ar
Feedback
Gurage Zone Government Communication Affairs

Gurage Zone Government Communication Affairs

الذهاب إلى القناة على Telegram

Gurage Zone Government Communication Affairs

إظهار المزيد
1 575
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+47 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
አመራሩ በሚቀጥሉት 20 ቀናት በበጀት ዓመቱ ልዩ ትኩረት የሚሹ ቀሪ ስራዎችን በፍጥነት በጥራትና በቁርጠኝነት ሊያሳካ ይገባል፦ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ ግንቦት 29/2018(ወልቂጤ)የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ በበይነ መረብ ልዩ ትኩረት የሚሹ ወቅታዊና መደበኛ ስራዎችን በመገምገም የበጀት አመቱ ቀሪ ስራዎች በሚቀጥሉት 20 ቀናት እንዲጠናቀቁ አቅጣጫ አስቀመጡ!! የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ልዩ ትኩረት የሚሹ ወቅታዊና መደበኛ የንቅናቄ ስራዎች በበይነ መረብ ገምግመዋል!! ክቡር ዋና አስተዳዳሪው የፋይዳ መታወቂያ ስርጭት፣የኢቲዮ ኮደርስ ስልጠና፣የገጠርና የከተማ ኮሪደር ልማት ስራዎች፣የገቢ ፣የግብርና፣የንግድ፣ የስራ እድል ፈጠራና የነዳጅ ስርጭት ሁኔታ የደረሱበት አፈፃፀም ገምግመው በቀጣይ 20 ቀናት ታቅደው መሰራት ባለባቸው ተግባራት ላይ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። ዞናችን በተያዘው በጀት ዓመት በሁሉም ዘርፎች ውጤት እያስመዘገበ የመጣና በሌሎች እካላትም በተለያዩ የሱፐርቪዥን ስራዎች የተረጋገጠ ነው በማለት እነዚህን የካበቱ ልምዶችንና የህዝባችንን አቅም በመጠቀም በሚቀጥሉት 20 ቀናት ውስጥ ቀሪ ስራዎች ሊጠናቀቁ እንደሚገባ አሳስበዋል። የህብረተሰባችን የኑሮ ጫናን ለመቀነስ በገበያ ዋጋ ማረጋጋት ላይ የምንሰራው ስራ ልዩ ትኩረት ልንሰጠው ይገባል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው የሰንበት ገበያዎች በቂ ግብዓት እንዲኖራቸው መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል። ህገወጥ የንግድ ስራዎች ላይ ልዩ ቁጥጥር በማድረግ አላስፈላጊ የዋጋ ንረት በሚፈጥሩ ነጋዴዎች ላይ አስተማሪ እርምጃ መውሰድ ይገባል ብለዋል። በነዳጅ አቅርቦት ስጭትና ህገወጥነቶች ላይ እየተሰሩ ያሉት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ቢሆንም አሁንም ቀሪ ስራዎች ስላሉ አቅዶ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። በዞኑ በተለይም በከተሞች ህገ ወጥ የነዳጅ ክምችት በሚያደርጉና በአላስፈላጊ መንገድ ነዳጅ እየሸጡ የሚገኙ አካላት ላይ ልዩ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚገባም ጠቁመዋል። በሚቀጥሉት 20 ቀናት ያላሳካናቸው ቀሪ የአመቱ እቅዶቻችንን ምርጫን ባሳካንበት መንገድ ሙሉ በሙሉ ልናሳካ ይገባል ያሉት ክቡር አስተዳዳሪው በተለይም የገቢ ስራችን ያሉንን ሁሉም አማራጮች ተጠቅመን ገቢን አሟጣን ልንሰበስብ እንደሚገባ አሳስበዋል። በገቢ አሰባሰብ ላይ አፈፃፀማቸው ዝቅተኛ የሆኑ መዋቅሮች በሚቀጥሉት 20 ቀናት በልዩ ሁኔታ እቅዳቸውን ሊያሳኩ እንደሚገባም በመግለፅ ሁሉም አስተዳደሮች 100% እቅዳቸው ማሳካት እንደሚገባቸው አፅንዎት ሰጥተዋል። በዞኑ የተከለሰውን የገቢ እቅድ ጨምሮ እስካሁን ለመሰብሰብ ከታቀደው ከ83 በመቶ በላይ መሰብሰብ መቻሉን