Amharic Spritual Books
Открыть в Telegram
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ መፅሐፍት ፣ መፅሐፍ ቅዱስን ለማጥናት የሚረዱ ... የመጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያዎች ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች እንዲሁም መንፈሳዊ ጹሑፎች ይቀርባሉ ። "Christlikeness is the goal of every true believer." @LovedandForgiven @Getu_Kebebe @mhbc74
Больше6 593
Подписчики
+424 часа
+317 дней
+12030 день
Архив постов
• Suffering in the Christian Life
በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ መከራ
📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌
📍መከራ የክርስቲያን ጉዞ አካል እንጂ የእግዚአብሔር መተው ምልክት አይደለም። እግዚአብሔር በመከራ ውስጥ እምነታችንን ያጠራዋል፣ ያጠነክረዋል፣ ውድነቱንም ይገልጣል። ወርቅ በእሳት እንደሚጠራ ሁሉ፣ እምነትም በፈተና ይጸናል።
📍በእግዚአብሔር ሀይል ጥበቃ መከለል ማለት መከራ አይገጥመንም ማለት አይደለም ።
አሁን በብዙ ዓይነት መከራ ብንፈተንም ስለተዘጋጀልን ሰማያዊ ርስት ስናስብ በእጅጉ እንደሰታለን ። እነዚህ መከራዎች እምነታችንን ለመፈተን ነው ።
በሰው እይታ ወርቅ በጣም የከበረ ነገር ነው ።
👉በእግዚአብሔር እይታ ደግሞ የሕዝቦቹ እምነት ከወርቅ የበለጠ የከበረ ነው ።
📍 ሰዎች ወርቃቸውን ከቆሻሻ ለማንጻት በእሳት ከፈተኑት እግዚአብሔርም የሕዝቦቹን እምነት እውነተኛነት ለመግለጥ እንዲሁም ለማጥራት እና ለማጠንከር በከባድ መከራ እንዴት አይፈትን !
📍አባት ልጆቹን ጥቅም አልባ ለቅሶ እንዲያለቅሱ አያደርግም። በመከራ ውስጥ አስፈላጊ የሆነው ነገር እምነታችንን ማሳደግ ነው ። 👉ይህ ማለት ግን እምነት እንዳለን ለማረጋገጥ ሳይሆን ያለንን የእምነታችንን ውድነት ለመግለጥ ነው።
📍ከመከራ በኋላ እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው ክብር እና ደስታ ይጠብቃቸዋል ።
📝 ስለዚህ መከራ የሚያልፍ የባሕር ሞገድ ነው፤ በእምነት እና በትዕግሥት ከቆምን በድል እንሻገረዋለን።
Repost from N/a
“ግን እኔ የምሄድበትን መንገድ ያውቃል፤ ከፈተነኝም በኋላ እንደ ወርቅ እወጣለሁ።”
— ኢዮብ 23፥10 (አዲሱ መ.ት)
“But He knows the way that I take (He has concern for it, appreciates, and pays attention to it). When He has tried me, I shall come forth as refined gold (pure and luminous).”
— Job 23፥10 (AMP)
ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ፣ ከእርሱ እውቅና ውጪ በሕይወታችን የሚሆን ምንም ነገር የለም።
