ru
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Открыть в Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Больше
2 756
Подписчики
+124 часа
+17 дней
+4230 дней
Архив постов
ቋሚ ሲኖዶስ ልዩልዩ ውሳኔዎችን አስተላለፈ። ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ከቤተክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ በፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር አዳራሽ የሰጡትን ትምህርትና በማኅበሩ ሚዲያ የተላለፈበትን ሁኔታ በተመለከተ በዛሬው መደበኛ ጉባኤው በሰፊው ተወያይቶ ለመወሰን በያዘው ቀጠሮ መሠረት በጉዳዩ ዙሪያ ጥልቅ ውይይት ካደረገ በኋላ የሚከተሉትን ውሳኔዎችን አስተላልፏል። 1. ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር በተለያዩ ጊዜያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ውጪ በሚዲያው ያስተላለፈው የስሕተት ትምህርት የቤተክርስቲያናችንን አባቶች፣ሊቃውንቱንና መላው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያሳዘነ በመሆኑ በማኅበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ በኩል ጊዜያዊ የእገዳ ደብዳቤ እንዲደርሰው እና በመምሪያው በኩል አስፈላጊው ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ ሆኖ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ መስጠት ይቻል ዘንድ አምስት አባላት ያሉት ኮሚቴ እንዲቋቋም አድርጓል። በዚህም መሠረት ቋሚ ሲኖዶስ ያቋቋማቸው አጣሪ ልዑካን አጠቃላይ የማህበሩን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እና በሚዲያው ያስተላለፋቸውን የስህተት ትምህርቶች በተመለከተ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና ከማህበራት ምዝገባ፣ ቁጥጥርና ክትትል መምሪያ ጋር በመነጋገር በሚገባ መርምረውና አጣርተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርቡ፣ 2. ብፁዕ አቡነ ገብርኤል “ማርያም ቤዛዊተ ዓለም” አትባልም በማለት ከቤተ ክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ የሰጡት ሕጸጽ ያለበት ትምህርት በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚገባ ተመርምሮና ተጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ በአስቸኳይ እንዲቀርብ ብፁዕነታቸውም ጉዳዩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በተአቅቦ እንዲቆዩ፣ 3. ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና ብፁዕ አቡነ በርናባስ የደቡብ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ያስተላለፏቸው የስሕተት ትምህርቶችና በሌሎችም መምህራን የተላለፉ ነቀፋ ያለባቸው ትምህርቶች ካሉ የሊቃውንት ጉባኤ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ አንጻር በሚገባ መርምሮና አጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር በአጭር ጊዜ ውስጥ ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርብ፣ 4. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኝ ብዙኃን ስርጭት ድርጅት ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር ሚዲያ የአየር ሰዓት የሰጠበትን ዝርዝር ሁኔታና ከማኅበሩ ጋር በተያያዘ አየር ላይ ያዋላቸውን ትምህርቶች የሚያሳይ ሪፖርት እንዲያቀርብ ይደረግ በማለት ቋሚ ሲኖዶስ ወስኖ የዕለቱን ጉባኤ በቅዱስነታቸው ጸሎተ ቡራኬ አጠናቋል። ምንጭ:- የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን  https://finotebirhan.com

