HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Открыть в Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Больше2 280
Подписчики
Нет данных24 часа
+77 дней
+3930 день
Архив постов
"...አንተም ልጄ እስከመቼ ነው ቸልተኛ የምትኾነው? የቸልተኝነትኽ ገደብ ምንድነው?ዛሬም ያለፈው ዓመት እንደነበረው በዚኽ ዓመትም እንዲኹ ነው፣ ትናንት እንደነበረው እንዲኹ ነው፤ ቸልተኛ እስከኾንክ ድረስ መንፈሳዊ እድገት ላንተ የለም፤ ንቁ ኹን፣ ልብኽን አንሣ ምክንያቱም በእግዚአብሔር ፍርድ ወንበር ፊት ትቆማለኽና፣ በግልም ኾነ በዐደባባይ ስለሰራኸው ነገር መልስ ትሰጣለኽና።"
(ታላቁ ቅዱስ ጳኩሚስ)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
በተደጋጋሚ የመደፈር ሙከራ የደረሰባት እህት አሳዛኝ ታርክ በቤተሰብ እንድንጠላ የሚያደርጉ ክፉ መንፈሶች ማስተርበሽን የሁሉ ሰው ፈተና #ebs 💥🔥🚩😭
https://youtu.be/g-DqK3PbdkU?si=bKBfPEuVT1bDtgUF
ሰይጣን በትህትና ፍት መቆም አይችልም || 3ቱ የማይታወቁ ነገሮች || ከሴት ጋር የመኖር ጥበብ || በተደጋጋሚ በአንድ ኃጢአት መውደቅን ለመከላከል 🚩🔥💥🙏 https://youtu.be/YgVrIG7FtuI
«ላይቪ ከቀሲስ ሄኖክ ተፈራ ጋር» ሁላችሁም ተጋብዛችኋል በሰዓቱ ተገኙ። => የተወደዳችሁ የፍኖተ ሕይወት ጉባኤ ተከታታዮች ዛሬ ሰኔ 26 እሮብ ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ላይ ልዩ የቀጥታ ስርጭት በቴሌግራም ይኖረናል። ዛሬ ከስር ባለው ሊንክ በቀጥታ ስርጭቱ ላይ በመግባት ይከታተሉ።
https://t.me/kesishenokLive
© መልአከ ሕይወት ቀሲስ ሄኖክ ተፈራ።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
«ላይቪ ከቀሲስ ሄኖክ ተፈራ ጋር» ሁላችሁም ተጋብዛችኋል በሰዓቱ ተገኙ። => የተወደዳችሁ የፍኖተ ሕይወት ጉባኤ ተከታታዮች ዛሬ ሰኔ 26 እሮብ ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ላይ ልዩ የቀጥታ ስርጭት በቴሌግራም ይኖረናል። ዛሬ ከስር ባለው ሊንክ በቀጥታ ስርጭቱ ላይ በመግባት ይከታተሉ።
https://t.me/kesishenokLive
© መልአከ ሕይወት ቀሲስ ሄኖክ ተፈራ።
«የሕይወት ዘመን ግብህ ምንድን ነው!»