የጠቀሱት ዋና አስተዳዳሪው በሚቀጥሉት 20 ቀናት ውስጥ ከ810 ሚሊየን ብር በላይ በመሰብሰብ ቀሪ እቅዱን ማሳካት ይገባል ብለዋል። ወቅታዊ የግብርና ልማት ስራዎችም በተገቢውና በልዩ ትኩረት መምራት እንደሚገባ በመጠቆም ዘወትር እንደምንለው አመራሩ ከግብርና ልማት ስራዎች አይኑ ሊነቅል አይገባውም ብለዋል። በዞኑ አንድም ያልታረሰ መሬት እንዳይኖር እየተሰራ ያለው ስራ ውጤት እያስገኘ ቢሆንም በአንዳንድ መዋቅሮች የሚታየው ጉድለት በፍጥነት ማረም እንደሚገባ አሳስበዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እውን ለማድረግ የፋይዳ መታወቂያ ሁሉም ሊኖረው ይገባል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ካለ ፋይዳ መታወቂያ ምንም አገልግሎት ማግኘት የማይቻልበት ደረጃ እየደረስን እንደሆነ ልናውቅና ህዝቡንም ልናስገነዝብ ይገባል ብለዋል። ክቡር ጠቅላይ ሚንስትራችን የ100% ግብ ብለው የያዙት የፋይዳ መታወቂያ ጉዳይ በተያዘው በጀት አመት 100% ለማሳካት መስራት እንደሚገባ በማመላከት አሁን ከተደረሰበት አፈፃፀም አንፃር ሰፊ ውስንነት እንዳለበት ጠቁመዋል። በአምስቱም ከተሞቻችን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች በአጭር ቀናት እንዲጠናቀቅ ተቋራጮች 24 ሰዓት እንዲሰሩ ማድረግ ይገባል ያሉት አቶ ላጫ ለዚህም አመራሩ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አሳስበዋል። የገጠር ኮሪደር በተመለከት በአንዳንድ መዋቅሮች ተስፋ ሰጪ ጅምሮች እንዳሉ በመጠቆም ፕሮግራሙ ከሌማት ትሩፋትና ከፅዱ መንደር ጋር ማያያዝ ያስፈልጋል ብለዋል። ሞዴል የገጠር መንደር መፍጠር ላይ ታዳጊ ማዘጋጃዎች ላይ ቦታ መርጦ ወደ ተግባር የገባ መዋቅር ቁጥር አነስተኛ መሆኑን በመግለፅ በቀሪ ጊዜት በአስሩም መዋቅር ስራው ሊጀመር እንደሚገባ አሳስበዋል። ከቋሚና ጊዜያዊ ስራ እድል ፈጠራ አንፃር ያሉ አፈፃፀሞች እድገት ቢያሳዩም በelmis ከመመዝገብ አንፃር ግን ያሉ ውስንነቶች እንዲታረሙና የተለዩ ስራ አጥ ዜጎችም ከአጋሮች ጋር በመሆን ወደ ስራ የሚገቡበት መንገድ ለማመቻቸት እየተደረገ ያለው ጥረት መጠናከር እንደሚገባው ጠቁመወል። ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገርነት ለመቀየር በምናደርገው ጥረት የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ወሳኝ ነው ያሉ ሲሆን የነገይቱን ኢትዮጵያን ከአለም ጋር ተፎካካሪ ለማድረግ ያለመና ለቴክኖሎጂ ቅርብ የሆነ ትውልድ ለመፍጠር ፕሮግራሙ ትልቅ ሚና እንዳለው አብራርተዋል። የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናው ከመስጠት ባሻገር ስልጠናውን ተጠቅመው ገቢ ማግኘትና ፈጠራ የጀመሩ ልጆችን ማበራከትና ማበረታታት ይገባል ብለዋል። ክቡር አስተዳዳሪው በመጨረሻም ወቅታዊ የግብርና የትምህርትና የጤና ስራዎችም በ20 ቀናት እንዲፈፀሙ ከታቀዱ ስራዎች ጋር አቀናጅቶ መምራት እንደሚገባ በመጠቆም ስራዎቹ ተገቢውን የክትትልና ግምገማ ስራዓት እንደተበጀላቸውም አስገንዝበዋል። በውይይቱ የክልል፣የዞን የወረዳና የከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ጨምሮ የሚመለከታቸው ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።

