fa
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

کانال የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 116 مشترک است و جایگاه 6 291 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 401 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 116 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 10 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 473 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 10 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 38.95% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً N/A% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 492 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 0 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 28 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 11 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

14 116
مشترکین
+1024 ساعت
+957 روز
+47330 روز
آرشیو پست ها
"የባሕርይ ገዥ ክርስቶስ ከዕለት ከሰዓት አስቀድሞ የነበረ ሲሆን የሰዎችን ልደት ዛሬ ተወለደ።" ሃይማኖተ አበው የቁስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳስ የሐዋርያት ደቀ መዝሙር የነበረ አጢፎስ በሃይማኖተ አበው ላይ የልደትን ነገር በተናገረበት ድርሳኑ ይህን መሰከረ። ክርስቶስን የባሕርይ ገዥ ጌታ አለው። ሌሎች ገዥ ቢባሉ በጸጋ በስጦታ፤ ሌሎች ጌታ ቢባሉ የምድር፤ ሌሎች ገዥ ቢባሉ በጊዜ የሚገደብ፤ በዘመን የሚወሰን ነው። ለእርሱ ግን ጌትነትን የሚሰጠው ሰጪ አልያም የሚወስድበት ወሳጅ የሌለበት የባሕርይ ገንዘቡ ነውና የባሕርይ ገዢ አለው። ዮሐ 13:13 ከዕለትና ከሰዓት አስቀድሞ ነበርም አለው። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዘመናት የማያረጅ እንዲሁም በጊዜ የማይወሰን ከ ብሎ መጀመርያ እስከ ብሎ መጨረሻ የሌለው ቀዳማዊ ድኃራዊ ነውና ከዕለት ከሰዓት አስቀድሞ የነበረ ብሎ መሰከረ። ዮሐ 1:1 ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም በመልእክቱ ቀዳማዊነቱን ሲናገር "በሰማይና በምድር ያለው ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋልና ከፍጥረት አስቀድሞ #በኩር ነው። ሁሉ በእርሱ ለእርሱ ተፈጥረዋል።" ብሎ የዘመናት ፈጣሪ ከዘመን አስቀድሞ የነበረ አምላክ መሆኑን መሰከረ። ቆላ 1:15 ጌታ በወንጌል ዓለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር የነበረ መሆኑን ሲናገር እንዲህ አለ። "አባት ሆይ ዓለም ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር አንተ በራስህ ዘንድ አክብረኝ።" አለ። ዮሐ 17:5 ይህ የባሕርይ ገዥ ከዕለት ከዓመት ከዘመናት አስቀድሞ የነበረ አምላክ ልዑል እግዚአብሔር የሰዎችን ልደት ዛሬ ተወለደ ተባለ። እንዴት የሚደንቅ እንዴትስ የሚረቅ ምሥጢር ነው??? ሥጋ ያልነበረ በመለኮቱ ጥንት ያልነበረው እርሱ ጥንት ያለውን ሥጋ ስለምን ተዋሐደ? አይታይ የነበረው አምላክ የሚታይ ሥጋን ተዋሕዶ ስለምን ታየ? ስለምንስ ተዳሰሰ? በባሕርይው የማይወሰንና ሰማይ ዙፋኑ ምድር የእግሩ መረገጫ የሆነ አምላክ ስለምን በድንግል ማኅጸን አደረ? የማይሰጡት ቸር የማያበድሩት ባለጠጋ ሲሆን ስለምን በከብቶች በረት ተጣለ? ሰማይን በደመና የሚሸፍን በከዋክብት የሚያስጌጥ እርሱ ስለምን በጨርቅ ተጠቀለለ? ለዚህ ሁሉ መልሱ ሰው ወዳጅ የሆነ እግዚአብሔር የሰው ልጅን ፍጹም ቢያፈቅረው አይደለምን? ሰው ሰውን ቢወድ ነቅ ፈልጎ ምክንያት አበጅቶ ነው። እግዚአብሔር ግን ሰውን የወደደው እንዴት ነው ቢሉ እንዲሁ ያለምክንያት ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ነው። እንደውም መወደድ የሚገባን ሆነን ሳለን እንኳን አይደለም። ስንጠላው ወደደን ስናምጽና ስንርቀው ቀረበን ስንበተን ሰበሰን ጠላቶቹ ሳለን ነፍሱን ስለኛ ቤዛ ሰጥቶ ታረቀን። ዮሐ 3:16 ሮሜ 5:10 የነገሥታት ንጉስ በትሕትና ከሰማይ ከመንበሩ ወርዶ ፍቅሩን ከገለጸልን እኛማ ምን ያህል ልንዋረድ ምን ያህልስ ልንዋደድ ይገባል? ይቆየን። መልካም የልደት በዓል ይሁንልን። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube https://www.youtube.com/@eotc-gssu 👉 Facebook https://www.facebook.com/gssu.eotc 👉 Telegram https://t.me/eotcgssu21 👉 Tiktok https://www.tiktok.com/@eotc_gssu 👉  Website https://eotc-gssu.org/a/

እንኳን ለእመቤታችን ወደ መቅደስ የገባችበ በዓል (በዓታ ለማርያም) በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት
እንኳን ለእመቤታችን ወደ መቅደስ የገባችበ በዓል (በዓታ ለማርያም) በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

ጽዮን ማርያም እንኳን አደረሳችሁ! “እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና፥ ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና፥ እንዲህ ብሎ፦ ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት፤ መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ።” መዝ 13
ጽዮን ማርያም እንኳን አደረሳችሁ! “እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና፥ ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና፥ እንዲህ ብሎ፦ ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት፤ መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ።” መዝ 131፡13-14 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

ቅዱስ ሚካኤል ሚዛን ይዞ መሣሉ፥ በፍርድ ቀን ሱታፌ እንዳለው ያስገነዝበናል። ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ዘገበው፥ ጌታችን ዳግመኛ የሚመጣው ከቅዱሳን መላእክት ጋር ነው፦ ማቴ ፲፮፥፳፯ “የሰው ልጅ ከመላእክቱ ጋር በአባቱ ክብር ይመጣ ዘንድ አለውና፤ ያን ጊዜም ለሁሉ እንደ ሥራው ያስረክበዋል።” እንዲል፡፡ በኢትዮጵያውያን ሊቃውንት አተረጓጐም መሠረት “መጽሐፍ ስም ካልጠራ ማብዛት ልማዱ ነው” እናም እዚህ ጋር እንደ ሰማይ ከዋክብት እንደ ምድር አሸዋ የበዙትን ቅዱሳን መላእክትን ብቻ ለመጥቀስ ብቻ ሳይሆን አለቃቸውን ቅዱስ ሚካኤልን ለማውሳትም ጭምር ነው። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ይህን የሚደግፍ ነገር ጽፎልናል፦ ፩ኛ ተሰ ፬፥፲፮ “ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክት አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና” በእርግጥም አለቃውን ትቶ ስለ ጭፍራው ብቻ መናገር ግር የሚያሰኝ ነገር ነው። በዘመን ፍጻሜ ስለሚከሰተው ነገር ራእይ የተመለከተው ነቢዩ ዳንኤልም ቅዱስ ሚካኤል በዚህ ወቅት ስለሚያደርገው ተግባር ፍንጭ ሰጥቶናል፡ “በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል” (ዳን ፲፪፥፩) እነዚህን ሁሉ ማስረጃዎች ግልጽ በሆነ ቋንቋ የሚያረጋግጥ ቃል በድርሳነ ሚካኤል ውስጥ ተጽፎ የምናገኝ ሲሆን ቃሉም፦ “ወለጻድቃንሰ ውሉደ ጥምቀት እለ የአምኑ ፍጹመ ትንሣኤ ሙታን ያበውኦሙ ውስተ ገነት ወኀበ ክርስቶስ ወያዓርጎሙ ኀበ አብ ወይትፌሣሕ በእንቲአሆሙ ወበእንተ ዘወሀቦ ሢመተ ለሚካኤል ሊቀ መላእክት ከመ ይፍርድ ላዕለ ሕያዋን ወሙታን” (ትንሣኤ ሙታንን የሚያምኑ በጥምቀት የተወለዱ ጻድቃንን ግን ወደ ገነት ያስገባቸዋል፤ አብም ልጁ ክርስቶስ ወዳለበት ያሳርጋቸዋል፤ ስለ እነርሱ እና ለቅዱስ ሚካኤል በሕያዋን እና በሙታን ላይ ይፈርድ ዘንድ ስለሰጠው ሹመት ደስ ይለዋል፡፡) ይህም የቅዱስ ሚካኤልን ፈራጀነት የሚገልጽ ነው፡፡ #2. “ሰላም ለመልክዕከ ዘኢይጤየቅ ለዓይንነ ኆኅያቲሁ ርብዓ በከመ ርኢነ” (በአራቱ መዓርገ ኆኅት እንደተመለከትነው በዓይን ታይቶ ለማይመረመር መልክህ ሰላም እላለሁ።) አራቱ መዓርገ ኆኅት የት ነው? መች ነው የተመለከትነው? አራቱ ኆኅያት የተባሉት <መልክዕ> የሚለው ቃል ፊደሎች ብዛት ናቸው። ኆኅያት ማለት የፊደል ደጅ ማለት ነውና። ከዚህ አተረጓጐም ጋር የሚመሳሰል መልክዕ በማኅሌተ ጽጌ ላይ ተጽፎ ይገኛል። “ዝንቱ መስቀል መንበረ ነበልባል ዘኪሩቤል ቢጽ፤ አምሳለ ስምኪ ድንግል ርቡዐ ኆኅያት ወገጽ” (ድንግል ሆይ፥ የኪሩቤል ቢጤ፣ የነበልባል ዙፋን የሆነው ይህ መስቀል እንደ ስምሽ አራት ፊደል እና ገጽ ነው) [ማለትም <ማርያም> እና <መስቀል> የሚሉት ስሞች አራት ፊደል ናቸው] “እንደ ተመለከትነው” ማለት ደግሞ እንደምናነበው፣ እንደምናየው ማለት ነው። ይህንን መልክዕ በተለየ ሁኔታ ስንገልጸው “እንደምናየው ኆኅያቱ (ፊደሎቹ) አራት ለሆኑ፣ በዓይንናችን ለማይመረመረው መልክዕህ ሰላም እላለሁ” ይሆናል። #3. ቅዱስ ሚካኤል ለምን ክነፈ ርግብ ይባላል? ይህንን የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤልን ተራዳኢነት ለመግለጽ ቤተክርስቲያን ‹‹ክነፈ ርግብ›› ብላ ትጠራዋለች፡፡ የድርሳኑ ፀሐፊ በተራዳኢነቱ ነፍሳትን በክንፎቹ ከሲዖል እሳት ዲን እንዲያወጣ፦ “ወውእቱ ሚካኤል ይጸውሮ በክነፊሁ ብሩሃት ወያዐድዎ ባሕረ እሳት ወያበውኦ ውስተ መንግሥተ ሰማያት ወኀበ ኩሉ መዝገበ ብርሃን” (እሱ ቅዱስ ሚካኤል በብርሃን ክንፎቹ ተሸክሞ ባሕረ እሳትን አሻግሮ ወደ መንግሥተ ሰማያትና የብርሃን ድንኳን ወዳለበት ያገባዋል) በማለት ይናገራል፡፡ መልአኩ በ<ክንፉ ይበራል> ሲባልም ለዓለም መዳን የሚፋጠን መሆኑን ያሳያል። “ይሠርር ለመድኃኒተ ኵሉ ዓለም በክልኤ ክንፍ” (ለዓለም ሁሉ መዳን በሁለት ክንፍ ይበራል) እንዲል፡፡ #4. “....ቀዊመከ አንተ በምሥዋዓ ሰማይ ሳብዕ...” (....በሰባተኛው ሰማይ የመሠዊያ አዳራሽ ቆመህ...) የተባለው ምንድን ነው? የትኛው ነው? እዚህ ጋር መሠዊያ የተባለው ሰባተኛው ሰማይ ጽርሓ አርያም ነው። ቅዱስ ሚካኤል በኅዳር ፲፪ ቀን ወደዚህ ሰማይ ገብቶ ለኃጢአተኞች ምሕረትን እየለመነ ይሰግዳል። ‹‹ወእምዝ ይበውእ ኀበ መንጦላዕቱ ለአብ ማር ሚካኤል ሊቀ መላእክት ወይሰግድ ታሕተ መንበሩ ለአብ በይእቲ ዕለት በእንተ ምሕረቱ ሰማያዊት ወምድራዊት›› (ከዚህ በኋላ ቅዱስ ሚካኤል ወደ አብ መጋረጃ ውስጥ ይገባል በዚች ዕለት ምድራዊትና ሰማያዊት ስለሆነች ምሕረቱም ከመንበሩ በታች ይሰግዳል) እንዲል። ስግደቱም የሚቀርበው ኃጢአተኞች ሥርየትን እስኪያገኙ ድረስ ነው። “ይሰግድ በብረኪሁ እስከ ይመጽእ ሥርየት ለኃጥአን” (ለኃጢአተኞች ሥርየት እስከሚመጣ ድረስ በጉልበቱ ይሰግዳል) እንዲል፡፡ እነዚህ የመልአኩ ክንፎች ባለ መልክኡ ‹‹ሰላም እብል ለአክናፊከ ስፉሐት ምስካቤ ኵሉ ፍጥረት …..