◈ ሰው በዚህ ምድር ላይ በሕይወት ሲኖር የህይወት ዘመኑ ከመጠናቀቁ በፊት ሊጨብጣቸው ወይም የራሱ ሊያደርጋቸው የሚፈልጋቸው ብዙ ነገሮች ይኖራሉ፡፡ ከብዙዎቹ ውስጥ አንዱን ምረጥና ተናገር ቢባል ደግሞ ከነዚያ ከብዙዎቹ ውስጥ በጣም የሚሻውን አንዱን ነገር ይናገራል፡፡ አንተስ ይህንን ብትጠየቅ በህይወት ዘመንክ እንዲሳካ የምትፈልገው ወይም የሕይወት ዘመን ግብህ ምንድን ነው። አንዳንዱ ቤት መስራት፣ መኪና መግዛት፣ ትዳር መመስረት፣ ዘሩን መተካት፣ ተምሮ አዋቂ መባል፣ መሪ ሆኖ ብዙዎችን መምራት፣ ገንዘብ ኖሮት የፈለገውን ማድረግ…ወዘተ ብዙ ነገሮችን መዘርዘር ይቻላል፡፡
◈ እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት ነገሮች በሙሉ በአግባቡ ከተደረጉ በራሳቸው ኃጢአትም ክፋትም የላቸውም፤ ነገር ግን የህይወት ዘመናችን ግቦች ሊሆኑ አይችሉም፡፡ ሰው ከሁሉ ነገር መጀመሪያ ሊያሳካው የሚገባው ነገር ቢኖር የዘለዓለማዊ ቤቱን መስራት እና የመንግስቱ ወራሽ ሊያደርጉት የሚችሉትን ምሥጢራት መፈጸም ነው፡፡
◈ ‹‹ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግስት ጽድቁንም ፈልጉ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል›› እንዲል። (ማቴ 6፥33) ሰው የተፈጠረበት ዋነኛ ዓላማ የእግዚአብሔርን መንግስት ለመውረስ እና ዘላለማዊ ህይወትን ለመኖር እንጂ ምድራዊውን ነገር /የስጋውን/ እያግበሰበሰ የነፍሱን ነገር ረስቶ እንዲሞት አይደለም፡፡
◈ የተፈጠረበትን ዓላማ የማያውቅ ሰው ግን ተኝቶም ተቀምጦም ሃሳቡ በሙሉ ስለምድራዊው ስኬት ብቻ ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹መልካሙን ስራ ለማድረግ ተፈጠርን›› እንዳለን ከሁሉ መልካም የሆነውን ተግባር እግዚአብሔርን በማመስገንና ለህጉ ተገዢ በመሆን ዘለዓለማዊ ህይወትን እንድንወርስ ተፈጥረናል፤ አሁን ግን ሰው ሁሉ ይህን ረሳና የህይወት ዘመን ግቡ ሁሉ አላፊና ጠፊው ሆኖ ሲባዝን ይስተዋላል፡፡ (ኤፌ 2፥10)
◈ በምንም ስሌት ቢሰላ፤ በየትኛውም እይታ ቢታይ የሰው ልጅ በዚህ ምድር ላይ መልካምና በጎ ሆኖ የፈጣሪውን የእግዚአብሔርን መንግስት እያሰበ ከመኖር ውጪ ሌላ ዋነኛ ግብ ሊኖረው አይችልም፤ ሰው ክቡርና ዘለዓለማዊ ሕይወት ያለው ፍጡር ነው፡፡
◈ በዚህ አነዋወሩ ደግሞ ጊዜያዊ ነገሮች ሁሉ የእግረ መንገድ ክንዋኔዎች እንጂ ዋነኛ ግቡ ሊሆኑ አይችሉም፡፡ አንድ ሰው ከአዲስ አበባ ጅማ ሲሄድ ወልቂጤ ላይ ወርዶ ምሳ መብላትና ሻይ መጠጣት የሚሄድበት መድረሻው ወይም የዓላማው ግብ አይደለም፤ ነገር ግን መብላትና መጠጣት ስለሚኖርበት በመንገዱ ላይ ወርዶ የሚያስፈልገውን ያደርጋል፡፡