ለምሳሌ አካባቢውን እና የመሬቱን አቀማመጥ የማያውቀው ስፍራ ዓይኖቹን በጨርቅ ታስሮ መንገድ እንዲሄድ የተደረገን ሰው ብናይ ከመጀመሪያው እርምጃው አንስቶ ቀጣዩን እስከሚዘረጋ ድረስ በብዙ ጭንቀት፣ የውድቀት ፍርሃት፣ ግራ መጋባት ውስጥ ነው የሚሆነው። ምክንያቱም ቀጣዩ እርምጃው ጉዞውን የሚያስቀጥለው ይሁን ወይንም ለውድቀት የሚያበቃው እንደሆነ አያውቅም ፤ ከፊቱ ለጥ ያለ ሜዳ፣ ተራራ፣ ሸለቆ፣ ገደል...ምን እንዳለ ለእርሱ ግልጽ አይደለም።
ከእግዚአብሔር ጋር ስንጓዝ የመንገዳችን እያንዳንዱ ዝርዝር በእኛ መታወቅ የለበትም። ምክንያቱም እኛ ሂደቱ ቢገባንም ባይገባንም ፣ መንገዱ ቀላል ወይም ከባድ ቢሆንም እግዚአብሔር የምንሄድበትን መንገድ ከማንም በላይ አጥርቶ ያውቀዋል።
መልካም እረኛ ፣ ሁሉን አዋቂ አምላክ እንዳለው ሰው ቀጣዩን እርምጃችንን በእርሱ ታምነን፣ ድፍረታችን ስለ መንገዳችን ያለን እውቀት ሳይሆን አምላካችን መሆኑ ገብቶን እንቀጥል።
ለወርቅ ያማረ፣ ውድ እና ተፈላጊ ሆኖ መውጣት ምክንያቱ ተፈትኖ ያለፈበት እሳት ነውና ከምንፈተንበት እሳት በላይ ስንወጣ ይዘን የምንወጣውን ማንነት እያሰብን እንታገስ።
✍️ መክሊት አየለ
📆 May 23, 2022
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
"ልጆቹ በሥጋና በደም እንደሚካፈሉ፣ እርሱ ራሱ ደግሞ ያንኑ ተካፈለ፤ ይኸውም በሞት ላይ ኀይል ያለውን ዲያብሎስን በሞቱ ኀይል እንዲደመስስ ነው፤ እንዲሁም በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ በሞት ፍርሀት ባርነት የታሰሩትን ነጻ እንዲያወጣ ነው።"
ዕብራውያን 2፥14-15
Repost from N/a
Ethiopia_Yosef_Alamrew_ልቤ_አንተን_አምኖ_ልቤ_new_worship_አስደናቂ_አምልኮ_2020.m4a7.99 MB
Repost from N/a
#Guide_the_Blind
በስልጠና (Training) ወቀት አሰልጣኞች የተሳታፊዎችን፣ የሰልጣኞችን ተሳትፎ ለመጨመር፣ ስልጠናውን አሳታፊ ለማድረግ፣ እንዲሁም ቁልፍ የሆኑ ነጥቦችን በማይራሳ መልኩ ለማስጨበት የተለያየ ጨዋታዎችን፣ አሳታፊ የቡድን ስራዎች (Activities) ይጠቀማሉ።
በአንድ ወቅት ታዳሚ ሆኜ በተገኘሁበት ስልጠና ላይ አሰልጣኙ የተጠቀመው #Guide_the_Blind (ማየት የተሳነውን ሰው መምራት) የተሰኘ የቡድን ስራ (group activity) ነበር። ጨዋታውን (ስራውን) ሁለት ሁለት ሆነን፣ የአንዱ ሰው አይን ምንም በማያሳይ ጨርቅ ታስሮ፣ አንዱ ሰው ደግሞ ልክ ማየት የተሳናቸውን ሰዎች በምንመራበት መንገድ የሚያየውን ሰው እጅ ይዞ በመምራት ነበር የሚተገበረው።
በአጋጣሚ እኔ አይናቸውን ከታሰሩት ሰዎች አንዷ ነበርኹ። በጊዜው ሥልጠናው ሲሰጥበት የነበረው አዳራሽ ደግሞ የሚገኘው ባለ ሶስት ወለል ሕንፃ ላይ፣ ሶስተኛው ወለል ላይ ነበር። ሕንጻው ሊፍት ስለሌለው መወጣጫችን ደረጃዎች ነበሩ።
ለጨዋታው አሰልጣኙ የሰጠው መመሪያ፦ ከላይ ከስልጠና አዳራሹ ጀምሮ መሪው አይኑ የታሰረውን ሰው እየመራ፣ ደረጃውን ሁሉ በጥንቃቄ ወርዶ፣ ስልጠናው የተዘጋጀበት ጊቢ የውጪው በር ጋር ደርሶ፣ ተመልሶ ደግሞ የሕንጻውን ደረጃዎች በመውጣት፣ ከሌሎች ቡድኖች ቀድሞ ወደ ስልጠናው አዳራሽ መድረስ ነው።
