💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
Открыть в Telegram
💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው። 👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው። 💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።
Больше9 030
Подписчики
-424 часа
-337 дней
-13630 день
Архив постов
🎀 ልባም ሴት......
ጠፋች ሲሏት ~ ያው ደመቀች፡
አዝና ነበር ~ አልፎ ሳቀች፡
ወድቃ ነበር ~ ዳግም ቆመች፡
ፀናች እንጂ ~ መች ደከመች፡
✍....ኑረዲን አል አረቢ...
يَا عِبَادَ اللهِ جِدُّوا ... رُبَّ دَاعٍ لَا يُرَادُ
የአላህ ባሮች ሆይ! ትጉ፤ ምናልባት የማይፈለገው ተጣሪ (ሞት) ሊመጣ ይችላልና።
💎ንግስት ለመሆን ዘዉድ አያስፈልግሸም
በራስ መተማመንሽ ብቻ ይበቃሻል።
المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎
የአንዲት ደግ (ሷሊህ) ሚስት ዋጋ፡
ሸይኽ አብዱረዛቅ አል-በድር (ሀፊዘሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦
"ሷሊህ (ደግ) ሚስት ለአንድ ሰው የዚህች ዓለም ደስታው አካል ናት። ምክንያቱም በሷሊህ ሴቶች ላይ እንጂ የማይገኙ ውድ ባህሪያትን ታቅፋለችና፤ እነሱም፦
=>ታማኝነትና ቅንነት
=>ለባል መልካም ተመካሪ መሆን
=>ሀቅን መናገርና ሚስጥር ጠባቂነት
=>የባልን ንብረትና ክብር መጠበቅ
=>ለባል ተገቢውን ክብር መስጠት
=>ልጆችን በጥሩ ስነ-ምግባር ማነፅ
በተጨማሪም የእሷ ደግነትና መልካምነት በቀጥታ በልጆቿ ላይ ይንጸባረቃል። ምክንያቱም ልጆቹን በቅርበት የምትንከባከባቸው፣ የምታሳድጋቸውና ዘወትር የምትመክራቸው እሷ በመሆኗ ነው። ይህም አላህ በሷሊህ ሚስት አማካኝነት ለባል የሚለግሰው ትልቅ የደስታ ምንጭ ነው።"
📚 ምንጭ: [አስሩ የልጆች ማሳደጊያ መርሆዎች (9)]
አቡ ዑበይዳ
t.me/AbuOubeida
~ብዙ ጊዜ የኛ የሴቶች መስተካከል ለልጆቻችንን ብቻ የሚጠቅም ይመስለናል
ባለንበት ዘመን በሚድያዉ አለም የሚሰራዉን ማየት ከቻልን" የኛ መበላሸት ለኡማዉ እንደት እንደሚጎዳና የኛ መስተካከል ለኡማዉ እንደት እንደሚጠቅም በቀላሉ ለመገንዘብ አያቅትም።"Repost from Abu useymin (Mohammed Ali)
«በሐያእ እየተራመደች መጣች...»
አላህም የነቢይ (የሙሳ ዐ.ሰ) ሚስት አደረጋት።
እህቴ! ውበትሽን በሐያእ ስትከናነቢ፣ አላህ ክብርሽን ከፍ ያደርገዋል። ሐያእ የአንቺ ንግሥትነት ነው። በሐያእ የተከናነበች ሴት ለጌታዋ ቅርብ ናት፤ ለሰዎችም ዘንድ የተከበረች ናት። 👑
ትዳርንም ሆነ ክብርን ለማግኘት "ተበሩጅ" (ለአጅነቢይ መገላለጥ) አያስፈልግሽም። የአላህ ስጦታ በሐያእ እንጂ እርሱን በሚያስቆጣ መንገድ አይመጣም።
አስታውሺ! ደስታሽም ሆነ ዕጣ ፈንታሽ ያለው በአላህ እጅ ብቻ ነው። ስለዚህ እርሱን በማስደሰት ላይ በርቺ፤ እርሱ ደግሞ አንቺን ሊያስደስትሽ በርግጥ ቻይ ነው። 🕊️✨
ወንጀል ላይ ያሉ ሰዎችን ስትከታተል ሁለት ፈተና ሊገጥምህ ነው....
•ያሉበትን ሁኔታ መመኘት (ሳታስበው)
•እነሱን መናቅ እና በእነሱ መሳለቅ (ኻቲማ በአሏህ እጅ ብቻ ከመሆኑ ጋር)
ወንጀል ላይ ያሉ ሰዎችን ባለመከታተል እና ስለነሱ ባለማውራት አፊያህን ጠብቅ!
🔖ጥሩ ጓደኛ ካለህ አጥብቀህ ያዘው!