◈ እኛም በዚህ ምድር ላይ ስንኖር ከእናታችን ማህጸን ወጥተን ወደ እግዚአብሔር መንግስት እስክንገባ ድረስ በመንገዳችን የምናደርጋቸው የስጋ ስራዎች ሁሉ የእግረ መንገድ ክንዋኔዎች እንጂ የሕይወታችን ዋነኛ ግቦች እንደሆኑ አድርገን ማሰብ አይገባንም፡፡
◈ ጠቢቡ ሰለሞን በመጽሐፈ መክብብ ሲናገር ‹‹ከፀሐይ በታች በሚደክምበት ድካም ሁሉ የሰው ትርፉ ምንድር ነው፤ ፀሐይ ትወጣለች፥ ፀሐይም ትገባለች፥ ወደምትወጣበትም ስፍራ ትቸኵላለች፤ ነፋስ ወደ ደቡብ ይሄዳል፥ ወደ ሰሜንም ይዞራል፤ ዘወትር በዙረቱ ይዞራል፥ ነፋስም በዙረቱ ደግሞ ይመለሳል፤ ነፋስ ወደ ደቡብ ይሄዳል፥ ወደ ሰሜንም ይዞራል፤ ዘወትር በዙረቱ ይዞራል፥ ነፋስም በዙረቱ ደግሞ ይመለሳል፤ ነፋስ ወደ ደቡብ ይሄዳል፥ ወደ ሰሜንም ይዞራል፤ ዘወትር በዙረቱ ይዞራል፥ ነፋስም በዙረቱ ደግሞ ይመለሳል፤ ነፋስ ወደ ደቡብ ይሄዳል፥ ወደ ሰሜንም ይዞራል፤ ዘወትር በዙረቱ ይዞራል፥ ነፋስም በዙረቱ ደግሞ ይመለሳል፤ እኔ ሰባኪው በእስራኤል ላይ በኢየሩሳሌም ንጉሥ ነበርሁ፤ ከሰማይም በታች የተደረገውን ሁሉ በጥበብ እፈልግና እመረምር ዘንድ ልቤን አተጋሁ፤ እግዚአብሔር ይደክሙባት ዘንድ ይህችን ለሰው ልጆች የሰጠ ክፉ ጥረት ናት፤ ከፀሐይ በታች የተሠራውን ሥራ ሁሉ አየሁ፤ እነሆም ሁሉ ከንቱ ነው ነፋስንም እንደ መከተል ነው›› በማለት የምንደክምላት እና የምንባዝንላትን ዓለም መጨረሻ አስረድቶናል፡፡ (መክብብ 1፥1-14)
◈ በጣም በመራቁ እና በመርቀቁ ምክንያት በስጋዊ አይናችን ልናየው ያልቻልነውን የህይወት ዘመን ግባችንን እንደቀልድ እንዳናጣጥል አሁን ሁላችንም እይታችንን እናስተካክል፤ አርቆ የሚያየውን የልቡናችንን ዐይን እንክፈት፡፡
◈ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው ተብሎ እንደተጻፈ፥ እንዲህ እንናገራለን›› በማለት ስለመንግስተ ሰማያት አስቀድሞ ነግሮናልና፤ ስለዚህ ለመንፈሳዊ ህይወት አብዝተን የምንተጋ እንሁን። (1ኛ ቆሮ 2፥9)
◈ በአጠቃላይ እኛ በዚህ ምድር ስንወርድ ስንወጣ ለስጋችን ብቻ መድላት የለብን ይበልጥኑ ለነፍሳችን አብዝተን ማሰብ ለዛ ለዘላለም ክብር የሚያበቁን ነገር መፈጸም፤ የተፈጠርነው መንግስቱ ለመውረስ ነውና።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ያልነቃንበት ግን ብዙ የተጎዳንበት ጸሎት ስጀምር ፈተናው በዛብኝ እንላለን አንደበትና የአጋንንቱ ሴራ || አጋንንት ይታገላል እኛ አንቀላፍተናል 🚩🔥💥
https://youtu.be/Rttw2Z-8tk4
ስሰግድ፣ ስጸልይ፣ ስንበረከክ ለምን ፈተናው ይበዛል? || ዓለማዊ ስንሆን ሁሉም ይሞላል || ጸበል ለመጠመቅ ከመሄዳችን በፍት ምን እናድርግ? #ebs 😱💥🔥🚩 https://youtu.be/E3f48VNXh2E
«በማንኛዉም ጊዜ ማድርግ ያለብን!»
