Diinii kee Anaakara (Md Ali)
Открыть в Telegram
دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol
Больше1 612
Подписчики
+324 часа
+117 дней
+1830 день
Архив постов
وَقَالُوا۟ ٱتَّخَذَ ٱلرَّحۡمَـٰنُ وَلَدࣰا * لَّقَدۡ جِئۡتُمۡ شَیۡـًٔا إِدࣰّا * تَكَادُ ٱلسَّمَـٰوَ ٰتُ یَتَفَطَّرۡنَ مِنۡهُ وَتَنشَقُّ ٱلۡأَرۡضُ وَتَخِرُّ ٱلۡجِبَالُ هَدًّا * أَن دَعَوۡا۟ لِلرَّحۡمَـٰنِ وَلَدࣰا * وَمَا یَنۢبَغِی لِلرَّحۡمَـٰنِ أَن یَتَّخِذَ وَلَدًا * إِن كُلُّ مَن فِی ٱلسَّمَـٰوَ ٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ إِلَّاۤ ءَاتِی ٱلرَّحۡمَـٰنِ عَبۡدࣰا * لَّقَدۡ أَحۡصَىٰهُمۡ وَعَدَّهُمۡ عَدࣰّا * وَكُلُّهُمۡ ءَاتِیهِ یَوۡمَ ٱلۡقِیَـٰمَةِ فَرۡدًا
«አልረሕማንም ልጅን ያዘ (ወለደ)» አሉ፡፡ ከባድ መጥፎን ነገር በእርግጥ አመጣችሁ፡፡ በእርሱ (በንግግራቸው ምክንያት) ሰማያት ሊቀደዱ፣ ምድርም ልትሰነጠቅ፣ ጋራዎችም ተንደው ሊወድቁ ይቃረባሉ፡፡ ለአልረሕማን ልጅ አለው ስለአሉ፡፡ ለአልረሕማን ልጅን መያዝ አይገባውም!! በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ (በትንሣኤ ቀን) ለአልራሕማን ባሪያ ኾነው የሚመጡ እንጂ ሌላ አይደሉም
Surah Maryam 88 - 95
@abujunaidposts
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
መልዕክት ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች
=====================
በገና እና በመሳሰሉት የከሀዲያን በዓላት ላይ የሚዘጋጀውን ልዩ የካፌ ምግብ መብላትን በተመለከተ:
1:
እንደ አጠቃላይ በነርሱ በዓል የተዘጋጀን ምግብ መብላት አይቻልም።
2:
ነገር ግን ካፌ ተጠቃሚ የሆናችሁ ሁሉ ማድረግ ያለባችሁ ነገር:
የተለያዩ አማራጮች ካላችሁ አትብሉ።
ለምሳሌ: ውጭ ላይ ቤተሰብና ዘመድ ካላችሁ ከነርሱ ዘንድ በመሄድ አሳልፉ፣።
ውጭ ላይ ገዝታችሁ መጠቀም የምትችሉ ከሆነም አትብሉ።
እነዚህና መሰል አማራጮች ከሌሏችሁ ግን፣
አላህ ከምንችለው በላይ አስገዳጅ ያልሆነ ውስጥ አዋቂ አምላክ ነውና
ካፌ ብትጠቀሙ ችግር የለውም።
" ክርስቲያን ወገኖችንም ሆነ የካፌ ሰራተኞችን ፣
<< እንኳን አደረሳችሁ! >> ማለት አይቻልም።
" እንኳን አደረሳችሁ!" ሲሉንም መመለስ የለብንም።
የካፌ ምግቡን በተመለከተ ሸይኽ ባሲጢይን አላህ ይዘንላቸውና በህይዎት ሳሉ እኛ የግቢ ተማሪ በነበርን ጊዜ ጠይቀናቸው ይህ ይዘት ያለው መልስ ነበር የመለሱልን።
በተረፈ አላህ ይበልጥ አዋቂ ነው።
||
t.me/MuradTadesse
Repost from 𝐃𝐈𝐈𝐍𝐈 𝐆𝐎𝐎𝐑𝐈 𝐌𝐄𝐃𝐈𝐀
تلاوة عطرة للقارئ أبو أيمن محمد محمود العفري حفظه الله تعالى ورعاه سورة البقرة من 190 - 195
