የጥበብ እመቤት 📜
Открыть в Telegram
╱◥██████◣ │∩│🪟▤│🪟│ ▓▆▇█▓🚪▓█▇ 🍹❤️🔥✨🍁𝐖𝐄𝐋𝐂𝐎𝐌𝐄🍁✨ 𝚜𝚞𝚌𝚌𝚎𝚜𝚜 እንኳን ደህና መጡ ወደ የጥበብ እመቤት "ሕይወት ትጠይቃለች፣ ጥበብ ትመልሳለች " https://Wisdomlady
БольшеСтрана не указанаКатегория не указана
271
Подписчики
-124 часа
+77 дней
+15230 день
Архив постов
271
ታላቁ ታላቅነት ከፍ ብሎ ማሰብ ነው!
ንስር የአእዋፋት ሁሉ ንጉስ ነው ቢባል አያንስበትም ህይወቱን ሙሉ እያደነ ነው ሚኖረው ያለፍርሃት ነገር ግን በስተመጨረሻ በእርጅናው ዘመን ህይውቱን የሚነጠቀው በትንሿ አእዋፍ ነው ክንፉ ውስጥ ትገባና እየበላች በቁሙ ታመነምነዋለች በስተመጨረሻም ለሷም ቢሆን ግን አንድ መላ አያጣም ከፍ ብሎ ከዳመና በላይ በመብረር ወፏ ልትቋቋመው የማትችለው የአየር ንብረት ውስጥ በመግባት ያሸንፋታል እንዲህ ነው ሰዎች ታላቅ ነኝ የሚል ጀግና በትንሽ ይሸነፉል።
ለዚህ ደግሞ ታላቁ ታላቅነት ከችግርና ችጋር በላይ ከፍ ብሎ ማሰብ ነው።
271
" ከልብ❤ የልብ❤ ጓደኛ "
ከልብህ ውሰጥ ጠልቆ ስቃይ ካልተረዳ፣
የጓደኛ መብዛት አንተን ምን ሊረዳ?
በደስታህ ዘመን ከቦ ከሚስቀው፤
በሀዘንህ ወራት አብሮ የሚያለቅሰው፤
ከሚግተለተለው ከሺህ ሳቅ አድማቂ!
ከልብ የሚረዳ አንድ ሰው ነው በቂ!
271
Out of all the things needed for a successful relationship, love barely makes the top 5. Honesty, loyalty, trust, and communication all have to be there.
271
አህያና ጅብ
ከዕለታት አንድ ቀን ፍቅር ሲደናበር
ወስዶ አላተማቸው አህያን ከጅብ ጋር
አላቻ ጋብቻ መመስረት አምሯቸው
ሰርግ ለመሰረግ ሲደርስ ቀናቸው
ፍሪዳ ፍለጋ ቢወጡ ቢወርዱ
ማግኘት ተስኗቸው ቢረዝም መንገዱ
ለማረፍ ወስነው በተቀመጡበት
አያ ጅቦ ታዲያ እራብ ቢጠናበት
የወደፊት ሚስቱን ድንገት ቆረጠማት
እስኪጠግብ ድረስ ከሆዱ እያስማማት
ጥንትም የማይሆን አህያ ከጅብ ጋር
ሆዳም አልታደለም መታመን ለፍቅር።
271
"ህይወት እንደ መፅሀፍ ናት፤ አንዳንድ ምዕራፎች ያስለቅሳሉ፣ አንዳንዶቹ ያስደስታሉ፣ አንዳንዶቹ ደግሞ እጅግ ይፈትናሉ። ነገር ግን አንድ ምዕራፍ መጥፎ ስለሆነ ብቻ የመፅሀፉ ታሪክ አበቃ ማለት አይደለም። ዛሬ ያለህበት ቦታ መጨረሻህ አይደለም፤ የጉዞህ
አንድ አካል እንጂ። በርታ! ታሪክህ ገና አላለቀም።"
271
አረ እኔ ራሱ በሻማ እንቁላል ሲጠበስ ዛሬ ነው ያየሁት!" — ሰይጣን 👹😂
በአንድ ገዳም ውስጥ ረቡዕ እንቁላል ያማራቸው አባት፣ ሰው እንዳያያቸው ብለው በሻማ ብርሃን በማንኪያ እንቁላል ሲጠብሱ በድንገት የገዳሙ አባት ያገኟቸዋል።
አባበ ረቡዕ እንቁላል?" ሲሏቸው...
"አረ እኔ አይደለሁም ሰይጣን አሳስቶኝ ነው" አሉ። በዚህ ጊዜ ሰይጣን ብቅ ብሎ ምን ቢል ጥሩ ነው?
"አረ እኔ ራሱ በማንኪያ እና በሻማ እንቁላል ሲጠበስ ዛሬ ነው ያየሁት!" አላቸው። 😂
የዛሬው መልዕክት፦
እኛም ብዙ ጊዜ ለጥፋታችን ሰበብ እና ምክንያት እንደረድራለን እንጂ ጥፋቱ የራሳችን መሆኑን አምነን መቀበል ይከብደናል። ጥፋትን በሌላ ሰው ማሳበብ መቼ ነው የሚያበቃው?
