ru
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Открыть в Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Больше
2 280
Подписчики
Нет данных24 часа
+77 дней
+3930 день
Архив постов
የቄስ ልጅ ነኝ ሰይጣን አይነካኝም || ዕድላችንን የወሰደ የእድሳት መተት || የእድሳት መተት ምንድነው? || በልጅነት የተዋረስነው መንፈስ #ebs #ንቁ 🔥💥 https://youtu.be/AP7vntNAXoo

የመምህር ተስፋዬ መልዕክት ለምስቶች || ቁረቡ እንቢ፣ ስገዱ እንቢ፣ ጸልዩ እንቢ አልን || የማንቆርበው ለምንድነው? ንስሐ ምንድነው? #ebs #eotc 💥🚩😭 https://youtu.be/vXzO2ouZu_E

"ጸሎትን የምንጸልየው እግዚአብሔር የማያውቀው ነገር ኖሮ ለመንገር ወይም የረሳው ነገር ኖሮ ለማስታወስ አይደለም፤ ወደ እርሱ እንድንቀርብ፣ ቀርበን ወዳጆቹ እንድንኾን፣ ዘወትር እንዲረዳን፣ ራሳችንን
"ጸሎትን የምንጸልየው እግዚአብሔር የማያውቀው ነገር ኖሮ ለመንገር ወይም የረሳው ነገር ኖሮ ለማስታወስ አይደለም፤ ወደ እርሱ እንድንቀርብ፣ ቀርበን ወዳጆቹ እንድንኾን፣ ዘወትር እንዲረዳን፣ ራሳችንን ዝቅ ለማድረግ፣ ኃጢአታችንንም እንድናሰብ ነው እንጂ፡፡" (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

"ከእርሱ ጋር ሆኔ አሸነፍኩት፥ ያንን ክፉ ቀን ተሻገርኩኝ፤ ለእኔስ ብዙ ነው ውለታው፥ ከአፌ አይቋረጥ ምስጋናው።" የልጅነት ትዝታችን ድንቅ መዝሙር! ተባረክ ወንድማችን! ዘማሪ እዝራ ኃ/ሚካኤል #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ዲያብሎስ ከፍተኛ ጥንቃቄ ያደርጋል ሰዎች ተለይተው እንዳይወጡ || ሰይጣን አውቆ በሥራና በኑሮ ወከባ ይወጥረናል || 4ቱ በቅዳሴ ጊዜ የተከለከሉ ነገሮች 🚩 https://youtu.be/5nCbvBeJKh4

"ኃጢአት ለመሥራት ቀጠሮ ትይዛለህ፤ ጽድቅ ለመሥራት ግን ጊዜ የለኝም ትላለህ፤ ጓደኛህን ለማግኘት ጊዜ አለህ፤ ንስሐ አባትህን ለማግኘት ግን ጊዜ የለህም፤ በሥጋ ስትራብ ከየትም አምጥተህ (ለምነህም
"ኃጢአት ለመሥራት ቀጠሮ ትይዛለህ፤ ጽድቅ ለመሥራት ግን ጊዜ የለኝም ትላለህ፤ ጓደኛህን ለማግኘት ጊዜ አለህ፤ ንስሐ አባትህን ለማግኘት ግን ጊዜ የለህም፤ በሥጋ ስትራብ ከየትም አምጥተህ (ለምነህም ቢኾን) ትበላለህ፤ ነፍስህ የክርስቶስ ሥጋ ከራባት ግን ዘመናት ተቆጠሩ፤ ወዳጄ ሆይ እባብ አሳተኝ ያለችውንና ከፍርድ ያላመለጠችውን ሔዋን ታስታውሳለህን፤ እንግዲያውስ፤ አንተም እንደ እርሷ ምክንያት በመደርደር ራስህን ለማጽደቅ አትሞክር፤ ይህ ሲነገርህም በተግባር እንጂ በከንፈርህ መልስ ለመስጠት አትጣር።" #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

በንስሐ ዙሪያ የሚታዩ ሕልሞችና ፍቺዎቻቸው ሰውና ሕልም ሰው ሕልምን እንዴት ያያል? ከእግዚአብሔር ይሁን አይሁን እንዴት እንወቅ? #ethiopia 🚩💥 https://youtu.be/UJzor8NdySE?si=sMKoicQ8tq9E9Oun