የማኅበራት ምዝገባና ቁጥጥር መምሪያ ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበርን ለጊዜው አገደ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የማኅበራት ምዝገባና ቁጥጥር መምሪያ ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር ሰጥቶት የነበረውን ፍቃድ ለጊዜው አግዷል።መምሪያው እገዳውን የጣለው ቋሚ ሲኖዶስ በማኅበሩ ሚዲያ የተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ነው። መምሪያው ያስተላለፈው ጊዚያዊ እግድ እንደሚከተለው ይነበባል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ሚያዝያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኀበር ፍኖተ ጽድቅ በተስኘው ሚዲያው በተለያዩ ጊዜያት ከቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ውጪ ያስተላለፈው ትምህርት የቤተ ክርስቲያኒቱን አባቶች፣ ሊቃውንቱንና መላው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያሳዘነ በመሆኑ ችግሩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥበት ድረስ በማኅበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ በኩል  ታግዶ እንዲቆይ በማለት ወስኗል። ስለሆነም የማኀበራት ምዝገባ፣ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ ከቅዱስ ሲኖዶስ በተሰጠው ስልጣን መሠረት ለማኀበሩ ሕግን ጠብቆና ተከትሎ ፈቃድ ሲሰጥ ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያኒቱን ዶግማ (እምነት)፤ ቀኖናና ትውፊት ጠብቆ እንዲሰራ መሆኑ እየታወቀ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ ውጪ በሚዲያው ላስተላለፈው የስህተት ትምህርት ማብራሪያ እንዲሰጥ በተጻፈው ደብዳቤ መሠረት ማብራርያና ምላሽ የሰጠበት ቢሆንም በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት ችግሩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስከሚሰጥበት ድረስ የፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኀበር በቤተ ክርስቲያናችን ስም ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርግ የታገደ መሆኑን እየገለጽን የቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ ተግባራዊ እንዲደረግ በጥብቅ እናሳውቃለን ።በማለት እገዳውን አስተላልፏል። ምንጭ :- የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን  https://finotebirhan.com

የማኅበራት ምዝገባና ቁጥጥር መምሪያ ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበርን ለጊዜው አገደ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የማኅበራት ምዝነባና ቁጥጥር መምሪያ ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር ሰጥቶት የነበረውን ፍቃድ ለጊዜው አግዷል።