Maxaqalle xongolooy cafizahû lah
------------------❀❀❀❀------------------
𝐃𝐈𝐈𝐍𝐈 𝐆𝐎𝐎𝐑𝐈 𝐌𝐄𝐃𝐈𝐀
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዩች ጠቅላይ ምክር ቤት የዑለማ ጉባዔ ጽ/ቤት፤ ከዛሬ እሁድ ታሕሳስ 27 ቀን 2017 ጀምሮ እስከ ጥር 2 ቀን 2017 ድረስ የሚቆይ "ልዩ የሆነ ወደ አላህ የመመለስና መልካም ሥራዎች እየሰሩ ለሀገር ሰላምና ደህንነት ዱዓ የማድረግ ቀን ተግባራዊ እንዲደረግ" ጥሪ አቅርቧል።
የዑለማ ጉባዔ ጽ/ቤቱ ለጠቅላላው ሕዝበ ሙስሊም ባስተላለፈው መልዕክት፤ "ሀገራችን ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ሰው ሰራሽን በተፈጥሮ ችግሮች ምክንቶች እየታመሰች ትገኛለች።" ብሏል።
"ለዚህም ዋና ምክንያቱ የሰው ልጆች የርስ በስርስ ፍቅር መጥፋት፤ ጥላቻ መስፋፋት የእርስ በርስ መገዳደል መበራከትና የሰው ልጅ ነብስ ከምን ጊዜውም በላይ ርካሽ የሆነበትና በቀላሉ ሕይወት የተቀጠፈ የሚገኝበት ደረጃ ላይ ደርሰናል፡፡" ሲልም ገልጿል።
"ይህ በእንዲህ እንዳለ ከጥፋቶቻችንና ከስህተቶቻችን ለመመለስ ባለመቻላችን ምክንያት ተለያዩ የተፈጥሮ አደጋዎች በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በመከሰት ላይ ይገኛሉ፡፡" ያለው ጽ/ቤቱ፤ ለአብነት ያህልም ባለፈው ክረምት በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በሲዳማ፤ እንዲሁም በአማራ ክልሎች በተከስተው የመሬት መንሸራተት በርካታ ሰዎች መሞታቸውና ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን አንስቷል።
በአሁኑ ወቅት ደግሞ የመሬት መንቀጥቀጥ በተደጋጋሚ በሀገሪቱ እየተከሰተ እንደሚገኝ በመግለጽ፤ "ይህ ሁሉ ክስተት እኛ የሰው ልጆች በምንሰራቸው ወንጀሎች ሳቢያ የሚመጡ ክስተቶች በመሆናችው ነው" ብሏል።
በዚህም ምክንያት ከላይ በተጠቀሱት ቀናቶ ለሀገር ሰላምና ደህንነት ዱዓ የማድረግ ቀን ተግባራዊ እንዲደረግ የኡለማ ጉባዔ ጽ/ቤት ለመላው ሕዝበ-ሙስሊም የሚከተሉትን መልእክቶች አስተላልፏል፡፡
በዚህ መሰረት ፦
1. ሕዝበ-ሙስሊሙ በአጠቃላይ ተውበት በማድገረግ ወደ አላህ እንዲመለስ
2. ሁላችንም እርስ በርስ ይቅርታ እንድንባባል፤
3. ለተቸገሩትና ረዳት ለሌላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ሶደቃ ( ምጽዋት) መስጠት
4. በሀገሪቱ ውስጥ በሚገኙ አጠቃላይ መስጂዶች በየአምስት አውቃት ሶላቶች ላይ ቁነት እንዲደረግ፤
5. የቀጣዩ ጁሙአ ቀን በሁሉም መስጂዶች የሚደረጉ ኹጥባዎች በዚህ ዙሪያ እንዲሆኑና አጠቃላይ ዱዓ እንዲደረግ ጽ/ቤቱ አሳስቧል፡፡
✍Wasu Mohammed
Repost from Wasu Mohammed - ዋሱ መሀመድ
+1
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዩች ጠቅላይ ምክር ቤት የዑለማ ጉባዔ ጽ/ቤት፤ ከዛሬ እሁድ ታሕሳስ 27 ቀን 2017 ጀምሮ እስከ ጥር 2 ቀን 2017 ድረስ የሚቆይ "ልዩ የሆነ ወደ አላህ የመመለስና መልካም ሥራዎች እየሰሩ ለሀገር ሰላምና ደህንነት ዱዓ የማድረግ ቀን ተግባራዊ እንዲደረግ" ጥሪ አቅርቧል።
የዑለማ ጉባዔ ጽ/ቤቱ ለጠቅላላው ሕዝበ ሙስሊም ባስተላለፈው መልዕክት፤ "ሀገራችን ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ሰው ሰራሽን በተፈጥሮ ችግሮች ምክንቶች እየታመሰች ትገኛለች።" ብሏል።
"ለዚህም ዋና ምክንያቱ የሰው ልጆች የርስ በስርስ ፍቅር መጥፋት፤ ጥላቻ መስፋፋት የእርስ በርስ መገዳደል መበራከትና የሰው ልጅ ነብስ ከምን ጊዜውም በላይ ርካሽ የሆነበትና በቀላሉ ሕይወት የተቀጠፈ የሚገኝበት ደረጃ ላይ ደርሰናል፡፡" ሲልም ገልጿል።
"ይህ በእንዲህ እንዳለ ከጥፋቶቻችንና ከስህተቶቻችን ለመመለስ ባለመቻላችን ምክንያት ተለያዩ የተፈጥሮ አደጋዎች በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በመከሰት ላይ ይገኛሉ፡፡" ያለው ጽ/ቤቱ፤ ለአብነት ያህልም ባለፈው ክረምት በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በሲዳማ፤ እንዲሁም በአማራ ክልሎች በተከስተው የመሬት መንሸራተት በርካታ ሰዎች መሞታቸውና ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን አንስቷል።
በአሁኑ ወቅት ደግሞ የመሬት መንቀጥቀጥ በተደጋጋሚ በሀገሪቱ እየተከሰተ እንደሚገኝ በመግለጽ፤ "ይህ ሁሉ ክስተት እኛ የሰው ልጆች በምንሰራቸው ወንጀሎች ሳቢያ የሚመጡ ክስተቶች በመሆናችው ነው" ብሏል።
በዚህም ምክንያት ከላይ በተጠቀሱት ቀናቶ ለሀገር ሰላምና ደህንነት ዱዓ የማድረግ ቀን ተግባራዊ እንዲደረግ የኡለማ ጉባዔ ጽ/ቤት ለመላው ሕዝበ-ሙስሊም የሚከተሉትን መልእክቶች አስተላልፏል፡፡
በዚህ መሰረት ፦
1. ሕዝበ-ሙስሊሙ በአጠቃላይ ተውበት በማድገረግ ወደ አላህ እንዲመለስ
2. ሁላችንም እርስ በርስ ይቅርታ እንድንባባል፤
3. ለተቸገሩትና ረዳት ለሌላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ሶደቃ ( ምጽዋት) መስጠት
4. በሀገሪቱ ውስጥ በሚገኙ አጠቃላይ መስጂዶች በየአምስት አውቃት ሶላቶች ላይ ቁነት እንዲደረግ፤
5. የቀጣዩ ጁሙአ ቀን በሁሉም መስጂዶች የሚደረጉ ኹጥባዎች በዚህ ዙሪያ እንዲሆኑና አጠቃላይ ዱዓ እንዲደረግ ጽ/ቤቱ አሳስቧል፡፡
ቤተሰብ❤ በቅንነት ሰብስክራይብ በማድረግ ተባበሩ 👇
https://www.youtube.com/channel/UCrdWHrcXNEhMfbp1ucgxd1g
አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
*የዱንያ ነገር!!*
~
ዐሊይ ኢብኑል ሀይሠም እንዲህ ይላሉ:–
"አምሳያ ያላየሁለት የዘመን መገለባበጥ፣ የጊዜ መለዋወጥ አይቻለሁ።
★ የአልፈድል ብኑ ረቢዕ ንብረት በአንድ ሺህ ግመል ተጭኖ አይቻለሁ። ሌላ ጊዜ ግን ጠቅላላ ንብረቱ አንዲት ዘንቢል ውስጥ ሆና ተደብቄ አይቻለሁ። በውስጧ መድሃኒቶቹ ተጨምረው።
★ አልሐሰን ብኑ ሰህልን ደግሞ ጠቅላላ ንብረቱ አንዲት ዘንቢል ውስጥ ሆና ተመልክቻለሁ። ከዚያ ግን ንብረቱ በአንድ ሺ ግመል ላይ ተጭኖ አይቼዋለሁ።"
||
ዱንያ እንዲህ ነች። መርጋት የማታውቅ ወላዋይ!!