›› (ሚካኤል ሆይ የፍጥረታት ሁሉ መጠለያ ለሆኑ አክናፎችህ ሰላም እላለሁ፡፡) እንዳለው የፍጥረታት መጠለያ ብቻ ሳይሆኑ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የክብሩ መገለጫዎችም ጭምር ናቸው፡፡ ይህንንም በአባታችን ፍስሐ ፅዮን( አቡነ ተክለ ሃይማኖት) ታሪክ ውስጥ የምናየው ነው፡፡አባታችን ገና ሕፃን ሳሉ ዲቁናን ተቀብለው በፍቅርና በንጽሕና በማገልገል ጎለመሱ፡፡ ባደጉም ጊዜ ለአደን ወደ ዱር ሲሄዱ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጎልማሳ ሰው አምሳል ሆኖ በመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ክንፍ ላይ ተገልጦ አራዊትን ሳይሆን የኃጢአተኞችን ነፍስ ወደ ሕይወት የሚያጠምድ እንደሚሆን ነግሮታል፡፡ ‹‹ወበ ጊዜ ቀትር አስተርአዮ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ሎቱ ስብሐት በዲበ ክንፉ ለቅዱስ ሚካኤል በአምሳለ ወሬዛ ዘሠናይ ላህዩ›› እንዲል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! #1. ቅዱስ ሚካኤል ሥዕሉ ላይ ሚዛን ይዞ የሚታየው ለምንድን ነው? ከዚህ ጋር በተያያዘ በአንዳንድ የመልአኩ ሥዕላት ላይ መልአኩ ሚዛን ይዞ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! #1. ቅዱስ ሚካኤል ሥዕሉ ላይ ሚዛን ይዞ የሚታየው ለምንድን ነው? ከዚህ ጋር በተያያዘ በአንዳንድ የመልአኩ ሥዕላት ላይ መልአኩ ሚዛን ይዞ ተስሎ እናገኛለን፡፡ ይህም የመልአኩን ፈራጀነት የሚገልፅ ነው፡፡ ሚዛን በቅዱሳን መጻሕፍት የፍትህ ወይም የፍርድ ምልክት ነው፡፡ ምንም እንኳን የቴክኖሎጂ አብዮቱ፥ የዘመኑን የክብደት መለኪያ መሣሪያዎችን ይዞልን ቢመጣም፤ በግብይት ሥርዓት የሚገኙ ነጋዴዎችና ደንበኞች የተለያዩ ቁሶችን በሚዛን ግራና ቀኝ ላይ በማስቀመጥ የትኛው በክብደት እንደሚበልጥ ለመለየት ሲጠቀሙበት እናስተውላለን። የፍርድ ጉዳይም በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በዚህ ምሳሌነት ቀርቦ እንመለከታለን። ለምሳሌ ያህል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በተሰጣት ቃልኪዳን የዳነው የ<በላዔ ሰብእ> ወይም ስምዖን ታሪክ ማሳያ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስም ጥበበኛው ሰሎሞን የእግዚአብሔርን ፍርድ በሚዛን ምሳሌነት ይናገራል፦ ምሳ ፲፮፥፲፩ “እውነተኛ ሚዛንና መመዘኛ የእግዚአብሔር ናቸው፤ የከረጢት መመዘኛዎች ሁሉ የእርሱ ሥራ ናቸው።” እንዲል።

"#ቤተ_ክርስቲያን_በዚህ_መልክ አስተምራ ያስመረቀቻችሁ በሌላኛው የሕይወት ገጽ የተማራችሁትን የዓለማዊ ትምህርትና እውቀት እንድትተው ሳይሆን ከመንፈሳዊ  ትምህርቱ ጋር  አጣጥማችሁና አቀናጅታትሁ ቤተ ክርስቲያን እንድታተርፍባችሁ ነው።" ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በሥርዓተ ትምህርት መሠረት ያስተማራቸው 11,885 ተማሪዎች ጥቅምት 30/2018 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ ለ5ኛ ጊዜ አስመርቋል። መርሐ ግብሩ ሕያውን የእግዚአብሔር ቃልና ግሩም ግብሩን  እንዲሁም ወርኃ ጽጌን የሚገልጹ ዝማሬዎች ፣ ኪነ ጥበብ፣ ሥነ ጽሑፍ እና ስብከት እንዲሁም በብፁዓን አባቶች ትምህርተ ወንጌል ተሰጥቶበታል።                    