ዕድላችንን፣ ኑሯችንን፣ ትዳራችንን የዘጋ አጋንንት ሲጋለጥ | ገዳም ለገዳም የሚያዞሩን ክፉ መንፈሶች | የጠቋር አጋንንት በመንፈሳዊ ሕይወታችን #ebs 💥🙏🚩😱 https://youtu.be/tiDLHPLLW5g

◈ "የአምልኮት ፍቅሩ ሐቅለ ሕሊና በሚያቃጥል በእሳታዊ እግዚአብሔር ስምና፤ ይህን ከንቱ ሰነፍ ዓለም በአማላጅነቱ ድንቅ ጥበብ በምትፈውስ፤ በሁለት ወገን ድንግል በምትሆን አምላክን በወለደች በድንግል
◈ "የአምልኮት ፍቅሩ ሐቅለ ሕሊና በሚያቃጥል በእሳታዊ እግዚአብሔር ስምና፤ ይህን ከንቱ ሰነፍ ዓለም በአማላጅነቱ ድንቅ ጥበብ በምትፈውስ፤ በሁለት ወገን ድንግል በምትሆን አምላክን በወለደች በድንግል ማሪያም ስም፤ ጽልመተ አበሳን የምታስወግድ የብርሃን መቅረዝ ቅዱስ ዮሐንስ ሆይ ቸርነትህን እመሰክር ዘንድ፤ አዋጅ ነጋሪ ቅዱስ አንደበትህ በአየር ሰማይ በልዕልና ጎልቶ ይሰማ። ቅዱስ ዮሐንስ ሆይ አዋጅ ነጋሪ በሆነ ቅዱስ አንደበትህ፤ የንስሐ ትምህርተ ስብከት ከሰዎች ላይ የኃጢአት ሸክምን እንዳስወገድክ ከእኔም ከአገልጋይህ ላይ የሚያሰቃየኝን ጽኑዕ የኃጢአት ክምር አስወግድልኝ።" (መልክአ ዮሐንስ መጥምቅ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

◈ "ማግባት ስትፈልግ አስቀድመህ ጸልይ፣ አሳብህን ለእግዚአብሔር ንገረው። እግዚአብሔር መርጦ እንዲሰጥህ ለምነው። ጭንቀትህን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣለው። አንተ እንደዚህ እርሱ እንድመርጥልህ የምታደርግ
◈ "ማግባት ስትፈልግ አስቀድመህ ጸልይ፣ አሳብህን ለእግዚአብሔር ንገረው። እግዚአብሔር መርጦ እንዲሰጥህ ለምነው። ጭንቀትህን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣለው። አንተ እንደዚህ እርሱ እንድመርጥልህ የምታደርግ ከሆነም፥ አክብረኸዋልና እርሱም ለአንተ በጎ የትዳር አጋርን በመስጠት ያከብርሃል። ስለዚህ በምታደርገው ነገር ሁሉ ሽማግሌህ እርሱ እግዚአብሔር እንዲሆን ዘወትር ጠይቀው። አስቀድመህ እንዲህ ካደረግህም፥ ወደ ትዳር ከገባህ በኋላ ፍቺ አይገጥምህም። ሚስትህ ሌላ ሰውን አትመኝም። በሌላ ሴት እንድትቀናም አታደርግህም። በመካከላችሁ (ለክፉ የሚሰጥ) ጠብና ክርክር አይኖርም። ከዚህ ይልቅ ታላቅ የኾነ ሰላምና ፍቅር በመካከላችሁ ይሰፍናል። እነዚህ ካሉ ደግሞ ሌሎች በጎ ምግባራትን፣ ትሩፋትን ለመፈጸም በፍጹም አትቸገሩም።" 🙏🙏🙏 (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ትዳር እንዳንይዝ፣ ብንይዝም እንድንፋታ የሚያደርጉ ክፉ መንፈሶች || ዓይነጥላ ያለበት ሰውና ትዳር || 8 ጊዜ አግብታ አፋታኋት ይላል አጋንንቱ #ebs 🔥💥 https://youtu.be/9g4GRofwjEU

