የጥበብ እመቤት 📜
Открыть в Telegram
╱◥██████◣ │∩│🪟▤│🪟│ ▓▆▇█▓🚪▓█▇ 🍹❤️🔥✨🍁𝐖𝐄𝐋𝐂𝐎𝐌𝐄🍁✨ 𝚜𝚞𝚌𝚌𝚎𝚜𝚜 እንኳን ደህና መጡ ወደ የጥበብ እመቤት "ሕይወት ትጠይቃለች፣ ጥበብ ትመልሳለች " https://Wisdomlady
БольшеСтрана не указанаКатегория не указана
271
Подписчики
-124 часа
+77 дней
+15230 день
Архив постов
271
#ሞትን ሸሽተህ አታመልጣትም።
የባግዳድ ነዋሪ የነበረ አንድ ባለጸጋ በጣም የሚወደው ባሪያውን ወደ ገበያ ይልከዋል፡፡ የተላከው ባሪያ ብዙም ሳይቆይ ላብ በላብ ሆኖ በፍርሀት እየተንቀጠቀጠ ይመለሳል፡፡
ጌታውም ምን እንደሆነ ሲጠይቀው ፦ “አንዲት ሴት በገበያው መሀከል ስትዘዋወር አየሁ፡፡ ቀረብ ብዬ ሳስተውላት ሞት ናት፡፡ እሷም ልክ እንዳዬችኝ በጣቷ የዛቻ ምልክት አሳየችኝ፡፡ ጌታዬ ሆይ፦ እባክህ ፈረስህን ስጠኝና ወደ ሳማራ ከተማ ሸሽቼ ሞትን ላምልጣት፡" አለው።
ባለፀጋውም ለባሪያው ፈረሱን ሰጠው፡፡
ባሪያውም ሞትን ሽሽት ወዲያውኑ ፈረሱ ላይ ወጥቶ ሽምጥ እየጋለበ ወደ ሳማራ ከተማ ገሰገሰ።
ባለፀጋውም የሚያስፈልገውን ነገር ራሱ ለመገብዬት ከጥቂት ከቆይታ በኋላ ወደ ገበያ ሄዶ ሲዘዋወር ሞትን አገኛት፡፡ ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላም፦ “ቅድም ባሪያዬ ስታይው ስለምን አስፈራራሽው?” ሲል ጠየቃት፡፡ ሞትም ፈገግ ብላ፦ “እያስፈራራኹትኮ አይደለም። ዛሬ ማታ ሳማራ ከተማ ላይ ቀጠሮ ስላለን፣ እዚህ ሳየው ተገርሜ ነው” አለችው።
ፈጣሪ የቀጠራት ቀን ከደረሰች ሞትን ሸሽተህ አታመልጣትም።ከባግዳድ አመለጥኳት ያልካት ሞት- ቀድሞ ሳማራ ገብታ ትጠብቅሀለች።
271
ኃላፊነት እየተወጣን በምንኖርበት የህይወት ውድድር ውስጥ፣ የገዛ ማንነታችንን እንዳናጣው መጠንቀቅ አለብን። ማሽን ዝም ብሎ ይሰራል፣ የሰው ልጅ ግን መኖርና መደሰት ይገባዋል። 🔥 Don't let the pressure of growing up turn you into a stranger to your own soul. ኃላፊነት መሸከም ማለት ራስን መቅበር ማለት አይደለም። በኑሮ ውጥረትና በዕድሜ ግፊት ውስጥ ራስን ማጣት እንደ ትልቅ ስኬት ሊቆጠር አይገባም። Stop confusing being functional with being alive; a machine functions, but a human soul needs to thrive. አሁን ምን ላድርግ?' ብለህ አትጠይቅ አዲስ ህይወት አያስፈልግህም፤ ማድረግ ያለብህ የፈለከውን አሁን ያለህን ህይወት ችላ ማለትን ማቆም ብቻ ነው። 🤝
271
" የሰው የእውነት ሀቁ "
ግዜ ባይጣደፍ ዘመን ባይገሰግስ፣
ምን ነበር ለጥቂት ልጅነት ቢታገስ፣
እድሜ በቀን ቀመር በዓመታት ሲሰላ፣
የሰው የእውነት ሀቁ ልጅነት ነው ጥላ፣
ክፋት ያልበረዘው ጭንቀት ያልከሰሰው፣
ማስመሰል የራቀው እምነት ያልጎደለው፣
ከሁላችን እድሜ አምላክ ቢመዝነው፣
ልጅነት ብቻ ነው የእውነት የተኖረው።
271
የቱንም ያህል ሰዎችን መውደድ፣ መደገፍ፣ እንዲሁም ጊዜና ልብን መስጠት ብትችልም፤ በጊዜ ሂደት እያንዳንዱ ሰው በራሱ መንገድና አስተሳሰብ እንደሚጓዝ ተረዳ። የእኛ ሰላምና ዋጋ ሙሉ በሙሉ በሌላ ሰው ህልውና ወይም ምርጫ ላይ የተመሰረተ እንዳልሆነ እወቅ! ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ከእኛ ጋር አብሮ የሚኖረው ብቸኛው ሰው እኛው እራሳችን ብቻ መሆንን ስታውቅ፣ ከሌሎች ጋር እንዴት አብረህ መጓዝ እንዳለብህ ትረዳለህ። መንገድህን ትተው የሚሄዱ ሰዎች የጉዞው አካል እንጂ እራስህን የምታጣበት ምክንያት እንