ru
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Открыть в Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Больше
2 631
Подписчики
+624 часа
+267 дней
+4830 день
Архив постов
የተወደዳችሁ የሰንበት ት/ቤታችን አባላት በሙሉ የፊታችን እሑድ ኅዳር 08/2017ዓ.ም የደብራችንን ቤተመቅደስ ስለምናጸዳ ሥርዓተ ቅዳሴው ከተጠናቀቀ በኋላ መገኘት የምትችሉ ለጽዳት የሚያገለግሉ እቃዎችን በመያዝ እንድትመጡና እንድናጸዳ በትህትና እንጠይቃለን። መጥረጊያ ፣መወልወያ የምንጣፍ ማጽጃዎች.... ያላችሁን ይዛችሁ እንድትመጡ ይሁን🙏 ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የሐዘን መግለጫ የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነችው የእህታችን ሰነይት ለማ ወላጅ እናት ስላረፉ ስርዓተ ቀብራቸው ነገ 9:00 ቀብር ደብረ አሚን ተክለሃይማኖት ስለሚፈጸም የምትችሉ አባላት ቀብሩ ላይ እንድንገኝ ይሁን እንዲሁም መኖሪያ ቤታቸው 43 ጅምናዜም ጎን በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን ።የእናታችንን ነፍስ ይማርልን ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችንhttps://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችንhttps://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ቅዳሜ ጥቅምት 9/2017 ዓ.ም ኦርቶዶክሳዊ የንባብ ሕይወት ትምህርት መሰጠቱ የሚታወቅ ነው። ስለዚህም ከላይ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በቀን አንድ ምዕራፍ ያንብቡ መልካም
ቅዳሜ ጥቅምት 9/2017 ዓ.ም ኦርቶዶክሳዊ የንባብ ሕይወት ትምህርት መሰጠቱ የሚታወቅ ነው። ስለዚህም ከላይ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በቀን አንድ ምዕራፍ ያንብቡ መልካም የንባብ ጊዜ እንዳሳለፉ እናምናለን አራተኛ ሳምንት የማቴዎስ ወንጌል እና የመጨረሻ ክፍል ነው በዚህ መሠረት ከዚህ ንባብ በኋላ የማቴዎስ ወንጌልን ጨረሰን ማለት ነው መልካም የንባብ ጊዜ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️ "ናሁ ተፈጸመ ማኅሌተ ጽጌ ፤ እነሆ የተወደደ ማኅሌተ ጽጌ ተፈጸመ።" ኅብረ ሐመልሚል ቀይሕ ወፀዓድዒድ አርአያ ኰሰኰስ ዘብሩር፤ ተአምርኪ ንጹሕ በአምሳለ ወርቅ ግቡር፤ ተፈጸመ ናሁ ማኅሌተ ጽጌ ሥሙር፤ አስምኪ ቦቱ ንግሥተ ሰማያት ወምድር፤ ከመ በሕጽንኪ ያሰምክ ፍቁር🌹🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️ ናሁ ተፈፀመ ማኅሌተ ፅጌ ስሙር አስምኪ ቦቱ ንግስተ ሰማያት ወምድር ከመ በህፅንኪ ያሰምክ ፍቁር። ንግስተ ሠማያት ወምድር ማርያም ድንግል { ፪ } ተፈፀመ { ፬ } ማኅሌተ ፅጌ      🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷ በሁላችንም ላይ ይደር። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ኦርቶዶክሳዊ የንባብ ሕይወት እንዲኖረን ትምህርት መሰጠቱ የሚታወቅ ነው። ስለዚህም ከላይ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የማቴዎስ ወንጌልን በቀን አንድ ምዕራፍ ያንብቡ መልካም
ኦርቶዶክሳዊ የንባብ ሕይወት እንዲኖረን ትምህርት መሰጠቱ የሚታወቅ ነው። ስለዚህም ከላይ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የማቴዎስ ወንጌልን በቀን አንድ ምዕራፍ ያንብቡ መልካም የንባብ ጊዜ እንዳሳለፉ እናምናለን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

     የተከበራችሁ የሰንበት ት/ት ቤታችን አባላት እንደ እግዚአብሔር አምላክ ቅዱስ ፈቃድ አገልግሎታችንን የምናስኬድበት ለአገልግሎቱ መስፋፋት ጉልህ አስተዋጽኦ የምናደርግበት የወርኃዊ መዋጮ ቀን ደረሰ!!!     ከጥቅምት 24 እስከ ጥቅምት 30 በመክፈል አገልግሎታችንን እናሳድግ መንፈሳዊ የአባልነታችን ግዴታ እንወጣ!!      በአካውንት የምናስገባ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000555650594 (ወርኃዊ አስተዋጽኦ) በማለት እናስገባ            አምላከ ቅዱስ ሚካኤል ማኀበራችንን ይባርክ                                     የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት ልማት ክፍል ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ልዩ የባለትዳር አባላት ጉባኤ ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ማኀበራዊ ሚዲያ እና ቤተሰብ በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ይህ ጉባኤ ለሶስት ተከታታይ
