Gurage Zone Government Communication Affairs
Открыть в Telegram
1 574
Подписчики
+224 часа
-17 дней
+630 день
Архив постов
የጉራጌ ዞን ቀይ መስቀል ማህበር በበጀት አመቱ 4 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በማውጣት ዘርፈ ብዙ ድጋፎችን ማድረጉን አስታወቀ።
ሰኔ 17/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)
የዞኑ ቀይ መስቀል ከአደጋ ምላሽ እስከ ቤት ግንባታ ድረስ የህዝብ አለኝታነቱን እያስመሰከረ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የጉራጌ ዞን ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፕሮግራም ዘርፍና የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ ተወካይ አቶ ሻሚል የሲሩ እንዳሉት፤ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ማህበረሰቡን የሚጠቅሙ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል።
የሰው ልጆች በየትኛውም ቦታ ለሚገጥማቸው የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ቀድሞ በመድረስ የማገዝና የተለያዩ ድጋፎች እያደረገ እንደሆነም አስረድተዋል።
ማህበሩ ለየት ብሎ በሚታወቅባቸው የገጠር የሳር ቤቶች ቃጠሎ ሲደርስ ፈጥኖ በመድረስ የአልባሳትና የቁሳቁስ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።
ማህበሩ በዞኑ የመድሃኑት መደብር ተደራሽነት በሌለባቸው ቦታዎችም መደብሮችን በመክፈት እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል
ከማህበረሰቡ የአሰፋፈር ሁኔታ ጋር ተያይዞ ጆፎረን ተከትሎ የሚሰፍሩ ቤቶች ብዛት ያላቸው በመሆኑ፣ በአንዱ ቤት እሳት ከተነሳ ብዙ ቤቶች የሚቃጠሉበት ሁኔታ መኖሩን አቶ ሻሚል ገልጸዋል።
በዚህም በየአመቱ ከሁለት መቶ እስከ ሶስት መቶ ቤቶች በእሳት የሚቃጠሉበት አጋጣሚ የሚኖር ሲሆን፣ ቅርነጫፍ ጽህፈት ቤቱ ፈጥኖ በመድረስ የቁሳቁስና የአልባሳት ድጋፍ እያደረገ እንደሆነም አመላክተዋል።
በተጨማሪም ጧሪና ደጋፊ ለሌላቸው አቅመ ደካሞች በመድረስ ምግብና ምግብ ነክ ነገሮች የማሰራጨት ስራ ይሰራል ያሉት አቶ ሻሚል፤ በየአመቱ ለሁለት አቅመ ደካሞች አዲስ ቤት ገንብቶ የማስረከብ ስራም እንደሚሰራም ጠቁመዋል።
የቀይ መስቀል በጎ ፍቃደኞች ወጣቶች በኢትዮጵያ ደረጃ ታዋቂ የሆኑበትና በየአመቱ "የመስጠት ቀን" በሚል በሚያከናውኑት የበጎ ፍቃድ ስራ ሊስትሮ በመጥረግ የሚያገኙትን ገንዘብ በማስቀመጥ እንዲሁም እግር ኳስ ውድድር ሲኖር የቀይ መስቀል አገልግሎት በመስጠት በሚያገኙት ገቢ ለምስኪኖች ምግብ የሚያበሉ እንደሆነ ተገልጿል።
በተጨማሪም እነዚህ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በቅርቡ በአጣጥ ሆስፒታል ተኝተው ለሚታከሙ 30 ረዳት ለሌላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ምግብ መመገባቸውን አቶ ሻሚል አስታውሰዋል።
የቀይ መስቀል ዋነኛ የበጀት ምንጩ አባላቱ ሲሆኑ፣ በእነዚህ አባላት በሚገኝ ገንዘብ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኝና በቀጣይም የተጠናከረ የአደጋ ስጋት ምላሽ እንደሚሰጥ ተገልጿል።
