Gurage Zone Government Communication Affairs
رفتن به کانال در Telegram
1 557
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
-1030 روز
آرشیو پست ها
የዞኑ የልማት ጸጋዎችና እሴቶች አጉልቶ ለማውጣት የኮሚኒኬሽንና ሚዲያ ዘርፉ በሰው ሀይል፣ በቁሳቁስና በበጀት መደገፍ ይገባል፦አቶ አበራ ወንድሙ
ነሀሴ 20/2018(ወልቂጤ)
መምሪያው የ2018 የስራ አፈጻጸም እና የ2019 እቅድ ላይ ያተኮር የውይይትና የምክክር መድረክ በወልቂጤ ከተማ አካሂዷል።
የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ ሚዲያ በዞኑ እየተሰሩ ባሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ላይ ህዝብና መንግስትን የሚያገናኝ ድልድይ መሆኑን ገልጸዋል።
የዞኑ የልማት ጸጋዎችና እሴቶች አጉልቶ ለማውጣት የኮሚኒኬሽንና ሚዲያ ዘርፉ በሰው ሀይል፣ በቁሳቁስና በበጀት መደገፍ ይገባል፦አቶ አበራ ወንድሙ
በዞኑ ጀፎረን ጨምሮ በርካታ ያልታዩና ያልተጎበኙ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ፀጋዎች መኖራቸውን ጠቁመው እነዚህ ሃብቶችን በማልማት በሃገር ደረጃ እንዲታወቁ በባለቤትነት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን በዚህ ወቅት እንዳሉት ለተቋሙ የአመለካከት ለውጥ በማድረግ በሰው ሀይል፣ በቁሳቁስና በበጀት መደገፍ ይገባል።
የሚሰሩ የሚዲያ ስራዎች በጥራት በፍጥነትና በተደራሽነት በመስራት የዞኑ ማህበረሰብ የሚመጥን የሚዲያ ስራ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
አቶ ሸምሱ አክለውም የጉራጊኛ ቋንቋ ለማሳደግ ሚዲያ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዷል ያሉ ሲሆን ዘገባዎችን በጉራጊኛ መስራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።
የሚዲያ ስራዎችን በገጽ ለገጽ፣በኤሌክትሮኒክስ ፣በህትመትና በማህበራዊ ሚዲያዎች ፕላትፎርሞች በመስፋት በመስራት የዞኑ ጸጋ፣እሴትችና ልማቶች ለአለም ማስተዋወቅ እንደሚገባ አስታውቀዋል።
ለኮሚኒኬሽንና ሚዲያ ስራዎች ውጤታማነት ከሚመለከታቸው ተቋሟትና ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንዲሰራ የተናግረዋል።
በቀጣይ በጀት አመትም የጉራጌ የማህበረሰብ ቴሌቪዥን ስራ ለማስጀመር የዞኑ መንግስት በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን አቶ ሸምሱ አመላክተዋል።
የዞኑ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሃዲሞ ሃሰን በኮሙኒኬሽን ዘርፉ የሚከናወኑ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን በመግለጽ በቀጣይም ማህበረሰቡን የሚመጥኑና ትውልድ ተሻጋሪ ተግባራትን መስራት እንደሚገባ አመልክተዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው መምሪያው መረጃን ተደራሽ ለማድረግ የሚያደርገው ጥረት አበረታች መሆኑን ገልጸው በቀጣይም ለስራ ማነቆ የሆኑ የግብዓትና የባለሙያ ውስንነቶችን በመቅረፍ በጥራት ላይ የተመሰረተ መረጃ ለህዝብ ማድረስ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የተለያዩ የሚዲያ አድማሶች በማስፋትና በማሰራጨት በበዞኑ በሚዲያ የበለጸገ ማህበረሰብ መፍጠር ይገባል ብለው ለዚህ ደግሞ አመራሩና ባለሙያዎች ስራቸው የበለጠ ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት።
በ2018 የተገኙ ጠንካራ ውጤቶች በማስቀጠልና ክፍተቶች በማስተካከል በ2019 የተሻለ ስራ ለመስራት አቅደው እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
በመጨረሻም መምሪያው ከሁሉም መዋቅሮች የ2019 እቅድ ላይ የግብ ስምምነት በማድረግ በ2018 የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ መዋቅሮች እና ተቋማት እውቅናና ሽልማት አበርክቶላቸዋል።