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን            ልዩ  የባለትዳር አባላት ጉባኤ             ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ማኀበራዊ ሚዲያ እና ቤተሰብ በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ይህ ጉባኤ ለሶስት ተከታታይ ጉባኤያችን የሚዘጋጅ በመሆኑ እንዳያመልጥዎት እንዳይቀሩ።    ጉባኤው:- እሑድ ጥቅምት 24/2017 ዓ.ም                  ከ5:30- 7:00 መደበኛ ጉባኤኤያችንም በወር አንድ ቀን ብቻ የሚከናወን በመሆኑ ባለመቅረት ተገኝተው ነፍስዎን በቃለ እግዚአብሔር  ያረስርሱ።               የባለትዳር ጉባኤ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን  https://finotebirhan.com

''የምስጋና ሕይወት'' እሑድ ጥቅምት 24/2017 ዓ/ም በመምህር ዲ/ን ዳንኤል ታደለ ኦርቶዶክሳዊ የሥነ አዕምሮ በሚል ለተከታታይ ሳምንት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና የፊታችን እሑድ የምስጋና ሕይወት በ
''የምስጋና ሕይወት'' እሑድ ጥቅምት 24/2017 ዓ/ም በመምህር ዲ/ን ዳንኤል ታደለ ኦርቶዶክሳዊ የሥነ አዕምሮ በሚል ለተከታታይ ሳምንት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና የፊታችን እሑድ የምስጋና ሕይወት በሚል ርዕስ ማጠቃለያ  ይሰጣል ስለዚህ እርስዎም በእለቱ ይገኙ እንዳይቀሩ እንዳያመልጥዎት። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የሐዘን መግለጫ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባል የሆነችው የእህታችን መውደድ አለሙ ወንድም ስላረፈ ስርዓተ ቀብሩ ዛሬ ጥቅምት 22/2017 ዓ.ም ተፈጽሟል ስለዚህ መኖሪያ ቤታቸው ሞላ ማሩ አካባቢ በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን።  የወንድማችንን ነፍስ ይማርልን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

በጣም አስቸኳይ የስራ ዕድል ማስታወቂያ ለሰ/ት/ቤታችን አባላት ብቻ ====================== -መሠረታዊ የኮምፒውተር ችሎታ ያለው/ያላት -የሚፈለገው የሰው ብዛት- 4 2 ወንድ 2 ሴት የሥራ ሁኔታው - ማተሚያ ቤት ውስጥ ደሞዝ:- በስምምነት ማሳሰቢያ:- የሰንበት ት/ት ቤታችን አባላት የሆናችሁና የስራ ዕድል ሲመጣልን እያለፈን በመሆኑ እንድናገናኝዎ የምትፈልጉ ወይም ይህ መረጃ የማይደርሳቸውና የሚያስፈልጋቸውን አባላት የምታውቁ ከታች በተቀመጡ ስልኮች በመደወል እንዲያስመዘግቡ በትህትና እንጠይቃለን። 0912-41-97-72 ዮናስ ይርዳው 0913-00-60-86 መቅደስ ቀፀላ 0966-25-87-38 ዮሐንስ ትዳሩ            የበጎ አድራጎት ክፍል የቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com          

በሶሪያ ኦርቶዶክስ ያዕቆባዊት ቤተክርስቲያን የሕንድ ሜትሮፖሊታን የነበሩት ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ ከዚህ ዓለም ድካም ዐረፉ ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ እ.ኤ.አ ሐምሌ
በሶሪያ ኦርቶዶክስ  ያዕቆባዊት ቤተክርስቲያን የሕንድ ሜትሮፖሊታን የነበሩት ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ ከዚህ ዓለም ድካም ዐረፉ   ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ እ.ኤ.አ ሐምሌ 22 ቀን 1929 ዓ.ም ቡቸንክሩዝ በተባለ የሕንድ ግዛት የተወለዱ ሲሆን እ.ኤ.አ ከሐምሌ 26 ቀን 2002 ዓ.ም ጀምሮ በሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሥር የምትተዳደረውን የሕንድ ቤተ ክርስቲያን ለበርካታ ዓመታት በሊቀ ጵጵስና መርተዋል። ብፁዕነታቸው በዕድሜና በሕመም ምክንያት ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ዕረፍት በማድረግ ሕክምናቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን በዛሬው ዕለት አመሻሽ ላይ በሕንድ ኮቺ በተወለዱ በ95 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል። በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ሞር አግናጢዮስ ኤፍሬም ዳግማዊ፣ ለሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣ ለመላው የቤተ ክርስቲያን አባላት፣ ቀሳውስትና ምእመናን በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።  