በዞኑ በ2018 በጀት ዓመት ኢኮኖሚው የሚያመነጨው የገቢ እቅድ ለማሳካትና ውጤታማ ለማድረግ የተቀናጀ ርብርብ መደረግ ይኖርበታል:- አቶ ሚነወር ሀያቱ ግንቦት 29/2018ዓ.ም(ወልቂጤ) የጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የቀሪ ጊዜያት ስራዎችንና የደረጃ "ለ" ግብር አሰባሰብ የቅድመ ዝግጀት የተግባር ስራዎች አስመልክቶ በየደረጃው ከሚገኙ የገቢ አመራርና አስተባባሪ አካላት ጋር በወልቂጤ ከተማ የምክክር መድረክ አካሂዷል። የጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሚነወር ሀያቱ እንዳሉት በዞኑ በ2018 በጀት ዓመት ኢኮኖሚው የሚያመነጨው የገቢ እቅድ ለማሳካት የቀሪ ጊዜያት ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም የገቢ አማራጮችን አሟጦ ለመሰብሰብ የተቀናጀ ርብርብ ማድረግ ይገባል። በዞኑ በበጀት አመቱ ለመሰብሰብ ከታቀደው 4 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ከነበረበት ዞኑ ካለው ፖቴንሺያል አንጻር እቅዱ በመከለስ 4 ነጥብ 8 ቢሊዮን ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልጸዋል። የተከለሰው እቅድ ሙሉ ለሙሉ ለማሳካት እየተሰራ መሆኑን አንስተው ይህ ዜና እስከጠናቀረበት ጊዜ ድረስ 4ቢሊዮን 18 ሚሊዮን ብር በመሰብሰብ የእቅዱ 83 ከመቶ ማሳካት መቻሉንም አቶ ሚነወር አመላክተዋል። የበጀት ዓመቱ እቅድ በማሳካት የተጀማመሩ የልማት ስራዎችን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ በቀሪ ጊዜያት የገቢ ስራዎችን አመራሩ በልዩ ትኩረትና ቁርጠኝነት መስራት እንዳለበት ተናግረዋል። በተለይም የተለከለሰው እቅድ ተከትሎ በእስካሁኑ የተሻለ የፈጸሙ ያሉ መዋቅሮች መኖራቸውን ያነሱት ኃላፊው ከዚህም ባለፈ የአፈጻጸም ልዩነት ያለባቸው መዋቅሮች በዞኑ ልዩ ድጋፍ በማድረግ እቅዳቸውን እንዲያሳኩ ይደረጋል ነው ያሉት። ከዚህም ባለፈ በበጀት አመቱ 1ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ከቫት ለመሰብሰብ እየተሰራ ስለመሆኑንም አንስተው ይህም በትኩረት በመሰብሰብ ገቢ ለማድረግ እየተሰራ ነው መሆኑን ጠቁመዋል። አክለውም ታክስ ካልሆኑ ከጤና፣ ከትምህርት ተቋማት፣ ከፍርድ ቤትና ንግድ ከሚያድሱ ነጋዴዎችና ከተወረሱ ንብረቶች የሚገኙ ገቢዎችን በመሰብሰብ ወደ መንግስት ቋት በማስገባት ለልማት መዋል እንዳለባቸውም ጠቁመዋል። በዞኑ በተሰበሰበው ገቢ በርካታ የልማት ስራዎች እየተሰራ መሆኑን የገለጹት አቶ ሚነወር በተለይም እየተከናወኑ ያሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ በቀሪ ጌዜያት የበጀት አመቱ እቅድ ማሳካት ይገባል ብለዋል። የበጀት ዓመቱን የገቢ ዕቅድ ለማሳካት የደረጃ 'ለ' የ2018 ግብር ዘመን ቅድመ ግብር ክፍያ በወቅቱ እንዲጠናቀቅ ልዩ ትኩረት ሠጥቶ መስራት እንደሚጠበቅም አውስተዋል። በ2019 በጀት ዓመት ለሚሰበሰበው የገቢ አሰባሰብ የመረጃ ማደራጀትና የቅድመ ዝግጅት ስራዎችም አመራሩና ባለሙያዎች በትኩረት መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። በመምሪያው የደንበኞች አገልግሎት የታክስ አሰባሰብና አወሳሰን ዳይሬክቶሬት አስተባባሪ አቶ ሷሊህ ጀማል የዉይይቱ ሰነድ ባቀረቡበት ወቅት ሁሉም አመራርና ባለሙያዎችን የቀሪ ጊዜት የእቅድ አፈጻጸም ለማሳካት በትኩረት መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች እንዳሉት በበጀት ዓመቱ የታቀደውን እቅድ በቀሪ ጊዜያት ለማሳካት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አውስተዋል። በተለይም በዞኑ በወረዳዎችና በከተማ አስተዳደር ያሉ የገቢ አማራጮችን አሟጦ በመሰብሰብ ህብረተሰቡ እያነሳቸው ያሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ምላሽ እንዲያገኙ አመራሩና ባለሙያዎች ርብርብ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