ለዚህ የቡድን ስራ መሳካት የሁለቱ ሰዎች መናበብ፣ መደማመጥ፣ የመሪው በሳል የመሪነት ክህሎት፣ የተመሪው ንቁ አድማጭነትና መሪውን መታመን ወሳኝ ነገሮች ናቸው። መሪው እግርህን ጣል ወዳለው አቅጣጫ ተመሪው እግሮቹን ይጥላል፣ አንሳ ወዳለው አቅጣጫ ደግሞ ያነሳል፤ እንዲህ እያሉ ደረጃውን በጋራ ይወርዳሉ፣ በጋራ ተመልሰው ይወጣሉ።
አሰልጣኙ በጨዋታው ውስጥ ማስተላለፍ የፈለገው መልዕክት ስለ አመራር፣ ንቁ አድማጭነት፣ ቡድን መመስረት (Leadership, Active listening, Team Building) ነው። ጨዋታው ጨዋታ ተብሎ በወቅቱ ቢያዝናናንም በውስጡ ቁልፍ መልዕክቶች ነበሩት። ጨዋታውን ጨርሰን ከተመለስን በኋላ በሂደቱ ወቅት ምን እንደተሰማን አሳባችንን፣ ስሜታችንን እንድናጋራ አሰልጣኙ ለተወሰኑ ሰዎች እድል ሰጠ፤ እድል የደረሳቸው ሰዎችም ከራሳቸው እይታ አንጻር የተሰማቸውን ገለጹ።
እኔ ግን ከስልጠናው ርዕስ ውጪ፣ አሰልጣኙ በጨዋታው ውስጥ ማስተላለፍ ከፈለገው መልዕክት ለየቀል የሆነ ነገር በውስጤ ተፈጠረ፣ ከእግዚአብሔር ጋር ስላለኝ ሕብረት፣ ስለ እምነት አንዳች ነገር እግዚአብሔር ሲናገረኝ፣ ያንን ምሳሌም ተጠቅሞ ሲያስተምረኝ ተሰማኝ፤ ደጋግሜ እያሰላሰልኹት ግን ለማንም ትንፍሽ አላልኹም፤ ወይ ጉድ! ብዬ መልዕክቴን ይዤ ቀኑ አለፈ።
ነገሩ እንዲህ ነው፦ እኔ አይኔ ታስሮ፣ አሰልጣኙ አደራ የሰጠው አንድ ሰው እጄን ይዞ ጉዞ ጀመርን። መሪዬ እንዳልወድቅ ከመፍራቱ የተነሳ እጆቼን ግጥም አድርጎ ይዟል፤ እንዳልፈራና በእርሱ ላይ እንድታመን ደጋግሞ አይዞሽ፣ እኔ አለሁ፣ ደርሰናል ይለኛል። እኔ ግን ከሚናገረኝ ከእርሱ ድምጽ ይልቅ የውስጤ ፍርሃት ጮኽ ብሎ ይሰማኝ ነበር። ከዛ ሕንጻ ላይ ስገለበጥ፣ ወድቄ ስሰበር ይታየኛል፣ ከአሁን አሁን ለቀቀኝ፣ ተጋጨሁ፣ እግሬ የማይሆን ቦታ ረገጠ፣ አደናቀፈኝ እያልኹ ራሴን ለመጠበቅ፣ ለራሴ ለመጠንቀቅ ብዙ ጣርኹ፣ በአጠቃላይ በመሪዬ ላይ ራሴን መጣልና በመሪነቱ መታመን አልቻልኹም፤ ከእርሱ ይልቅ እኔ ለራሴ የማስብ፣ የምጠነቀቅ፣ የማውቅ መስሎ ታየኝ። እንዲሁ እንደፈራሁ፣ እንደ ጮኽሁ፣ እንደታገልኹት፣ እንዳስቸገርኹት ምንም ሳልሆን ጨዋታውን በሰላም ጨረስን።
ለእኔ ግን አንድ ትምህርት ቀረልኝ። እግዚአብሔር ላይ ራሴን አለመጣሌ፣ በፍጹም ልቤ እርሱን አለመታመኔ፣ ተጠራጣሪነቴ፣ ከአንተ በላይ ለራሴ አውቃለሁ፣ እጠነቀቃለሁ ባይነቴ ፍንትው ብሎ ታየኝ፤ ልክ ጨዋታው ላይ መሪዬ የነበረውን ሰው አላምን ብዬ እንዳስቸገርኹት ሁሉ እግዜርንም ማስቸገሬ ታየኝ።
በዚህ Guide the Blind በተሰኘ ጨዋታ ውስጥ ከተመሪው ኃላፊነት የመሪው ኃላፊነት ይከብዳል። የመሪው ኃላፊነት አንድን መንገዱን የማያውቅ፣ የማያይን ሰው፦ ኃላፊነት ወስዶ፣ ተጠንቅቆ፣ ተንከባክቦ፣ አይን ሆኖ፣ መንገድ እየመረጠ፣ አደጋ ሳያደርስበት ከግቡ ማድረስ ነው፤ ቢወድቅ፣ አንዳች ጉዳት ቢደርስበት ኃላፊነት የወሰደው፣ ተጠያቂው እርሱ ነውና ክፉ እንዳይነካው አብዝቶ ይጠነቀቅለታል። ተመሪው ግን ስለ እርሱ ኃላፊነት የወሰደ መሪ፣ የሚጠነቀቅለት መሪ አለውና እርሱን አምኖ፣ ታምኖ፣ ራሱን መሪው ላይ ጥሎ መሄድ፣ መንገዱን የሚመርጥለትን በሙሉ ልብ መከተል ነው።
የዚያች ዕለት ስልጠናው እስኪያልቅ፣ ወደ ቤቴም ገብቼ ትኩረቴ በዚህ አሳብ፣ ጸሎት ተወስዶ ነበር፦ እግዚአብሔር ሆይ እንዳምንህ፣ አንተ ላይ ራሴን ጥዬ እንድከተልህ እርዳኝ!!
