66 ኪሎ ቮልት ለማይጨው፣ ሰቆጣና ላሊበላ ኤሌክትሪክ እየሰጠ ይገኛል፡፡
ባለሙያው እንደገለፁት ጣቢያው ካሉት አራት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች መካከል አንዱ ብቻ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን ቀሪዎቹ ሦስት መስመሮች ለኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ዝግጁ ተደርገው ተቀምጠዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የየኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዝያ 24 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
በማከፋፈያ ጣቢያዉ የብሬከር ቅየራ እየተከናወነ ነው
…….///…….
የይርጋለም ቁጥር 1 ባለ 132 ኪሎ ቮልት የማከፋፊያ ጣቢያን ለማዘመንና የኦፕሬሽን ሥራውን ለማቀላጠፍ የሚያስችል የመቆጣጠሪያ ወይም ብሬከር ቅየራ እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ ገለፁ፡፡
ኃላፊው አቶ ፈይሰል ዋቤ እንደገለፁት የደንበኞችን ፍላጎት ለማሟላት የማከፋፈያ ጣቢያዉን አቅም የማሳደግና የማሻሻል እንዲሁም መቆጣጠሪያዎችን የማዘመን ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው፡፡
የማከፋፈያ ጣቢያዉ ሦስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት እና ሦስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ሲኖሩት ለይርጋለም ከተማና አካባቢው፣ ለይርጋለም ችፑድ ፋብሪካ፣ ለአፖስቶ፣ ለሀንጠጤ፣ ለለኩ ከተማ፣ ሀገረ ሰላም፣ በንሳ ዳዬ እና በዙሪያቸው ላሉ አካባቢዎች ኃይል እያቀረበ መሆኑን ኃላፊው ገልፀዋል፡፡
በደቡብ አንድ ሪጅን የማከፋፊያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ክፍል ሥራ አስኪያጅ አቶ ያለው አማረ በበኩላቸው የብሬከር ቅየራው ኃይል ሳይቋረጥ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ቀደም ሲል በሪጅኑ በሚገኙት በሻኪሶና ሻሸመኔ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ባለ 33 ኪሎ ቮልት መቆጣጠሪያዎች ቅየራ መከናወኑን አስታውሰው በአሁኑ ወቅት በዲላ፣ ሻሸመኔና በይርጋለም ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ተመሳሳይ ሥራ እየተከናወነ እንደሆነ አብራርተዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር
↠https://twitter.com/EEPethiopia
ሊንክዲን↠
https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
ዩትዩብቻናል↠
https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ሚያዝያ 24 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
ዓለም አቀፍ የሠራተኞች (የላብ አደሮች) ቀን !
📌ሜይ ደይ ወይም ሌበር ደይ በሚሉ ስያሜዎች የሚታወቀው ዓለም አቀፍ የላብ አደሮች ቀን ሚያዚያ 23 ወይም እ.ኤአ. ግንቦት 1 ይከበራል።
📌 በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ የኢንደስትሪ መስፋፋትን ተከትሎ በርካታ የዓለማችን ሀገራት ሠራተኞች እስከ 16 ሰዓታት ድረስ ለመስራት ይገደዱ እንደነበር በታሪክ ድርሳናት ላይ ሰፍሯል፡፡ ይህም በርካቶችን ለከፍተኛ የጤና ጉዳት፣ ለዘላቂ የጤና ቀውስ እና ለሞት ዳርጓል። በዚህ የተነሳ በ1886 የተካሄደው የአሜሪካ የሠራተኞች ማህበራት ንቅናቄ ለላብ አደሮች ቀን መጀመር ምክንያት ሆኗል፡፡
📌 የላብ አደሮች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ሚያዚያ 23 ወይም እ.ኤአ. ግንቦት 1 ቀን እንዲከበር የተወሰነው እ.ኤ.አ. ግንቦት 4 ቀን 1886 በቺካጎ ሄይማርኬት በነበረው ህዝባዊ ሰልፍ ላይ በፈነዳ ቦንብ የሞቱና የታሰሩ ሰዎችን ታሳቢ በማድረግ ነው።
📌 በውሳኔው መሰረት ዝቅተኛ የክፍያ ወለል እንዲወሰን፣ በቀን 16 ሰአታት መስራትና ሌሎችንም የሠራተኞች የመብት ጥያቄዎች ባነገቡ ማህበራትና ንቅናቄዎች የሥራ ሠዓት በቀን ወደ 8 ሠዓት ዝቅ እንዲል ተደርጓል። ይህም ዛሬ ላለው የሥራ ሰዓት መነሻ ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡
📌 በዓለምአቀፍ ደረጃ 3 ነጥብ 62 ቢሊየን ላብ አደሮች እንደሚገኙ ይገመታል።
📌 ዓለምአቀፉ የሠራተኞች (የላብ አደሮች) ቀን “በአምራች ኢንዱስትሪዎች እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ምቹ የሥራ ሁኔታ ለማህበራዊ ፍትህ” በሚል መሪ ቃል በዓለምአቀፍ ደረጃ ለ136ኛ ፤ በሀገራችን ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ ይከበራል፡፡
እንኳን ለዓለም አቀፍ የላብ አደሮች ቀን አደረሳችሁ!