ዞን አቀፍ የጥያቄና መልስ ውድድሩ በተማሪዎች መካከል ጤናማ የፉክክር መንፈስ ከመፍጠር ባለፈ በክልልና ሀገር ፈተናዎች ላይ ከፍተኛ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች ቁጥር ከፍ ለማድረግ ፋይዳው የጎላ ነው:- አቶ መብራቴ ወልደማርያም ግንቦት 28/2018ዓ.ም(ወልቂጤ) የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የ2018 ዓ.ም ዞን አቀፍ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል አመታዊ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር በወልቂጤ ከተማ አካሂዷል። የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መብራቴ ወልደማርያም እንዳሉት የዘንድሮ ዞን አቀፍ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል አመታዊ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር ከዚህ ቀደም ከትምህርት ቤቶች ጀምሮ በወረዳና ከተማ አስተዳደሮች ሲካሄድ መቆየቱን አስታውሰዋል። የውድድሩ አላማ በዞኑ ከፍተኛ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች ቁጥር የማሳደግና በሁሉም የክፍል ደረጃ የሚገኙ ተማሪዎች በቀጣይ ለዞን አቀፍ ውድድር እንዲዘጋጁ ለማድረግና በተማሪዎች መካከል ጤናማ የውድድር መንፈስ ለመፍጠር ያለመ ነው ብለዋል። ከዚህም ባለፈ በክልልና ሀገር አቀፍ ፈተናዎች ከፍተኛ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች ለማፍራት ፋይዳው ከፍተኛ መሆኑንም ገልጸዋል። ይህ ውድድር ከዞኑ የተወጣጡ የተለዩ ጎበዝ 45 ተማሪዎች የተሳተፉበት መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ይህም በተማሪዎቹ መካከል ከፍተኛ ትንቅንቅ የታየበትና በወረዳዎችና በከተማ አስተዳደሮች መካከል ተቀራራቢ ውጤት መመዝገቡንም አስረድተዋል። በዚህ ውድድር የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የገንዘብና የሰርተፊኬት ሽልማት እንደተበረከተላቸው ያነሱት አቶ መብራቴ ይህም ሌሎችም ተማሪዎች ይህን ተሞክሮ በመውሰድ ለቀጣይ ውድድር ዝግጅት እንዲያደርጉ ያነሳሳቸዋል ብለዋል። ይህ ዞን አቀፍ የአሸናፊዎች አሸናፊ የአሸናፊ ውድድር በቀጣይ የመማር ማስተማር ስራ የበለጠ የሚያጠናክር ከመሆኑም ባለፈ መዋቅሮች ተማሪዎቻቸው እየለዩ እያበቁ እንዲሄዱና ጎበዝ ተማሪዎች እንዲለዩ የሚያደርግ መሆኑንም አመላክተዋል። ለውድድር የቀረቡ ጥያቄዎቹ የተሻለ አቅምና ስነምግባር ባላቸው መምህራን መዘጋጀቱን ጠቅሰው፣ በቀጣይም በተሻለ መልኩ በማጠናከር እንደሚዘጋጅ ጠቁመዋል። ቀጣይ የሚሰጠው ክልልና ሀገር ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች በቀሪ ጊዜያት ከትምህርት ቤት ሳይነጠሉ ከመዘጋጀት ባለፈ ቤተሰብ፣ ወላጆች፣ መምህራንና የትምህርት አመራሮች ተማሪዎችን መከታተል፣ መደገፍና ማብቃት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። በጥያቄና መልስ ውድድሩ የተሳተፉ ተማሪዎች እንዳሉት በውድድሩ የተሻለ ውጤት በማስመዝገባቸው ደስተኛ መሆናቸውን አንስተው ይህም በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አንስተዋል። ተማሪዎች ሳይዘናጉ በቀጣይ ለሚሰጠው ለክልልና ሀገር አቀፍ ፈተናዎች በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉም መክረዋል።

