ውሉደ ብርሃን ሚድያ
Открыть в Telegram
የመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ውሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት መንፈሳዊ ጽሑፎችን፣ ወቅታዊ ሁኔታዎችን የሚገልፁ መረጃዎችን እንዲሁም ማስታወቂያዎችን የምንለቅ ስለሆነ እንድትከታተሉን እንጠይቃለን። 👋👋👋👋👋👋👋👋👋👋 መልእክት ካሎት በዚህ ሊንክ ይላኩልን ⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️ @saint_kirkos ግሩፕ ውስጥ ለመቀላቀል @weludebirhanGroup
Больше3 604
Подписчики
-124 часа
+87 дней
+1030 день
Архив постов
3 604
3 604
3 604
3 604
3 604
3 604
3 604
3 604
3 604
+1
“ሁለቱም አንድ አካል ይሆናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡”
ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት
በዕለት ሐሙስ ሐምሌ ፲፮/፳፻፲፰ ዓ.ም. በመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ጋብቻችሁን የፈጸማችሁትን የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት ወንድማችን ካሳሁን አለሙ እና እህታችን ሰላማዊት ወልዴ የፈጸማችኹትን ጋብቻ፤ የአብርሃምንና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፥ ያጣምራችሁ፥ ያዋሕዳችሁ።
መልካም ምኞት ይመኛሉ የውሉደ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በሙሉ።
3 604
3 604
3 604
+5
ቅዱስ ቂርቆስ በዕለተ ቀኑ የምስራች አሰምቶናል
✍️ ደብራችን ሊያስገነባው ላሰበው ከበር አስከ በር ፕሮጀክት የግንባታ ፈቃድና ሌሎች ተያያዥ ዶክመንቶች ከሚመለከተው የመንግስት አካል ፈቃድ አግኝቶ ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም. በቅዱስ ቂርቆስ በእለተ ቀኑ የደብራችን አስተዳዳሪ የነበሩትና በቅርቡ ወደ ጎላ ሚካኤል የተዘዋወሩት መልኣከ ፀሐይ አባ ብርሃነሥላሴ እና ጉዳዩን በቅርበት ሲከታተል የነበረው የሰንበት ት/ቤታችን አባል አርክቴክት ሮቤል አበበ ተቀብለዋል። አምላከ ቂርቆስ ስሙ የተመሰገነ ይሁን።
✍️ ከታህሳስ ጀምሮ አታካች ምልልሶች የነበሩት የግንባታውን ፈቃድ የማግኘት ሂደት ከደብሩ አካውንት ምንም ወጪ ሳይደረግ በሰበካ ጉባኤው ም/ሊቀ መንበር በነበሩት በኢ/ር ሄኖክ ቦጋለ እና አብረውት በነበሩ ወንድምና እህቶች ከ140,000 (መቶ አርባ ሺህ) ብር በላይ ወጪ ወጥበት ለዚህ ደርሷል። ( ይህ ወጪ የኮንሰልታንት ቢሮ ቅጥርና ተያያዥ መሆኑን ማሳወቅ እንወዳለን)
✍️ በስራው .... ጊዜና ጉልበታችሁን እንዲሁም ገንዘባችሁን ለሰጣችሁ አምላከ ቂርቆስ አብዝቶ አትረፍርፎ እንዲሰጣችሁ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ሁሉ እንጸልያለን።
(የመረጃ ምንጭ:- አርክቴክት ሮቤል አበበ)
3 604
3 604
3 604
3 604
+1
የሰበካ ጉባኤ ምርጫ ተካሄደ
በትላንትናው እለት ሐምሌ 12/2018 ዓ.ም. በመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን በተካሄደው የሰበካ ጉባኤ ምርጫ ላይ ሰባት ካህናት እጩ የሆኑ ሲሆን አራቱ በድምጽ ብልጫ ተመርጠዋል እንዲሁም ከአምስት ምዕመናን መካከል ሦስቱ በድምጽ ብልጫ ተመርጠዋል በተጨማሪም ከሰንበት ትምህርት ቤት የሚገቡ እጩዎች የሰንበት ትምህርት ቤቱ ጽሕፈት ቤት ከአባላት ጋር በመነጋገር የመረጣቸውን ሁለት እጩዎች በስም ጠቅሶ በደብዳቤ በእለቱ አስገብቷል፡፡ በአጠቃላይ ስምንት ሰው ለቀጣይ ሦስት ዓመታት ሰበካ ጉባኤውን እንዲያገለግሉ በካህናት ፣ በሰንበት ትምህርት ቤት አባላት እና በምዕመናን ተመርጠዋል፡፡
ከካህናት
1. መምህር ዲ/ን ብሩክ ሶሎሞን (217)
2. ቀኝ ጌታ ጽጌ መንበሩ (210)
3. ሊቀ ጉባኤ ግርማ ቀሬ (198)
4. ሊ/ጠ አምሳሉ መንበሩ (80)
ከምዕመን
1. ዲ/ን ደስታ ገላየ (254)
2. ኢኒስፔክተር ሙሉቀን ልሞ (227)
3. አቶ ደምሴ ኃ/ማርያም (189)
ከሰንበት ት/ቤት
1. ወ/ሮ ድርሻዬ ተሰማ
ውሉደ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ለተመረጡት በሙሉ እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ከእነሱጋር እንዲሆን ዘወትር በጸሎት እና በመታዘዝ ለማገልገል ዝግጁ መሆኑዋን ማሳወቅ እንወዳለን፡፡
