ru
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Канал የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 16 089 подписчиков, занимая 5 168 место в категории Религия и духовность и 2 137 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 16 089 подписчиков.

Согласно последним данным от 19 сентября, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 409, а за последние 24 часа — 3, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 24.66%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 12.08% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 962 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 941 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 13.

📝 Описание и контентная политика

Описание канала не предоставлено.

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 20 сентября, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

16 089
Подписчики
+324 часа
+947 дней
+40930 дней
Архив постов
‎በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በደ/ጎንደር ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍልና በሰ/ት/ቤቶች አንድነት ሲሰጥ የቆየው የመምህራን ስልጠና ተጠናቀቀ። ሐምሌ 29/11/2018ዓ.ም የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ስልጠናው የተሰጠው ከሐምሌ 12-26/ 2018 ዓ.ም ሲሆን ከወረዳዎች የተውጣጡ 71 የሚደርሱ የአሰልጣኞች ሥልጠና ተሳታፊዎች በ15 ቀናት ለ200 ሰዓታት የተሰጠውን ሥልጠና ጨርሰው ተመርቀዋል። በምርቃት መርሐ ግብሩ የሀገረ ስብከቱ  ዋና ሥራ አሰኪያጅ ሊቀ ስዩማን ቀሲስ ምሕረት ሞላ፣ የሀገረ ስብከቱ  ዋና ፀሐፊ መላከ ብርሐን ቀሲስ ዘውዱ አበጀ፣  የሀገረ ስብከቱ  ስብከተ ወንጌል ሓላፊ ሊቀ ጉባኤ ሳሙኤል እንየው እንዲሁም የየመምሪያ ሓላፊዎች ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የሰ/ት/ቤት አባላት ተገኝተዋል። ‎በዕለቱም ትምህርተ ወንጌል በሀገረ ስብከቱ  ስብከተ ወንጌል ሓላፊ ሊቀ ጉባኤ ሳሙኤል እንየው የተሰጠ ሲሆን በተመራቂ መምህራን ለዕለቱ የሚስማማ ወረብ ቀርቧል። ‎የዚህ ስልጠና ዋናው ዓላማው በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት ሕፃናት ከልጅነታቸው ነገረ እግዚአብሔርን አውቀው ለቤተክርስቲያናቸው እና ለሀገራቸው ዘብ የሚቆሙና የሚጠቅሙ ትውልድ ማፍራት ነው። ‎በመጨረሻም ለተመራቂዎች የምስክር ወረቀት የተሰጠ ሲሆን ሥልጠናው የተሳካ እና ውጤታማ እንዲሆን አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦች የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቷል ። ‎ መረጃው፦ የደ/ጎ/ሀ/ስ/ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ለ3ኛ ጊዜ የሀገረ ስብከት አቀፍ ፈተና ለ4ኛ ፣ ለ8ኛ እና ለ10ኛ ክፍል ከ2500 በላይ የሰ/ት/ቤት ተማሪዎች ሐምሌ 26/2018 ዓ/ም መስጠቱን
+7
የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ለ3ኛ ጊዜ የሀገረ ስብከት አቀፍ ፈተና ለ4ኛ ፣ ለ8ኛ እና ለ10ኛ ክፍል  ከ2500 በላይ የሰ/ት/ቤት ተማሪዎች ሐምሌ 26/2018 ዓ/ም መስጠቱን አስታወቀ፡፡ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በ2018 ዓ/ም ለ3ኛ ጊዜ የሀገረ ስብከት አቀፍ ፈተና ለ4ኛ፣ ለ8ኛ እና ለ10ኛ ክፍል የሰ/ት/ቤት ተማሪዎች 6 ፈተናዎች በየትምህርት ዓይነቱ በ2ቱም ቋንቋ (በአማርኛ እና በአፋን ኦሮሞ)  በትላንትናው ዕለት ጠዋትና ከሰዓት እንዲሰጥ አድርጓል፡፡ በመንበረ ጵጵስና፣ በቢሾፍቱ አካባቢውና በአድአ፣ በአዳሚ ቱሉ፣ በሉሜ፣ በዱግዳ፣ በቦሰት እና በፈንታሌ በድምሩ በ8 የወረዳ ቤተክህነት ሥር በሚገኙ ሰ/ት/ቤቶች በተመረጡ ማዕከላዊ የምዘና ጣቢያዎች  ምዘናው ተሰጥቷል፡፡ መረጃው የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