በዞኑ በቀጣይ በሚሰጠው የ8ኛና የ12ኛ ክፍል ክልልና ሀገር አቀፍ ፈተና የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ሁሉም ተማሪዎች ሳይዘናጉ በቂ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ተሸላሚ ተማሪዎች መከሩ። ግንቦት 28/2018ዓ.ም(ወልቂጤ) የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የ2018 ዓ.ም ዞን አቀፍ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል አመታዊ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር በወልቂጤ ከተማ አካሂዷል። በዞን አቀፍ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል አመታዊ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር ላይ አንደኛ በመሆን ካጠናቀቁ ተሸላሚ ከሆኑ ተማሪዎች መካከል ተማሪ ብሩክ ሰንብት ከጉንችሬ፣ ተማሪ የሺወርቅ አበበ ከወልቂጤና ተማሪ ሪሃና ሹሜ ከእምድብር ከተማ ይገኙበታል። ተማሪዎቹ በጋራ በሰጡት አስተያየት በዞን አቀፍ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር ላይ ከአጠቃላይ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ተሸላሚ በመሆናቸው ደስታ እንደተሰማቸው አንስተዋል። ለዚህ ውድድር አሸናፊ የመሆናቸው ሚስጥር ከመምህራኖቻቸው በቅርበት በመሆን የሚሰጣቸው ትምህርት በተገቢው ከመከታተል ባለፈ በራሳቸው ጥረት በቂ ዝግጅት እያደረጉ በመሆናቸው ስለመሆኑንም ገልጸዋል። ከዚህም ባሻገር ፕሮግራም በማውጣት ጊዜያቸውን በአግባቡ እንደሚያነቡ አንስተው ከዚህም ባለፈ ለትምህርታቸው አጋዥ የሆኑ ቪዲዮዎችን በማየትና ወርክ ሺቶችን እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ጎበዝ የመሆናቸው ሚስጥር ተማሪዎች የሚሰጣቸው መደበኛና የድጋፍ ትምህርት በተገቢው ከመከታተል ባሻገር በራሳቸው የተለያዩ ጥረቶችን እንደሚያደርጉም አውስተዋል። ቀጣይ የ8ኛና 12ኛ ክፍል ክልልና ሀገር አቀፍ ፈተናዎች መቃረቡን ተከትሎ ከሌሎች ተማሪዎች ለመወዳደርና የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በቂ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ያነሱት ተማሪዎቹ ሌሎችም ተማሪዎች ሳይዘናጉ ለትምህርታቸው ትኩረት በመስጠት በቀሪ ጊዜያት ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉም መክረዋል።

በተካሄደው የ2018 ዓ.ም ዞን አቀፍ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል አመታዊ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር. አጠቃላይ ውጤት ከከተማ አስተዳደሮች ወልቂጤና ከወረዳዎች ምሁር አክሊል ወረዳ አሸናፊ ሆኑ። ግንቦት 28/2018ዓ.ም(ወልቂጤ) የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የ2018 ዓ.ም ዞን አቀፍ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል አመታዊ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር በወልቂጤ ከተማ አካሂዷል። በተካሄደው የ2018 ዓ.