መምሪያው እገዳውን የጣለው ቋሚ ሲኖዶስ በማኅበሩ ሚዲያ የተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ነው። መምሪያው ያስተላለፈው ጊዚያዊ እግድ እንደሚከተለው ይነበባል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ሚያዝያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኀበር ፍኖተ ጽድቅ በተስኘው ሚዲያው በተለያዩ ጊዜያት ከቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ውጪ ያስተላለፈው ትምህርት የቤተ ክርስቲያኒቱን አባቶች፣ ሊቃውንቱንና መላው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያሳዘነ በመሆኑ ችግሩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥበት ድረስ በማኅበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ በኩል  ታግዶ እንዲቆይ በማለት ወስኗል። ስለሆነም የማኀበራት ምዝገባ፣ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ ከቅዱስ ሲኖዶስ በተሰጠው ስልጣን መሠረት ለማኀበሩ ሕግን ጠብቆና ተከትሎ ፈቃድ ሲሰጥ ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያኒቱን ዶግማ (እምነት)፤ ቀኖናና ትውፊት ጠብቆ እንዲሰራ መሆኑ እየታወቀ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ ውጪ በሚዲያው ላስተላለፈው የስህተት ትምህርት ማብራሪያ እንዲሰጥ በተጻፈው ደብዳቤ መሠረት ማብራርያና ምላሽ የሰጠበት ቢሆንም በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት ችግሩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስከሚሰጥበት ድረስ የፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኀበር በቤተ ክርስቲያናችን ስም ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርግ የታገደ መሆኑን እየገለጽን የቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ ተግባራዊ እንዲደረግ በጥብቅ እናሳውቃለን ።በማለት እገዳውን አስተላልፏል። ምንጭ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን  https://finotebirhan.com

የማኅበራት ምዝገባና ቁጥጥር መምሪያ ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበርን ለጊዜው አገደ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የማኅበራት ምዝነባና ቁጥጥር መምሪያ ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር ሰጥቶት የነበረውን ፍቃድ ለጊዜው አግዷል።መምሪያው እገዳውን የጣለው ቋሚ ሲኖዶስ በማኅበሩ ሚዲያ የተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ነው። መምሪያው ያስተላለፈው ጊዚያዊ እግድ እንደሚከተለው ይነበባል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ሚያዝያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኀበር ፍኖተ ጽድቅ በተስኘው ሚዲያው በተለያዩ ጊዜያት ከቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ውጪ ያስተላለፈው ትምህርት የቤተ ክርስቲያኒቱን አባቶች፣ ሊቃውንቱንና መላው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያሳዘነ በመሆኑ ችግሩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥበት ድረስ በማኅበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ በኩል  ታግዶ እንዲቆይ በማለት ወስኗል። ስለሆነም የማኀበራት ምዝገባ፣ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ ከቅዱስ ሲኖዶስ በተሰጠው ስልጣን መሠረት ለማኀበሩ ሕግን ጠብቆና ተከትሎ ፈቃድ ሲሰጥ ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያኒቱን ዶግማ (እምነት)፤ ቀኖናና ትውፊት ጠብቆ እንዲሰራ መሆኑ እየታወቀ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ ውጪ በሚዲያው ላስተላለፈው የስህተት ትምህርት ማብራሪያ እንዲሰጥ በተጻፈው ደብዳቤ መሠረት ማብራርያና ምላሽ የሰጠበት ቢሆንም በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት ችግሩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስከሚሰጥበት ድረስ የፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኀበር በቤተ ክርስቲያናችን ስም ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርግ የታገደ መሆኑን እየገለጽን የቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ ተግባራዊ እንዲደረግ በጥብቅ እናሳውቃለን ።በማለት እገዳውን አስተላልፏል። ምንጭ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን  https://finotebirhan.com

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ወርኃዊ የባለትዳር አባላት ጉባኤ ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ የፊታችን እሑድ ከረፋዱ 5:30 ጀምሮ መርሐ ግብራችን የሚከናወን በመሆኑ ተገኝ
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን            ወርኃዊ የባለትዳር አባላት ጉባኤ             ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ የፊታችን እሑድ ከረፋዱ 5:30 ጀምሮ መርሐ ግብራችን የሚከናወን በመሆኑ ተገኝታችሁ የጉባኤው ተሳታፊ እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን። ጉባኤው:- እሑድ ሚያዝያ 26/2017 ዓ.ም                  ከ5:30- 7:00 መደበኛ ጉባኤኤያችንም በወር አንድ ቀን ብቻ የሚከናወን በመሆኑ ባለመቅረት ተገኝተው ነፍስዎን በቃለ እግዚአብሔር  ያረስርሱ።               የባለትዳር ጉባኤ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን  https://finotebirhan.com

ሕጸጽ የሌለበት ትምህርት ለትውልዱ ለማስተላለፍ አርትዖት ላይ ትኩረት በመስጠት መሥራት እንደሚገባ ተገለጸ! ዝክረ ኒቅያ በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ በሚገኘው ዓለም አቀፍ የሊቃውንት ጉባኤ በትናትናው ዕለት ሚያዚያ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ በመካሄድ ላይ ሲሆን በዛሬ ውሎው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ በርካታ ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው የቡድን ውይይት ተካሂዶባቸዋል። መምህር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል አርትዖትን አስመልክቶ ባቀረቡት ጥናታዊ ጽሑፍ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕፀፅ የሌለበት ትምህርቷን ለትውልዱ ለማስተላለፍ አርትዖት ላይ ትኩረት በመስጠት መሥራት እንደሚገባት ገልጸዋል። ንቡረ ዕድ ኤልያስ አብርሃ በበኩላቸው በማእከላዊና ማእከላዊ አሠራር ላይ በተመለከተ ባቀረቡበት ጽሑፍ እንደገለጹት ማዕከላዊ አሠራርን በመከተል  የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ ማሳካት እንደሚገባ አሳስበው በጥናቱም ሌሎች በርካታ ጉዳዮችን አንሥተዋል። በተያያዘም በተለያዩ ዘርፎች ላይ የጉባኤ ቤቶችን ወደ ፊት ለማራመድ እንዲሁም ደቀ መዛሙርቱን ተወዳዳሪ ለማድረግ እና የትምህርት ጥራቱንም ለማሻሻል እንደሚረዳ በጥናት