1. አልችልም ብለህ በምታስብበት ጊዜ...ይህንን አስታውስ => "ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ" (ፊል 4፥13)
2. አንድ ነገር እንደሚጎድልህ በምታስብበት ጊዜ.....ይህንን አስታውስ => "አምላኬም እንደ ባለ ጠግነቱ መጠን በክብር በክርስቶስ ኢየሱስ የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ ይሞላባችኋል" (ፊል 4፥19)
3. በምትፈራበት ጊዜ......ይህንን አስታውስ => "እግዚአብሔር የኃይልና የፍቅር ራስንም የመግዛት መንፈስ እንጂ የፍርሃት መንፈስ አልሰጠንምና።" (2ኛ ጢሞ 1፥7)
4. እግዚአብሔር የሚፈልገውን ለማድረግ በቂ እምነት የለኝም ብለህ በምታስብበት ጊዜ....ይህንን አስታውስ => "እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ የእምነትን መጠን እንዳካፈኝ" (ሮሜ 12፥3)
5. ደካማ ነኝ ብለህ በምታስብበት ጊዜ.....ይህንን አስታውስ=> "እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው፤ የሚያስፈራኝ ማን ነው፤ እግዚአብሔር የሕይወቴ መታመኛዋ ነው፤ የሚያስደነግጠኝ ማን ነውና አምላካቸውን የሚያውቁ ሕዝብ ይበረታሉ፥ ያደርጋሉም" (መዝ 27፥1፤ ዳን 11፥32)
6. ሰይጣን ሕይወትህን እስኪቆጣጠር ድረስ የፈተነህ በሚመስልህ ጊዜ....ይህንን አስታውስ => "በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና።" (1ኛ ዮሐ 4፥4)
7. ተሸንፌለሁ ብለህ በምታስብበት ጊዜ.....ይህን አስታውስ => "ነገር ግን በክርስቶስ ሁልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ሁሉ የእውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይሁን፤" (2ኛ ቆሮ 2፥14)
8. ጥበብ ጎድሎኛል ብለህ በምታስብበት ጊዜ....ይህንን አስታውስ => ክርስቶስ ለአንተ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበብ እንደ ሆነልህና ሳይነቅፍ በልግስና እግዚአብሔር እንደሚሰጥ የሚያረጋግጠውን ቃል" (1ኛ ቆሮ 1፥30፤ ያዕ 1፥5)
9. መንፈስህ ሲጫጫንህና ሲከብድህ በምታስብበት ጊዜ.....ይህንን አስታውስ => ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው፤ ርኅራኄው አያልቅምና፤ ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው፤ ታማኝነትህ ብዙ ነው" (ሰቆ ኤር 3፥21-23)
10. ጭንቀትና ውጥረት በሚሰማህ ጊዜ.....ይህን አስታውስ => "እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት" (1ኛ ጴጥ 5፥7)
11. የታሰርክ መስሎ በሚሰማህ ጊዜ.....ይህን አስታውስ => "ጌታ ግን መንፈስ ነው፤ የጌታም መንፈስ ባለበት በዚያ አርነት አለ" (2ኛ ቆሮ 3፥17)
12. እንደ ተኮነንክ መስሎ በሚሰማህ ጊዜ.....ይህንን አስታውስ => "እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም" (ሮሜ 8፥1)