▪️قَالَ الشَّافِعِيُّ ـ رَحِمَهُ اللهُ ـ :
👈«مَثَلُ الْأُخُوَّةِ فِيٰ اللهِ كَمَثَلِ الْيَدِ وَ الْعَيْنِ، إِذَا دَمَعَتِ الْعَيْنُ مَسَحَتِ الْيَدُ دَمْعَهَا، وَ إِذَا تَأَلَّمَتِ الْيَدُ بَكَتِ الْعَيْنُ لِأَجْلِهَا،
إِذَا كَانَ لَكَ صَدِيقٌ يُعِينُكَ عَلَىٰ الطَّاعَةِ فَشُدَّ يَدَيْكَ بِهِ، فَإِنَّ اِتِّخَاذَ الصَّدِيقِ صَعْبٌ، وَ مُفَارَقَتُهُ سَهْل».
📖•|{حِلْيَةُ الْأَوْلِيَاء ١٠١/٤}|.
ለአላህ ብሎ መዋደድና ጓደኛ የመሆን ምሳሌው ልክ እንደ እጅና አይን ምሳሌ ነው። አይን ስታለቅስ እጅ እምባዋን ታብሳለች። እጅ ስትታመም ደግሞ በሷ ህመም አይን ታለቅሳለች። ወደ መልካም የሚመራህና በአላህ ትእዛዝ ላይ የሚያግዝ ጓደኛ ካለህ እንዳይለይህ አጥብቀህ ያዘው። ምክንያቱም በአሁን ሰአት መልካም ጓደኛ ማግኘት በጣም ከባድ ነው። ከመልካም ጓደኛ መለየት ግን በጣም ቀላል ነው።
t.me/https_Asselfyaአላህ ቁርአን ውስጥ وليال عشر ብሎ የማለበት ትል ቀን .......... ነው
«ሲቀጥር ኢንሻ አሏህ …ሲገረም እና ያልጠበቀው ነገር ሲከሰት ሱብሃነሏህ…መብራት ሲጠፋ ኢና ሊላሂ ወኢና…….በየ ንግግሩ መኃል ሸሃዳ ሲልማ ስንት ቀን ሰዎችን አስደንግጧል…ከሰው ጋር ሲያወራ ለራሱ አሏሁል ሙስተዓን ሲል ቆመን እየቆጠርን ነበር…..አንዳንዴማ አዎ ወይ አይ ማለት ሲጠበቅበት አልሀምዱሊላህ እያለ መድረክ ሲፈጥርልንስ…ሲያወሩት ደግሞ ሌላ አለም ያለ ነው የሚመስለው … ከንፈሩ ብቻ ሲንቀሳቀስ እንጂ የሚታየው የሚያዳምጥም አይመስል…»
በየ ሁኔታው ግን አሏህን ማውሳት እንዴት ደስ ይላል…🔥
Copy
ዛሬ ላይ ከሐራም ወከባ የሚያመልጡት ጥቂት ናቸው።እነርሱም ቢሆኑ ሐራም ነገር ሳይስባቸው፣
ሳያምራቸው ቀርቶ አይደለም።የሐራም መጨረሻው እንደማያምር፣ቁጭቱ ከባድ እንደሆነ የፀፀት ግርፋቱ እንደማያስተኛ ስለ ተገነዘቡ ነው።〰 ሶላት ውስጥ ሆነህ የምትዘነጋ ሰው ሆይ! አካልህ እዚህ ነው፤ ልብህ ሀገሩን ሁሉ ያዳርሳል፡፡ ሶላትህ ሩህ የሌለው በድን፤ ሕይወት የሌለው አካል ነው፡፡ የምትናገረውን አትረዳውም።
የአንተ ምሳሌ ወዲህ ነው፡- ንጉሱን ለማግኘት ውድ ስጦታ እንዲያበረክት እንደተነገረው ሰው። ሰውዬው ስጦታውን እንዲያስቀምጥ የተነገረው የእንግዳ መቀበያ ሳሎን ውስጥ ነበር፡፡ ታዲያ ይህ ሰው እፍኝ አፈር ዘገነና በስጦታ ወረቀት ጠቅልሎ ሳሎን ውስጥ አስቀመጠ፡፡ ስጦታውንም ለንጉሱ አበረከተ፡፡ ንጉሱ ስጦታውን ከፍቶ ሲመለከት በእጅጉ ተቆጣ፤ የሰውዬው እጣ ፋንታ ወደ ንጉሱ ከመቅረብ ይልቅ መራቅና መባረር ሆነ፡፡
ያ የስጦታ እድል ወደ ንጉሱ ለመቃረብና የእርሱ ባለሟል ለመሆን ትልቅ እድል ነበር ነገር ግን ሰውየው እድሉን አወደመ እህህህ ስለ ሰላት ነው ማወራችሁ
የተሰናባች_ሰላት_ስገድ
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
