💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
Открыть в Telegram
💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው። 👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው። 💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።
Больше9 029
Подписчики
+624 часа
-97 дней
-11130 день
Архив постов
🔖የነሲሀቲ ሊኒሳእ ኪታብ ቂርአት
📍ክፍል ❸❷
ጀ
መ
ረ
https://t.me/durusuabihizam?livestream
🔖አንዳንዴ……
👉ከሰዎች ርቀህ ለብቻህ ከጌታህ ጋር አግልል። ይቺን ቁርአንህ ይዘህ እየቀራህ፤ የአላህን ተአምር በዙሪያህ እየቃኘህ፤ እጅህን አንስተህ ያረብ እያልክ ነፍስህን እየመረመርክ ወደ ጌታህ ተመለስ። የዛኔ ኢማንህ ይጨምራል። ውስጥህ ይታደሳል። የኢባዳ ጥፍጥና ውስጥህ ይገባል።
Repost from «🔵Abu_Aisha (Awel_kasaw)»
قال العلامةابن السعدي رحمه الله:
" إذا ذهب الدين،
فبأي شيء تفرح؟!
وإذاخسرت الأخلاق الفاضلة،
فبأي سلعة تربح؟! ".
[الفواكه الشهية(٢٠٩)]
https://t.me/Abuebrahim22322
አዲስ ሙሓደራ
ርእስ:- የተውሒድ አንገብጋቢነትና የሺርክ አደጋወች
አቅራቢ:- አሽሸይኽ አወል አሕመድ አል ኸሚሲይ
ቦታ:-ደሴ
ቀን:-6/8/1447
🔖«የፈለከውን ያክል ኑር አንተ ሟች ነህ »
🎙 Abu Aisha( Awel ibnu kasaw)
t.me/Abuebrahim22322
ለረመዷን መዘጋጀት
🎙በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ሓፊዘሁላህ
👇👇👇👇
https://youtu.be/3YcjXthAgsQ?si=Rd8NhRvDoFV5t4OW
Repost from ስለ ቀልባችን
⏰ለማስታዎስ!
~
⌛ዛሬ ማታ አድ-ዳእ ወድ-ደዋእ(ሙኽተሶር)
مختصر الداء والدواء
ደርስ ይኖረናል! (ኢንሻ አላህ)–
🔔በዛሬው ደርሳችን የልብ ዶክተሩ ኢብኑል ቀይም «የስሜት መፍትሔ» በሚል ርዕስ ስሜት ለሚያስቸግረው ሁሉ፤ያስቀመጡትን ቋሚና ነቀል መፍትሔ እንመለከታለን።
🌟 t.me/Sle_qelbachn1
﴿ قَالَ إِنَّمَا أَشْكُو بَثِّي وَحُزْنِي إِلَى اللَّهِ وَأَعْلَمُ مِنَ اللَّهِ مَا لَا تَعْلَمُونَ﴾
[ يوسف: 86]
~
🔖 ቀልቤን እንዴት ማስተካከል እችላለሁ
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
🔺ሰበቦቹና ምክንያቶቹ፦
①) አላህን መፍራትና መጠባበቅ
②)ቁርአን ማንበብን ማብዛት
③)የነብዩን የህይወት ታሪክ ማንበብ
④)የደጋግ ሰዎች ታሪክ ማጥናት
⑤)ገሳጭ የሆኑ መፅሀፎች ማንበብ
⑥)የኸይር ሰዎችን መጎዳኘት
⑦)ከመጥፎ ጓደኞች መራቅ
⑧)ዱአ ማብዛት በተይ የሌሊቱ መጨረሻ
🎙لِفضِيلـة الشَّـيخ مُحمّـدُ بنُ هـادِي المدخـلِي -حَفِظـه الله.
الآدَابُ_الْمُهِمَّةُ_لِنِسَاءِ_الْأُمَّةِ_⑧.mp317.65 MB
✍️استحباب الإكثار من الصيام في شهر شعبان!!