የሸገር ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት የ4ኛ፣ 8ኛ እና 10ኛ ክፍል ሀገረ ስብከት አቀፍ ምዘና አከናወነ። ሐምሌ 27/2018ዓ.ም የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሸገር ሀገረ ስብከት የሰንበ
+7
የሸገር ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት የ4ኛ፣ 8ኛ እና 10ኛ ክፍል ሀገረ ስብከት አቀፍ ምዘና አከናወነ። ሐምሌ 27/2018ዓ.ም የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሸገር ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በዚህ ዓመት ለኹለተኛ ጊዜ በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት ሲማሩ የቆዩ  የ4ኛ፣ 8ኛ እና 10ኛ ክፍል የሰ/ት/ቤት ተማሪዎችን  በ5ቱም ክፍላተ ከተማ (በሰበታ፣ ገላን ጉዳፉሪ፣ በቡራዩ ጉጄ ገፈርሳና መልካ ሸኖ ፣ በኮዬ ገላን ፣ በሱሉልታ መነ አቢቹ እና በለገጣፎ ለገዳዲ ኩራ ጂዳ ክፍላተ ከተማ) አከናውኗል። የምዘና መርሐ ግብሩ በተያዘለት ጊዜ እንዲከናወን የተለያዩ የሀገረ ስብከት ሐላፊዎች ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ት ቤት ማደራጃ ክፍል ኃላፊ መጋቤ ወንጌል ሄኖክ ታዬን ጨምሮ የክፍላተ ከተማ አመራሮች በፈተና ጣቢያዎቹ በመገኘት ተማሪዎችን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት ትውልዱን አበረታተዋል። ሁሉም የፈተና ጣቢያዎች በጥሩ ሁኔታ የተጠናቀቀ ሲሆን በሀገረ ስብከቱ በዘንድሮ  ዓመት 3100 ለሚጠጉ ተማሪዎች 4ኛ፣ 8ኛ እና 10ኛ ክፍል  ምዘና ማከናወን እንደቻለ የሀገረ ስብከቱ ሰ/ት/ቤት አንድነት ተናግሯል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሀገረ ስብከት ደረጃ ለ3ኛ ጊዜ ሲያሰለጥናቸው የቆዩ ተተኪ መምህራንን አስመረቀ። የሰ/ት/ቤቶች አንድነት  ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ለ5ቀናት በመንበረ ጵጵስና ቅድስት ልደታ ቤተ ክርስቲያን ለ3ኛ ጊዜ ሲሰጠው የቆየውን የተተኪ መምህራን ሥልጠና የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እንጦንስ በተገኙበት አስመረቀ። ሥልጠናው ከ 9 ወረዳ ቤተ ክህነት የተውጣጡ 120 ያህል የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች የተካፈሉበት ሲሆን፣ ታች በወረዳ እና በአጥቢያ ደረጃ የሰ/ት/ቤቶችን አገልግሎት የሚያሳድግና  የሥርዓተ ትምህርት ትግበራውን የሚያሳልጥ መሆኑን የሀገረ ስብከቱ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል ሓላፊ መጋቤ ሥርዓት ቀሲስ ዘነበ ብርሃኑ ተናግረዋል። ይህ የሀገረ ስብከት ሥልጠና በአዲስ አበባ ለሚደረገው የሀገር አቀፍ የአሰልጣኝ መምህራን ሥልጠና መመልመያ አንዱ መድረክ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የሀገረ ስብከቱ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ም/ሰብሳቢ መ/ር መኮንን አብዩ ናቸው። ሥልጠናው የተሰጠው ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በተወከሉ መምህራን ነው። ይህ ሥልጠና በሀገር አቀፍ አንድነቱ በዘንድሮው ዓመት ሀገረ ስብከቶች እንዲያሳኳቸው ከሚጠበቁ እና እንደ ዕቅድ ተይዞ ከሚሠራባቸው የሥልጠና ማዕከላት  አንዱ እንደሆነ በምርቃት መርሐ ግብሩ የተገኙትና ሥልጠናውን የሰጡት፣ የሀገር አቀፍ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ሥርዓተ ትምህርት አስተባባሪ መ/ር ሚኪያስ ግዛቸው ገልጸዋል። አያይዘውም ሥልጠናው ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ፣ የመምህራን ክህሎት ግንባታ፣ የክፍላተ ትምህርት ገለጻ ላይ ያተኮረ ሀገረ ስብከት አቀፍ ሥልጠና እንደሆነ ተናግረዋል። በምርቃት መርሐ ግብሩ የሥልጠና ሪፖርትና የሀገረ ስብከቱን አንድነት የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ አካሔድ እና ሥልጠናውን በተመለከተ 12 ያህል የአቋም መግለጫ በማውጣት እንዲሁም ሠልጣኞችን ለላኩ እና በሥልጠናው ለተሳተፉ ተተኪ መምህራን የምስክር ወረቀት በመስጠት ተጠናቋል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