13. ብቸኝነት በሚሰማህ ጊዜ....ይህንን አስታውስ => "ኢየሱስ እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ" (ማቴዎ 28፥19-20)
14. የተረገም መጥፎ ዕድል የተፀናወተህ መስሎ በሚሰማህ ጊዜ .....ይህን አስታውስ => "ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማን ሆኖ ከሕግ እርግማን ዋጀን" (ገላ 3፥13)
15. አለመርካት በሚሰማህ ጊዜ.....ይህን አስታውስ => "ይህን ስል ስለ ጉድለት አልልም፤ የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል ማለትን ተምሬአለሁና" (ፊል 4፥11)
16. ዋጋ ቢስ እንደ ሆነክ በሚሰማህ ጊዜ......ይህንን አስታውስ => "እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው" (2ኛ ቆሮ 5፥21)
17. እየተሰደድክ መሆንህ በሚሰማህ ጊዜ....ይህን አስታውስ => "እንግዲህ ስለዚህ ነገር ምን እንላለን? እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ማን ይቃወመናል?" (ሮሜ 8፥31)
18. ግራ የገባህ መስሎ በሚሰማህ ጊዜ...ይህን አስታውስ => "እግዚአብሔርስ የሰላም አምላክ ነው እንጂ የሁከት አምላክ አይደለምና" (1ኛ ቆሮ 14፥33) እኛ ግን ከእግዚአብሔር እንዲያው የተሰጠንን እናውቅ ዘንድ ከእግዚአብሔር የሆነውን መንፈስ እንጂ የዓለምን መንፈስ አልተቀበልንም" (1ኛ ቆሮ 2፥12)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ጸሎታችን እንድሰማ ምን እናድርግ? | ባለ አንድ አይኑ የቡዳ መንፈስ | ዘመኑን መምሰል ሳይሆን መብለጥ ነው ሃይማኖት | ዘመኑን መዋጀት እንዴት ነው? 💥🔥🚩😱
https://youtu.be/VTS1KxIbhLM?si=YpXtIbDarpvgf1en
"ስፕከር (Speaker) እና ፍላሽ" | ሰላም ውድ ቤተሰቦቼ እንዴት ናችሁ! የመምህር ተስፋዬ ገጠመኞች፣ የመምህር ግርማ ትምህርቶች፣ የቀሲስ ሄኖክ ወልደማሪያም ትምህርቶችንና የመናፍስት ውጊያ ትምህርቶችን ለሎችንም የማንቂያ ትምህቶችን ጭነን እንድንሰጣቸው በገጠራማው ሀገራችን የሚገኙ ቤተሰቦች በውስጥ መስመር እየጠየቁን ስለሆነ በተለይም አባቶች፣ እናቶች እንዲሁም ወጣቶች እየጠየቁን ስለሆነ በዚህ የበረከት ሥራ መሳተፍ የምትፈልጉ ቤተሰቦቼ በውስጥ መስመር እንድታናግሩኝ ስል በትህትና እጠይቃለሁኝ። በተለይም እነዚህ ቤተሰቦች የሚገኙት በገጠራማው አከባቢ ስለሆኑ እንተርነት፣ መብራት ለሎችም ብዙ ነገሮች የሌሉበት ቦታ ስለሆነ ትምህርቶችን መከታተልና መማር ይፈልጋሉ ግን በብዙ ምክንያት ማግኘት አልቻሉምና በዚህ ሥራ ብንሳተፍና ብናግዛቸው ብዙ በረከትን እናገኛለን ቤተሰቦቼ። የሚገርመው ደግሞ እነዚህ ቤተሰቦች በባዕድ አምልኮና የመናፍስቱ አሰራር ከቤዛባቸው አከባቢ ነውና እነዚህን ትምህርቶች መከታተልና መዋጋት ስለ ፈለጉ ይሄን ሥራ ብንሰራ እላለሁኝ። ስለዚህ ፍላሽና ስፕከር ገዝተን እንድንሰጣቸው እንተጋገዝ እላለሁ። ሰላሜ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እላለሁ!