በዚህም እኖር እና ምሁር አክሊል ወረዳዎች 1ኛ፣ቸሀ ወረዳ ደግሞ 2ኛ ሲወጡ በከተሞች ወልቂጤ ከተማ 1ኛ በመሆን እውቅናና ሽልማት አግኝተዋል።
ወቅታዊና ጥራት ያለው መረጃ ማሰባሰብ ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል እንዲኖርና የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ፋይዳው ከፍተኛ በመሆኑ በዘርፉ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይገባል:- አቶ ላጫ ጋሩማ
ነሀሴ 20/2018ዓ.ም(ወልቂጤ) የጉራጌ ዞን ፕላን ልማት መምሪያ የ2019 በጀት አመት የወረዳዎች ሼር (ድርሻ) የማሳወቅ እና የሀብት ማከፋፈያ ቀመር አሰራር አስመልክቶ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በወልቂጤ ከተማ ውይይት አካሂዷል።
የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በመድረኩ ተገኝተው እንዳሉት በዞኑ ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል እንዲኖር የመረጃ አሰባሰብና አያያዝ ስርአቱ እያደገ መምጣቱን ጠቁመው፤ ይህ በቀጣይም የበለጠ ማጠናከር ይገባል።
በቀጣይ ከመረጃ አሰባሰብ ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮችን በየተቋማት ማጥራት ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።
በዞኑ ትላልቅ ግዙፍ እየተገነቡ ያሉ ፕሮጀክቶች በተለይም የአስተዳደር ህንጻና የማህበረሰብ የቴሌቪዥን ጣቢያ ለማጠናቀቅ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ያነሱት አቶ ላጫ በዘንድሮ አመትም ተጨማሪ የአዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ ለማስጀመር እንደሚሰራ አመላክተዋል።
ወቅታዊና ጥራት ያለው መረጃ ማሰባሰብ ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል እንዲኖርና የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ፋይዳው ከፍተኛ በመሆኑ በዘርፉ የተጀማመሩ ስራዎችን በቀጣይም በማጠናከር መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የጉራጌ ዞን ፕላን ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ከበደ ሀይሌ በበኩላቸው በዞኑ በ2018 በጀት አመት ጥራትና ትክክለኛነት ያለው መረጃ ማሰባሰብ ላይ በተሰራው ስራ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱንም ገልጸዋል።
ለዚህም ከወረዳ ፕላን መዋቅሮች፣ ከአስተዳዳሪዎች፣ ከሚመለከታቸው የመምሪያ ኃላፊዎችና ከክልል መዋቅር መረጃ የማጥራት ስራ መሰራቱን ያነሱት ኃላፊው በቀጣይም ለመረጃ ተገቢውን ትኩረት በመስጠት መሰብሰብና መያዝ እንደሚገባም ጠቁመዋል።
በቀጣይ የተሻለ የመረጃ አሰባሰብ ስርአት እንዲኖር ከዞኑ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ጋር በመሆን ሶፍት ዌር ማልማት መቻሉን አንስተው ይህም የበለጠ የመረጃ አሰባሰብና አያያዝ ስርአቱ ውጤታማ እንደሚያደርገውም ተናግረዋል።
በዞኑ የገቢ መሰረቶችን በማስፋት፣ የገቢ አማራጮችን አሟጦ ከመሰብሰብ ባለፈ የበጀት ብክነት መቀነስ እንደሚገባም አስረድተዋል።
የ2019 ዓ.ም በጀት በፍትሃዊነት በመረጃ ቀመሩ መሰረት ማከፋፈል መቻሉን ጠቅሰው፤ በዚህም በሀብት ክፍፍሉ ከታችኛው መዋቅሮች ጋር መግባባት መቻሉንም ገልጸዋል።
የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ አቶ አብዶ ሀሰን የ2019 ዓ.ም በጀት አከፋፈል በቀመሩ መሰረት በፍትሃዊነትና በግልጸኝነት ለወረዳዎች ማከፋፈል ተችሏል ብለዋል።
አክለውም በጀቱ በዞኑ ያሉ ፕሮጀክቶችና በአምና ደረጃ ተጨማሪ የተደረገው የሰራተኛ ደሞዝ ታሳቢ ባደረገ መልኩ በፍትሃዊነት ክፍፍል መደረጉንም ተናግረዋል።