በበጀት አመቱ በተለያዩ ወረዳዎች ለተፈጠሩ የእሳት አደጋዎች ማህበሩ በመድረስ ምላሽ መስጠት የቻለ ሲሆን፤ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ከዞኑ አስተዳደር፣ ከዞኑ አደጋ ስጋት ጽህፈት ቤት፣ ከዞኑ ጤና መምሪያ እንዲሁም ከሌሎች የመንግስት ተቋማት ጋር ተቀናጅቶ እየሰራ መሆኑን አመላክተዋል።
አደጋ ለደረሰባቸው የማህበረሰብ ክፍሎች የሚረዱት ከአባላቱ በሚሰበሰበው ገንዘብ እንደሆነ ያስረዱት አቶ ሻሚል፤ በዚህ በጀት አመት ብቻ ወደ 4 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር ለአደጋ ስጋት ምላሽ፣ ለቤት ግንባታ፣ ለምግብና ምግብ ነክ ለሆኑ ነገሮች እንዲሁም ለተለያዩ ቁሳቁሶች ማዋል መቻሉን ገልጸዋል ሲል የዘገበው የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን መምሪያ ነው።
በዞኑ ለአረንጓዴ አሻራ ልማት ከፍተኛ ትኩረት በመሰጠቱ ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡ ይገኛል:- አቶ እንዳለ ስጦታው
በእኖር ወረዳ ከዚህ ቀደም ተራቁቶ የነበረ አንድ መቶ ሄክታር መሬት በአረንጓዴ አሻራ ልማት ውጤታማ መሆኑን ተገልጿል።
ሰኔ 13/2018ዓ.ም(ወልቂጤ) በጉራጌ ዞን እኖር ወረዳ ወቅታዊ ያረንጓዴ አሻራ ልማት እንቅስቃሴ የመስክ ምልከታ ተካሂዷል።
የጉራጌ ዞን ደንና አከባቢ ጥበቃ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ እንዳለ ስጦታው በመስክ ምልከታው ወቅት እንዳሉት እንደ ሀገር ከለውጡ መንግስት ወዲህ ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተሰጠው ልዩ ትኩረት ተከትሎ በዞኑ በዘርፉ በተሰራው ስራ በተባጭ ዘርፈ ብዙ ውጤቶች ተመዝግቧል ።
ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በዞኑ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በየአመቱ የደን ሽፋን መጠን እያደገ መምጣቱን የጠቀሱት ኃላፊው አሁን ላይ 26 ነጥብ 6 ፐርሰንት መድረሱንም ተናግረዋል።
መሬት መንከባከብና መጠበቅ እንደሚገባ አንስተው፣ ለዚህም የተጎዱና የተራቆቱ መሬቶችን ላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን እንደሚተከልም ገልጸዋል።
የዞኑን ማህበረሰብ በማሳተፍ ከዚህ ቀደም የተራቆቱና ለልማት የማይውሉ ከ16 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በመለየት የየአካባቢው አግሮኢኮሎጂ በጠበቀ መልኩ የተለያዩ ጠቀሜታ ያላቸው በሚሊየን የሚቆጠሩ ችግኞች በየአመቱ ሲተከሉ መቆየቱን አውስተዋል።
በዚህም በዞኑ የከርሰና ገጸ ምድር ውሃ እንዲጎለብት፣ በተለያዩ ምክንያቶች በጎርፍ ታጥቦ የሚሄደውን ለም መሬት ማዳን ከመቻሉም ባለፈ የዝናብ መጠን ከፍ እንዲልና ምርትና ምርታማነት እንዲያድግ አስችሏል ብለዋል።
ችግኝ መትከል ብቻ ግብ አይደለም የተተከሉትን ተንከባክቦ እንዲጸድቁ ማድረግ ነው ያሉት ኃላፊው በዚህም በተሰራው ስራ የዞኑ የችግኝ የጽድቀት መጠን 93 ፐርሰንት መድረሱንም አስረድተዋል።
በተለይም በዞኑ በሁሉም መዋቅሮች በአብዛኛው የተራቆቱና ለምርትና ምርታማነት የማይውሉ የተጎዱ መሬቶች ላይ ጥናት በማድረግ በደን የመሸፈን ስራ እየተሰራ መሆኑን አንስተው በእኖር ወረዳ ካሳይና ኮሰድ ቀበሌዎች ላይ በመስክ ምልከታ የታየው የደን ማሳ የዚሁ አንዱ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።