ለተጨማሪ መረጃ በውስጥ መስመር አናግሩኝ @haile_gebriel_tube_bot 🙏🙏🙏
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ሰይጣን መንፈሳዊ ሕይወትን ለመኖር ወስነህ ስትጀምር በእነዚህ ሁለት ሐሳቦች ይዋጋሃል።
1. አንተ ለዚህ ሕይወት እንደማትሆን እና መቼም እንደማትለወጥ ሹክ ይልሃል። ይህን የሚያደርገው ተስፋ ቆርጠህ የያዝከውን ሩጫ እንድታቆም ነው። የሚገርመው ግን መለወጥ ባትጀምር ኖሮ ሰይጣን “አልተለወጥህም” አይልህም።
2. ገና ከመጀመርህ የደረስህ እና ለመፈጸም ጥቂት የቀረህ አስመስሎ ያሳይሃል። ብዙ ርቀህ እንደ ሄድህ አስበህ ልክ እንደ ጥንቸሏ ተዘናግተህ እንድትተኛ እና የጽድቅ ነገር ሁሉ ጠላት የሆነው ትዕቢት እስረኛ እንድትሆን ያደርግሃል። አሁንም ሰይጣን “ደርሰሃል” እያለ ሲክብህ ገና እግርህን ለማንሣት የምትጣጣር እንደ ሆንህ አቅምህን በደንብ ያውቀዋል።
ጀማሪ ስትሆን ሰይጣን “አትችልም” ብሎ ተስፋ በማስቆረጥ ወይም “ደርሰሃል” እያለ ያለ ልክ በማመስገን ወጥመዱ ውስጥ ሊጥልህ ይሞክራል።
“በሰይጣን እንዳንታለል፤ የእርሱን አሳብ አንስተውምና” 2ኛ ቆሮ 2:11
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
selam@dnabel.com
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
20 ዓመታት በመተት የተሰቃየች እህት ለጸሎትና ስግደት ጉልበት ያጣ ትውልድ የአጋንንት ውጊያዎችና ሴራው || በማለዳ ንቁ 2024 #ethiopia 🔥💥
https://youtu.be/-ZW2HtFePQk?si=S8RUXB_P4xE8-Tw5
የዲያብሎስን ሥራ የሚደብቁ አባቶች || መንፈሳዊ ሰው ለመሆን ምን እናድርግ? || ለማውደም፣ ለማጥፋት ገንዘብ አለን || የሰይጣንን ሥራ መናቅ የለብንም 🔥💥 https://youtu.be/sXvg9fqepXs
"እግዚአብሔርን ከሀብትህ አክብር፥ ከፍሬህም ሁሉ በኵራት፤ ጐተራህም እህልን ይሞላል፥ መጥመቂያህም በወይን ጠጅ ሞልታ ትትረፈረፋለች። (ምሳ.3:9-10) ለተቸገረው ሰው በጎ ነገርን ማድረግ አትከልክል፥ ልታደርግለት የሚቻልህ ሲሆን።" (ምሳ.3:27)
"ያለውን የሚበትን ሰው አለ፥ ይጨመርለታልም፤ ያለ ቅጥ የሚነፍግ ሰውም አለ፥ ይደኸያልም። የምትባረክ ነፍስ ትጠግባለች፥ የረካም እርሱ ደግሞ ይረካል። የድሀውን ጩኸት እንዳይሰማ ጆሮውን የሚደፍን ሰው፥ እርሱ ራሱ ይጮኻል አይሰማለትምም።" (ምሳ.11:24,25)
"ለሚለምንህ ስጥ፥ ከአንተም ይበደር ዘንድ ከሚወደው ፈቀቅ አትበል። (ማቴ.5:42) እንግዲህ ምጽዋት ስታደርግ፥ ግብዞች በሰው ዘንድ ሊከበሩ በምኩራብ በመንገድም እንደሚያደርጉ በፊትህ መለከት አታስነፋ፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል። አንተ ግን ምጽዋት ስታደርግ ምጽዋትህ በስውር እንዲሆን ቀኝህ የምትሠራውን ግራህ አትወቅ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል።" (ማቴ.6:2-4)
"ስጡ ይሰጣችሁማል፤ በምትሰፍሩበት መስፈሪያ ተመልሶ ይሰፈርላችኋልና፥ የተጨቈነና የተነቀነቀ የተትረፈረፈም መልካም መስፈሪያ በእቅፋችሁ ይሰጣችኋል።" (ሉቃ.6:38)
"ይህንም እላለሁ። በጥቂት የሚዘራ በጥቂት ደግሞ ያጭዳል፥ በበረከትም የሚዘራ በበረከት ደግሞ ያጭዳል። እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፥ በኀዘን ወይም በግድ አይደለም። በተነ፥ ለምስኪኖች ሰጠ፥ ጽድቁ ለዘላለም ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ እግዚአብሔር፥ ሁልጊዜ በነገር ሁሉ ብቃትን ሁሉ አግኝታችሁ ለበጎ ሥራ ሁሉ ትበዙ ዘንድ፥ ጸጋን ሁሉ ሊያበዛላችሁ ይችላል። ለዘሪ ዘርን ለመብላትም እንጀራን በብዙ የሚሰጥ እርሱም የምትዘሩትን ዘር ይሰጣችኋል ያበረክትላችሁማል፥ የጽድቃችሁንም ፍሬ ያሳድጋል፤ በእኛ በኩል ለእግዚአብሔር የምስጋና ምክንያት የሚሆነውን ልግስና ሁሉ እንድታሳዩ በሁሉ ነገር ባለ ጠጎች ትሆናላችሁ። የዚህ ረድኤት አገልግሎት ለቅዱሳን የሚጎድላቸውን በሙሉ የሚሰጥ ብቻ አይደለምና፥ ነገር ግን ደግሞ በብዙ ምስጋና ለእግዚአብሔር ይበዛል። (2ኛ ቆሮ.9:6-12)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
«ለጋብቻ የምትኾን ሴት ሥሩ!»
