Mesfin mekuria @ Ambo University (WFSBSS)
Открыть в Telegram
3 418
Подписчики
-324 часа
-207 дней
-7530 день
Архив постов
የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ
AMN- ነሐሴ 16/2018 ዓ.ም.
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱት ተማሪዎች መካከል 12.8 በመቶ የሚሆኑት የማለፊያ ውጤት ማግኘታቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፣ የ12ኛ ክፍል ፈተና ከተፈተኑት 550 ሺህ ተማሪዎች መካከል 70 ሺህ 500 የሚሆኑት ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ማስመዝገባቸውን ገልጸዋል።
አዲስ አበባ ከተማ 32.3 በመቶ በማሳለፍ ከሁሉም ክልሎች አንደኛ ደረጃ ማስመዝገቧን አንስተዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደረጃ ከፍተኛው የተመዘገበው ውጤትም 569.1 ከቦሌ ትምህርት ቤት መሆኑ ተገልጿል።
በማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ተማሪዎችን ለፈተና ካቀረቡት ትምህርት ቤቶች መካከል 565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ ማሳለፍ እንዳልቻሉም አስታውቀዋል።
88 ትምህርት ቤቶች ደግሞ ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ማሳለፋቸውን ተናግረዋል።
እንዲሁም የዘንድሮው ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበው በተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ 591 ከ600 ከአዳማ ኦዳ ልዩ ቦርዲንግ ትምህርት ቤት ሲሆን፣ በማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ደግሞ 576 ከ700 ከዶዶላ ኢፋ ቦሩ ትምህርት ቤት መሆኑን ገልጸዋል።
ተማሪዎች ውጤታቸውን ከጥቂት ቀናት በኋላ በበይነ መረብ እና በአጭር የጽሁፍ መልዕክት ማየት እንደሚችሉም ተናግረዋል።
ማስታወቂያ
ለፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ተቀብሎ ለማስተማር የምዝገባ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወሳል። ሆኖም አንዳንድ ክልሎች ዘግይተው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት በመልቀቃቸውና በኢንተርኔት ምክንያት ያልተመዘገቡ ተማሪዎች በመኖራቸው ምዝገባው እስከ ነሃሴ 20/2018 ደረስ የተራዘመ መሆኑን እንገልጻለን።
የመመዝገቢያ መስፈርቶች
✍️ ለ9ኛ ክፍል ተመዝጋቢዎች
👉 የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና 80 በመቶ እና በላይ አማካኝ ውጤት ያለው/ያላት እንዲሁም በእንግሊዝኛና በሂሳብ ትምህርቶች 80 እና በላይ ያመጣ/ያመጣች ።
👉 ጥሩ ስነ -ምግባር ያለው/ያላት
✍️ ለ10ኛ ክፍል ተመዝጋቢዎች
👉 በ2017 የትምህርት ዘመን በ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና 70 እና በላይ አማካኝ ውጤት ያመጣ/ያመጣች
👉 በ9ኛ ክፍል ትራንስክሪብት 85 በመቶና በላይ አማካኝ ውጤት ያመጣ/ያመጣች እንዲሁም በእንግሊዝኛ እና ሂሳብ ትምህርት ዓይነቶች 80 በመቶና በላይ ያመጣ/ያመጣች፤
መሆኑን በድጋሚ እያስታወስን በዚህ ሊንክ https://sbs.moe.gov.et/apply በመግባት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
ዘጠኝ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችን ተቀብለው ለማስተማር ዝግጅት አጠናቀቁ
********
በ2019 የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን ተቀብለው ለማስተማር 9 የፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ዝግጅታቸውን ማጠናቀቃቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ገለጹ።
በትምህርት ሚኒስቴር የሚተዳደሩት እነዚህ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ብቃት ያላቸው፣ ተወዳዳሪ የሆኑ፣ ሥነ-ምግባርን የተላበሱ እንዲሁም ለሀገር የሚበቁ የወደፊት መሪዎችን ለማፍራት የሚያግዙ ተቋማት መሆናቸውን ፕሮፌሰር ክንደያ አስገንዝበዋል።
ከመደበኛ ትምህርት ቤቶች በተለየ መልኩ በልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶቹ የተግባር እና የክህሎት ትምህርት ላይ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥም ተገልጿል።
ይህም ተማሪዎች የተለያዩ ክህሎቶችን እንዲያዳብሩ፣ ቴክኖሎጂን በተግባር እንዲጠቀሙ እና ለወደፊት የሥራ እና የትምህርት ዓለም ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ያግዛል።