ይህ የተከፋፈለው ውስን በጀት በቁጠባ በተገቢው ለልማት በማዋል ህብረተሰቡ ተጠቃሚ ለማድረግ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች እንዳሉት ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል እንዲኖር የቀመር መረጃ አሰባሰብ ስርአት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን ጠቁመው በቀጣይ የመረጃ ስርአቱ ይበልጥ ለማሻሻል በትኩረት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
በተለይም የመረጃ አሰባሰብና የመረጃ አያያዝ ስርአቱ ለማዘመን በዞኑ ሶፍት ዌር ለማልማት የተኬደበት ርቀት የሚበረታታ ነው ብለዋል።
የጉራጌ ማህበረሰብ የቲቪ ጣቢያ በፍጥነት ወደ ተግባር ለማስገባትና የአማርድ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለማጠናከር በበጀት ታሳቢ መደረጉ አበረታች መሆኑን ገልጸዋል።
በመድረኩም የጉራጌ ዞን ምክር ቤት የኢኮኖሚ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ጠጄ ደነቀ፣ የወረዳና ከተማ አስተዳደር አስተዳዳሪዎችና ከንቲባዎች እንዲሁም ፕላን ልማትና ፍይናንስ ጽህፈት ቤት ኃላፊዎችና ሌሎችም ተገኝተዋል።
የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን መምሪያ የ2018 የስራ አፈጻጸም እና የ2019 እቅድ ተኮር የውይይትና የምክክር መድረክ በወልቂጤ ከተማ ማካሄድ ጀመረ።
ነሀሴ 20/2018(ወልቂጤ)
የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ የ2018 ዓ.ም ስራ አፈጻጸምና የ2019 እቅድ ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
የሚዲያ ዓላማ ወቅታዊ፣ ተዓማኒና ሚዛናዊ የሆነ መረጃን በማሰባሰብ ለማህበረሰቡ የመረጃ ፍላጎት ማሟላትና ተደራሽ ማድረግ ነው።
የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ በመክፈቻ ንግግራቸው መምሪያው በአመቱ በሰራቸው ስራዎች የዞኑ ጸጋዎችን ጎልተው እንዲወጡ አስችሏል ብለዋል።
ለአብነትም በዞኑ እየተከናወኑ ያሉ የተለያዩ የልማት ስራዎች፣የጉራጌ ማህበረሰብ በባህል እና ታሪክ፣ የህዝቦች የእርስ በርስ ግንኙነት እንዲጎለበት የማድረግ እና ሌሎችም ስራዎች መሰራታቸው በቀጣይ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አስገንዝበዋል አቶ አበራ።
የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን እንዳሉት መምሪያዉ እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ በየወቅቱ የድጋፍና የክትትል ስራዎችን በመስራት ጠንካራ የኮሚኒኬሽን ተቋም እንዲገነባ ሲሰራ ቆይቷል።
የተለያዩ የመረጃ አማራጮች በመጠቀም ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ ወቅታዊ፣ ሚዛናዊና ተዓማኒነት ያለው መረጃ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት በመሰራቱ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉ ገልጸዋል።
በተጨማሪ ዞናዊ፣ ክልላዊ፣ ሀገራዊና አለም አቀፋዊ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ በፍጥነት እና በጥራት በማዳረስ ረገድ አበረታች ውጤቶችን ተመዝግቧል ብሏል አቶ ሸምሱ አማን።
በመድረኩም የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ ፣የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን፣የጉራጌ ዞን ምክር ቤት የሴቶችና ወጣቶች ማህበራዊ ዘርፍ ቋሚ ሰብሳቢ ወ/ሮ ጥሩነሽ ምኑታ፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ረዳት የመንግስት ተጠሪዎች፣ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
በጉራጌ ዞን የውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት ዞናዊ የንቅናቄ መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
ነሀሴ 18/2018(ወልቂጤ)