ም ዞን አቀፍ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል አመታዊ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር. አጠቃላይ ውጤት ከከተማ አስተዳደር ወልቂጤና ከወረዳዎች ምሁር አክሊል ወረዳ አሸናፊ ሲሆኑ ከከተማ አስተዳደሮች ጉንችሬ 2ኛ ደረጃ ሲወጣ ከወረዳዎች ደግሞ ጌታና አበሽጌ ወረዳዎች በእኩል ውጤት 2ኛ ደረጃ በመውጣት እውቅናና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። ከተማሪዎች ጠቅላላ ውጤት ከ8ኛ ክፍል 1ኛ, ተማሪ ሪሃና ሹሜ ከእምድብር ከተማ፣ 2ኛ ተማሪ መካሪ አ/ኸኒን ከወልቂጤና 3ኛ, ተማሪ ሳሙኤል ጠንክር ከምሁር አክሊል ወረዳ አሸናፊ ሲሆኑ ከ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ 1ኛ, ተማሪ የሺወርቅ አበበ ከወልቂጤ ከተማ፣ ተማሪ ማትዮስ ጦርበዛ ከጉንችሬ ከተማና 3ኛ, ተማሪ ታረቀኝ መንጂየ ከአገና ከተማ እንዲሁም ከ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ብሩክ ሰንብት ከጉንችሬ ከተማ፣ 2ኛ, ተማሪ ያሬድ ሰክቱ ከቸሃ ወረዳና ተማሪ ቃልኪዳን ገ/ጻዲቅ ከእንደጋኝ ወረዳ አሸናፊ በመሆን የሰርተፊኬትና የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የጥያቄና መልስ ውድድሩ በተማሪዎች መካከል ከፍተኛ ትንቅንቅ የታየበት እንደነበር ተገልጿል።

የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የ2018 ዓ.ም ዞን አቀፍ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል አመታዊ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር በወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። ግንቦት 28/2018ዓ.ም(ወልቂጤ) የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መብራቴ ወልደማርያም በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት የጥያቄና መልስ ውድድሩ አላማ ጎበዝ ተማሪዎች በየአመቱ ለእውቀትና ፈተና ከሚዘጋጁት ዝግጅት ባሻገር በዞን አቀፍ የጥያቄና መልስ ውድድር መሳተፍና ማሸነፍ አለብኝ የሚል ቁጭት እንዲያድርባቸው ለማድረግ ያለመ ነው። ከዚህም ባለፈ በመንግስት ትምህርት ቤቶች በተማሪዎችና በመዋቅሮች መካከል ጤናማ የፉክክር መንፈስ እንዲኖር በማድረግ በቀጣይ ተወዳዳሪ ተማሪዎች ለመፍጠር መሆኑን ገልጸዋል። ይህ የጥያቄና መልስ ውድድሩ ከትምህርት ቤት ጀምሮ በየደረጃው በክላስተር፣ በወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ሲካሄድ መቆየቱንም አቶ መብራቴ ተናግረዋል። በዚህም የጥያቃና መልስ ውድድር ከሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር ላይ የተሻለ ውጤትና አቅም ያላቸው ተማሪዎች መሳተፋቸውም ገልጸዋል። በጥያቄና መልስ ውድድሩ የዞኑ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መብራቴ ወልደማርያም፣ የየወረዳና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽህፈት ቤት የትምህርት ቤት መሻሻል ሱፐርቪዥን ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪዎች፣ የመምሪያው የማኔጅመንት አካላትና ከሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደር የተወጣጡ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ተገኝተዋል።

