fa
Feedback
Gurage Zone Government Communication Affairs

Gurage Zone Government Communication Affairs

رفتن به کانال در Telegram

Gurage Zone Government Communication Affairs

نمایش بیشتر
1 569
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+77 روز
-630 روز
آرشیو پست ها
ዞን አቀፍ የጥያቄና መልስ ውድድሩ በተማሪዎች መካከል ጤናማ የፉክክር መንፈስ ከመፍጠር ባለፈ በክልልና ሀገር ፈተናዎች ላይ ከፍተኛ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች ቁጥር ከፍ ለማድረግ ፋይዳው የጎላ ነው:- አቶ መብራቴ ወልደማርያም ግንቦት 28/2018ዓ.ም(ወልቂጤ) የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የ2018 ዓ.ም ዞን አቀፍ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል አመታዊ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር በወልቂጤ ከተማ አካሂዷል። የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መብራቴ ወልደማርያም እንዳሉት የዘንድሮ ዞን አቀፍ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል አመታዊ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር ከዚህ ቀደም ከትምህርት ቤቶች ጀምሮ በወረዳና ከተማ አስተዳደሮች ሲካሄድ መቆየቱን አስታውሰዋል። የውድድሩ አላማ በዞኑ ከፍተኛ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች ቁጥር የማሳደግና በሁሉም የክፍል ደረጃ የሚገኙ ተማሪዎች በቀጣይ ለዞን አቀፍ ውድድር እንዲዘጋጁ ለማድረግና በተማሪዎች መካከል ጤናማ የውድድር መንፈስ ለመፍጠር ያለመ ነው ብለዋል። ከዚህም ባለፈ በክልልና ሀገር አቀፍ ፈተናዎች ከፍተኛ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች ለማፍራት ፋይዳው ከፍተኛ መሆኑንም ገልጸዋል። ይህ ውድድር ከዞኑ የተወጣጡ የተለዩ ጎበዝ 45 ተማሪዎች የተሳተፉበት መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ይህም በተማሪዎቹ መካከል ከፍተኛ ትንቅንቅ የታየበትና በወረዳዎችና በከተማ አስተዳደሮች መካከል ተቀራራቢ ውጤት መመዝገቡንም አስረድተዋል። በዚህ ውድድር የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የገንዘብና የሰርተፊኬት ሽልማት እንደተበረከተላቸው ያነሱት አቶ መብራቴ ይህም ሌሎችም ተማሪዎች ይህን ተሞክሮ በመውሰድ ለቀጣይ ውድድር ዝግጅት እንዲያደርጉ ያነሳሳቸዋል ብለዋል። ይህ ዞን አቀፍ የአሸናፊዎች አሸናፊ የአሸናፊ ውድድር በቀጣይ የመማር ማስተማር ስራ የበለጠ የሚያጠናክር ከመሆኑም ባለፈ መዋቅሮች ተማሪዎቻቸው እየለዩ እያበቁ እንዲሄዱና ጎበዝ ተማሪዎች እንዲለዩ የሚያደርግ መሆኑንም አመላክተዋል። ለውድድር የቀረቡ ጥያቄዎቹ የተሻለ አቅምና ስነምግባር ባላቸው መምህራን መዘጋጀቱን ጠቅሰው፣ በቀጣይም በተሻለ መልኩ በማጠናከር እንደሚዘጋጅ ጠቁመዋል። ቀጣይ የሚሰጠው ክልልና ሀገር ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች በቀሪ ጊዜያት ከትምህርት ቤት ሳይነጠሉ ከመዘጋጀት ባለፈ ቤተሰብ፣ ወላጆች፣ መምህራንና የትምህርት አመራሮች ተማሪዎችን መከታተል፣ መደገፍና ማብቃት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። በጥያቄና መልስ ውድድሩ የተሳተፉ ተማሪዎች እንዳሉት በውድድሩ የተሻለ ውጤት በማስመዝገባቸው ደስተኛ መሆናቸውን አንስተው ይህም በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አንስተዋል። ተማሪዎች ሳይዘናጉ በቀጣይ ለሚሰጠው ለክልልና ሀገር አቀፍ ፈተናዎች በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉም መክረዋል።

በዞኑ በቀጣይ በሚሰጠው የ8ኛና የ12ኛ ክፍል ክልልና ሀገር አቀፍ ፈተና የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ሁሉም ተማሪዎች ሳይዘናጉ በቂ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ተሸላሚ ተማሪዎች መከሩ። ግንቦት 28/2018ዓ.ም(ወልቂጤ) የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የ2018 ዓ.ም ዞን አቀፍ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል አመታዊ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር በወልቂጤ ከተማ አካሂዷል። በዞን አቀፍ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል አመታዊ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር ላይ አንደኛ በመሆን ካጠናቀቁ ተሸላሚ ከሆኑ ተማሪዎች መካከል ተማሪ ብሩክ ሰንብት ከጉንችሬ፣ ተማሪ የሺወርቅ አበበ ከወልቂጤና ተማሪ ሪሃና ሹሜ ከእምድብር ከተማ ይገኙበታል። ተማሪዎቹ በጋራ በሰጡት አስተያየት በዞን አቀፍ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር ላይ ከአጠቃላይ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ተሸላሚ በመሆናቸው ደስታ እንደተሰማቸው አንስተዋል። ለዚህ ውድድር አሸናፊ የመሆናቸው ሚስጥር ከመምህራኖቻቸው በቅርበት በመሆን የሚሰጣቸው ትምህርት በተገቢው ከመከታተል ባለፈ በራሳቸው ጥረት በቂ ዝግጅት እያደረጉ በመሆናቸው ስለመሆኑንም ገልጸዋል። ከዚህም ባሻገር ፕሮግራም በማውጣት ጊዜያቸውን በአግባቡ እንደሚያነቡ አንስተው ከዚህም ባለፈ ለትምህርታቸው አጋዥ የሆኑ ቪዲዮዎችን በማየትና ወርክ ሺቶችን እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ጎበዝ የመሆናቸው ሚስጥር ተማሪዎች የሚሰጣቸው መደበኛና የድጋፍ ትምህርት በተገቢው ከመከታተል ባሻገር በራሳቸው የተለያዩ ጥረቶችን እንደሚያደርጉም አውስተዋል። ቀጣይ የ8ኛና 12ኛ ክፍል ክልልና ሀገር አቀፍ ፈተናዎች መቃረቡን ተከትሎ ከሌሎች ተማሪዎች ለመወዳደርና የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በቂ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ያነሱት ተማሪዎቹ ሌሎችም ተማሪዎች ሳይዘናጉ ለትምህርታቸው ትኩረት በመስጠት በቀሪ ጊዜያት ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉም መክረዋል።

በተካሄደው የ2018 ዓ.ም ዞን አቀፍ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል አመታዊ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር. አጠቃላይ ውጤት ከከተማ አስተዳደሮች ወልቂጤና ከወረዳዎች ምሁር አክሊል ወረዳ አሸናፊ ሆኑ። ግንቦት 28/2018ዓ.ም(ወልቂጤ) የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የ2018 ዓ.ም ዞን አቀፍ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል አመታዊ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር በወልቂጤ ከተማ አካሂዷል። በተካሄደው የ2018 ዓ.ም ዞን አቀፍ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል አመታዊ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር. አጠቃላይ ውጤት ከከተማ አስተዳደር ወልቂጤና ከወረዳዎች ምሁር አክሊል ወረዳ አሸናፊ ሲሆኑ ከከተማ አስተዳደሮች ጉንችሬ 2ኛ ደረጃ ሲወጣ ከወረዳዎች ደግሞ ጌታና አበሽጌ ወረዳዎች በእኩል ውጤት 2ኛ ደረጃ በመውጣት እውቅናና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። ከተማሪዎች ጠቅላላ ውጤት ከ8ኛ ክፍል 1ኛ, ተማሪ ሪሃና ሹሜ ከእምድብር ከተማ፣ 2ኛ ተማሪ መካሪ አ/ኸኒን ከወልቂጤና 3ኛ, ተማሪ ሳሙኤል ጠንክር ከምሁር አክሊል ወረዳ አሸናፊ ሲሆኑ ከ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ 1ኛ, ተማሪ የሺወርቅ አበበ ከወልቂጤ ከተማ፣ ተማሪ ማትዮስ ጦርበዛ ከጉንችሬ ከተማና 3ኛ, ተማሪ ታረቀኝ መንጂየ ከአገና ከተማ እንዲሁም ከ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ብሩክ ሰንብት ከጉንችሬ ከተማ፣ 2ኛ, ተማሪ ያሬድ ሰክቱ ከቸሃ ወረዳና ተማሪ ቃልኪዳን ገ/ጻዲቅ ከእንደጋኝ ወረዳ አሸናፊ በመሆን የሰርተፊኬትና የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የጥያቄና መልስ ውድድሩ በተማሪዎች መካከል ከፍተኛ ትንቅንቅ የታየበት እንደነበር ተገልጿል።

የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የ2018 ዓ.ም ዞን አቀፍ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል አመታዊ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር በወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። ግንቦት 28/2018ዓ.ም(ወልቂጤ) የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መብራቴ ወልደማርያም በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት የጥያቄና መልስ ውድድሩ አላማ ጎበዝ ተማሪዎች በየአመቱ ለእውቀትና ፈተና ከሚዘጋጁት ዝግጅት ባሻገር በዞን አቀፍ የጥያቄና መልስ ውድድር መሳተፍና ማሸነፍ አለብኝ የሚል ቁጭት እንዲያድርባቸው ለማድረግ ያለመ ነው። ከዚህም ባለፈ በመንግስት ትምህርት ቤቶች በተማሪዎችና በመዋቅሮች መካከል ጤናማ የፉክክር መንፈስ እንዲኖር በማድረግ በቀጣይ ተወዳዳሪ ተማሪዎች ለመፍጠር መሆኑን ገልጸዋል። ይህ የጥያቄና መልስ ውድድሩ ከትምህርት ቤት ጀምሮ በየደረጃው በክላስተር፣ በወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ሲካሄድ መቆየቱንም አቶ መብራቴ ተናግረዋል። በዚህም የጥያቃና መልስ ውድድር ከሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር ላይ የተሻለ ውጤትና አቅም ያላቸው ተማሪዎች መሳተፋቸውም ገልጸዋል። በጥያቄና መልስ ውድድሩ የዞኑ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መብራቴ ወልደማርያም፣ የየወረዳና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽህፈት ቤት የትምህርት ቤት መሻሻል ሱፐርቪዥን ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪዎች፣ የመምሪያው የማኔጅመንት አካላትና ከሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደር የተወጣጡ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ተገኝተዋል።

በጉራጌ ዞን 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላም መጠናቀቁን የዞኑ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ አስታወቀ። ግንቦት 25/2018 ዓ.ም(ወልቂጤ) ሕዝቡ በምርጫው ወቅት ያሳየውን የሰላም፣ የዲሞክራሲ፣ የመቻቻልና የሀገር ወዳድነት እሴቶች ከምርጫው በኋላም አጠናክሮ እንዲያስቀጥል አስታውቋል። የጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ነጋ አስፋው እንደገለጹት፣ ምርጫው በ10 የምርጫ ክልሎችና በ602የምርጫ ጣቢያዎች በተሳካ ሁኔታ ተካሂዶ ተጠናቋል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ዜጎች በሀገረ-መንግስት ግንባታ ላይ ያላቸውን የላቀ ተሳትፎ ያሳዩበት ዕለት መሆኑን የጠቀሱት አቶ ነጋ አስፋው፤ በዞኑ 12:00 ሰዓት ጀምሮ የተካሄደው ድምፅ የመስጠት ሂደት ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም መጠናቀቁን አስታውቀዋል። ለዚህም ከዞን እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ የተቀናጀ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ሲተገበር መቆየቱን ገልጸዋል። ከመራጭ ካርድ አሰጣጥ ጀምሮ እስከ ድምፅ መስጫ ቀን ድረስ ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ መደረጉን የገለጹት ኃላፊው፣ ከምርጫው በፊት፣ በምርጫው ወቅትና ከምርጫው በኋላ በሰላምና ጸጥታ ዙሪያ ትኩረት የተሰጠው ሥራ ለስኬቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳበረከተ ጠቁመዋል። ሁሉም የጸጥታ አካላት በተሰጣቸው ሀገራዊ ተልዕኮ መሰረት ቀንና ሌሊት በመሥራት ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ እንዳደረጉ ተናግረዋል። የዞኑ ሕዝብም ለሰላም፣ ለዲሞክራሲና ለልማት ያለውን ቁርጠኝነት በማሳየት ለምርጫው ስኬት የጎላ ሚና መጫወቱን አስገንዝበዋል። የምርጫ ቁሳቁሶችም ከምርጫ ጣበያ ወደ ምርጫ ክልል በሰላም እንዲገቡ ተደርጓል። አቶ ነጋ አክለውም ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት መሆኑን በመግለጽ በዞኑ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሕዝቡ በምርጫው ወቅት ያሳየውን የሰላም፣ የዲሞክራሲ፣ የመቻቻልና የሀገር ወዳድነት እሴቶች ከምርጫው በኋላም አጠናክሮ እንዲያስቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ፣ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የዞን፣ የከተማና የወረዳ የጸጥታ አካላት እንዲሁም ለመላው የጉራጌ ዞን ሕዝብ ምስጋናቸውን አቅርበዋል አቶ ነጋ አስፋው።