◈ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ወላጆች ልጆቻቸውን እንዴት ማሳደግ እንዳለባቸው ወርቃማ የኾኑና የተዋቡ ልብን የሚመስጡ ትምህርቶችን አስተምሯል። ለምሳሌ "እናቶች ኾይ እናንተም ሴት ልጆቻችኹን በደንብ ለመቆጣጠር ልዩ ጥንቃቄን አድርጉ። እነርሱን ለመቆጣጠር ቀላል ነውና። ተከታተሏቸው እነርሱም ጥሩ የቤት እመቤት ሊኾኑ ይችላሉና። ከኹሉም በላይ ለሃይማኖታቸው ቀናዒና ራሳቸውን መሥዋዕት የሚያደርጉ አለባበሳቸው ትሑት ስብእናቸው የሚናገር እንዲኾን፣ ሀብትን የሚንቁ፣ ለጌጥ ፍላጎት የሌላቸው ይኾኑ ዘንድ አስተምሯቸው። በዚህ መንገድ ለጋብቻ ምቹ እንዲኾኑ አመቻቿቸው። በዚህ መንገድ ከቀረጻችኋቸው የምታድኑት እነርሱን ብቻ አይደለም። እነርሱን ለማግባት የወሰነውን ባል እንጂ። ባልንም ብቻ አይደለም የልጅ ልጆችንም ጭምር እንጂ። ሥሩ መልካም ኾኖ ከተሠራ መልካም ቅርንጫፍ ይወጣል። ቅርንጫፎቹ አኹንም የተሻሉ ይኾናሉ። ለእነዚህ ኹሉ ሽልማትን ትቀበላላችኹ። ስለዚህ የምንጠቅመው አንዲትን ነፍስ ብቻ አይደለም በዚያች ነፍስ ብዙ ሰዎችን ነውና ኹሉንም ሥራዎች እንሥራ። ታጋዮች ከመለማመጃ ትምህርት ቤት በሚያስፈልጋቸው ዕውቀት ኹሉ ተሞርደውና ለስልሰው እንደሚወጡና እንደ እርሾ ኹሉንም ዐመጸኛ ሰው ወደ መልካም ሥነ ምግባር እንደሚያሻግሩ ኹሉ እነርሱም ከአባታቸው ቤት ተሞርደውና ለስልሰው ወደ ጋብቻው መሄዳቸው ግድ ነው።" በማለት እጅግ ግሩም በኾነ ኹኔታ አስተምሮናል።
ጠቃሚ ምክር ነውና ለሁሉም እንዲደርስ ሸር እናድርግ!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
"ስለ ጽዮን ዝም አልልም፥ ስለ ኢየሩሳሌምም ጸጥ አልልም፥ ጽድቅዋ እንደ ጸዳል መዳንዋም እንደሚበራ ፋና እስኪወጣ ድረስ። አሕዛብም ጽድቅሽን ነገሥታትም ሁሉ ክብርሽን ያያሉ፤ የእግዚአብሔርም አፍ በሚጠራበት በአዲሱ ስም ትጠሪያለሽ። በእግዚአብሔር እጅ የክብር አክሊል፥ በአምላክሽም እጅ የመንግሥት ዘውድ ትሆኛለሽ።" (ኢሳ.62፡1-3)
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም
አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ሸር ይደረግ!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