በወረዳው በካሳይ ቀበሌ ላይ 100 ሄክታር መሬት በላይ በፓይነስ መሸፈኑ አንስተው ይህም ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ አርሶ አደሩ ተጠቃሚ መሆናቸውም አመላክተዋል።
በኮሰድ ቀበሌ አርሶ አደሩ ባህርዛፍ እየነቀለ ፓይነስ ፓቹላ እየተከለ መሆኑን ማየታቸውን ጠቁመው፣ ይህም የግንዛቤ ስራ በመሰራቱና ጠቀሜታው በመረዳታቸው በመሆኑ ነው ያሉት።
በቀጣይ በዘርፉ የበለጠ ስራ በመስራት ህብረተሰቡ በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚ እንዲሆን እንደሚሰራም አስገንዝበዋል።
የእኖር ወረዳ ደንና አከባቢ ጥበቃ ልማት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ በቀለ በዙ በበኩላቸው፣ በወረዳው በዘርፉ በተሰራው ስራ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ጠቅሰው በዚህም የደን ሽፋን 25 ነጥብ 5 መድረሱን አንስተዋል።
በየአመቱ ከ1 ሺህ 4 መቶ በላይ ሄክታር መሬት በተለያዩ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው የተለያዩ ችግኞችን እንደሚተከል አንስተው በዚህም የጽድቀት መጠናን 91 ፐርሰንት በላይ ማድረስ ተችላል ብለዋል።
በወረዳው በካሳይ ቀበሌ በተራቆቱና በተጎዱ የወል መሬቶች ላይ ፓይነስ ፓቹላ፣ የጽድና የግራቪሊያ በመትከል ለማህበረሰቡ በማስረከብ አርሶ አርሶ በመንከባከብና በመጠበቅ ተጠቃሚ እየሆኑ መሆኑን ተናግረዋል።
ይህም ዝናብ በወቅቱ እንዲዘንብ፣ የገጸና የከርሰ ምድር ውሃ እንዲፈልቅና የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት እንዲያድግ ማድረጉንም አመላክተዋል።
አርሶ አደር ባምበታ ወጋደና አርሶ አደር ኧስዊጋ አባተ በእኖር ወረዳ የካሳይ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው፣ ነዋሪዎቹ እንዳሉት ስፍራው ችግኝ ሳይተከልበት በፊት መሬቱ በጎርፍ ተጠርጎ በወሰዱ ምንም ጥቅም የማይሰጥ እንደነበር አንስተዋል።
አጠቃላይ ማሳው 50 ሄክታር መሬት መሆኑን አንስተው በዚህም ፓይነስ ፓቹላ፣ ጽድና ሌሎችም ችግኞች ይገኙበታል ብለዋል።
በአካባቢው ችግኝ በመተከሉ የአፈር ለምነቱ ከመጠበቁ የተነሳ ሳር ማብቀል ጀምሯል፣ የአከባቢው የአየር ሁኔታ ከማስተካከሉም ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚ መሆናቸውን አንስተዋል።
ለዚህም ችግኞቹ ከመትከል ባለፈ እንዲጸድቁ ከእንሰሳትና ከሰው ንክኪ ነጻ እንዲሆኑ በአጥር በመከለል ሲጠብቁትና ሲንከባከቡት እንደነበር አንስተው ይህም በቀጣይም አጠናክረው እንዲቀጥሉም ገልጸዋል።
በጉራጌ ዞን ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው የዘንድሮ የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በሰላማዊ መልኩ ተጠናቀቀ።
ፈተናቸው ያጠናቀቁ ተማሪዎችም የአረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር በሌሎች የክረምት በጎ አድራጎት ስራዎችም ተሳትፈዋል።
ሰኔ 12/2018ዓ.ም (ወልቂጤ) በዞኑ ክልል አቀፍ ፈተናው በስኬት እንዲጠናቀቅ በቅንጅት በተሰራው ስራ ያለምንም ችግር በሰላማዊ መልኩ መጠናቀቁን የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ገለጸ።
የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መብራቴ ወልደማርያም የፈተናው መጠናቀቅ አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ የዘንድሮ የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ያለምንም ችግር በሰላማዊ መልኩ ተጠናቋል።
ፈተናው በ3መቶ 28 ትምህርት ቤቶችና በጉድኝት ማዕከላት 19 ሺህ 580 ተማሪዎች ፈተናው መውሰዳቸውን ጠቅሰው 2መቶ 91 ተማሪዎች ደግሞ በተለያዩ ምክንያቶች በፈተና ያልተቀመጡ መሆኑንም አቶ መብራቴ ገልጸዋል።
በዞኑ የዘንድሮ የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በሰላማዊ መልኩ ለማጠናቀቅ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ በቅንጅት በተሰራው ስራ ፈተናው ያለምንም ኩረጃ በስኬት ማጠናቀቅ መቻሉንም አስረድተዋል።
ክልል አቀፍ የ8ኛ ክፍል ፈተና በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ በየደረጃው ላሉ አመራሮች፣ ለፈተና አስፈጻሚዎች፣ ለትምህርት መምሪያና ጽህፈት ቤት የማኔጅመንት አካላትና ባለሙያዎች፣ ለወላጆች፣ ለተማሪዎች እና ለጸጥታ አካላት አቶ መብራቴ ምስጋና አቅርበዋል።
በፈተና መጨረሻ ተማሪዎቹ በተፈተኑባቸው ጣቢያዎች ግቢ የማፅዳት፣ ችግኝ የመትከል፣ የችግኝ መትከያ ጉድጓዶች የማዘጋጀት ስራዎች ያከናወኑ ሲሆን ዩኒፎርምና የተለያዩ ለፈተና የተጠቀሟቸው ቁሳቁሶችን ለቀጣይ ድጋፍ ለሚፈልጉ ተማሪዎች አበርክተዋል።
በዞኑ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በሰላማዊ መልኩ መጠናቀቁን የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ገለጸ።
ሰኔ 9/2018ዓ.ም (ወልቂጤ) በዞኑ የዘንድሮ የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በስኬት እንዲጠናቀቅ በቅንጅት የተሰራው ስራ በቀጣይም በ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ላይ መድገም እንደሚገባም ተመላክቷል።
የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መብራቴ ወልደማርያም የፈተናው መጠናቀቅ አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ በዞኑ የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ያለምንም ችግር በሰላማዊ መልኩ መጠናቀቁን ገልጸዋል።
በዞኑ በ3መቶ 80 አስፈታኝ ትምህርት ቤቶችና በጉድኝት ማእከላት በማደራጀት 18 ሺህ 3 መቶ 90 ተማሪዎች ክልል አቀፍ ፈተናው መውሰዳቸው ገልፀዋል።
በዞኑ የዘንድሮ የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በሰላማዊ መልኩ ለማጠናቀቅ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ በቅንጅት በተሰራው ስራ ፈተናው በስኬት ማጠናቀቅ መቻሉንም አስረድተዋል።
ክልል አቀፍ ፈተናው በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ በየደረጃው ላሉ አመራሮች፣ አስፈጻሚዎች፣ ለትምህርት አመራሮች እና ለጸጥታ አካላት አቶ መብራቴ ምስጋና አቅርበውዋል።
ይህ ውጤታማነትና ቅንጅት በቀጣይ ከሰኔ 11 እስከ 12 በሚሰጠው የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ላይ መድገም እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