«ሰውነታችሁን ለሰይጣን ምቹ አታደርጉ!» ◈ ተወዳጆች ሆይ የብዙዎቻችን ሰውነት ለሰይጣን ምቹ ነው፤ ለሰይጣን ምቹ ሰውነት ማለት ንስሐ ያልገባ በኃጢአት ግራ የሚጋባ ሰውነት ነው፤ ለሰይጣን ምቹ የሆነ ሰውነት ማለት በሐሜት፣ በቧልት፣ በምቀኝነት፣ በክፋት፣ በዝሙት፣ በስኳር፣ በአድመኝነት፣ በዘረኝነት ወዘተ የረከሰ ሰውነት ማለት ነው፡፡ ለሰይጣን ምቹ ሰውነት ማለት ለፈጣሪ የማይንበረከክ፣ ሰማያዊ አምልኮት የማያቀርብ፣ የማይሰግድ፣ የማይጸልይ፣ የማይጾም፣ ቅዱስ ቁርባን የማይቀበል ነው፤ የአንዳንዶቻችን ሰውነት ለምጽዋት የተዘረጋ ነው፤ ነገር ግን በዝሙት የረከሰ ነው፤ ይህ ለሰይጣን ምቹ ነው አንዳንዶቻችን ጸሎተኛ ነን በጸሎተኝነታችን ልክ እጅግ ሐሜተኛ እና ቅናተኛ ነን፤ በዚህም ለሰይጣን ምቹ ነን፡፡ ◈ አንዳንዶቻችን እጅግ አማኝ እና ሰርክ ለኪዳን፣ ለቅዳሴ እና ለጉባኤ ከቤተ ክርስትያን የማንርቅ ነን ነገር ግን ሲበዛ ቂመኛ እና ይቅርታ የለሾች ጨካኝ ነን፤ በዚህም ለሰይጣን ምቹ ነን አንዳንዶቻችን ቅዱስ ቁርባን ተቀብለን አንደበታችንን በመዓዛ መለኮት ማጣፈጥ እየቻልን ‹‹እግዚአብሔር ይቅር ይበለኝና›› እያልን አንደበታችን በሐሜት የመረረ ነው፤ በዚህም ለሰይጣን ምቹ ነን፡፡ አንዳንዶቻችን በመንፈሳዊ እውቀታችን ሰዎችን መክረን፣ አስተምረን ከኃጢአት መልሰን ለንስሐ እናበቃለን እኛ ግን ተመክረን የማንሰማ፣ ከኃጢአታችን መመለስ ያቀተን፣ ንስሐ የማንገባ ለቅዱስ ቁርባን የማንበቃ ነን፤ በዚህ ለሰይጣን ምቹ ነን፡፡ ◈ አንዳንዶቻችን የወሲብ ፊልም ማየት፣ ግለ ወሲብ መፈጸም ኃጢአት እንደሆነ ለሰው እንናገራለን እናስተምራለን በዚህም እነዛ ሰዎች ከዚህ ሰይጣናዊ ሱስ ተላቀው ንስሐ ይገባሉ ልማደ ሰይጣንንም ይተዋሉ፤ እኛ ግን ሰው ባላየ እግዚአብሔር ባየ የወሲብ ፊልም እናያለን ግለ ወሲብ እንፈጽማለን፤ በዚህም ለሰይጣን እንመቻለን፡፡ አንዳንዶቻችን መጽውቱ ብለን ሰዎች እንዲመጸውቱ፣ ድሆችን እንዲረዱ እናደርጋለን፤ የእኛ እጅ ግን በታንክ ፍሬን ተይዟል፣ መመጽወትም እንቢ ብሎናል፤ በዚህም ለሰይጣን ምቹ ነን፡፡ ◈ አንዳንዶቻችን ሰዎች ሲያማቸው እንዲጸልዩ፣ ጸበል እንዲጠመቁና በዚህም እንደሚድኑ መክረን እነዛ ሰዎች በምክራችን ተጠቅመው ጸልየው ተጠምቀው ይድናሉ፤ እኛ ስንታመም ግን እምነት አጥተን በየሆስፒታሉ እንንከራተታለን፤ በዚህ ለሰይጣን ምቹ ነን፡፡ ወዳጆቼ በየትኛውም ጉድለታችን ሰይጣን ወደ ሕይወታችን ይገባል፤ ሰይጣን ትንሿን ስህተታችንን፣ የኃጢአት ፍላጎታችንን አይቶ ወደ እኛ ጎራ ይልና ትንሿን ስህተት ትልቅ፣ ኃጢአትን ደግሞ ጽድቅ አድርጎ የእሱ መጫወቻ ያደርገናል፡፡ ◈ ሰይጣን አንዴ በዝሙት ከጣለን ስሜታችን ደግሞ ደጋግሞ ይጥለናል፤ ሰይጣን በመርፌ ቀዳዳ ስህተት ይገባና እኛ ግን ከስህተታችን በሰፊው በር መውጣት ያቅተናል፤ ዛሬ ሥጋዊ ፍላጎታችን፣ ዓላማችን፣ እውቀታችን፣ ትምህርታችን፣ ርእዮተ ዓለማችን፣ አመለካከታችን በራሱ ለሰይጣን ምቹ ስለሚሆን ልናስተውል እና ልንነቃ ይገባናል፤ ዛሬ ከላይ እስከታች፣ ከቤተ ክህነት እስከ ቤተ መንግስት፣ ከዓለማዊው እስከ መንፈሳዊው፣ ከምሁሩ እስከ ፊደል ነውሩ፣ ከወጣቱ እስከ አዛውንቱ ያለነው ሰውነታችን ለሰይጣን ምቹ ስለሆነ ሕይወታችን በፈተና፣ በስቃይ፣ በመንፈሳዊ ባዶነት የተመላ ነው፡፡ ‹‹እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝና፣ ሰውነታችሁን ቀድሱ፣ ቅዱሳንም ሁኑ›› ብሎ አዞናል፡፡ ◈ ነገር ግን ሰውነታችንን በኃጢአት አረከስን፣ ሕገ እግዚአብሔርንም አፈረስን፤ በዚህም ለሰይጣን ምቹ ሆንን፤ ሰይጣን ለራሱ ምቹ በሆነ ሰው እና ሰውነት ላይ እንደፈለገ ይሆናል፣ የፈለገውን ዓላማ ይፈጽማል፣ ለሚፈልገው ዓላማ መጠቀሚያ ያደርገዋል፡፡ (ዘሌ 11÷44) ቅዱስ ጳውሎስም ‹‹ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኃለሁ›› በማለት የልመና ጥሪ ያቀርብልናል፡፡ (ሮሜ 12÷1) ◈ በእውነት ሰውነታችን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ነው? ሰውነታችን ቅዱስ እና መሥዋዕት ነው? ሰውነት በኃጢአት ሲረክስ ነፍስም ትረክሳለች፡፡ ልብ በሉ ቆሻሻ ነገር ላይ እና ቆሻሻ ስፍራ ላይ ዝንቦች ይሰፍራሉ፤ በኃጢአት የቆሸሸ እና የተበላሸ ሰውነት ላይ አጋንንት ይሰፍራሉ፤ በቆሻሻ ነገር እና በቆሻሻ ስፍራ ላይ ዝንቦች ለሰው ጎጂ የሆኑ በሽታዎችን ያከማቻሉ፤ በኃጢአት በቆሸሸ ሰውነት ላይም አጋንንት መንፈሳዊ ሕይወታችንን የሚያጠለሽ፣ ነፍሳችንን የሚያቆሽሽ ክፉ መርዙን ይረጫል፣ ጎጂ የሆነ ኃጢአትንም ያጠራቅማል፣ የሥጋ እና የነፍስ በሽታ ይሆናል፡፡  ◈ "በእነርሱ እንዳትረክሱ ሰውነታችሁን አታርክሱ" ብሎናል «በእነርሱ እንዳትረክሱ» ያለው አንድም በሰይጣን ክፉ ምሪት እና ተግባራት ሰውነታችንን፣ ነፍሳችንን እንዳናረክስ ነው፡፡ (ዘሌ 11÷43) ስለዚህ ሰውነታችሁን ለንስሐ፣ ለጽድቅ፣ ለጾም፣ ለጸሎት፣ ለስግደት እና ለቅዱስ ቁርባን ምቹ አድርጉ እንጂ በፍጹም ለሰይጣን ምቹ አታድርጉ፡፡ "የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል" (ምሳ 1፥33) «በቀሲስ ሄኖክ ወልደ ማርያም» #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