ተመላክቷል። ©ማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ይኽ ማኅበር ከኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተህምሮ ውጪ ስሑት ትምህርት የሚሰጥበት ተቋም እንደሆነ  በተጨባጭ እየታወቀ እና በአካል ቀርበው  አረጋግጠው  እንኳን ቅዱስ ፓትርያርኩን በዚያ ሥፍራ እንዲገኙ በማድረግ  ቤተ ክርስቲያንን አሳልፈው የሰጡ  የቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች መኖራቸው የአደባባይ ሐቅ ነው፡፡ በመሆኑም ከዚህ በታች የዘረዘርናቸው ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ተገቢው ትኩረት እንደሚሰጣቸው እና የእርምት እርምጃ እንደሚወሰድባቸው  እናምናለን።  1. የሊቀ ጳጳሱ ኢ-ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ በቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖናዊ እርምጃ እንደሚወሰድበት ብናምንም በሚገባ እና በትኩረት ጉዳዩ እንዲታይና መፍትሔ እንዲሰጠው፡፡ እንዲሁም በተመሳሳይም ስሑት ትምህርቶችን የሚያስተምሩ እና ያስተማሩ ሌሎች ጳጳሳት እና መምህራን  ጉዳይም አብሮ እንዲታይ፣ ይኽን አጋጣሚ ተጠቅሞ የሊቃውንት ጉባኤም በስሑት አስተምህሮዎች ላይ ተገቢውን ምላሽ እንዲሰጥ ቢደረግ፡፡ 2. ሓላፊነቱን በአግባቡ ያልተወጣው የማኅበራት ምዝገባና ክትትል እና ቁጥጥር መምሪያ ከሊቀ ጳጳሱ ጀምሮ በየደረጃው ያሉ ሓላፊዎች  እንዲጠየቁ፡፡ 3. የማኅበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ የዕውቅና ሰርተፊኬት ከመቸርቸር ወጥቶ፣ ደንቡና አሠራሩን ዳግመኛ በመፈተሽ፣ የዕውቅና አመዘጋገብ፣ ክትትልና ቁጥጥር ሒደቱም ንጥር ያለ እና መስፈርቶች የወጡለት እንዲሆን፡፡ 4. ቅዱስ ፓትርያርኩን በማሳሳት " ፍኖተ ጽድቅ " በተባለው ማኅበር ዝግጅት ላይ እንዲገኙ ያደረጉ የቅዱስ ፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት ሓላፊና የፖትርያርኩ የፕሮቶኰል ሹም እንዲጠየቁ፡፡ 5. ‹‹ፍኖተ ጽድቅ›› የተሰኘው ማኅበር በቤተክርስቲያን ላይ እያደረሰ ያለውን የተሐድሶ ኑፋቄ ትምህርት ባለማረሙ ምክንያት ማኅበሩ የምዝገባ ፈቃዱ ተሰርዞ ባስተላለፈው ትምህርቶች በቀኖና እንዲጠየቅ እና በዚሁ አጋጣሚ ከመምህራን እስከ ሊቃነ ጳጳሳት “ፍኖተ ጽድቅ” ከተባለ ማኅበር ጋር የጀመሩት በነዋይ ላይ የተመሠረተ ግንኙነት በአስቸኳይ እንዲቆም እንዲደረግ። እንዲሁም በቤተ ክህነቱ የበላይ ሓላፊዎች በኩል  እናት ቤተ ክርስቲያናችን አንዳች ሳይጎድልባት ባልተገባ መሻት ከባለ ጸጋ እጅ ለማኝ በማድረግ ቅድስት ቤተክርስቲያንን የማዋረድ እና አሳልፎ የመስጠት  እኩይ ተግባር እንዲቆም። 6. የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ኦርቶዶክሳዊት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ አገልግሎቷን እንዳታሰፋ እጅ ተወርች ቀፍድዶ የያዛት ደካማ፣ ብልሹ አስተዳደር እንዲስተካከል በልጅነት መንፈስ በተደጋጋሚ የችግሮቹን ማሳያና መፍትሔዎቹን፣ ሥርዓተ መዋቅርን  በመጠበቅ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ  ጉባኤ ድረስ ቢያቀርብም ተጨበጭ ምላሽ አልተሰጠውም ። ይህም ጉዳይ ከግንዛቤ ገብቶ አፋጣኝ መፍትሔ ሊሰጠው ይገባል። ነገር ግን አሁንም እንደ ቀድሞው ተሸፋፍኖ የሚታለፍ  እና መፍትሔ ከመስጠት ይልቅ ታላቋን ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስትያን  የማይመጥነው ብልሹ አስተዳደር የሚቀጥል ከሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚገኙ ሊቃውንት፣ ምእመናን፣ እና የሰንበት ት/ቤት አባላት ጋር በመሆን የምንረከባትን እና ለትውልድ የምናሰረክባትን እናት ቤተ ክርስቲያን የምንታደግበትን መንገድ የምንከተል መሆኑን በዚሁ አጋጣሚ ለመግለፅ እንወዳለን። የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሚያዚያ ፳፩ቀን ፳፻፲ወ፯ ዓ.ም አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