💭 እናንተስ እንዲህ አይነት ገራሚ ሰበብ ገጥሟችሁ ያውቃል? ኮሜንት ላይ አጋሩኝ!
271
ቀምሼው አላውቅም
እያልኳት አትስጭኝ
ልብሱን ገለጥ አርጋ
መልኩን ብታሳየኝ
እኔው ሰፍ ብዬ
አልኳት ስጭኝ ስጭኝ
እርሷም ሳትሳሳ
አንድ ጊዜ ብትሰጠኝ
ሁሌም ስጭኝ አልኳት
በጣም ነው የጣመኝ
ስሙንም ስትነግረኝ
እንዳይጠፋኝ ብላ
ለካስ የማውቀው ነው
ደስታ ከረሚላ!!!
😁😁😁
271
I'm not saying that love always takes you to heaven. Your life can become a nightmare. But that said, it is worth taking the risk.
- Paulo Coelho
271
" እፎይ ትበል ነፍሴ "
ውሰደኝ ፈረሴ ወደ ዓለም ዳርቻ፣
ሰዎች ከሌሉበት እንድኖር ለብቻ፣
ግፍና ሰቆቃ ከማይሰማበት!!!
ገስግሰህ አድርሰኝ ወደ ብቸኝነት፣
የምታውቀው ቦታ ሰው የማይኖርበት፣
አንድ የዓለም ዳርቻ ይኖር እንደሁ ድንገት፣
ግዜ ሳታጠፋ በል ገስግስ ፈረሴ፣
ለቀናትም ቢሆን እፎይ ትበል ነፍሴ።
271
+1
" መፍትሔ አልባ ተስፋዎች !
የተስፋውን መንገድ ጎዳና ሳይመሩ፣
ተስፋ አትቁረጥ ቢሉት ስሙን እየጠሩ፣
የምላስ ወጌሻ ሳይደርብ ተግባርን፣
አሽቶ መች ሊፈውስ ተስፋ ያጣ ልብን፣
ከልብ ባልመነጨ እውነት አልባ ምክር፣
በማስመሰል ቅኔ ቢሉት በርታ ጠንክር!
ተስፋን የተራበ መንገድ ለጠፋው ሰው፣
በተግባር ተከብሮ መንገዱን ማን ይምራው?
የመካሪ ምክሩ ከልብ ካልፈለቀ፣
በፍቅር ውቂያኖስ ተግቶ ካልጠለቀ!
አሉ! ለመባሉ ተስፋ አትቁረጥ ቢሉ፣
መች ተስፋን ሊመልስ ተስፋ የለሽ ቃሉ።
✍️ayb
271
ጡሩ ወዳጆ እና ጡሩ ቡና ሁለቱም ልብን የማሞቅ አቀም አላቸው በሂወታችን ውሥጥ መከፋትን በትዝታ ድብርትን በፈገግታ የሚቀይሩ ውድ ሰወች አሉ ልክ እንደማለዳ ቡና ቀናችንን ለሚደምቁልን ንፁህ ልቦች ሰላም ለነሱ ይሁንላቸው ❤🥰
271
Repost from ⚜ከምጡቃን አንደበት⚜
<<ሰው በውስጡ ያለውን ብቃት ቢረዳ አሁን ያለበት ቦታ ባሳፈረው ነበር... ማሰብ ሚችለው ፍጡር ማሰብ ለማይችሉ አማልክት እንዴት ይሰግዳል?>>
ይህ አስተምህሮ ሶቅራጥስን ለሞት ያበቃ ትምህርት ነበር...
ሚገርመው ግን ሰው አሁንም ያንን ብቃቱን አልተረዳም 💔
🔗Join - @mtuk_hasab
271
ከማይመጥንህ ፍልሚያ ራስህን አርቅ!