«በጥፋት ዳዊትን ከመሰልከው አይቀር፤ በንስሐም እርሱን ልትመስለው ይገባል።» ቅዱስ አምብሮስ (ለንጉሥ ቴዎስዮስ የተናገረው)
«በጥፋት ዳዊትን ከመሰልከው አይቀር፤ በንስሐም እርሱን ልትመስለው ይገባል።» ቅዱስ አምብሮስ (ለንጉሥ ቴዎስዮስ የተናገረው)

ፆምና ስግደት በአጋንንት ላይ ያለው የበላይነት || ጾም ፀሎት ያዝ ለቀቅ ለምናደርግ ሰዎች || ለጆሮ የተመቸንን ሁሉ መቀበል ትልቅ ስህተት ነው #ebs 🚩💥🔥 https://youtu.be/_3BmcoEfk8M

ሰይጣንና ዲያብሎስ የለም ለምትሉ ሁላ ይሄን አድምጡ | የእህታችን ፈተና፣ ገጠመኝ እና በመጨረሻም ውጤቱ | ሁላችሁም ይሄን ትምህርት አድምጡ! https://youtu.be/BGF391HyfYw

ሰዎች ርኩሳን መንፋስትን ለምን ይዋረሳሉ? ክፍል 18 | በማለዳ ንቁ 2022 | በማለዳ መያዝ ቁ2 | Pagumen Tube Podcast 🙏😭 https://youtu.be/0BA9FaSkK2I

«ሰኔ ፳፰ ቅዱስ አማኑኤል» ◈ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ለአባቶቻችን አምላክ ለቅዱስ አማኑኤል ወርሐዊ መታሠቢያ ክብረ በአል እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ። አማኑኤል ማለ
«ሰኔ ፳፰ ቅዱስ አማኑኤል» ◈ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ለአባቶቻችን አምላክ ለቅዱስ አማኑኤል ወርሐዊ መታሠቢያ ክብረ በአል እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ። አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው ማለት ነው። የአባቶቻችን የአብርሐም የይስሐቅ የያእቆብ አምላክ ቅዱስ እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን በቸርነቱ ይጠብቀን። አማኑኤል ማለት የአምላክ ሰላም፣ የእግዚአብሔር እርቅ፣ የጌታ አንድነት ማለት ነው። አማኑኤል ማለት "አማኑ" እና "ኤል" ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከኛ ጋር ማለት ነዉ። ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልጅንም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ትለዋለች ትርጉሙም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው።(ኢሳ 7፥14) ቸሩ ቅዱስ አማኑኤል ለእኛ ስትል በመስቀል ሞት የገለፅከዉን ፍቅርህን እያሰብን ከሐጢአት እና ከአመፅ እንድንርቅ ፍቅርህ በልቦናችን ይታተም በትንሣኤህ የኛን ትንሣኤ የገለፅክልን ጌታችን እናመሰግንሃለን፤ ክብር ኃይልና ምስጋና ለአምላካችን ለቅዱስ አማኑኤል ይሁን። በዚህ እለት በመታሰቢያ በአላቸዉ የምናስባቸው የአባቶቻችን የአብርሃም የይስሐቅ የያዕቆብ ረድኤትና በረከት አይለየን። ፀሎታቸው ይጠብቀን "አሜን" #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