በማ/ስ/ቅ/ ልደታ ለማርያምና ደ/መ/መድኃኔዓለም አብያተክርስቲያናት የተክለ ሳዊሮስ ሰንበት ትምህርት ቤት: ወቅታዊ መልእክት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ (ሀገር አቀፍ) የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከውጪና ከውስጥ የሚቃጡባትን ፈተናዎች በመቋቋም ከውጭ የሚቃጡባትን ፈተናዎች ሰማዕትነትን በሚቀበሉ ልጆቿ ምስክርነት፣ ምንፍቅናን በቃል የመጣውን በቃል በመጻሕፍት የመጣውን በመጻሕፍት በመመከት ሐዋርያዊ ቅብሎሿን ጠብቃ መሠረተ እምነቷን፣ ዶግማና ቀኖናዋን ቅዱስ ትውፊቷን ለትውልዱ እያስተማረች ጸንታ ቆይታለች፤ ወደ ፊትም ትኖራለች፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ዛሬ በልዩ ልዩ ውጫዊ ፈተናዎች ዋጋ እየከፈለች ያለች ቢሆንም ከሁሉ የከፋው ግን ከክብር በላይ የላቀ ክብር ባጎናጸፈቻቸውና እረኛና ጠባቂ እንዲሆኑ ባሰማራቻቸው ልጆቿ በተደጋጋሚ እየገጠማት ያለው የቀኖና ጥሰት ነው። የጥር ፲፬ ጳጳሳት ሹመት፣ የትግራይ ሲኖዶስ፣ የቅባት ጳጳሳት ሹመት ፤ ፖለቲካን ተጠግቶ ቤተክርስቲያንን የማጥቃት ክፉ ግብር ሳያንሳት ፤በተገኘው አጋጣሚ ኹሉ የምንፍቅና ትምህርቶች የሚያስተላፉትን  በዝምታ መመልከት እየበዛና በዚህም በጎቿን ከበረቷ ለማስነጠቅ ለሚሠሩ ሁሉ ተባባሪ በመሆን የሚኬድበት ርቀት ቤተክርስቲያኒቱን ዋጋ እያስከፈለ በመሆኑ በቃ ሊባል ይገባዋል፡፡ ለማሳያ ይሆን ዘንድ በአቡነ በርናባስ መባልእትንና ነገረ ክርስቶስን አስመልክቶ፤ በአቡነ ፊልጶስ እመቤታችንና ሥላሴን አስመልክቶ የተናገሩትን የስሕተት ትምህርቶች ቅዱስ ሲኖዶስም ሆነ የሊቃውንት ጉባኤ በወቅቱ ማስጠንቀቂያም ሆነ የእርምት እርምጃ ባለመውሰዳቸው ዛሬ በአቡነ ገብርኤል እመቤታችንንና ነገረ ክርስቶስን አስመልክቶ ያውም በዐውደ ምሕረት፣ እንዲሁም በዕለተ ስቅለት በተደረገ የአዳራሽ ጉባኤ ለተናገሩት የኑፋቄ  ትምህርት አድርሶናል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ቤተ ክርስቲያን ገፊ እንደሆነች እና ስለክርስቶስ የሚዘምሩትን እንደምታባርር እርሷም ስለ ክርስቶስ እንደማትዘምር በአደባባይ በጉባኤ ያለምንም ፍርሀት ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ የማኅበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያን ጨምሮ የተለያዩ ሊቃነ ጳጳሳት በኑፋቄ ትምህርት ማስፋፋት ላይ የተሰማራውን “ፍኖተ ጽድቅ” ማኅበርን በገንዘቡ በሚሠራቸው የስቱዲዮ ግንባታ፣ የመጽሐፍ ኅትመት እና የመሳሰሉት ተግባራት በመማረክ የቤተክርስቲያንን ክብር አሳልፈው ሰጥተዋል፡፡ በዚህ ሂደት ላይ አንዳንድ መምህራን እና ማኅበራትም ተሳታፊ መሆናቸው በእጅጉ አሳዛኝ ነው፡፡ ይህ እንዲሆን ምክንያት ከሆኑ ነገሮች መካከል የሚከተሉት በዋናነት ተጠቃሽ ናቸው። 1. የአስተዳደር ብልሹነት የወለደው  ዘርፈ ብዙ ችግር በእኛ መረዳት አሁናዊው ፈተና እና ችግር ከውጪያዊው የዝግጅት ጥቃትና ፈተናም በላይ የበረታው የውስጥ ችግር ነው። ለዚህም ዋናውና አንደኛው የሁለንተናዊ ድካማችን ምክንያት የቤተ ክህነቱ ብልሹ አስተዳደር  ነው። አሁን ላይ ያለው የቤተ ክህነት  አስተዳደር ዘመኑን በመዋጀት  የቤተ ክርስቲያንን መንፈሳዊ ተልዕኮ  በማስፈፀም  ነፍሳትን ለመንግሥተ እግዚአብሔር ለማብቃት  የሚያስችል  ቁመና እና ብቃት ላይ አይገኝም ።  ሕግ አውጪ፣ ሕግ ፈፃሚ እና ሕግ ተርጓሚ አንድ አካል በመሆን፣ ተጠቅልሎ በተያዘ ሥልጣን ቤተ ክርስቲያኒቱ እጅ ተወርች ተቀፍድዳ  ወደ ትውልዱ እንዳትደርስ እየተሠራ ይመስላል። ቤተ ክርስቲያን በማይመጥናት ደካማ አስተዳደር ምክንያት ከተመሠረተችበት ነፍስ የማዳን መንፈሳዊ ተግባር ተናጥባለች። አስተዳደሩ ምእመናንን ለመንፈሳዊ ፍሬ ከማብቃት ይልቅ   ለውድቀታቸው ምክንያት ሆኗል። በተለያዩ ጊዜያት ተጠንተው የቀረቡ ልዩ ልዩ የአስተዳደር ማሻሻያዎች እየተኮላሹ ጉዞው ከድጡ ወደ ማጡ ሆኗል:: በ ፳፻ወ፬ ዓ.