ለሚመጣውና ለሚሄደው፣ ለሚወጣውና ለሚወርደው ሁነቱ ሁሉ አትናደድ፤ የገዛ ነፍስህንና ስሜትህን በብስጭት ጅራፍ አትቅጣ። በነገሮች መሃል ሆነህ በጥበብ ስትመለከት፦ «ይህ ቦታ ለእኔ አይመጥንም፣ ይህ ክርክር ምንም ትርፍ የለውም፣ ይህ ፍልሚያ ለጊዜዬም ሆነ ለጉልበቴ አይገባውም» ብለህ ራስህን የምታርቅበትን የብስለት መንገድ ፍጠር።
ምክንያቱም በትግሉ መሃል ብትቆይም፣ በመጨረሻ ዝቅ ብሎ የሚደክመውና የሚቆስለው፣ ህመም የሚሰማውም የገዛ ልብህ ብቻ ነው።
ለራስህ ልታደርግ የምትችለው ትልቁ ውለታና ልትቀዳጀው የሚገባህ መብትህ፦ ያንተ ሚና የሌለበትን የሌሎችን የሁከት ፊልም ትተህ መውጣት እና የውስጥህን ሰላም በፅኑ ጠባቂነት ማስከበር ብቻ ነው።
ለቀሩት ተዋናዮች መድረኩን ልቀቅላቸው፤ አንተ ግን የነፃነትህን መንገድ ተጓዝ።
271
❤️🩹 ይቅርታ ለራሴ🙏❤️🩹
ይዠው ስለኖርኩኝ አልባሌ ቦታ
ስላሰቃየሁት ጠዋት እና ማታ
እራሴን በራሴ ልጠይቅ ይቅርታ
መድረስ እያለበት ስላዘገየሁት
በከንቱ አድክሜ ስላሰቃየሁት
ገና አሁን ነው እና እራሴን ያየሁት
ብዙ ባንገላታው ብዙ ብበድለው
ግዴለም እራሴን ይቅርታ ልበለው
ትልቅ ቦታ እንዳይደርስ ትልቅ ነገር ይዞ
አሰልችቸዋለሁ በአድካሜ በጉዞ
ተስፋን ምግብ አርጋ በምትኖር አለም
የማይጠቅም እቅድ ክፋ ህልም በማለም
እኔማ እራሴን ያልበደልኩት የለም
ዛሬ ሲረጋጋ ሲያስተውል መንፈሴ
ይቅርታ አረኩለት እኔማ ለራሴ
እናተም እንደኔ እራሳችሁን ከምትበድሉ
ከራሳችሁ ጋር ይቅር ተባባሉ
ከማይጠቅም ቦታ መቸም እንዳትውሉ
እናንተው በናተ ከምትሰቃዩ
እስኪ እራሳችሁን ዘወር ብላችሁ እዩ
እንዲታያችሁ ሂወት በቀላሉ
እስኪ ለራሳችሁ እኔ ማንነኝ በሉ
ምንም ይፈጠር ምን እራሳችሁን እንዳበድሉ
#መልካም አዳር
271
" ሳይኖር አለቀ "!!!
ከአለማነው ይልቅ የአጠፋነው በዝቶ
የቃረምነው እውቀት በዜሮ ተባዝቶ
ቁሳቁስ ተከብሮ ሰውነት ተናቀ
ኖርነው ያልነው ህይወት ሳይኖር አለቀ
የጋራነት ቀርቶ የግል ያልነው በዝቶ
ጥሎ ማለፍ ሆነ እርስ በእርስ ተጋፍቶ
271
ውጣ ከተራራው
እንዳሳለፍከው እንዳምና ታቻምና
በመንገድህ ሁሉ ቢበዛ ፈተና
ጉልበትህም ቢዝል ቢደክምህም ስራው
እጅግ ቢመርህም ስቃዩ መከራው
ወንድሜ ሆይ በርታ ውጣ ከተራራው
ሽንፈትህን እንጅ ድካምክን አትፍረው
በአውራ ጣት ተቁሞ እጅ ቢዘረጋ
ከፍ ያለ ያውቀዋል የከፍታን ዋጋ
መቸም ሁኖ አያውቅም ሁሉም አልጋ በአልጋ
እንደምንም ብለህ ከድልህ ተጠጋ
በዚህ ውጣ ውረድ ግዴለም አትሰልች
ለአፍታም አትቁሚ እህቴ ሆይ በርች
ከንፈሩን ቢመጥም ሰው ሁሉ ስላንቺ
በሩጫ ዘመን በፉክክር አለም
ጥሎ እሚሮጥ እንጅ የሚጠብቅ የለም
እሩጠሽ ቅደሚ አይዞሽ እህታለም
የማይታመንን ሰውን ተስፋ አድርገሽ
እንዳትወድቂ እህቴ ድጋፍን ፈልገሽ
ሰው ምርኩዝ ነውእና ቶሎ ይሰበራል
የራስ ጥንካሬ ከራስ ጋር ይኖራል
በል አንተ ወንድሜ ጉልበትክን አበርታው
እራስክን አስረሀል ማሰራያህን ፍተው
ጥረህ ተጣጥረህ ውጣ ከከፍታው
271
ህይወት ሁልጊዜ የምንፈልገውን ነገር አትሰጠንም
ነገር ግን የምንፈልገውን ለመሆን የሚያስፈልገንን ትምርት ትሰጠናለች።
ዛሬ የምናለቅስበት ምክንያት ነገ የምንጠነክርበት ታሪክ ሊሆን ይችላል ።
ስለዚህ ታጋሽ እንሁን፣ ተስፋ አንቁረጥ ምክንያቱም ቆንጆ ቀናት ገና ከፊታችን አሉ።
271
የወንድነት ግርማ እንዲኖርህ ና ተከተለኝ ...
🔹 ቃልህ አጥብቀህ አክብር
🔹 አቋምህ ቀጥ አድርግ
🔹 ድክመትህ በሚስጢር ያዝ
🔹 ንፅህና ዘወትር ጠብቅ
🔹 ፁኑ አቋም ይኑርህ
🔹 ደንበርህን ለሰው አሳውቅ
🔹 በትህትና መሪ ሁን
🔺 ለምትፈልገው ነገር ይ ላመንክበት መስወአቲ ክፈል
🔹 በራስህን ብቃት ተማመን