የብፁዕነታቸው በረከት አይለየን !!! © ተሚማ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡ በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ እንዲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 እስከ ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ መደበኛ ስብሰባውን ሲያካሂድ ሰንብቷል፡፡ ምልዓተ ጉባኤው ልዑል እግዚአብሔርን አጋዥና መሪ በማድረግ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት፣ ስለምጣኔ ሀብት እድገት፣ በሀገራችን እየተከሰቱ ስላሉት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች፣ ስለ ሀገር ሰላምና አንድነት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና ሐዋርያዊ ተልእኮ ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነት በስፋት በመወያየት ለቤተ ክርስቲያንና ለሀገር ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ በዚሁ መሠረት፡- 1. ከጥቅምት 4 ቀን እስከ ጥቅምት 9 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ የተካሄደው ዓለም አቀፍ ጉባኤ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ 43ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፍ ስብሰባ ተሳታፊዎች የቀረበው ቃለ ጉባኤና የአቋም መግለጫ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አህጉረ ስብከት የበጀት ዓመቱ የሥራ መመሪያ እንዲሆን ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡ 2. በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች እየተከሰተ ባለው የሰላም እጦት፣ የእርስ በርስ ግጭት ምክንያት የሰው ሕይወት እየተቀጠፈ፣ አካል እየጎደለ፣ ማኅበራዊ ትሥሥር እየተናደ፣ ሰብአዊ ክብር እየተጎዳ፣ መብት እየተጣሰ፣ በዜጎች ላይ ሥጋትና አለመረጋጋት እየበዛ ሀብትና ንብረት እየወደመ ስለሆነ ጉዳዩ አስቸኳይ መፍትሔ የሚያስፈልገው መሆኑ አጠያያቂ አይደለም፡፡ ስለሆነም በጦርነትና በግጭት የመጣ ሰላም፣ የተገነባ ሀገር የለምና በሀገራችን እያጋጠመ ያለውን ችግር ለመፍታት ካለፈው በመማር በጥበብ፣ በማስተዋልና በሰለጠነ አካሄድ በሰላማዊ መንገድ በመወያየት ችግሩ በእርቅ እንዲፈታ ለሁሉም ወገኖቻችን ቅዱስ ሲኖዶስ የሰላም ጥሪውን በአጽንኦት ያቀርባል፡፡ 3. በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትና በሥሩ ባሉ ገዳማትና አድባራት ውስጥ እየቀረቡ ያሉ መጠነ ሰፊ የአስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱ ለማድረግ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ጀምሮ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት፣ በክፍላተ ከተሞችና ችግር አለባቸው ተብለው በጥናት በሚለዩት አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ላይ የማጣራት ሥራ እንዲሠራና ውጤቱ ለውሳኔ እንዲቀርብ በሦስት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡ 4. የኦሲኤን ቴሌቪዥን ስርጭት የተቋረጠ በመሆነ በአዲስ መልክ ሁሉንም የአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ተናጋሪዎች ማህበረሰብ ባቀፈ መልኩ አገልግሎት እንዲሰጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአፋን ኦሮሞ ኔትወርክ በሚል ስያሜ በጠቅላይ ቤተ ክህነት በኩል ውል ተፈርሞ በአዲስ መልክ የሳተላይት ግዥ እንዲፈጸም ሆኖ አስተዳደሩን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን ድርጅት ጋር በአንድ ሊቀ ጳጳስና ቦርድ ራሱን በቻለ ሥራ አስኪያጅ እየተመራ አገልግሎቱ ከነበረው በተሻለ ሁኔታ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 5. የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለደቀ መዛሙርት የሚሰጠው የምስክር ወረቀት አድቫንስ ዲፕሎማና ዲግሪ እንዲሆን ሥርዓተ ትምህርቱ ለሚሰጠው የትምህርት ማስረጃ በሚመጥን መልኩ ተሟልቶ፣ ሊኖረው የሚገባው የሰው ኃይል በየዘርፉ ተጠናክሮ ወደ ትግበራ እንዲገባ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፣ 6. የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በሥነ ሕንጻና በኪነ ጥበብ በዓለም ደረጃ ከፍተኛ አድናቆትና ክብር የሚሰጠው ከመሆኑ በተጨማሪ በመዐርገ ጵጵስና ፕትርክና የሚሾሙ አባቶች ሥርዓተ ሲመት የሚፈጸምበት፣ ጥንታዊና ታሪካዊ ካቴድራል መሆኑን ታሳቢ በማድረግ ለዕድሳት ሥራው የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግለት ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤ በተጨማሪም ምእመናን እስከ አሁን እንደሚያደርጉት ሁሉ ለእድሳት ሥራው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳስባል፡፡ 7. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዐቢይ ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥልና በንቃት እንዲሳተፍ ሁሉንም አህጉረ ስብከት ባቀፈ ሁኔታ የአጀንዳ መረጣና ተሳታፊ የመለየት ሥራ እንዲከናወን ሆኖ ዐቢይ ኮሚቴው የሥራ ዕቅዱንና አፈጻጸሙን ለቋሚ ሲኖዶስ እያቀረበ በማስወሰን እንዲሠራ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ በአጠቃላይ ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ እየተመራ ላለፉት ተከታታይ ቀናት በመንፈሳዊ፣ በማኀበራዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ተገቢውን ውሳኔ በማስተላለፍ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት በጸሎት አጠናቅቋል፡፡ መሐሪና ሁሉን ቻይ የሆነ እግዚአብሔር አምላካችን ለሀገራችን፣ ለሕዝባችን፣ ለዓለሙ ሁሉ ሰላሙን፣ ፍቅሩንና አንድነቱን ይስጥልን፡፡ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን። አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ጥቅምት ፳፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም. ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ©Eotc የቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

''ኦርቶዶክሳዊ ራስን መግዛት'' የቅዳሜ መርሐግብር ቅዳሜ ጥቅምት 23/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ። የቴሌግራ
''ኦርቶዶክሳዊ ራስን መግዛት'' የቅዳሜ መርሐግብር  ቅዳሜ ጥቅምት 23/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ  ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ። የቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ለ10 ቀናት በዝግ ሲካሔድ የቆየው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ  ዛሬ ከሰዓት በሚሰጠው መግለጫ እንደሚጠናቀቅ ተገለጸ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት  የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ በጥቅምት 12 እና በግንቦት ርክበ ካህናት (የትንሣኤ 25ኛ ቀን) ይካሔዳል። በዚህ ዓመት የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ከጥቅምት 12/2017 ዓ/ም ጀምሮ ለተከታታይ 10 ቀናት ሲካሔድ የቆየ ሲሆን ዛሬ ከሰዓት በተሰጠው የጉባኤ መግለጫ ተጠናቋል  ። የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መግለጫን ቀጥለን እናቀርባለን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ለ10 ቀናት በዝግ ሲካሔድ የቆየው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ  ዛሬ ከሰዓት በሚሰጠው መግለጫ እንደሚጠናቀቅ ተገለጸ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት  የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ በጥቅምት 12 እና በግንቦት ርክበ ካህናት (የትንሣኤ 25ኛ ቀን) ይካሔዳል። በዚህ ዓመት የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ከጥቅምት 12/2017 ዓ/ም ጀምሮ ለተከታታይ 10 ቀናት ሲካሔድ የቆየ ሲሆን ዛሬ ከሰዓት በተሰጠው የጉባኤ መግለጫ ተጠናቋል  ። የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መግለጫን ቀጥለን እናቀርባለን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ኦርቶዶክሳዊ የንባብ ሕይወት እንዲኖረን ትምህርት መሰጠቱ የሚታወቅ ነው። ስለዚህም ከላይ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ከማቴዎስ ወንጌል በቀን አንድ ምዕራፍ ከምዕራፍ 8-14
ኦርቶዶክሳዊ የንባብ ሕይወት እንዲኖረን ትምህርት መሰጠቱ የሚታወቅ ነው። ስለዚህም ከላይ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ከማቴዎስ ወንጌል በቀን አንድ  ምዕራፍ ከምዕራፍ 8-14 በዚህ ሳምንት ያንብቡ መልካም የንባብ ጊዜ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com