የዘንድሮ የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናው ከኩረጃ ነጻና በሰላማዊ መልኩ በመስጠት በስኬት ለማጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ ተገለጸ።
ሰኔ 8/2018ዓ.ም (ወልቂጤ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ በዛሬው እለት እየተሰጠ ያለውን ክልል አቀፍ ፈተና አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሀን ማብራሪያ ሰጥተዋል
በአዲሱ ትምህርት እና ስልጠና ፖሊሲ በ6ኛ፣በ8ኛ እና በ12 ኛ ክፍል በተለያዩ እርከኖች ተማሪዎች ክልል አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ፈተና ይወስዳሉ በማለት ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።
በተያዘው የትምህርት ዘመን የ6 ኛ ክፍል ተማሪዎች ለፈተና በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ በትኩረት መሰራቱን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት በክልሉ 91ሺህ 9መቶ 18 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ክልላዊ ፈተናውን እየወሰዱ ይገኛሉ።
ቢሮው በዘንድሮ ዓመት ለሚሰጠው ሀገራዊና ክልላዊ ፈተና ተማሪዎች የማዘጋጀት ስራ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።
የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናው ከሰኔ 8 እስከ 9 ከኩረጃ ነጻ በሆነ መልኩ እንደሚሰጥ የጠቀሱት አቶ አንተነህ በቀጣይ ከሰኔ 10 ጀምሮ በክልሉ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ይሰጣል ብለዋል።
የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መብራቴ ወልደማርያም በበኩላቸው ፈተናው በዞኑ በ3መቶ 80 አስፈታኝ ትምህርት ቤቶችና በ2 መቶ 24 የፈተና ማዕከላት 18 ሺህ 4መቶ 60 ተማሪዎች እንደሚወስዱ አንስተው ከነዚህም ውስጥ 8ሺህ 9መቶ 71 ተማሪዎች ሴቶች መሆናቸውንም ተገልጿል።
ለፈተናው ከአመቱ መጀመሪያ ጀምሮ ተማሪዎች የማብቃትና የመደገፍ ስራ መሰራቱን ያነሱት አቶ መብራቴ ከዚህም ባለፈ ለፈታኞች፣ ለሱፐርቫይዘሮች፣ ለጣቢያ ኃላፊዎች፣ ለፈተና ማዕከላትና ለጸጥታ አካላት ልየታና ኦረንቴሽን የመስጠት ስራ ሲሰራ መቆየቱንም ተናግረዋል።
በዞኑ የዘንድሮ የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በስኬት ለማጠናቀቅ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱንም አንስተዋል።
ፈተናው ከአዲስ አበባ ከህትመት ማዕከል በሰላማዊ መልኩ ወደ ዞኑ በማስገባት ከዞኑ ወደ ሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደሮችና ፈተና ጣቢያዎች በሰላማዊ መልኩ እንዲሰራጭ መደረጉንም አመላክተዋል።
ክልል አቀፍ ፈተናው በሰላማዊ መልኩና ከኩረጃ ነጻ በመስጠት በስኬት እንዲጠናቀቅ ወላጆች፣ ፈታኝ መምህራን፣ ፈተና አስፈጻሚዎች፣ ቤተሰብና የጸጥታ አካላት ጨምሮ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና አስጀመሩ
ሰኔ 8/2018(ወልቂጤ)