♣️ ሃያላን ይዋረዳሉ። ደካሞች ይነግሳሉ።
♣️ ሀብታሞች ጎዳና ላይ ይወድቃሉ። ምንዱባን በሰማይ ጠቀስ ህንፃ ይንፈላሰሳሉ።
♣️ ሳር ቅጠሉን የተፀየፈው ጨፍጫፊ አረመኔ አለም ጠባው ከአይጥ ጎሬ ሲያደፍጥ ታየዋለህ። የትላንቱ ተሳዳጅ ተራውን ሲያሳድድ ትመለከታለህ።
® ይሄው ነች ዱንያ!! ብልጭ ብላ ድርግም፣ ቦግ ብላ እልም የምትል። ሁሌ ሳቅ የለም! ሁሌ ድል የለም።
|
♣️ በድር ላይ ለያዥ ለገናዥ ያስቸገሩ፣ ጥጋብ ያስከራቸው ቁረይሾች፣ 70 መኳንንቶቻቸው ትላንት ሲያሳድዷቸው በነበሩ ሶሐቦች ሰይፍ ተበልተው፣ ሌላ 70 ደግሞ በምርኮ አስረክበው የሐዘን ማቅ ለብሰዋል። መካ በዋይታ ተንጣለች።
|
♣️ ኡሑድ ሌላ ቀን ነው። ሌላ ተራ!! አጋሪዎች የፈነደቁበት፣ እነ ሐምዛን፣ እነ ሙስዐብን ጨምሮ ከ70 በላይ ታላላቅ ጀግኖች ወድቀው ሌላ 70 የቆሰሉበት፣ አሳዝኝ ክስተት እውን የሆነበት ቀን። ሶሐቦች አካላቸው በስለት፣ ልባቸው በሐዘን ቢቆስል ጊዜ አላህ እንዲህ ሲል አሳሰባቸው: –
(إِنْ يَمْسَسْكُمْ قَرْحٌ فَقَدْ مَسَّ الْقَوْمَ قَرْحٌ مِثْلُهُ ۚ وَتِلْكَ الْأَيَّامُ نُدَاوِلُهَا بَيْنَ النَّاسَ)
"ቁስል ቢያገኛችሁ ሰዎቹንም መሰሉ ቁስል አግኝቷቸዋል፡፡ እናም እነዚህን ቀናት በሰዎች መካከል (በመልካምና በሌላ) እናቀያይራቸዋለን፡፡" [ኣሉ ዒምራን: 140]
|||
ዱንያ አመሏ ነው። ዛሬም እንዲሁ ናት።
ግን ማነው የሚማረው? ግን ማነው የሚመረምረው? ግን ማነው የዱንያን ከንቱነት ተገንዝቦ ለዘላለም ቤቱ ከልብ የሚጨነቀው?
እስከ መቼ ነው የምናንቀላፋው?
እስከ መቼ ነው የምንዘናጋው?
እስከ መቼ ነው በከንቱ የምንባዝነው?
ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን!
ኢላሂ ልብ ስጠን!