📍የሸዕባን ወር ላይ ፆምን ማብዛት የተወደደ መሆኑ!!
🎤በኡስታዝ አቡ ሙስሊም حفظه الله
https://t.me/AbumuslimAlarsi
▶️የሁለተኛዉ ፕሮግራም▶️
🙁☹️😭🙁😭🙁☹️🙁
በወንድም አቡ ሂበቲላህ
ርዕስ إحياء السنة في كل مكان وزمان
ሱናን ሂያው ማድረግ በሁሉም ቦታ በሁሉም ወቅት
ተ⭐️
ጀ🔴
መ⭐️
ረ🔴
ገባ ገባ በሉ ባረከሏሁ ፊኩም
https://t.me/ABUOMAR_AMIRMUHAMMED?livestream=17f9c7f1cfa5da9757
ኢብራሂም– አንድ ሰው፣ ሁለት ስም!
~
አንተ ከሰዎች ዘንድ ማነህ? ደግ ወይስ ክፉ? ትሁት ወይስ በጥራራ? ፊተ በሻሻ ወይስ ጨፍጋጋ? ምራቅ የዋጠ በሳል ወይስ በቀዳዳ ሱሪ የሚጀነን ከንቱ ፍንዳታ? አንተ ማነህ? ሰዎች ስላንተ ምን ይላሉ? ምን እንደሚሉ ታውቃለህ? በክፉ መነሳት ያሳስብሀል? ወይስ የሰው ጉዳይ የማይጨንቅህ በራስህ ዛቢያ ላይ የምትሽከረከር ፍጡር ነህ?
አንቺስ ከሰው ዘንድ ማነሽ? ማን መባል ያምርሻል? ምን ስም እንዳይወጣልሽ ይጨንቅሻል? ባገር በመንደሩ ምን ስም አለሽ? ጨዋ? ዘል.ዛላ? ምላሳም? ቁጥብ? አጉል ነቃሁ ባይ? ግብረ ገብ? ቀብራራ? ኮስታራ?
ይህ ከሰው ዘንድ ነው። ከአላህ ዘንድስ እኛ ማነን? ምንስ ቦታ አለን? እስኪ ራሳችንን እንመልከት? አላህ ካዘዘብን ቦታ አለን? አላህ ከከለከለን ቦታ ርቀናል? ከሆነ ምንኛ መታደል ነው?! ከሆነ ከሰው ዘንድ ያለን ስም አያስጨንቀንም።
ከሰዎች ዘንድ እፍኝ የማይሞሉ፣ አይን የማይገቡ፣ ቢናገሩ ቃላቸው የማይሰማ፣ ቢጠይቁ ፊት የማይስሰጣቸው፣ በሰዎች መለኪያ እዚህ ግባ የማይባሉ ከአላህ ዘንድ ግን የላቀ የራቀ ደረጃ ያላቸው ስንትና ስንት የአላህ ሰዎች አሉ?! አላህ ዘንድ "ሰው" ከሆኑ በኋላ ሰዎች እንደ ሰው ባይቆጥሯቸው ምን ያጣሉ?! ኢብራሂምን አታይም? ከነዚያ ከበርቴዎች ዘንድ ማን ነበሩ? አንድ ተራ ወጣት!
(قَالُوا سَمِعْنَا فَتًى يَذْكُرُهُمْ يُقَالُ لَهُ إِبْرَاهِيمُ)
"ኢብራሂም የሚባል #ወጣት (በመጥፎ) ሲያነሳቸው ሰምተናል ተባባሉ።" [አልአንቢያእ: 60]
ከአላህ ዘንድስ ማን ነበሩ?