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድ እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በወልቂጤ ከተማ በያበሮስ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት አስጀምረዋል።
ርዕሰ መስተዳድ እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በማዕከሉ የፈተና አሰጣጥ ሂደት ምን እንደሚመስል በየክፍሉ ተዟዙረው የተመለከቱ ሲሆን ተማሪዎች በራስ መተማመን መንፈስ ፈተናውን በተረጋጋ መልኩ እንዲሰሩ አበረታተዋል።
በክልሉ 91918 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ክልላዊ ፈተናውን እየወሰዱ እንደሆነ ተጠቅሷል።
የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናው ዛሬ እና ነገ ተሰጥቶ የሚጠናቀቅ ሲሆን ቀጥሎ በክልሉ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና መሰጠት እንደሚጀምር ተገልጿል።
ቢሮው በዘንድሮ ዓመት ለሚሰጠው ሀገራዊና ክልላዊ ፈተና ተማሪዎች የማዘጋጀት ስራ በትኩረት ሲከናወን መቆየቱን ጠቁመዋል።
በማስጀመርያ መርኃ ግብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)፣ የክልሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ክብርት ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ ጨምሮ ሌሎችም የክልሉ፣ የዞኑና የከተማው ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና ሌሎችም ተገኝተዋል።
በጉራጌ ዞን የጽዱ ኢትዮጵያ እሳቤ አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ ከመሆኑም ባሻገር ህብረተሰቡ ባህል እያደረገው ይገኛል፦አቶ አየለ ፈቀደ
ሰኔ 6/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)
በጉራጌ ዞን ጌታ ወረዳ የኽብያቴ ጽዱ ቀበሌ የተለያዩ እንግዶችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ነጭ ባንድራ በመስቀል በዛሬው እለት ተመርቋል።
በወረዳው ከጽዱ ቀበሌነት ባለፈ ከቤት ለቤት ወሊድ ነጻ የሆኑ መንደሮችን የመፍጠርና የጆፎረ ማስፋት የኮሪደር ልማት ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በምረቃው ስነ ስርአት ላይ የተገኙት የጉራጌ ዞን ጤና መምሪያ ሀላፊ አቶ አየለ ፈቀደ እንዳሉት በዞኑ የጽዱ ኢትዮጵያ ኢንሼቲቭ ተግባራዊ በማድረግ በርካታ ቀበሌዎች ጽዱ ማድረግ መቻሉም አስታውሰዋል።
በዞኑ 87 በመቶ የሚሆኑ ቀበሌዎች ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነፃ በሚል የማስመረቅ ስራ መሰራቱም የተናገሩት አቶ አየለ እስከ ሰኔ 30/2018 ድረስ ሁሉም ቀበሌዎች ጽዱ በማድረግ ለማስመረቅ አቅደው እየሰሩ እንደሆነ ተናግረዋል።
የዞኑ የተሻሻለ መጸዳጃ ቤት ሽፋኑ ከፍ ለማድረግ አጽኖት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ የተናገሩት አቶ አየለ በዞኑ አጠቃላይ ካለው አባወራ 69 በመቶ የሚሆኑ አባወራዎችና እማወራዎች መጸዳጃ ቤታቸው የተሻሻለ ማድረግ ችለዋል ብለዋል።
በጌታ ወረዳ የኽብያቴ ቀበሌ ከአር ነጸና ጽዱ ቀበሌ በሚል በዛሬው እለት ነጭ ባንድራ የመስቀል ማስመረቅ እንደተቻለ የጠቆሙት ሀላፊው በወረዳው እናቶች ገንዘብ በሠቆጠብ የአካባቢና የግል ንጽህና ስራዎች በስፋት እየሰሩ ያለበት ሁኔታ መኖሩም አስረድተዋል።
የጌታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ በህሩ ኽይረዲን በበኩላቸው እንዳሉት ጤና የሁሉም ነገር መሰረት ነው ብለው በጤናው ዘርፍ የሚሰሩ ስራዎች በተደራጀ መንገድ በመምራት የተሻለ ውጤት ማምጣት ይቻላል ብለዋል።
የአካባቢና የግል ንጽህና ለመጠበቅ በወረዳው ከ2017 መግቢያ ጀምሮ በብዙ ቀበሌዎች ተግባራዊ ማድረግና በዘርፉ ውጤታማ ስራዎች በመስራት ማህበረሰቡ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉም አስረድተዋል።
ስንቀናጅና ስንተባበር ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል የተናገሩት አቶ በህሩ በወረዳው ጽዱ ቀበሌና መንደር ለመፍጠር እየተሰሩ ያሉ ውጤታማ ስራዎች በሁሉም ቀበሌዎች ማስፋት እንደሚገባም አመላክተዋል።
ከግልና ከአካባቢ ጽዱ ቀበሌነት ባለፈ የቤት ለቤት ወሊድ ጭምር ነጻ የሆነ ቀበሌ ነጻ ቀበሌ እንዲሁም ከኮሪደር ልማት ጋር ተያይዞ በገጠር ቀበሌ የጆፎሮ ማስፋት በሚል በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውም አስረድተዋል።
የጌታ ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አብድሃሚድ መሀመድ እንዳሉት ጥራቱን የጠበቀ፣ ፍትሃዊና ተደራሽ የጤና አገልግሎት ለማህበረሰቡ በመስጠት በወረዳው የህዝቡ የጤና ደህንነት ለመጠበቅ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወነ ይገኛል።
በንጽህና ጉድለት የሚመጡ ተላላፊና መሰል በሽታዎች ለመከላከል ደረጃውን የጠበቀ የግለሰብና የጋራ መጸዳጃ ቤቶች ገንብተው እንዲጠቀሙ በማድረግ እንዲሁም ከመጸዳጃ ቤት መልስ እጅን በአግባቡ በውሃና በሳሙና እንዲጠቀሙ ለማድረግ ሰፊ የግንዛቤ ስራ መሰራቱና በዚህም በተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ ይገኛል ብለዋል።
የጽዱ ኢትዮጵያ ኢንሼቲቭ በወረዳው ተግባራዊ መደረግ ከተጀመረ በኋላ በርካታ ስራዎች ማከናወን የተቻለ ሲሆን በዚህም ጽዱ ቀበሌ ለመፍጠር ሰፊ የማህበረሰብ ንቅናቄ በመፍጠርና በዘርፍ ውጤታማ ስራ ማከናወን መቻሉም አስታውሰዋል።
የጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አብይ አህመድ የጽዱ ኢትዮጵያ ኢንሼቲቭ ከዩኒሴፍ ጋር በመተባበር ላውንች ከተደረገበት ጊዜ አንስቶ በርካታ ስራዎች ማከናወን የቻሉ እንደሆነም የተናገሩት ሀላፊው በ2018 በጀት አመት በወረዳው 7 ቀበሌዎች ታርጌት በማድረግ ሶስት ቀበሌዎች ሙሉ ለሙሉ ጽዱ በማድረግ ነጭ ባንድራ በመስቀል ማስመረቅ እንደተቻለና 4 ቀበሌዎች ለማስመረቅ ጫፍ መድረሳቸውም አስረድተዋል።
ወይዘሮ አመቱ ብዛ እና ወይዘሮ ወርቅነሽ ንበርጋ በወረዳው የኽብያቴ ቀበሌ ልዩ ስሙ የሰህረይ መንደር ነዋሪ ሲሆኑ ቀበሌያየው ጽዱ ለማድረግ የተሻሻለ መጸዳጃ ቤት ገንብተው እየተጠቀሙ እንደሆነም ተናግረዋል።
የግልና የአካባቢ ንጽህና ለመጠቅ ሴቶች በአንድ ለአስር አደረጃጀት ገንዘብ በመቆጠብ የተሻሻለ መጸዳጃ ቤት መገንባት ፣ግቢያቸው በማጽዳትና ጆፎሮን በመጥረግና በማስዋብ ውጤታማ ስራ እየሰሩ እንደሆነ ተናግረዋል ሲል የዘገበው የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን መምሪያ ነው።
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