በጉራጌ ዞን 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላም መጠናቀቁን የዞኑ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ አስታወቀ። ግንቦት 25/2018 ዓ.ም(ወልቂጤ) ሕዝቡ በምርጫው ወቅት ያሳየውን የሰላም፣ የዲሞክራሲ፣ የመቻቻልና የሀገር ወዳድነት እሴቶች ከምርጫው በኋላም አጠናክሮ እንዲያስቀጥል አስታውቋል። የጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ነጋ አስፋው እንደገለጹት፣ ምርጫው በ10 የምርጫ ክልሎችና በ602የምርጫ ጣቢያዎች በተሳካ ሁኔታ ተካሂዶ ተጠናቋል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ዜጎች በሀገረ-መንግስት ግንባታ ላይ ያላቸውን የላቀ ተሳትፎ ያሳዩበት ዕለት መሆኑን የጠቀሱት አቶ ነጋ አስፋው፤ በዞኑ 12:00 ሰዓት ጀምሮ የተካሄደው ድምፅ የመስጠት ሂደት ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም መጠናቀቁን አስታውቀዋል። ለዚህም ከዞን እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ የተቀናጀ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ሲተገበር መቆየቱን ገልጸዋል። ከመራጭ ካርድ አሰጣጥ ጀምሮ እስከ ድምፅ መስጫ ቀን ድረስ ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ መደረጉን የገለጹት ኃላፊው፣ ከምርጫው በፊት፣ በምርጫው ወቅትና ከምርጫው በኋላ በሰላምና ጸጥታ ዙሪያ ትኩረት የተሰጠው ሥራ ለስኬቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳበረከተ ጠቁመዋል። ሁሉም የጸጥታ አካላት በተሰጣቸው ሀገራዊ ተልዕኮ መሰረት ቀንና ሌሊት በመሥራት ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ እንዳደረጉ ተናግረዋል። የዞኑ ሕዝብም ለሰላም፣ ለዲሞክራሲና ለልማት ያለውን ቁርጠኝነት በማሳየት ለምርጫው ስኬት የጎላ ሚና መጫወቱን አስገንዝበዋል። የምርጫ ቁሳቁሶችም ከምርጫ ጣበያ ወደ ምርጫ ክልል በሰላም እንዲገቡ ተደርጓል። አቶ ነጋ አክለውም ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት መሆኑን በመግለጽ በዞኑ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሕዝቡ በምርጫው ወቅት ያሳየውን የሰላም፣ የዲሞክራሲ፣ የመቻቻልና የሀገር ወዳድነት እሴቶች ከምርጫው በኋላም አጠናክሮ እንዲያስቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ፣ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የዞን፣ የከተማና የወረዳ የጸጥታ አካላት እንዲሁም ለመላው የጉራጌ ዞን ሕዝብ ምስጋናቸውን አቅርበዋል አቶ ነጋ አስፋው።

የኢፌዲሪ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ አዛዥ አቶ እርስቱ ይርዳው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ በዕጩነት በተወዳሩበት በጉራጌ ዞን እነሞርና ኤነር ቁጥር 1 ምርጫ ክልል ቀርበው ድምጽ ሰጥተዋል፡፡ ግንቦት24/2018ዓ.ም(ወልቂጤ) የኢፌዲሪ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ አዛዥ አቶ እርስቱ ይርዳው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ በዕጩነት በተወዳሩበት በጉራጌ ዞን እነሞርና ኤነር ቁጥር 1 ምርጫ ክልል ቀርበው ድምጽ ሰጥተዋል። ሀገሪቱ በየጊዜው ምርጫ እያካሄደች እንደምትገኝ በማውሳት ይህም በጊዜው እየተሻሻለ መምጣቱንና ሀገርን የማጽናት ተልዕኮ እንዳለው አንስተዋል። ምርጫው ታሪካችንን የሚያድስ በመሆኑ መራጩ ህዝብ በንቃት መሳተፍ እንዳለበትም ጥሪ አቅርበዋል። Fm Wolkite 89.2 Radio