ዛሬም እግዚአብሔርን ስለ ማመን፣ ስለ መታመን፣ ራስን እርሱ ላይ ጥሎ እርሱን ስለመከተል ሳስብ፣ ሳሰላስል፣ ስጸልይ ይህ ከዛሬ አራት ዓመት በፊት የተፈጠረ ምሳሌ ትዝ አለኝ፤ ትማሩበት እና ጸሎቴንም ትጋሩኝ ዘንድ ለእናንተም ላካፍላችሁ ወደድኹ።
ዛሬም ጸሎቴን አልየርኹም ያው ነው፦ እግዚአብሔር ሆይ እንዳምንህ፣ አንተ ላይ ራሴን ጥዬ እንድከተልህ እርዳኝ!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 5, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
ላውድልህ_መስፍን_ዱጉና_Devotional_Worship_Night_Lawedeleh_Mesfin_Duguna.m4a16.41 MB
Repost from N/a
ይድነቃቸው_ተካ_ቸኮለብኝ_ልቤ_Yidnekachew_Teka_chekolebgn_lbe_eliron_lyrics128k.m4a7.05 MB
Repost from N/a
#የዝናብ_ልብስ!
#በመነካት_ከውስጥ_ሰውነት_የሆነ_ክርስትና!
የዝናብ ልብስ ስሪቱ በላዩ ላይ የሚወርደውን ውኃ ወደ ውስጥ እንዳያሳልፍ ተደርጎ ነው። የውስጠኛው የሰውነታችን ክፍል በልብሱ ተሸፍኗልና ከዝናቡ ጋር የመነካካት እደሉ በጣም ጠባብ ነው። ከላይ የሚዘንበው ውኃ ኩልል እያለ ወደ መሬት ይወርዳል እንጂ ወደ ውስጥ አይዘልቅም።
ይሄን ምሳሌ የተጠቀምኹት ስለ ዝናብ ልብስ ላወራ ፈልጌ ሳይሆን በዚህ ሂደት ውስጥ ከምናየው ነገር ለመንፈሳዊ ሕይወታችን የሚጠቅምን ትምህርት ለመቅሰም ነው። በክርስትናችን መነካት (የውስጥ ሰውታችን በእግዚአብሔር ቃል፣ በመንፈስ ቅዱስ መነካት) ቁልፍ ነገር ነው።
የውስጥ ሰውነታችን በእግዚአብሔር ካልተነካ መንፈሳዊ የሆነውን ነገር ሁሉ ለምደን ከማድረግ አንቆጠብም፤ ነገር ግን ክርስትናችን የልማድ ነው።
የቤተክርስቲያን መደበኛ ፕሮግራሞችን ያለማቋረጥ እንሳተፋለን፣ መዝሙር ስለምናውቅ እንዘምራለን፣ ትምህርቶች እንማራለን፣ ስብከት እንሰማለን፣ እድል ከቀናን ደግሞ እኛ ራሳችን ሰባኪዎችም ነን። ይሄ ሁሉ ሲሆን ግን መነካት የተባለውን ነገር ስለማናውቀው ሕይወታችን ፍሬ አልባ አዙሪት ይሆናል።
በቤተክርስቲያን ስንሆን በተለምዶ የምናደርገውን ተግባር ሁሉ እናደርጋለን፤ ከዚያ ስንወጣም እንደማንኛውም ሰው የሆነውን መደበኛ ኑሮአችንን እንቀጥላለን። አንዳንዴ እኛን ከ ኢ-አማንያኑ የሚለይ ፍንጭ እንኳን ሕይወታችን ላይ አይታይም፤ ተመሳስለን እንኖራለን። ልክ እንደ ዝና ልብሱ ከሰማይ የሆነው ነገር በላያችን ይፈሳል እንጂ ወደ ውስጣችን አይዘልቅም ከእኛ ጋር በእምነት አይዋሃድምና አይጠቅመንም።