በዕለቱ የተመረቁ ተማሪዎች ከ164 ገዳማት እና አድባራት የተውጣጡ የሀገረ ስብከቱን ምዘና ወስደው ወደ ቀጣይ ክፍል የተዘዋወሩ 11,885 የሰንበት ት/ቤት የ4ኛ፣ የ8ኛ እና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች  መሆናቸውን ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶችን አድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሰቢ ገልጸዋል። ተማሪዎቹ በ8 የትምህርት ዘርፎች የተከፋፈለውን  ሥርዐተ ትምህርት መሠረት በማድረግ በየገዳማቱና አድባራቱ ባሉ ሰንበት ት/ቤቶች ቅዳሜና እሑድ  ትምርታቸውን የተከታተሉ መሆናቸውን አስታውሰዋል። አክውለም "በዚሁ ሁሉ የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ  የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት  ድጋፉና የኔባይነቱ በእጅጉ የሚያስመሰግን ሲሆን የዛሬውን የምርቃት መርሐ ግብር አስፈላጊ በሆነው በጀት በማገዝና የሥርዐተ ትምህርቱ መጻሕፍትን አጥቢያዎች ለየሰንበት ትምህርት ቤቱ እንዲገዙ ከማድረግና የምዝና ፈተና በሚሰጥበትም ወቅት ከብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ጀምሮ በየቦታው በመዘዋወር ምልክታና ክትትል በማድረገቸው በእጅጉ ኮርተናል በልጅነት ልብም እናመሰግናለን" ብለዋል። በመርሐ ግብሩ  ለ160 ሰንበት ትምህርት ቤቶችና  ከፍተኛ ነጥብ ላስመዘገቡ ተመራቂዎች፣  ሰንበት ት/ቤቶች እና ክፍለ ከተሞች ከአባቶች እጅ ቡራኬና ሽልማት ሲቀበሉ የጀሞ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት የዋንጫ ተሸላሚ። በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ የሆኑት መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወ/ትንሣኤ ተመራቂ ተማሪዎቹ ትምህርቱን በአግባቡ እንዲከታተሉ ዘወትር በመማርና በማንበብ እንዲተጉና ለቤተ ክርስቲያን ጠበቃ ሆነው እንዲቆሙ አሳስበዋል። በምርቃት መርሐ ግብሩ አባታዊ መልእክት  ያስተላለፉት  ብፁዕ አቁነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና የሀዲያ ስልጤ አህገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባዩት መልካም ቤተ ክርስቲያናዊ ትልቅ ተግባር  ተደንቀው የእግዚአብሔር መንግሥት ወንጌል በትውልድ እንዲጸና የተቀበሉትንም የእምነትና የእውቀት ቤተ ክርስቲያናዊ  አደራቸውን እንዲጠብቁ ተመራቂዎችን አሳስበዋል። ብፁዕነታቸው"ቤተ ክርስቲያን በዚህ መልክ አስተምራ ያስመረቀቻችሁ በሌላኛው የሕይወት ገጽ የተማራችሁትን የዓለማዊ ትምህርትና እውቀት እንድትተው ሳይሆን ከመንፈሳዊ  ትምህርቱ ጋር  አጣጥማችሁና አቀናጅታትሁ ቤተ ክርስቲያን እንድታተርፍባችሁ ነው።" ብለዋል። ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ "በዚህ ሁሉ አገልግሎት ለሚታይ ቤተ ክርስቲያናዊ ስኬት በማድረስ ረገድ  ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የመንበረ ፓትርያክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ የበላይ ሊቀ ጳጳስ ሊመሰግኑ ይገባል የሀገረ ስብከቱ ዋና ክፍልና የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት መሪዎችና  አስተባባሪዎችንም በእጅጉ እናመስግናልን" ብለዋል። የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ  መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ  "አባቶቻችን የተረፋቸውን ሳይሆን ያላቸውን ሳይቀር ሳይሰስቱ ሰጥተው ያስረከቡንን ቤተ ክርስቲያን በእምነትና በእውቀት በመታዘዝ የተማርነውን ለሕይወት ዋጋ ማድረግ ይገባለናል" በማለት ለተመራቂዎች መልእክት