የ2018 ዓ.ም የሀገረ ስብከት አቀፍ ምዘና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተከናወነ። የዘንድሮውን #የ4ኛ፤ #የ8ኛ እና #የ10ኛ ክፍል የእርከን ማጠናቀቂያ ምዘና ዛሬ ሀምሌ
+9
የ2018 ዓ.ም የሀገረ ስብከት አቀፍ ምዘና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተከናወነ። የዘንድሮውን #የ4ኛ፤ #የ8ኛ እና #የ10ኛ ክፍል የእርከን ማጠናቀቂያ ምዘና ዛሬ ሀምሌ 26/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3 ሰዓት  ጀምሮ በ191 ሰንበት ት/ቤቶች ከ20000(ሃያ ሺ) በላይ ተማሪዎች ወስደዋል፡፡ በዚህ ምዘና ከአዲስ አበባ እና ክፍለ ከተሞች አንድነት የተወጣጡ ከ80 በላይ አስተባባሪዎች እና ከየአጥቢያዉ የተወጣጡ ከ 400 በላይ ፈታኞችና ሱፐርቫይዘሮች ሥልጠና ወስደዉ የፈተና ሂደቱን በተገቢው መልኩ አከናውነዋል። ዘገባው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ምዘና ማጠናቀቁን የሀገር አቀፍ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት አስታወቀ። ሐምሌ 26/2018 ዓ.ም የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የ
+9
የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ምዘና ማጠናቀቁን የሀገር አቀፍ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት አስታወቀ። ሐምሌ 26/2018 ዓ.ም የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሀገር አቀፍ ደረጃ በቅድመ ሙከራ ሥርዓተ ትምህርቱን ሲከታተሉ ቆይተው ለ12ኛ ክፍል የማጠቃለያ ፈተና የደረሱ አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ምዘናንውን በዛሬው ዕለት ወስደዋል። ምዘናው በ4 የፈተና ማዕከላት (ሲ ኤም ሲ ቅዱስ ሚካኤል፣ ሰዋሰወ ብርሃርን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም፣  አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም እና ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኒዓለም) አጥቢያዎች በአዲስ አበባ እና በሸገር ሀገረ ስብከት ስር የሚገኙ ለ20 ሰንበት ትምህርት ቤቶች ሰጥቷል። በየፈተናው ጣቢያ ፈተናው  በአበው ካህናት ጸሎት የተከፈተ ሲሆን ስለፈተናው አጠቃላይ ገለጻ ከሀገር አቀፍ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የተወከሉ ፈታኞች ገለጻ ከሰጡ በኋላ ክርስቲያናዊ ሥነምግባርን በጠበቀ መልኩ ፈተናው ተከናውኖ የመርሐግብሩ ፍጻሜ ሆኗል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