ለራሴ፣ ለዘመናችን ቤተክርስቲያን እና አማኞች፣ ለትውልዴ ይሆን ዘንድ ለእግዚአብሔር የማቀርበው አንድ መሻት፣ ናፍቆት፣ ልመና አለኝ፤ ይህም ፦ የውስጥ ሰውነታችን በመንፈስ ቅዱስ እንዲነካ፣ የልቦና አይኖቻችን እንዲበሩ፣ ኢየሱስን እንድናይ፣ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንደሆነ እንድናስተውል፣ በቅዱሳን ዘንድ ያለ የርስት ክብር ባለጠግነት እንዲገባም፣ ለምናምን ለእኛ ከሁሉ በላይ ታላቅ የሆነውን ኀይሉን እንድናውቅ ነው። አቤቱ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ሆይ በሕያው እጆችን ዳሰን፤ ውስጠታችንን ንካው!! አሜን!!
ኤፌሶን 1 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁷ የክብር አባት የሆነውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክ ይበልጥ እንድታውቁት፣ የጥበብና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ ያለ ማቋረጥ እለምናለሁ።
¹⁸ እንዲሁም በእርሱ የተጠራችሁለት ተስፋ፣ ይህም በቅዱሳኑ ዘንድ ያለውን ክቡር የሆነውን የርስቱን ባለጠግነት ምን እንደሆነ ታውቁ ዘንድ የልባችሁ ዐይኖች እንዲበሩ
¹⁹ ለእኛ ለምናምነውም ከሁሉ በላይ ታላቅ የሆነውን ኀይሉን እንድታውቁ እጸልያለሁ። ይህም ኀይል እንደ እርሱ ታላቅ ብርታት አሠራር፣
²⁰ ክርስቶስን ከሙታን ሲያስነሣውና በሰማያዊ ስፍራ በቀኙ ሲያስቀምጠው የታየው ነው።
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 4, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
_ድሮ_ገና_Diro_Gena_lyrics_video_by_Dawit_Getachew_from_Volume_1128k.m4a5.34 MB
Repost from N/a
በእኛ ጊዜ፣ በእኛ ሁኔታ፣ በእኛ ዘመን፣ በእኛ ትውልድ....ከእግዚአብሔር ተሰጥቶን የእኛ በሆነው ነገር ሁሉ እግዚአብሔር መስራት፤ ፈቃዱን መፈጸም ይችላል። ነገር ግን እኛን ጨምሮ የሁሉ ነገር ባለቤት ለሆነው ለእግዚአብሔር ከእርሱ ተቀብለን የእኛ የሆነውን ነገር ሳንሰስት መስጠት፣ ለፈቃዱ ማዋል ካቃተን በምድር መቆየታችን ጥቅሙም ትርፉም ለእኛ እንጂ ለእግዚአብሔርና ለመንግሥቱ አይሆንም።
እስትንፋሳችን ለምን ይቀጥላል? ለምን በምድር ያቆየናል? ለምን ሌላ ሰዓት፣ ሌላ ማለዳ፣ ሌላ ቀን፣ ሌላ ሳምንት፣ ሌላ ወር፣ ሌላ የምህረት ዓመት ይሰጠናል? ደግሞም ሌላ ብዙ አቅርቦት ለምን ያፈስልናል? የእግዚአብሔር የለጋስነት ዓላማው እኛን ማብላት፣ ማጠጣት፣ ማልበስ፣ ማስጌጥ.....እና ምንም ያልጎደለባቸው ቅምጥል የእግዚአብሔር ልጆች ማድረግ ነው? ኢየሱስስ የታረደው ስለ መብልና ስለ መጠጥ ጉዳይ ነው? የእግዚአብሔር መንግሥት አሳብስ የሚያጠነጥነው ስለዚህች ምድር አበይት ክስተቶች፣ የሰዎች የኑሮ ጉዳይ ላይ ነው?