ም ለሲኖዶስ የቀረበው የመሪ ዕቅድ ትግበራ ጥያቄ ፲፫ ዓመታት ሲገፋ ቆይቶ አሁንም ቦታ ተነፍጐታል። አስተዳደራዊ ለውጥ ጠልነቱ ተባብሶ ቀጥሏል። እኔ ብቻ በሚሉ ፣ ቤተ ክርስቲያን እንደ ግል ተቋማቸው በሚያዩ አካላት ተወራለች:: በሃይማኖት ችግር ፣ በቀኖና ጥሰት እና በሙስና ተጠያቂ መሆን የሚገባቸው አካላት የተሻለ ሹመትና ሽልማት ይሰጣቸዋል፡፡ 2. ለሊቃውንት ጉባኤ ትኩረት መነፈጉ የሊቃውንት ጉባኤ ተገቢው ትኩረት ሳይሰጠው በመቅረቱ ፣ እንዲሁም ሊቃውንት ክብራቸው ባለመጠበቁ እና ከውሳኔ ሰጪነት ድርሻ በመገለላቸው ፤ ለስሑት ትምህርት በሚገባው መልኩ ምላሽ መስጠት የማይችል ሆኗል:: እንዲሁም በቤተክርስቲያኒቱ ስም ለሚታተሙና ለሚሰራጩ መጻሕፍትና ልዩ ልዩ የምስልና የድምፅ እንዲሁም የኅትመት ውጤቶች የመገምገምና ዕውቅና የመስጠት ሥልጣኑ ተነጥቋል። የአደረጃጀትና የመከላከል አቅሙ   በመዳከሙ፤ በመዋቅሩ ውስጥ የተሰገሰጉ  ሐሰተኛ መምህራን በአፍም በመጽሐፍም  ስሁት ትምህርታቸውን  በቤተ ክርስቲያኒቱ ዐውደ ምሕረት እያሰራጩ ይገኛሉ። ትናንት አባቶች ያቆዩትን ሀብት መንዝሮ መጠቀም እንጂ የራሳቸውን አሻራ የማያኖሩ፣ ሀብት ንብረቷን ጠብቀው ከማቆየት ይልቅ ለግል መዝብረው ቀሪውን ለዘራፊ አሳልፈው የሰጡ ከመንፈሳዊ ክብር በጐደሉ፣ በሥጋ ሐሳብ ጨርሶውኑ በተወሰዱ፣ ምግባር በጎደላቸው ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ ሊቃነ ጳጳሳት ድረስ ባሉ አገልጋዮች እየተፈተነች ትገኛለች። ያለ ዋጋ ከሚሰጠው መንፈሳዊ ሹመት ጀምሮ የቤተ ክርስቲያንን መንፈሳዊ አገልግሎት የሚጎዳ  እኩይ ተግባር በእጅ መንሻ የሚፈጽሙ አካላት በሁሉም መዋቅር ውስጥ ተሰግስገው ቤተ ክርስቲያን የተመሠረተችበትን  ዓላማ እንዳታሳካ ሳንካ ሆነውባታል። ስንዱዋ እመቤት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሕግ እና በሥርዓት ዝግጅቷ እንከን አይወጣላትም። ነገር ግን ከሕግና ከሥርዓት ባፈነገጡ፣ ሐሰተኛ ትምህርት በሚያሰራጩ እና ኢ-ክርስቲያናዊ በሆነ ሕይወት ወስጥ በሚመላለሱ በተለይ በሁሉም መዋቅር ወስጥ በሚገኙ አገልጋይ ሠራተኞች ላይ ተግባራዊ ርምጃ አለመወሰዱ ለምእመናን ተስፋ መቁረጥ እና ፍልሰት ምክንያት ሆኗል ። 3. በሕግ ከተሰጣቸው መብት ውጪ በማስተማር የሚሰማሩ ማኅበራትን በሕግ አግባብ ወደ መስመር አለማስገባት የሰሞኑ ስሁት ትምህርት በሕጋዊ ዕውቅና ስም የሚንቀሳቀሱ ማኅበራት እኩይ ተግባር ከትናንት የቀጠለ የብልሹ አስተዳደር መገለጫ ነው። የማኅበራት አስተዳደር ደንብ ፀድቆ ሥራ ላይ ከመዋሉ በፊት ደንቡ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በማስረጃ በማስደገፍ የማሻሻያ ሐሳብ  ብናቀርብም ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል። በመሆኑም የፈራነው ደርሶ ፤ ደንቡን ለማስፈፀም የተቀመጠው የማኅበራት ምዝገባ ክትትል እና ቁጥጥር  መምሪያ፤ በማኅበራት አስተዳደር ደንብ አንቀጽ ፲ ላይ የማኅበራት ዓለማ "ለትምህርት ተጠሪ ተቋማት ድጋፍ መስጠት ነው" በሚል የተደነገገ ቢሆንም  እንደ ‹‹ፍኖተ ጽድቅ›› ያለ ማኅበር ድጋፍ ሰጪ ሳይሆን ፈፃሚ ሆኖ፣ ማኅበሩ ከተመሠረተበት ዓላማ ውጭ ትምህርተ ወንጌልን በአዳራሽ ውስጥ  ሲሰጥ፤ በሚዲያ ትምህርት ሲያስተላልፍ አልፎ ተርፎ የቤተ ክርስቲያን መዝሙሮቿን ከሥርዓቷና ከቀኖናዋ ውጪ በሆነ ሁኔታ በሚዲያ እያቀናበረ ሲያስተላልፍ ተገቢው አስተዳደራዊም ሆነ ቀኖናዊ  እርምጃ እንዲወሰድ ከማድረግ ይልቅ በማኅበርነት በመመዝገብ እንዲሁም በደንቡ የተሰጠውን የመቆጣጠር ሓላፊነት የማኅበራት ማደራጃ ምዝገባ ክትትል እና ቁጥጥር መምሪያ ባለመወጣቱ ዛሬ ለደረሰው ስሑት ትምህርት ዝግጅትና ስርጭት አብቅቶናል፡፡