የ2018ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ምዘና ለመስጠት ዝግጅት ማጠናቀቁን የሀገር አቀፍ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት አስታወቀ። ሐምሌ 24/2018ዓ.ም የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ
የ2018ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ምዘና ለመስጠት ዝግጅት ማጠናቀቁን የሀገር አቀፍ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት አስታወቀ። ሐምሌ 24/2018ዓ.ም የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል የማጠቃለያ ፈተና ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለጠ። ፈተናው የፊታችን እሑድ ሐምሌ 26/2018ዓ.ም በተመረጡ 4 ማዕከላት እንደሚሰጥ አንድነቱ አስታውቋል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

4ኛው የአህጉረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር ተከናወነ። የሰ/ት/ቤቶች አንድነት (ሐምሌ 22 / 11 / 2018 ዓ.ም) 4ኛው የአህጉረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር በትላንትናው ዕለት በቅድስ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ አዳራሽ ተከናወናውኗል። በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ሳዌሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የራያና አካባቢው አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ የሰሜን ሸዋ እና የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ (ዶ/ር) የደቡብ ኦሞ እና አሪ ዞኖች አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የበላይ ሐላፊ ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያና የድርጅት ሐላፊዎች ፣ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አመራሮች እንዲሁም ከ37 አህጉረ ስብከት ተወጣጥተው ከሐምሌ 06 ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ሥልጠናቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ተመራቂ ሰልጣኝ መምህራን በተገኙበት ተከናውኗል። የዕለቱን ቃለ እግዚአብሔር በብፁዕ ሊቀ ጳጳሱ መልካም ፈቃድና በመምሪያው ሊቀ ጳጳስ ጋባዥነት ያስተማሩት ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ሲሆኑ በ1ኛ ቆሮ 8፡2 ላይ "ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም" የሚለውን የቅዱስ ጳውሎስን ቃል አንስተው ልናውቀው የሚገባውን ምሥጢር እግዚአብሔርን መውደድና መፍራት መሆኑን አስተምረዋል። በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ የማደራጃ መምሪያ ሐላፊ መጋቤ ሐዲስ ኃይለ እግዚእ አሰፋ "በእግዚአብሔር ቤት ተተክለዋል። በአምላካችን አደባባይ ይበቅላሉ።" መዝ 91፡13 የሚለውን የልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊትን ቃል መነሻ በማድረግ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክታቸውን እንዲሁም ለሥልጠናው መሳካት አስተዋጽዖ ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ አጠቃላይ የሥልጠናውን ሒደት የተመለከተ ሪፖርት በዲ/ን ስንታየሁ ምስጋና የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ በኩል የቀረበ ሲሆን ሠልጣኞቹ የነበራቸውንም ቆይታ የተመለከተ ሪፖርት በተወካያቸው በኩል አቅርበዋል። በመጨረሻም አባታዊ ቡራኬ ቃለ ምዕዳን እና መመሪያ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ተሰጥቶ የምርቃቱ ፍጻሜ ሆኗል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