=
የቴሌግራም አድራሻ
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የችግሩ መንስኤ ክፋት ነው። የቅንነት መጥፋት ነው። እንጂ አገሪቱ የጋራ ናት፤ እኩል የመጠቀምም የመወሰንም መብት አላቸው የሚል እምነት ቢኖር ኖሮ ማንም በእብሪት እየተነሳ የራሱን ውሳኔ ባላሳለፈ ነበር። ዋናው ችግር ግን ከላይ ነው። ዋና ወሳኝ ክፍሎች ላይ ቁርጠኝነት ቢኖር ሁሉም ባይሆን እንኳ ብዙ ቦታዎች ችግሩ ይቀረፍ ነበር። ግን ምን ዋጋ አለው? መርፌ ከለገመ ቅቤ አይወጋም።
የጊዜ ጉዳይ እንጂ መብታችን ሳይሸራረፍ የሚከበርበት ጊዜ እንደሚመጣ እናምናለን፣ ኢንሻአላህ። ብቻ ትዝብት ነው ትርፉ። በታሪክ ጥቁር መዝገብ ላይ ስምን ከማኖር በበጎ መታወስ ይሻል ነበር። ዛሬ እያሳለፍነው ያለው ተጨባጭ ትናንት አባቶቻችን ምን አይነት ዘግናኝ ዘመን እንዳሳለፉ የሚጠቁም ነው፡፡ "ለዓለም ምሳሌ የሚሆን መቻቻል ... " የሚለው ፉገራ እንዴት እንደሚያስጠላ!
ሰውየው አብዛኞች ዘንድ የሌለ ሚዛናዊነት ስላሳየን አላህ ሂዳያ ይስጥልን። እናመሰግናለን።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Arbaquuna Cadiis Darsi
TaShricem:
Dr. Mucammad Cuseen Weeqisa.
Arac: Qafar Ra/Logyah Magaalak Icsaan Masjidi.
Cadiis Loowo(8)
"شرح كتاب الأربعين حديثًا"
الشارح: فضيلة الشيخ الدكتور محمد حسين ويعسى
اللغة: العفرية.
المكان: جامع الإحسان، مدينة لوغيا.
الحديث الثامن: (8)
https://t.me/AfarMahaNetwork/937?single
#Iggimâ tû kaloot kee Qilmi leh yan muxxol yabta khutba.
🎙 Khutba lem: Shek Cuseen Acmad Cafizahullaah
⤵️⤵️⤵️
https://t.me/Kassisfaage
Repost from N/a
Yitoobokoy
Axaqalle Giilalat Anuk Eddeey Qibaadak Abiteenim Muxxo Eddele Alsat Anuk Itlen Kee Khameesih Xayyuh(Soomuh) Assaanamak Magarcitina, Inki Ayro Yallih Taagah Xayyuh Asaanamat Tan Muxxo Waado Malik..!!!
Elle Aninnaan Qaraanih Gubal Meqem Ittak Naabbay
@HassanAbdoulkaderOfficialChannel
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ከ1400 ዓመታት በፊት ትግራይ ውስጥ ከዛሬው የተሻለ የሃይማኖት ነፃነት ነበር። መካ ውስጥ በገዛ ወገኖቻቸው የተገፉ የተንገላቱ ሙስሊሞች ባህር አቆራርጠው የተሰደዱት ወደ ሐበሻ ነበር። "እዚያ ከሱ ዘንድ ማንም የማይበደልበት ፍትሃዊ መሪ አለ" ተብሎ በነብዩ ﷺ የተመሰከረለት ድንቅ መሪ ነበር፣ ነጃሺ። ያኔ በግዛቱ ውስጥ ማንም እንዳይነካቸው ዋስትና ሰጥቷቸው ነበር ለስደተኛዎቹ ሙስሊሞች።
ዛሬ ከ1400 ዓመታት በኋላ በ21ኛው ክ/ዘመን ሙስሊም ለጋ ልጆች፣ ከሩቅ የመጡ እንግዶች ሳይሆኑ ተወላጆች፣ ሻሽ ካልጣላችሁ ተብለው በእምነታቸው ተለይተው ከትምህርት ገበታ ተገፍተዋል። ይበልጥ መሰልጠን ሲገባ ጭራሽ እንደ ግመል ሽንት ወደ ኋላ መሄድ የሚያሳዝንም፣ የሚያሳፍርም፣ የሚገርምም ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