የኢፌዲሪ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ አዛዥ አቶ እርስቱ ይርዳው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ በዕጩነት በተወዳሩበት በጉራጌ ዞን እነሞርና ኤነር ቁጥር 1 ምርጫ ክልል ቀርበው ድምጽ ሰጥተዋል፡፡ ግንቦት24/2018ዓ.ም(ወልቂጤ) የኢፌዲሪ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ አዛዥ አቶ እርስቱ ይርዳው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ በዕጩነት በተወዳሩበት በጉራጌ ዞን እነሞርና ኤነር ቁጥር 1 ምርጫ ክልል ቀርበው ድምጽ ሰጥተዋል። ሀገሪቱ በየጊዜው ምርጫ እያካሄደች እንደምትገኝ በማውሳት ይህም በጊዜው እየተሻሻለ መምጣቱንና ሀገርን የማጽናት ተልዕኮ እንዳለው አንስተዋል። ምርጫው ታሪካችንን የሚያድስ በመሆኑ መራጩ ህዝብ በንቃት መሳተፍ እንዳለበትም ጥሪ አቅርበዋል። Fm Wolkite 89.2 Radio

በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ያነጋገርናቸው የሀገር ሽማግሌዎች ድምጻቸው ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መስጠታቸው ገልጹ። ግንቦት 24/2018(ወልቂጤ ) በጉራጌ ዞን እዣ ቁጥር 2 ምርጫ ክልል ምሁር አክሊል ወረዳ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ያነጋገርናቸው የሀገር ሽማግሌዎች፣ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸው፣ በነጻነት ድምፃቸውን በመስጠታቸው ደስተኞች መሆናቸውን ተናግረዋል። በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ያነጋገርናቸው የሀገር ሽማግሌዎች፣ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በነቃ ተሳትፎ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። የሀገር ሽማግሌዎቹ እንደገለጹት፣ ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እየተካሄደ ሲሆን፣ የህብረተሰብ ክፍሎች ያለምንም ጫና በነጻነት ድምፃቸውን እየሰጡ ነው ብለዋል። ምርጫ መምረጥ ለሀገር ልማት፣ ለዴሞክራሲ ግንባታ እና ለህዝብ ተሳትፎ መጠናከር ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፣ ዜጎች የዜግነት ግዴታቸውን በመወጣት በምርጫው እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል። በተጨማሪም የምርጫውን ውጤት በጸጋ እንደሚቀበሉ ገልጸው፣ የሀገሪቱ የዴሞክራሲ ጉዞ እንዲጠናከር ሁሉም ወገኖች ሰላምንና መቻቻልን ሊያስቀድሙ ይገባል ብለዋል።

ሕዝቦች በልማትና በመልካም አስተዳደር ተሳትፎ እንዲኖራቸው ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አስፈላጊ መሆኑን በጉራጌ ዞን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ታደለ በቀለ ገለፁ ። ግንቦት24/18(ወልቂጤ)በጉራጌ ዞን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ታደለ በቀለ ድምጻቸውን ሰጥተው ሲወጡ እንደገለፁት ሕዝቦች በልማትና በመልካም አስተዳደር ተሳትፎ እንዲኖራቸው ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አስፈላጊ ነው። ሀገሪቱም በየአምስት አመቱ ጠቅላላ ምርጫ በማድረግ ህዝቦች በመረጡት መንግሥት እንዲተዳደሩ እንደሚደረግ ገልፀው ምርጫው ሰላማዊ ፍትሀዊና ተአማኒ እንዲሆን ሁሉም ሀላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። በከተማው ምርጫው ሠላማዊ በሆነ መልኩ እየተካሄደ መሆኑን የገለፁት አቶ ታደለ ዜጎች መብታቸውን በመጠቀም የሚፈልጉትን ፓርቲ መምረጥ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል ። @top fans

በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን በእዣ ቁጥር ሁለት ምርጫ ክልል ድድጋር ምርጫ ጣቢያ ድምጽ አሰጣጥ ሂደት ።