የመጋቤ ሐዲስ ኀይለ እግዚእ አሰፋ በ2018 ዓ.ም የአህጉረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች የአሠልጣኞች ሥልጠና መክፈቻ መርሐ ግብር ላይ ያስተላለፉት መልእክት “ዘጸምአ ይምጻእ ኀቤየ ወይስተይ ወዘሂ የአምን
+1
የመጋቤ ሐዲስ ኀይለ እግዚእ አሰፋ በ2018 ዓ.ም የአህጉረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች የአሠልጣኞች ሥልጠና መክፈቻ መርሐ ግብር ላይ ያስተላለፉት መልእክት “ዘጸምአ ይምጻእ ኀቤየ ወይስተይ ወዘሂ የአምን ብየ አፍላገ ማየ ሕይወት ይውሕዝ እምከርሡ” “የተጠማ ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ፣ በእኔም የሚያምን መጽሐፍ እንደተናገረ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል” (ዮሐ7፡37) ይኸን ቃል የተናገው መድኅነ ዓለም ክርስቶስ ነው፡፡ ቃሉም የተነገራቸው በሥልጠና ላይ ለነበሩ ደቀ መዛሙርት ነው፡፡ ቃሉን ጠጥተው ጽምዐ ነፍሳቸውን እንዲያርቁ፣ ከዓለማዊ ግብር እንዲላቀቁ፣ በሃይማኖትና በምግባር እንዲልቁ ፣ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን አንዲለብሱ፣ ከብሌት እንዲታደሱ፣ በአእምሮ እንዲጎለብሱ ስለጠራቸው “የተጠማ ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ” በማለት የሰውን ልጆች ሁሉ ወደ እርሱ ጠርቷቸዋል፡፡ በመተርጒማን ዘይቤ ደረቅ ሐዲስ በሚል የትንቢት መጽሐፉ የሚታወቀው ነገረ ክርስቶስን በተመለከተ በምልአትና በስፋት የጻፈው ልዑለ ቃል ኢሳይስም “እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ ወደ ውኃ ሂዱ” ሲል ትንቢታዊ ምክሩን ለግሶአል፡፡ ( ትን .ኢሳ 55፡1) .... https://eotc-gssu.org/a/የመጋቤ-ሐዲስ-ኀይለ-እግዚእ-አሰፋ-በ2018-ዓ-ም/

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት የውስጥ ዝርዝ
+7
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት የውስጥ ዝርዝር ማስፈጸሚያ ሰነድ በ2016 ዓ.ም በተዘጋጀው እና በ2018 ዓ.ም የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ ሰነድ መሠረት ሁሉም ሀገረ ስብከቶች ወደ ተግባራዊ ሥራ በመግባት ላይ መሆናቸው ይታወቃል። በመዋቅራዊ አሠራሩም በተገለጸው መሠረት አጥቢያ ሰንበት ት/ቤት፣ ክፍለ ከተማ፣ መንበረ ጵጵስና እና መንበረ ፓትርያርክ ደረጃ በደረጃ ወጥ በሆነ አሠራርና ጊዜ እንዲፈጸም ትግበራ ላይ ይገኛል። በዚህም መሠረት የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በሀገረ ስብከቱ የሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማከናወናቸውን ተከትሎ በአዲሱ አደረጃጀት የተመረጡ ከ2300በ ላይ የሰንበት ት/ቤት ሥራ  አመራሮች  እና የአፈጻጸም ቁጥጥር እና ክትትል ጉባኤ አባላትን  ሐምሌ 11 ፣12 እና 25 /2018 ዓ.ም በተመረጡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሥልጠና ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቅቆ  ሥልጠናው ዛሬ ሐምሌ 11/12/18/25 /2018 ዓ.ም ከቀኑ 7:30 አስከ 11:30  በአስራ ኹለት የስልጠና ጣቢያዎች መስጠት ጀምሯል። የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት 4ኛው የአህጉረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ አዳራሽ በዛሬው ዕለት ተጀመረ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 06/2018 ዓ.ም በዛሬው የመክፈቻ መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ አገልግሎት መምርያ ሊቀ ጳጳስ ፣ መጋቤ ሐዲስ ኃይለ እግዚእ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ ፣ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት መምሪያ ሐላፊ ፣ ሊቀ ጉባኤ መሐሪ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ምክትል ሐላፊ ፣ ዲ/ን ስንታየሁ ምስጋና የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሥራ አመራር አባላት እና የመምሪያው ልዩ ልዩ ሠራተኞች በተገኙበት በጸሎተ ወንጌል ተጀምሯል። ብፁዕ አቡነ ማርቆስ በመዝሙር 125(126):5 ላይ "በልቅሶ የሚዘሩ በደስታ ያጭዳሉ።" የሚለውን የዳዊት መዝሙር መነሻ አድርገው ገበሬ በልቅሶ በመከራ በክረምት ዘርን እንደሚዘራ በገበሬ አምሳል መምህራንም ዘር የተባለ ቅዱስ ወንጌልን በልቅሶ በመከራ ለማስተማር  መዘጋጀት ይገባችዋል በማለት ለሰልጣኝ መምህራኑ አባታዊ ቡራኬና መልእክት አስተላልፈዋል። "የተጠማ ቢኖር ወደኔ ይምጣና ይጠጣ በእኔ የሚያምን ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚል የሕይወት ውኃ ምንጭ ከሆዱ ይፈልቃል።" ዮሐ 7:38 በሚል ቃል መነሻ አድርገው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። በመቀጠልም በዲ/ን ስንታየሁ ምስጋናው አጠቃላይ የሥልጠናውን ይዘትና አካሄድ ላይ ገለጻ አድርገዋል። ሥልጠናው በ3 መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሲሆን እነርሱም መሠረተ እምነት ዶግማ እና የሥርዓተ አምልኮ ጉዳዮች ፣ ሥርዓተ ትምህርትን የሚመለከቱ ሥልጠናዎች እንዲሁም ተግባራዊ ሥራና የሕይወት ክህሎት ናቸው። በሥልጠናውም ላይ ከ37 አህጉረ ስብከት የተወጣጡ ከ315 በላይ ሠልጣኞች ይሳተፋሉ። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