ይሄ ሁሉ ሲሆን የክርስቶስ የክብሩ ወንጌል ብርሃን በልባችን በርቶ፣ የድነትን ወንጌል ሰምተን፣ በእርሱም አምነን፣ ደህንነትን አግኝተን በእግዚአብሔር ቤት ካለን እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ያልጨረሰው ጉዳይ፣ በእኛ ሊሰራው ያሰበው ስራ አለ ማለት ነው። ስለዚህ ጠዋት በማለዳ ተነስቶ ለራስ ጉዳይ ሲሯሯጡ ማምሸቱ አያዛልቀንም! በእግዚአብሔርም አልታየልንምና ወደ ልቡ አሳብ በመመለስ፣ ሸክም በመቀየር፣ ትኩረታችንን የእግዚአብሔር መንግሥት ጉዳይ ላይ በማድረግ በምድር ያለ ቀሪ ጊዜያችንን በትጋት መኖር ይሁንልን!!
“.... ብዙ ከተሰጠው ሁሉ ብዙ ይፈለግበታል፤ ብዙ ዐደራም ከተቀበለም ብዙ ይጠበቅበታል።”
— ሉቃስ 12፥48 (አዲሱ መ.ት)
✍️ መክሊት አየለ
📆 September 13, 2024
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
Repost from N/a
“.... ብዙ ከተሰጠው ሁሉ ብዙ ይፈለግበታል፤ ብዙ ዐደራም ከተቀበለም ብዙ ይጠበቅበታል።”
— ሉቃስ 12፥48 (አዲሱ መ.ት)
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
t.me/hopministry10
Repost from Gara Innovation hub
+1
🚀 የጋራ ሚሽናል ቡትካምፕ (Gara Missional Bootcamp) 2026 ምዝገባ ተጀምሯል!
ችሎታዎትንና ፍላጎትዎትን ወደ ትልቅ አላማ የሚቀይሩበት የአንድ ወር የተጠናከረ ስልጠና አዘጋጅተንልዎታል።
በግሬት ኮሚሽን ሚኒስትሪ ኢትዮጵያ (Great Commission Ministry Ethiopia) የሚዘጋጀው ይህ ቡትካምፕ፤ በቴክኖሎጂ፣ በዲጂታል ሚዲያ እና በፈጠራ ጥበባት ዘርፎች በገበያው ውስጥ ከፍተኛ ተፈላጊነት ያላቸውን ተግባራዊ ክህሎቶች ለማስታጠቅ የተዘጋጀ ነው።
ከተዘጋጁት 8 ልዩ የስልጠና ዘርፎች ውስጥ የእርስዎን ይምረጡ፡
🎥 ሲኒማቶግራፊ (Cinematography)
📱 የሞባይል መተግበሪያ (Mobile Dev)
🎨 ግራፊክስ ዲዛይን (Graphics Design)
💻 ፉልስታክ ዌብ(Fullstack Dev)
📸 ፎቶግራፊ (Photography)
🎤 የግጥምና ዜማ ዝግጅት እንዲሁም መዝሙር (Songwriting & Singing)
📈 ዲጂታል ማርኬቲንግ (Digital Marketing)
🎵 የሙዚቃ ፕሮዳክሽን (Music Production)
የስልጠናው ዝርዝር መረጃ
🗓 ቀናት፦ ከሰኔ 29 እስከ ሐምሌ 30 (July 06 – Aug 06)
🔗 ለመመዝገብ፦ https://bootcamp.dsethiopia.org/
ያስተውሉ፦ በምስሉ ላይ እንደሚታየው ምዝገባው ተጀምሯል፤ ፈጥነው በመመዝገብ የዕድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ! ቡትካምፕ የሚጀምረው ሰኔ 29 ፣ 2018 ዓም ነው።
"እግዚአብሔር ጥበብን ይሰጣልና፤
ከአንደበቱም ዕውቀትና ማስተዋል ይወጣል።
እርሱ ለቅኖች ትክክለኛ ጥበብ ያከማቻል፤
ያለ ነቀፋ ለሚሄዱትም ጋሻ ይሆናቸዋል፤"
ምሳሌ 2፥6-7
Repost from N/a
10,000 Reasons (Bless the Lord)
Song by Matt Redman and Steve
"Bless the Lord O my soul
O my soul
Worship his holy name
Sing like never before
O my soul
I'll worship your holy name
The sun comes up
It's a new day dawning
It's time to sing your song again
Whatever may pass and whatever lies before me
Let me be singing when the evening comes
Bless the Lord O my soul
O my soul
Worship his holy name