እንዴት የአጋንንትን ውጊያ አትወቁ ይባላል? መጀመር እንጂ ማቆም ያቃቱን ነገሮች | አባ ገብረኪዳን ስለ 666 ይናገራሉ | የቀሲስ ሄኖክ ልዩ መልዕክት 😱💥https://youtu.be/BgUCaBf5c7A
ዕቅዳችን፣ አሳባችን፣ ትዳራችን የማይሳካው ለዚህ ነው || ደብተራ መተተኛን እንዴት ማወቅ ይቻላል? እውነተኛ ትዳር ምን ይመስላል? አባ ገብረኪዳን #eotc 💥 https://youtu.be/LUUgkbIagUQ
◈ ልጆቼ! ይህን ታውቁ ዘንድ እወዳለው፤ ዲያብሎስ የሚፈትነው በየገዳማቱ፣ በየዋሻውና በየገደሉ ያሉትን ብቻ አይደለም፤ ዲያብሎስ በከተማ ላለነውም እንዲኹ ይፈትነናል፤ በገበያው ቦታ ይፈትነናል፤ በየወኅኒው ቤቱ ይፈትነናል፤ በቁሙ ራሱ ላይመጣ ይችላል፤ ደቀ መዛሙርቱን በመላክ፣ በራሳችን ምኞት አድሮም ይፈትነናል እንጂ፡፡
◈ ታዲያ ምን እናድርግ? ፈጽመን አንመነው፤ ጆሯችንን አንስጠው አመስጋኝ መስሎ ቢመጣም ፈጽመን እንጥላው፤ አብዝቶ "ይህን ላድርግልህ" ቢለንም እኛም አብዝተን እንራቀው፤ ምክንያቱም በቀዳማይቱ ሔዋን ያደረገውን ስንመለከት አስቀድሞ ልቧ ከንቱ በኾነ ተስፋ እንዲሞላ አደረገ፤ ቆይቶ ግን በዚሁ "ተስፋ" ጣላት፣ ታላቅ በደልም እንድትፈጽም አድርጓታልና፡፡
◈ ልጆቼ! ዲያብሎስ እጅግ አረመኔ የኾነ ጠላት ነው፤ የተሰጠንን ጸጋ እስክንጥል ድረስ እኛን እንዲህ ባሉ ጦርነቶች አብዝቶ ይዋጋናል፤ ስለዚህ እንራቀው፤ በቃል ብቻ ግን አይደለም፤ በገቢርም እንጂ በሕሊና ብቻ አይደለም፤ በስራም ጭምር እንጂ፤ እርሱ የሚወደውን ሥራ ከመሥራት ፈጽመን እንከልከል፤ መከልከል ብቻ ግን በቂ አይደለም ፤ እግዚአብሔር የሚወደውንም ጭምር እናድርግ እንጂ፡፡
◈ ዲያብሎስ መጠነ ብዙ ተስፋ ሊሰጠን ይችላል፤ ኾኖም ይህን የሚያደርገው እኛን ለመውሰድ እንጂ ለመስጠት አይደለም፤ ከባባድ የስርቆት ወንጀሎችን ሠርተን ባለጸጋ እንድንኾን ይጋብዘናል፤ በዚህ ምድር ፍሬ ብቻ እንድንቀማጠል አግዝፎ ያሳየናል፤ ኾኖም ይህን የሚያደርገው ጽድቅ ከእኛ እንድትርቅ፣ ደግሞም ሰማያዊውን ሀብት እንድናጣ ፈልጎ ነው፤ እዚህ ምድር ላይ ባለ ጸጋ ኾነን በላይኛው ቤታችን ለምነን እንኳን የማናገኝ ድኾች ሊያደርገን ሽቶ ነው፡፡ (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