«ክረምትን ለምን ፈራሁ?» ◈ በጋና ክረምትን እያፈራረቀ የሰውን ልጅ ሁሉ የሚመግብ እግዚአብሔር ነው፤ በክረምት ገበሬው ይዘራል፣ እግዚአብሔር ደግሞ ከሰማይ ጠሉን ይልክለታል። በክረምቱ ጊዜ ተዘርቶ ያደገው ሰብል እንዲበስል ፈጣሪው የበጋውን ፀሐይ ያወጣለታል፤ ትጉሁ ገብሬም የደረሰውን አዝመራ ሊሰበስብ በበጋው ማጭዱን ይዞ ይታያል፤ ክረምት ለገበሬው የሥራ ጊዜ ነው። ◈ ለእኔ ግን ክረምት ያስፈራኛል እንዳልጽፍ እጆቼ በብርዱ ቆፈን ይያዛሉ፣ እንዳላነብ አይኖቼ በእንቅልፍ ሽፋሽፍት ይፈዝዛሉ፤ ማልጄ በቤቴ መስኮት የማያት ፀሐይ በደመና ስትሸፈን ቀኑ የጀመረ ሌሊቱም የነጋ አይመስለኝ ከአልጋዬ ተነሥ ተነሥ አይለኝም ውጪው ሲጨልም ቤቴም ይደበዝዝብኛል፤ ወጥቼ ሥራዬን እንዳልሠራ፣ ከወዳጆቼ ጋር ተገናኝቼ እንዳላወጋ ዝናቡ አላላውስ ይለኛል። ለእኔ ክረምት ያስፈራኛል ግን ለምን ክረምትን ፈራሁት? እንደ ገበሬው የዝናብን በረከት ማየት ስላቃተኝ ይሆን? ወይስ የምዘራው ዘር በእጄ ስለሌለ? እንዲጸድቅ የምፈልገው ተክል፣ ልምላሜውን ማየት የሚያጓጓኝ እጽ የለኝ ይሆን? ◈ በሥራ እና በግል ጉዳዮቼ ተጠምጄ ከራቅኋቸው ከቤቸሰቦቼ ልብ ላይ የምዘራው ብዙ የፍቅር ዘርማ አለኝ፤ በሰዎች ሆታ እና ጩኸት ስከበብ የዘነጋሁት በመልካም ሰብእና እንዲጸድቅና እንዲለመልም የምፈልገው እኔነት አለኝ፤ ታዲያ ለራሴ የሚሆን በቂ ጊዜ አግኝቼ ውስጤን አርስ፣ እመረምርና አለሰልስ ዘንድ ክረምት የመጣው፣ ዝናቡስ የዘነበው ለእኔ ብሎ አይደል? ◈ ለካ የብርዱ ቆፈን የበረታብኝ፣ የአይኖቼ ሽፋሽፍት በእንቅልፍ የደከሙብኝ ክረምትን ስለማልወደው ሳይሆን የክረምትን በረከት ማስተዋል ስላልቻልኩ ነው፤ ለካስ ክረምቱ የደበተኝ "ደግሞ ሊመጣ ነው" ብዬ ቀድሜ ስላወገዝኩትና ራሴን ለሥራ ስላላዘጋጀሁ ነው። ሰማዩ ሲደምን እና ዝናቡ አላስወጣ ብሎ ሲዘንብ በእኔ ውስጥ ያለችውን ፀሐይ ፈልጌ እንድገልጣት እድል እየሰጠኝ ነው፤ ክረምት የደረቀው እጽ መልሶ የሚያቆጠቁጥበት ብቻ ሳይሆን ያረጀውና ሊወድቅ ያዘመመው ውስጤ የሚታደስበትና የሚጠገንበት ጊዜ ነው፤ ለካስ ክረምት ለገበሬ ብቻ የመሰለኝ ስህተት ነው። ክረምት ለእኔም ነው! ◈ ክረምት ሲገባ እና ፀሐይ አዘውትራ መታየት ስታቆም ከዚህ ጋር ተያይዞ "Seasonal affective disorder" የተባለ ድባቴ ውስጥ ለሚገቡ ሁሉ መታሰቢያነት የተጻፈ። "የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል" (ምሳ 1፥33) (ዲያቆን አቤል ካሳሁን) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

🚩 የጠቋር ክፉ መንፈስ የፍርሃት ጥላዎች || የጠቋር መንፈስ የጥቃት ስልቶቹ https://youtu.be/GMQVmykAWiE?si=uYTbhij5xYaB2krf

"የእርግማን ዘር ምልክቶች || የእርግማን መንፈስ ምንድነው?" https://youtu.be/W3hHfc0-GZ4?si=qHV9J_t1KmAjM3rw