ክህሎት መር የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ስራ እድል ፈጠራ ለማህበራዊ እና ለኢኮኖሚያዊ እድገት እጅግ ወሳኝ በመሆኑ በዘርፉ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።
በጉራጌ ዞንም ባለፉት 3 አመታት ውስጥ 23 ሺ 318 ዜጎች የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት ስልጠና ተሰጥቷል።
ህገ ወጥ ደላሎችን በመከላከል ፣የዜጎች ደህንነት በመጠበቅ፣ ህጋዊ የስራ ስምሪት መስመሮችን ለማጠናከር እና ፍትሀዊ ጥቅም እንዲያገኙ ጉልህ ሚና እንዳለው ተመላክቷል።
በጉራጌ ዞን በ2019 በጀት አመት 16ሺ 153 ዜጎች የውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት ይሰራል ተብሏል።
በመድረኩ የጉራጌ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ደሳለኝ ፈቀደ፣የጉራጌ ዞን ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙራድ ያሲን፣የጉራጌ ዞን ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ አርሺያ አህመድ፣የጉራጌ ዞን ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ስርግማ፣የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር የብልጽግና ጽ/ቤት አመራሮች፣የጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ባለሙያዎችና የኮሌጅ ዲኖች ተገኝተዋል።
በጉራጌ ዞን በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እየተሰሩ ያሉ ውጤታማ ስራዎች የፓርቲው እሳቤ በተጨባጭ ያረጋገጡ መሆኑ የሚያሳዩ እንደሆነ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የበጎ ፍቃድ ቴክኒክ ኮሚቴ አስታወቀ።
ነሀሴ 16/2018 ዓ.ም ( ወልቂጤ )
ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተወጣጡ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ቴክኒክ ኮሚቴ የሱፐርቪዥን አባላት በዞኑ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተዛዙረው ተመልክተው ግብረ መልስ ሰጥተዋል።
የሱፐርቪዥን ቡድን አባላቱ ከዞን ማዕከል እስከ እስከ ቤተሰብ ድረስ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተዛዙረው ተመልክተዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊና የክረምት በጎ ፍቃድ ቴክኒክ ኮሚቴ አባል አቶ ታምራት ተስፋሁን እንዳሉት በዞኑ በሁሉም አካባቢዎች በ16 የትኩረት መስኮች ላይ ውጤታማ ስራ እየተሰራ ይገኛል።
በዞኑ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የተሰሩ ስራዎች በትኩረት የቃኙበትና የተሻለ ስራ የተሰራበት መሆኑን በመግለፅ የዘማች ቤተሰቦች ማዕከል ያደረገ የክረምት በጎፍቃድ ስራ እየተሰራ እንደሆነም ጠቁመዋል።
የበጎ ፍቃድ አገልግሎት አብይና የቴክኒክ ኮሚቴዎች እየሰሩት ያለውን የተጠናከረ ስራ ሞዴል እንደሆነና በሌሎችም አካባቢዎች መስፋት እንዳለበትም አስረድተዋል።
ከመንግስት ድጋፍ በተጨማሪ ሌሎች የበጀት አማራጮችን በመጠቀም በዞኑ እየተሰሩ ያሉ የበጎ ፍቃድ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል ያለበት ተግባር መሆኑም አመላክተዋል።
በዞኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ ህዝባዊ ሆኖ እየተሰራበት ነው ያሉት አቶ ታምራት ለአቅመ ደካሞች እየተሰሩ ያሉ ቤቶች ጥራት ያላቸው ደረጃቸው የጠበቁ ጥሩ ቤቶች ሲሆኑ ይህንንም ስራ አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።
በክረምት በጎፈቃድ አገልግሎት እየተሰሩ ያሉ ውጤታማ ስራዎች የፓርቲው እሳቤ በተጨባጭ ያረጋገጠ መሆኑ የሚያሳይ ነው ብለዋል።
ሚዲያ ለበጎ አላማ በመጠቀም ረገድ የተሻለ ስራ መኖሩና በጉንችሬ ከተማ ወጣቶች የቴሌግራም ቻሌንጅ በመክፈት ለጤና ጣቢያ የሚሆን ሲቢሲ ማሽን ለመግዛት ገንዘብ የማሰባሰብ ስራዎች እየተሰራ ሲሆን ይህንንም በጎ ልምድ በሌሎችም አካባቢዎች ማስፋት እንደሚገባም አመላክተዋል።