በተጨማሪም፣ ከቻይና መንግሥት ጋር በተደረገው የትብብር ስምምነት መሠረት ከሚቀጥለው የትምህርት ዘመን ጀምሮ የቻይንኛ ቋንቋ በእነዚህ ትምህርት ቤቶች እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት እንደሚሰጥ ፕሮፌሰር ክንደያ ገልጸዋል።
በመሆኑም ወላጆች፣ መምህራን እና የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ተማሪዎች ይህንን አንደ ዋና የትምህርት እድል አድርገው እንዲጠቀሙበት የማበረታታት እና የማስተባበር ሥራ እንዲያከናውኑ ፕሮፌሰር ክንደያ ጥሪ አቅርበዋል።
የትምህርት ፕሮግራሞች ጥራት ማሻሻል መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ዮሐንስ ወጋሶ በበኩላቸው የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ባለፉት 5 ዓመታት በትምህርት ዘርፉ ከተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል።
ባለፈው ዓመት ሥራ በጀመሩ 5 የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የተውጣጡ 1,250 የተሻለ ችሎታ ያላቸው ተማሪዎች የትምህርት እድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውንም ዶ/ር ዮሐንስ ገልጸዋል።
በ2019 የትምህርት ዘመን አዲስ ትምህርት በሚጀምርባቸውና ባለፈው ዓመት ትምህርት በተጀመሩባቸው ትምህርት ቤቶች የ9ኛና 10ኛ ክፍል ተማሪዎች ምዝገባ እየተከናወነ ሲሆን፣ ተማሪዎች ካሉበት ቦታ ሆነው በበይነ መረብ መመዝገብ እንደሚችሉም ዶ/ር ዮሐንስ አብራርተዋል።
የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች በመላ ሀገሪቱ በስፋት እንዲዳረሱ ትምህርት ሚኒስቴር በሁሉም ክልሎች 13 ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑም ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#Ethiopia #EBC #education
ኢንተርኔት የማይፈልገው የጉግል አዲሱ የኤአይ ትርጉም መሣሪያ
* በEdge AI ቴክኖሎጂ የታየ አዲስ ምዕራፍ
#Ethiopia | አዲስ አበባ / ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ዘገባ — የዓለማችን የቴክኖሎጂ ግዙፍ ኩባንያ የሆነው ጉግል (Google)፣ ሙሉ በሙሉ ያለ ምንም የኢንተርኔት ግንኙነት የሚሰራ አዲስ የኤአይ የትርጉም መሣሪያ በሙከራ ደረጃ ማልማቱን ይፋ አድርጓል።
«Gemma Translator» የተሰኘው ይህ የፈጠራ ውጤት፣ የቴክኖሎጂው ዓለም ከትላልቅ የመረጃ ማዕከላት (Data Centers) ወደ አነስተኛና በራሳቸው ወደሚሰሩ መሣሪያዎች (Edge Computing) ያደረገውን ትልቅ ሽግግር የሚያሳይ ተደርጎ ተወስዷል።
ይህ የትርጉም መሣሪያ የተገነባው «Raspberry Pi 5» በተባለች አነስተኛና ተንቀሳቃሽ የኪስ ኮምፒውተር ላይ ነው። መሣሪያው ድምፅን በቀጥታ ተቀብሎ በቅጽበት ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች ለመተርጎም የጉግልን አነስተኛና ቀልጣፋ የኤአይ ሞዴል «Gemma» ን ይጠቀማል።
ትርጉሙ የሚካሄደው በመሣሪያው ውስጣዊ ፕሮሰሰር ላይ ብቻ በመሆኑ ምንም ዓይነት ዋይፋይ (Wi-Fi)፣ የሞባይል ዳታ ወይም የደመና (Cloud) ግንኙነት አይፈልግም።
ማይክሮፎን እና ስፒከር በ3D ፕሪንተር በተሠራ ቀላል ሳጥን ውስጥ ተካተውበታል።
ተናጋሪው የሚናገረውን ድምፅ በቀጥታ በማዳመጥ ወደሚፈልገው ቋንቋ በድምፅ ይተረጉማል።
የኢንተርኔት አገልግሎት በሌለባቸው ወይም ደካማ በሆነባቸው ስፍራዎች ይህ መሣሪያ ትልቅ የመገናኛ ድልድይ ይሆናል ተብሎ ይታመናል፦
በተፈጥሮ አደጋዎች ወይም በጦርነት ቀጠናዎች የመገናኛ መስመሮች በሚቋረጡበት ወቅት ፈጣንና ቀጥተኛ የመረጃ ልውውጥ ለማድረግ።
የኔትወርክ ሽፋን በሌላቸው ገጠራማና አስቸጋሪ ቦታዎች በሚጓዙበት ወቅት የቋንቋ እንቅፋትን ለመቅረፍ።
ንግግሮች ወደ የትኛውም ሰርቨር ስለማይላኩና ውሂቡ (Data) እዚያው መሣሪያው ላይ ብቻ ስለሚከናወን ሙሉ የመረጃ ምስጢራዊነትን ያረጋግጣል።
ምንም እንኳን ጉግል ይህንን ምርት በቀጥታ ለገበያ የንግድ ሽያጭ ባያቀርበውም፣ የቴክኖሎጂውን ፍልስፍና ግን ለህዝብ ክፍት አድርጎታል።
የሃርድዌር (Raspberry Pi 5) ወጪ፦ በግምት 80 የኣሜሪካ ዶላር
የኤአይ ሶፍትዌር እና 3D ዲዛይን ፋይሎች፦ በነጻ የሚወርዱ (Open Source)
ይህ አካሄድ ማንኛውም ፍላጎት ያለው የቴክኖሎጂ ባለሙያ ወይም አዳጊ ፈጣሪ የራሱን ኦፍላይን የትርጉም መሣሪያ በቤቱ ማዘጋጀት እንዲችል መንገድ የሚከፍት ነው።
የ«Gemma Translator» ፕሮጀክት ትልቅ ትርጉም ያለው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የሚጠይቀውን ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይልና የኃያላን ኮምፒውተሮች አቅም (Computing Power) በመቀነስ፣ አነስተኛ በሆኑ መሣሪያዎች ላይ ማሄድ እንደሚቻል ማረጋገጡ ነው።
ይህም ወደፊት ስማርትፎኖች፣ የቤት ውስጥ ቁሳቁሶች እና ተለባሽ ቴክኖሎጂዎች ያለ ኢንተርኔት ድጋፍ በተሻለ ሁኔታ በራሳቸው ኤአይ እንዲሰሩ ለሚደረገው ጥረት ትልቅ ማሳያ ተደርጎ ይወሰዳል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