Sing like never before
O my soul
I'll worship your holy name
You're rich in love and you're slow to anger
Your name is great and your heart is kind
For all your goodness I will keep on singing
10, 000 reasons for my heart to find
Bless the Lord O my soul
O my soul
Worship his holy name
Sing like never before
O my soul
I'll worship your holy name
Sing like never before
O my soul
I'll worship your holy name
And on that day when my strength is failing
The end draws near and my time has come
Still my soul will sing your praise unending
10, 000 years and then forever more
Bless the Lord O my soul
O my soul
Worship his holy name
Sing like never before
O my soul
I'll worship your holy name
Bless the Lord O my soul
O my soul
Worship His holy name
Sing like never before
O my soul
I'll worship your holy name
O I'll worship your holy name
I will worship your holy name
Holy name"
Repost from N/a
Matt_Redman_-_10,000_Reasons__Bless_the_Lord_(128k).m4a4.03 MB
Repost from N/a
የሰው ልጅ ረሃብን ፈልጎ ሊራብ አይችልም፤ ነገር ግን በውስጡ የጎደለው ነገር ሲኖር እርሱ ቢፈልግም ባይፈልግም የረሃብ ስሜት ይሰማዋል። ረሃብ የአንድን ነገር ጉድለት ያሳያል፣ በሚያስፈልገው ነገር መገኘት የሚሞላ ጉድለትም ነው። ስለዚህ ረሃብ ከውስጥ ነው፣ ከጉድለቱ የተነሣ በውስጥ የሚፈጠር መሻት ነው።
እግዚአብሔር እንደሚያስፈልገን ካላወቅን፣ በእርሱ ካልሆነ በቀር በሌላ በምንም የማይረካ ማንነት፣ የማይሞላ ውስጠት እንዳለን ካላወቅን እንዴት እግዚአብሔር ሊርበን ይችላል?
ሁሉ ሞልቶ፣ የዕለት ተዕለት ክንውናችን ሳይቋረጥ፣ የምንበላውና የምንጠጣው ነገር ሳናጣ፣ መልበስ ማጌጥ ሳያቅተን፣ ቤታችን ሳይጎድል፣ አሉን በምንላቸውና በምንወዳቸው ሰዎች ተከበን....ሌላም፣ ሌላም ብዙ ነገር.....በአጠቃላይ እንደ ሰው ልማድ ለመኖር አንዳች ሳይጎድልብን ልባችን አላርፍ ካለ፣ ጉድለት ከተሰማን፣ ሁሉ ሞልቶን ሳለ ነገር ግን አንዱም አላረካ ካለን፤ ታዲያ ክፍተታችን የልባችን ሰሪ፣ የሕይወታችን ፈጣሪ ራሱ እግዚአብሔር አይደለም?
በምንም የማይተካ #አንድ_ነገራችን፣ #ዋናችን፣ #አሳራፊያችን እግዚአብሔር!!! ሁሉ ጎድሎን በእርሱ ከእኛ ጋር መኖር፣ በእርሱ መገኘት እንረካለን፤ ሁሉን እየጣልን እርሱን ለመያዝ ልባችን ስፍስፍ ይላል፤ ከእርሱ ጋር ለመሆን የማንሰዋው ነገር አይኖርም፤ ለእናንተ ውዱ ነገር፣ ምርጡ ጊዜ የቱ ነው ተብለን ስንጠየቅ የእርሱ እግር ስር መሆን፣ በፊቱ መቆየት ቀዳሚ መልሳችን ይሆናል።
ምንም ሳናጣ እግዚአብሔር ይራበን፤ ሁሉ እያለን እርሱ ጉድለታችን ሆኖ ወደ ፊቱ ያሩጠን፤ ሁሉን አጥተንም ፍለጋችን እርሱ ብቻ ይሁን፤ ወደ እርሱ በመገስገሳችን ውስጥ ሊነግሱብን የሚሹና የገዘፉብን ነገሮች ይረሱ፤ የእርሱ ፍቅር፣ የመገኘቱ ረሃብ ብቻ በፊቱ ያክርመን!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 2, 2024.
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