አስተላላፈዋል። በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና የሀድያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ቀሌምጦስ የመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት  ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ከፍተኛ የሥራ ሓላፊዎችና ሠራተኞች፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ሓላፊዎችና ሠራተኞች፣ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ሊቃነ መናብርት፣ የሰንበት ት/ቤት አመራሮች፣  መዘምራንና ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ እንግዶች ተገኝቷል። ዘገባው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

በነገው ዕለት በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ የ4ኛ , የ8ኛ እና የ10ኛ ክፍል ከ11_000 በላይ ተማሪዎች የሚመረቁ ሲሆን በዚሁ መርሐ ግብር ላይ ከ1ኛ እስከ 7ኛ ክፍል የሰንበት ት/ቤቶች መማሪያ
በነገው ዕለት በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ   የ4ኛ , የ8ኛ እና የ10ኛ ክፍል ከ11_000 በላይ ተማሪዎች የሚመረቁ ሲሆን በዚሁ መርሐ ግብር ላይ ከ1ኛ እስከ 7ኛ ክፍል የሰንበት ት/ቤቶች መማሪያ መጻሕፍት በሽያጭ ለምዕመናን እና ለወላጆች ቀርበዋል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

መድኃኔዓለም እንኳን አደረሳችሁ! "በእውነት ክርስቶስ የዓለም መድኃኒት እንደ ሆነ እናውቃለን!" ዮሐ ፬፡ ፵፪ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትም
መድኃኔዓለም እንኳን አደረሳችሁ! "በእውነት ክርስቶስ የዓለም መድኃኒት እንደ ሆነ እናውቃለን!" ዮሐ ፬፡ ፵፪ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

🎓🎓🎓 የተማሪዎች ምርቃት #4_ቀን_ቀረው 🎓🎓🎓 " ኅየንተ አበውኪ ተወልዱ ለኪ ደቂቅ " {"በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ"} (መዝ 44:16) በ2017 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤቶች አንድነ
🎓🎓🎓 የተማሪዎች ምርቃት #4_ቀን_ቀረው  🎓🎓🎓 " ኅየንተ አበውኪ ተወልዱ ለኪ ደቂቅ " {"በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ"} (መዝ 44:16)      በ2017 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ትምህርታቸውን  ተከታትለው  ያጠናቀቁ እና በሀገረ ስብከት በብሔራዊ ደረጃ ምዘና ተደርጎላቸው ያለፉ  #የ4ኛ , #የ8ኛ እና #የ10ኛ ክፍል #ከ11_000 በላይ ተማሪዎች ብጹዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ፤ አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ፤ የተመራቂ ተማሪ ወላጆች እንዲሁም ምዕመናን/ት በተገኙበት የምርቃት መርሐ ግብር ይከናወናል!!! 🎓🗓 #ጥቅምት_30_2018_ዓ_ም      🎓 🕰 #ከቀኑ_5_30_ጀምሮ            🎓  🏢 #በሚሊኒየም_አዳራሽ አይቀርም!!! ኑ ተማሪዎቻችን በጋራ እንመርቅ!!!   የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት 🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓

የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም 2ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አከናወነ።  የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም 2ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤን በሀገረ ስብከቱ የመሰብሰቢያ  አዳራሽ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ፣  የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሳሕል  ቀሲስ ነጋሽ ሀብተወልድ፣ የሀገረ ስብከቱ የስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ መጋቢ ሐዲስ አባ ኃይለ ገብርኤል ተስፋ፣ የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ ሊቀ ካህናት  ቀሲስ ሻውል ታዬ ፣ የሀገረ ስብከቱ እና ወረዳዎች አንድነት የሥራ አመራሮች ፣ ሰባኪያነ ወንጌል እና ተጋባዥ  እንግዶች  በተገኙበት ጥቅምት 23/2018 ተካሂዷል። ጠቅላላ ጉባኤውም በጠዋት እና ከሰዓት መርሐ ግብር የተካሄደ ሲሆን የጠዋቱ መርሐ ግብር  በብፁዕ  አቡነ ጎርጎርዮስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ጸሎተ ቡራኬ የተከፈተ ሲሆን የናዝሬት ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፈለገ  ሰማዕት ሰንበት ትምህርት ቤት  አባላት ዝማሬ አቅርበዋል። ብፁዕነታቸው ለጠቅላላ ጉባኤው ተሳታፊዎች አባታዊ መመሪያ በመስጠት ወጣቱ ዘመኑን ዋጀቶ እንዲያገለግል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ የአንድነቱ የ2017 የሥራ ሪፓርት  በአንድነቱ ጸሐፊ ወጣት ከተማ ደረጀ  በኩል የቀረበ ሲሆን ከጠቅላላ ጉባኤውም በሪፓርቱ  ዙሪያ ለተነሱ  ጥያቄዎች  ከሥራ አመራሩ ግብረ መልስ ተሰጥቶበት ሪፖርቱ   በጠቅላላ ጉባኤው ጸድቋል። ከዚህ በመቀጠልም ከሀገረ ስብከቱ ከሚገኙ የወረዳዎች የተሻለ አፈፃፀም ያሳየውን የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ  የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ያለውን  ተሞክሮ በተወካዩ በኩል ለጠቅላላ ጉባኤው አቅርቧል። በከሰዓቱ መርሐ ግብር ለጠቅላላ ጉባኤ አባላት  ስድስት የመወያያ አጀንዳዎች ተሰጥቶ በቡድን  በመሆን እንዲወያዩ ተደርጓል። የውይይቱ ሪፓርት ማጠቃለያም በጠቅላላ ጉባኤው ውሳኔዎች ውስጥ ተካተዋል፡፡ በመቀጠል በአንድነቱ ተቀዳሚ ም/ሰብሳቢ  መ/ር ዓለምአንተ አበጀ የ2018 ዓ.ም ስልታው ዕቅድ ቀርቦ በቀረበው ዕቅድ ላይ ውይይት ተደርጎ  በጠቅላላ ጉባኤው ፀድቋል። በማስከተል የሀገረ ስብከቱ አንድነት የጎደሉ የሥራ አመራር እና የሥራ አስፈጻሚ እጩ ቀርበው በጠቅላላ ጉባኤው ፀድቀዋል። በዕለቱ  የቀድሞው  የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ማደራጃ ክፍል ሐላፊ ለነበሩት ለመጋቤ ሐዲስ ቆሞስ አባ  ኃይለ ገብርኤል ተስፋ የሽኝት እና አሁን የማደራጃው ሐላፊ በመሆን እያገለገሉ ላሉት ለሊቀ ካህናት  ቀሲስ ሻዉል ታዬ የእንኳን ደህና መጣችሁ  የስጦታ መርሐ ግብር  ከአንድነቱ ሥራ አመራር በብፁዕነታቸው  አማካኝነት   ተከናውኗል። በመጨረሻም የጠቅላላ  ጉባኤው ቃለ ጉባኤ እና  የተወሰኑ ውሳኔዎች ተነቦ በጋራ ድምፅ ጸድቆ የማጠቃለያ ሀሳብ በማደራጃው ሐላፊ ሊቀ ካህናት ቀ/ሻውል ታዬ የቀረበ ቀርቦ በሀገረ ስብከቱ  ዋና ሥራ አስኪያጅ  የማሳረጊያ መልእክት አቅርበው አባታዊ መመሪያ ሰጥተው መርሐ ግብሩ ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡ መረጃው የሀገረ ስብከቱ አንድነት ሚዲያ እና ህዝብ ግንኙነት ክፍል ነው፡፡ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website