(إِنَّ إِبْرَاهِيمَ كَانَ أُمَّةً قَانِتًا لِلَّهِ حَنِيفًا وَلَمْ يَكُ مِنَ الْمُشْرِكِينَ)
"ኢብራሂም ለአላህ ታዛዥ ወደ ቀጥተኛ ሃይማኖት ተዘንባይ የሆነ #ሕዝብ ነበር፡፡ ከአጋሪዎቹም አልነበረም፡፡፡" [አንነሕል: 120]
ከሰዎች ዘንድ እንደ ዋዛ "አንድ ወጣት" ተብለው የተቃለሉት ኢብራሂም ከአላህ ዘንድ "ህዝብ" ተብለው ነበር የተሞካሹት!! አንዱ ኢብራሂም ሁለት ስም ሲኖራቸው ተመልከት። አንዱ እንደ ምድር፣ አንዱ እንደ ሰማይ። አንዱ ከምድር፣ ሌላው ከሰማይ። ልዩነቱን አየኸው?! አላህ እንዲህ ከሰቀላቸው በኋላ ፍጡር ሊያወርዷቸው ቢጣጣር ምን ያመጣል?! በተውሒድ የነገሰን ማን ያወርደዋል?!
·
ድሮ ነው። ወሎ፣ ወረባቦ ወረዳ ውስጥ የሚኖሩ ዑካሻ የተሰኙ በተውሒድ ጠንካራ የሆኑ፣ ህዝቡን የወረረውን ሺርካ ሺርክ የሚነቅፉና የሚፀየፉ ሸይኽ ነበሩ። "ከዘልማዳችን ወጥጣ" ብለው በጊዜው የነበሩ መሻይኾች ተሰብስበው "ፌንጥ" አሏቸው። ("ፌንጥ" አሁንም ድረስ ያለ አደገኛ ማህበራዊ ማእቀብ ነው። "ፌንጥ" የተባለ ሰው ከየትኛውም ማህበራዊ ህይወት ይገለላል። ሰላምታ እንኳን ይነፈጋል። ከሕዝብ መሐል እየኖረ በጫካ ውስጥ ከመኖር በላይ እየተሳቀቀ ባይተዋርነትን ይገፋል።)
ዑካሻ በጠንካራው የተውሒድ አቋማቸው የተነሳ አድማ ተመታባቸው። ከአቋማቸው ሊያሽመደምዷቸው በማለም ሸይኾቹ ተሰብስበው "ፌንጥ ብለንሀል" አሏቸው። የዑካሻ መልስ ግን ያልተጠበቀ ነበር። "እኔም ፌንጥ ብያችሁዋለሁ! ምን ታመጣላችሁ?!"
·
አዎ ሁለ ነገሩን ለአላህ የሰጠ ሰው፣ የሰው ሴራ ለአላህ ብሎ ከያዘው አቋሙ አያጥፈውም። የሰው ጭብጨባ በሙቀት አያቀልጠውም። አላህን የያዘ ምን አጥቷል? ከአላህ ጋር የሆነ ምን ያስፈራዋል?!
·
ወንድሜ ሆይ! እህቴ ሆይ! ከምንም በፊት ከአላህ ዘንድ ሰው እንሁን። በምኞት ሳይሆን በተግባር ሰው ለመሆንም እንጣር።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
🔖ተናፋቂው ወር የአንድ ወር እድሜ ብቻ ቀርቶታል:: በሰላም በአፍያ ያድርሰን::
የምንጠቀምበትም ያድርገን:: ቀዷ ያለባችሁ ቀዷችሁን ማውጣትን አስታውሱ:: የሰዉ እዳ ያለባችሁ ከቻላችሁ ስጡ ።ካልቻላችሁ አንድት ነፍስ ከአቅሟ በላይ አያስገድዳትምና ችግራችሁን ተናገሩ።በመጥፎ እንዲጠረጥሯችሁ /እንዲያስቧችሁ አታድርጉ።
በተረፈ እንደ ረመዷን ተወዳጅ ተናፋቂ ጠቃሚ ያድርገን ••• አሚንንን አቦ!
ለማንኛውም የተበደሩትን ሳይከፍሉ መወፈር አበዳሪን መናቅ ነው።
t.me/https_Asselfya
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