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር
↠https://twitter.com/EEPethiopia
ሊንክዲን↠
https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
ዩትዩብቻናል↠
https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ሚያዝያ 23 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
የማከፋፈያ ጣቢያውን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች ተጀምረዋል
……..///……
የይርጋለም 2 ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ መጫን ከሚችለው 450 ሜጋ ዋት ኃይል ውስጥ እስከ 410 ሜጋ ዋት የሚሆነውን ለደንበኞችና ለተለያዩ ማከፋፈያ ጣቢያዎቹ እያቀረበ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ተስፋዬ ኢርባ እንደተናገሩት ማከፋፈያ ጣቢያው የሚቀርቡለትን የኃይል ጥያቄዎች ለመመለስ የአቅም ማሳደግ ሥራ ማከናወን ያስፈልገዋል፡፡
ጣቢያው በአራት የባለ 400 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመሮች ከወላይታ ሶዶ 2 ማከፋፈያ ጣቢያ እና ከገናሌ ዳዋ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ኃይል ተቀብሎ የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ባላቸው 13 ወጭ መስመሮች ለጩኮና አለታ ወንዶ ከተሞች፣ ለይርጋለም ኢንዱስትሪ ፓርክ፣ ለዳታ ማይኒንግ እንዲሁም ለሐዋሳ 2፣ ዲላና ይርጋለም 1 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል እያቀረበ ይገኛል፡፡
በጣቢያው ላይ ያሉት የባለ 400/230 ኪሎ ቮልት ትራንስፎርመሮች እየሞሉ በመምጣታቸው በ2016 ዓ.ም 50 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ ቢቀመጥም ተጨማሪ የኃይል ጥያቄዎችን ማስተናገድ እንዳልተቻለ ተናግረዋል፡፡
በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ የፕሮግራም 3 ተወካይ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራ እንደተናገሩት ይርጋለም 2 ማከፋፈያ ጣቢያን ጨምሮ በወላይታ ሶዶ 2 እና ሱሉልታ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የአቅም ማሳደግ ሥራ ለማከናወን የሚያስችሉ ሥራዎች ተጀምረዋል፡፡
ለአቅም ማሳደግ ሥራው የሚያስፈልጉ የትራንስፎርመሮች ግዢ፣ የዲዛይን፣ የሙከራ እና ፍተሻ ሥራዎችን ለማከናወን የሚያስችል ዓለም አቀፍ ጨረታ ወጥቶ በአሁኑ ወቅት የተወዳዳሪዎችን የጨረታ ሰነድ የመገምገም ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡
በ2011 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረው የይርጋለም 2 ማከፋፈያ ጣቢያ በባለ 400/230 ኪሎ ቮልት 500 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች እንዲሁም በባለ 230/132/15 ኪሎ ቮልት 250 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች አሉት፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዝያ 23 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
ጣቢያው የኃይል አቅርቦትን በማሻሻል የላቀ ድርሻ እየተወጣ ነው
………///…….
በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሆለታ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ወደስራ ያስገባቸው አዳዲስ የቴክኖሎጂ ውጤቶች የኃይል አቅርቦትን በማሻሻል የላቀ ድርሻ እየተወጡ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ።
ሥራ አስኪያጁ አቶ ጥላሁን አዘዘው እንደገለፁት ጣቢያው ለአካባቢው ማህበረሰብ እና በኢንቨስትመንት ዘርፍ ለተሰማሩ በርካታ አምራች ድርጅቶች የተሟላ ኃይል በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡
የጥገና ባለሙያ ተዳቻ ገናሌ በበኩላቸው ጣቢያው የተገጠመለት ጂ አይ ኤስ መቆጣጠሪያ እና ሌሎች የቴክኖሎጂ ውጤቶች ጣቢያው ኃይል ሳይቆራረጥ ደንበኞች ጋር ለማድረስ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ተናግረዋል።
የኃይል መቋረጥ በሚከሰትበት ወቅት በቀላሉ ችግር የደረሰበትን መስመር እና የችግሩን ዓይነት እንዲሁም የችግሩን መጠን በመለየት የተሳካ፣ ፈጣንና ደህንነቱ የጠበቀ መፍትሔ ለመስጠት እንደረዳቸው ገልፀዋል።
የሆለታ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ500 ኪሎ ቮልት በደዴሳ በኩል በመቀበል ወደ 400 ኪሎ ቮልት ፤ለውጦ ለአቃቂ፣ ሰበታ እና ሱሉልታ ማከፋፈያ ጣቢያዎች፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ለዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች፣ ለደይሊ ውሃ እና ሀበሻ ሲሚንቶ ኃይል እያቀረበ ይገኛል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዝያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
በሪጅኑ በኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት 90 በመቶ ቀንሷል
……..///……….
የምስራቅ ሁለት ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ በጅግጅጋ ከተማ ሲያካሂድ የቆየውን የ2017 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ አጠናቀቀ።
የሪጅኑን የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም ያቀረቡት በሪጅኑ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቁ ሙሉ እንደገለፁት ሪጅኑ አምስት የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ያላቸውን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እያስተዳደረ ይገኛል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በ1 ሺህ 643 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች እና 719 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የቁጥጥር እና ጥገና ሥራዎች መከናወናቸውን እንዲሁም በጅግጅጋ ማከፋፈያ ጣቢያ የ33 እና 15 ኪሎ ቮልት የጂ.አይ.ኤስ ስዊችጊር ቅየራ ሥራ መከናወኑንም በሪፖርቱ አንስተዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሪጅኑ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ስርቆትን ለመከላከል ከሶማሌ፣ ኦሮሚያ እና ሐረሪ ክልሎች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች መደረጋቸውን የገለፁት አቶ ወርቁ በዚህም ምክንያት አንድም የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ካለመውደቁም ባሻገር በሪጅኑ ያለው የስርቆት መጠን 90 በመቶ መቀነሱን ጨምረው ጠቅሰዋል።
የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ አብዱላሂ አብሽር በግምገማው ማጠናቀቂያ ላይ እንደተናገሩት ለህብረተሰቡ ያልተቆራረጠና አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል አለበት።
በአራተኛው ሩብ ዓመት የሪጅኑ ዕቅዶች ለማሳካት ሁሉም የሪጅኑ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ርብርብ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዝያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