እንኳን ደስ አላችሁ!!! በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አድነት ከዚህ በፊት ከ1ኛ እስከ 7ኛ ክፍል በአማርኛ እንዲሁም ከ
እንኳን ደስ አላችሁ!!! በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አድነት ከዚህ በፊት ከ1ኛ እስከ 7ኛ ክፍል በአማርኛ እንዲሁም ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል በኦሮምኛ የመማርያ መጻሕፍትን በማዘጋጀት የግዥ ጥቅል (Package) ተዘጋጅቶላችሁ እየወሰዳችሁ እንደሆነ ይታወቃል። አሁን ደግሞ የቅድመ ሕጻናት ሀ እና ለ 2 ጥራዝ መጻሕፍት እና ከ8ኛ እስከ 10ኛ ክፍል 3 ጥራዝ መጻሕፍት ህትመት መድረሱን እያበሰርን ከ2019 ዓ.ም የትምህርት ዓመት አስቀድሞ መጻሕፍቱን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ገዝታችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

#ታላቅ_የምሥራች የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ 2ኛ ዙር የበይነመረብ (ኦንላይን) የነገረ መለኮት ትምህርት ምዝገባ እያካሄደ ይገኛል። እርስዎም የዚህ መልካም እድል ተጠቃሚ ይሆኑ ዘ
#ታላቅ_የምሥራች የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ 2ኛ ዙር የበይነመረብ (ኦንላይን) የነገረ መለኮት ትምህርት ምዝገባ እያካሄደ ይገኛል። እርስዎም የዚህ መልካም እድል ተጠቃሚ ይሆኑ ዘንድ እየጋበዝንዎት መላው ኦርቶዶክሰዊ ተሳታፊ እንዲሆን ይህን መልእክት በማጋራት ክርስቲያናዊ  ኃላፊነትዎን እንዲወጡ በማለት ከታች የምዝገባ ማመልከቻ ቅጽ እና የኦንላይን ትምህርት ማስተባበሪያው የቴሌግራም ገጽ ማስፈንጠሪያ (#Link) አስቀምጠንልዎታል:: የምዝገባ የማመልከቻውን ቅጽ ለመሙላት 👇👇👇👇👇👇👇👇 https://forms.gle/bHGroCYF5a3MDxV19 ለተጨማሪ መረጃ እና ማስታወቂያዎችን ለመከታተል የቴሌ ግራም ገጹን ይቀላቀሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/Sewasiwe_Birhan_Kidus_Pawlos
ይህ መልእክት ለኦርቶዶክሳውያን ሁሉ እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግ ክርስቲያናዊ ኃላፊነትዎን ይወጡ።

በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነተ  በሀገረ ስብከቱ ሥር ለሚገኙ  በአዲሱ ሥርዓተ  ትምህርት መሠረት የ4ተኛ እና የ8ተኛ ክፍል  የሚኒስትሪ ፈተና ተሰጠ።   የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ምዘናው በጭሮ  በአራቱ አድባራት  ተማሪዎች  የፈተናውን አሰጣጥ ሊቀ ኅሩያን ቆሞስ አባ ፍቅረ ዮሐንስ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ   ከማደራጃው ኃላፊ  መጋቤ ሥርዓት ዘነበ ብርሐኑ  እንዲሁም የአንድነቱ ተቀዳሚ ሰብሳቢ  መ/ር መኮንን አብዩ  ሌሎቹችም የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አማራር በመገኘት  የሀገረ ስብከቱ ስራ  አስኪያጅ ቡራኬና ጸሎት ሰጥተው  ፈተናውን አስጀምረዋል።  ፈተናውም በሀገረ ስብከቱ አዳራሽ   እንዲሁም  በአቡነ ጎርጎሪዎስ ትምህርት ቤት ተሰጥቷል። በተጨማሪም በወረዳ  ላሉት የሰንበት ትምህርት  ቤት ተፈተኞች   1. በጡሎ  ዶባ ወረዳ  በሂርና  ሁለቱ አድባራት ና በዶባ  ቅ/ሚካኤል  ቤተክርስቲያን 2.በቦኬ ኦዳ ቡልቱም ወረዳ  በበዴሳ  ሁለቱ አድባራት ና በመካኒሳ ቅ/ገብርኤል  ቤተክርስቲያን  3. በዳሮ ለቡ ወረዳ  መቻራ መድኃኔዓለም    ቤተክርስቲያን 4. በሀብሮ ወረዳ   ገለምሶ ሁለቱ አድባራት እና  በልበሊቲ ቅ/ጊዮርጊስ   ቤተክርስቲያን   5. በገመቺስ ወረዳ  በቁኒ ሁለቱም አድባራት ፈተናው መስጠት ተችሏል።  ይህ የስርዓተ ትምህርት የምዘና ስራ አምና በአንድ ወረዳ ብቻ ተሰጥቶ ቢሆንም  ዘንድሮ በ5 ወረዳ እና  ከ16 ለሚበልጡ ሰንበት ትምህርት ቤቶች  ፈተናው ተዘጋጅቶ መበተን ተችሏል። በርዕሰ ከተማው ለሚገኙ ተፈታኞችም የሀገረ ስብከቱ    ሊቀ ጳጳስ  አቡነ እንጦንስ  በፈተናው ማብቂያ ላይ በመገኘት ልጆቻቸውን ሲያበረቱ ምክር ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬን በመስጠ በጸሎት ማጠቃለያ ማድረግ ተችሏል። የሰንበት ትምህርት ቤቱ ማደራጃ እና የሰንበት ትምህርት  ቤቶች አንድነት በሚቀጥለው የትምህርት  ዘመን  በ9 ወረዳዎች  ተዳራሽ ለማድረግ ስራዎችን ከወዲሁ እየሰራ ይገኛል። የረዳን እግዚአብሔር  ይመስገን። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

በምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት የ2018 ዓ.ም ሀገረ ስብከት አቀፍ የ4ኛ ፣ 8ኛ እና 10ኛ ክፍል የሞዴል ፈተናዎች ሰጠ፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ስር የሚገኙ ሰንበት
+3
በምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት የ2018 ዓ.ም ሀገረ ስብከት አቀፍ የ4ኛ ፣ 8ኛ እና 10ኛ ክፍል የሞዴል ፈተናዎች ሰጠ፡፡   በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ  የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ስር የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የ2018 ዓ.ም ሀገረ ስብከት አቀፍ  የሞዴል ተሰጠ። በሀገረ ስብከቱ በሚገኙ 6 ወረዳ ቤተ ክህነት  መንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ አዳማ ፣ቢሾፍቱና አካባቢው፤ ሉሜ ፣አዳሚ ቱሉ፤ዱግዳ ፣እና በቦሰት ወርዳ ቤተ ክህነት በስሮቻቸው ባሉ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርቱን ሲከታተሉ ለቆዩት 3000 ተማሪዎች የ2018 ዓ.ም ሞዴል  ፈተና በቀን 07/09/2018 ዓ.ም  ተሰጥቷል፡፡  የሞዴል ፈተናው  ስድስት የትምህርት አይነቶችን   ለየብቻቸው ተዘጋጅቶ  ተሰጥቷል። የተሰጠው ፈተና  መሠረተ ሃይማኖት፤ ክርስቲያናዊ ሥነ-ምግባር ፤ልሳነ ግዕዝ ፤የቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት፤ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ እና ሥርዓተ ቤተክርስቲያን ለእያንዳንዱ ትምህርቶችን 50 ጥያቄዎችን ያከተተ ሲሆን  በሀገረ ስብከቱ አንድነት የሚዘጋጀው የ4ተኛ 8ተኛ እና 10ኛ ክፍል ሀገረ ስብከት አእቀፍ የሚኒስትሪ ፈተና በወጣይ ወር  በሁሉም ወረዳዎች ባሉ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ይሰጣል። መረጃው የምሥራቅ ሸዋ ሀገረስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

"የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫ እንኳን ለዓመታዊው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ! የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በጋራ ጉባኤ በአንድነት ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሚመክሩበት፣ የትውልዱን መጻኢ ጉዞ የሚተልሙበት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለነገው ትውልድ ሊያሻግሩ የሚችሉ ዐውደ ሐሳቦች ለውይይት የሚቀርቡበት ታላቅ በዓል ነው። ይህ በቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅና ተሰጥቶት በየዓመቱ እየተከናወነ የሚገኘው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ዘንድሮ በሀገራዊ ጉዳይ ምክንያት በመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ደረጃ ጠቅላላ ጉባኤውን በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማከናወን ባይችልም በሁሉም አህጉረ ስብከት፣ በየወረዳው እና በየአጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ዕለቱ በደማቅ ሁኔታ "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫ በሚል መሪ ቃል ተከብሮ ይውላል። ቅዱስ ጳውሎስ "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ብቻ አይደለም ያለን ይህንንም የመንፈስ አንድነት እንዴት መጠበቅ እንዳለብን በመንገርም ጭምር ነው እንጂ። ይኸውም በፍጹም የዋሕነት፤ ራሳችሁን ዝቅ አድርጋችሁ፣ እየታገሣችሁ፣ ለወንድሞቻችሁም እሺ እያላችሁ፣ በፍቅር እየተጋችሁና እየተባበራችሁ በማለት ነው። የአንድነታችንንም ዓላማ እንዳንዘነጋ ሲገልጽልን “ለአንዱ ተስፋችሁ እንደመጠራታችሁ” ይለናል። እኛም የ15ኛ ዓመት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ቀንን ስናከብር ከወትሮ በላቀ የመንፈስ አንድነታችንን ለመጠበቅ መትጋት እንዲገባን ይህን የቅዱስ ጳውሎስን ምክር መርሐችን አድርገናል። ከሁል ጊዜው በላይ ዓለምም ሆነ ሀገራችን እየተጓዘችበት ካለው አስፈሪ የጥፋት ጉዞ ትውልዱን መጠበቅ፣ ማዳንና ማሰማራት የሚቻለው የመንፈስ አንድነታችንን ለመጠበቅ ስንተጋ ብቻ ነው። የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ትውልዱን በቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር ለመጠብቅ የመንፈስን አንድነት መርሕ ይዞ የሚጓዝ መዋቅር ነው። ታዲያ ይህንን አንድነታችንን ከውስጥም ከውጭም ፈተናዎች ለመጠበቅ እየታየ ያለውን በጎ ፍሬ ለማስቀጠል ትጋትን ገንዘብ ልናደርግ ይገባናል እንላለን። ምን እንኳን በበዓለ ጰራቅሊጦስ የዘንድሮውን ዓለም አቀፋዊ ጠቅላላ ጉባኤያችንን ማከናወን ባንችልም በያለንበት መዋቅር ዕለቱን ልንዘክረው ይገባናል። በመጨረሻም የዘንድሮውን ዓለም ዓቀፍዊ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ የሚከናወንበትን ዕለት በቅርቡ የምናሳውቅ መሆኑን እየገለጽን እንኳን ለዓመታዊው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ እንላለን።   የመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ግንቦት 22/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website