ፓርቲው ሰው ተኮር ስራዎች የሚሰራ ሲሆን ይህንን በህብረተሰቡ ዘንድ ባህል ሆኖ ቀጥሏል ብለው
በቀበሌ ደረጃ በደም ልገሳ ፣ተማሪዎችን በማስተማር፣ በቤት ግንባታ እንዲሁም ሌሎች ስራዎች ለመስራት የሚሳተፉ ወጣቶች በተገቢው ተለይቶ ወደ ስራ እንዲገቡ የተደረገበት አግባብ የሚበረታታ እንደሆነ ተናግረዋል።
የጉራጌ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ እና የቴክኒክ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ሄኖክ አብድልሰመድ እንዳሉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የበጎ ፍቃድ ቴክኒክ ኮማቴዎች በእኖር ወረዳ፣ በጉንችሬና በወልቂጤ ከተሞች በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተዛዙረው የድጋፍና የክትትል ስራ ማድረጋቸውም አስረድተዋል።
ቴክኒክ ኮሚቴዎች በጥንካሬ የሰጡት ግብረመልስ የበለጠ አጠናክሮ የሚሰራና በጉለት ያመላከቱትን በአጭር ጊዜ ለመቅረፍ ይሰራልም ብለዋል።
የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የማህበረሰቡ ነባር እሴት ነው ያሉት አቶ ሄኖክ በዞኑ ምርጥ ተሞክሮ የሚቀመርባቸው በርካታ ስራዎች መኖራቸውም ተናግረዋል።
በዞኑ ከ4መቶ ሺህ በላይ ወጣቶች በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራ ላይ ተሰማርተው እየተሳተፉ ሲሆን እነዚህም ከ8 መቶ ሺህ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነና በዚህም ከፍተኛ ውጤት እየመጣ ይገኛል ብለዋል።
የቤት ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖችን ቤት የመስራት ስራ የሚሰራ ሲሆን በዚህ ክረምት ከ333 በላይ የጭቃ ቤቶች ለመገንባት አቅደው እስካሁን ባለው ከ320 በላይ ቤቶች መሰራታቸውም አብራርተዋል።
ወጣቶች በድልድይ ግንባታ ፣በአካባቢ ጽዳትና በሌሎችም ማህበረሰቡን ነሚጠቅሙ ስራዎች በስፋት እየተሰራ ሲሆን በደም ልገሳ አገልግሎት ከእቅድ በላይ ደም የማሰባሰብ ስራ መሰራቱም ጠቁመው በዚህም የቴክናክና የአብይ ኮሚቴዎች የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል ውጤት መሆኑም ተናግረዋል።
የጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ሀላፊ አቶ ሙራድ ረሻድ እንዳሉት በዞኑ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በ16 የቱኩረት ዘርፎች ማህበረሰቡን የሚጠቅሙ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ነው።
የአቅመ ደካሞች አዲስ ቤት የመገንባትና የመጠገን ስራ በስፋት እየተሰራ ሲሆን በዚህም በተጨባጭ ለውጥ እየመጣ እንደሆነም አስረድተዋል ሲል የዘገበው የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚናኬሽን መምሪያ ነው።
በወረዳው በተቀናጀ የግብርና ልማት የህብረተሰቡ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው:- አቶ ሚፍታ ሁሴን
ነሀሴ 13/2018(ወልቂጤ) በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የዞን ደጋፊ አመራርና የወረዳው የስራ ኃላፊዎች የግብርናና ሌሎችም ወቅታዊ የልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ አካሂደዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን እንዳሉት በወረዳው በመኸር እርሻ ልማት 17ሺ 814 ሄክታር መሬት በገብስ፣ በስንዴ፣ በመኸር ድንች፣ በባቄላ፣ በአተርና በጤፍ በዘር መሸፈን ተችሏል።
በመኸር ከለማው ማሳ ውስጥ ስንዴ፣ ጤፍና ገብስ በሰፊው በክላስተር መልማቱንም አንስተው፤ ይህም በወረዳው በክላስተር የማልማት ዘዴ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል ብለዋል።
ወረዳው በግብርና ልማት ዘርፍ እምቅ አቅም እንዳለ ያነሱት አቶ ሚፍታ በዚህም የየአካባቢው ስነምህዳር መሰረት ባደረገ መልኩ በዘንድሮ የመኸር ወቅት በአርሶ አደር ማሳ፣ በመንግስት፣ በእምነት ተቋማት፣ በተደራጁ ህብራት ስራ ማህበራትና በወጣቶች መልማቱንም ተናግረዋል።
ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እርሻ በወቅቱ ከማረስ ባለፈ ግብአት በአግባቡ በመጠቀም ዘር መዝራት መቻሉን ጠቅሰው፤ በቀጣይ የማሳ እንክብካቤ በትኩረት ይሰራልም ብለዋል።
በወረዳው በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ8 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን መትከል መቻሉን አውስተዋል።
አክለውም የቡና መንደር ከመመስረት ባለፈ 30-40-30 የፍራፍሬ መንደር በመፍጠር አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በወረዳው በዘንድሮ አመት ከዚህ ቀደም ታርሰው የማይታወቁ ከ4 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ አዳዲስ ማሳዎችን በማረስ በሰብልና ፍራፍሬ መተካት መቻሉንም አስረድተዋል።
በሌማት ትሩፋት የወተት፣ የዶሮ፣ የስጋ፣ የማር መንደር በመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ በዚህም ወጣቱና አርሶ አርሶ በወተት፣ በዶሮ እርባታ፣ በድለባና በንብ ማነብ በመሰማራት ከምግብ ፍጆቻ አልፈው ኢኮኖሚያዊ ጠቃሚ እየሆኑ መሆኑንም አመላክተዋል።
በወረዳው በተቀናጀ የግብርና ልማት የተጀማመሩ ስራዎችን ይበልጥ በማጠናከር የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራ አስገንዝበዋል።
አቶ መሀመድ ያሲንና አቶ ሙዲ ዝዬ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ አግኝተን ያነጋገርናቸው አርሶ አደሮች ናቸው።
አርሶ አደሮቹ እንዳሉት በመኸር ወቅት ማሳቸውን በተገቢው በማረስና ግብአት በመጠቀም ስንዴና ገብስ መዝራታቸውን አንስተዋል።
ለዚህም ከማሳ ዝግጅት ወቅት ጀምሮ የግብርና ባለሙያ የሚሰጣቸውን ምክረ ሃሳብ በመጠቀም መስራታቸው ያነሱት አርሶ አደሮቹ በቀጣይም ከማሳቸው ሳይነጠሉ የመንከባከብ ስራ እንደሚሰሩም ገልጸዋል።
ከዚህም ባለፈ በሌማት ትሩፋት በዶሮ እርባታና በግ ከማሞከት ባለፈ በፍራፍሬ ልማት አቮካዶ፣ ቡና፣ ካሮትና ሌሎችም ሰብሎችን በማልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን አንስተዋል።
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ወቅታዊ የግብርናና የትምህርት እንደዚሁም ሌሎች የልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ እየተካሄደ ይገኛል።
ነሀሴ 13/2018(ወልቂጤ) የዞን ደጋፊ አመራርና የወረዳው የስራ ኃላፊዎች በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የግብርናና ሌሎችም ወቅታዊ የልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ በመካሄድ ላይ ነው።
በወረዳው በዘንድሮ የመኸር እርሻ ልማት 20ሺ 518 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እስካሁን 17ሺ 814 ሄክታር መሬት በገብስ፣ በስንዴ፣ በመኸር ድንች፣ በባቄላ፣ በአተርና በጤፍ ለምቷል።
በመስክ ምልከታው በወረዳው የሀጂ ለገሰ ሸረፋ (ኤች ኤል ኤስ)አበባ እርሻ ልማት የተጎበኘ ሲሆን እርሻ ልማቱ 36 ሄክታር መሬት በመረከብ 11 ነጥብ 5 ሄክታር መሬቱ ወደ ተግባር ገብቷል።
እርሻ ልማቱ 76 አይነት የአበባ ዝርያ ከማምረት ባለፈ ለ465 ሰራተኞች ቋሚ የስራ ዕድል መፍጠሩንም ተጠቁሟል።
ከግብርና ልማት ስራ በተጨማሪ የተማሪዎች የምዝገባ ሂደትና ሌሎችም ወቅታዊ የልማት ስራዎችን ምልከታ በማድረግ ላይ ናችው።
በመስክ ምልከታው የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን፣ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን፣ የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አብድረሂም ርዳ ጨምሮ የወረዳው የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
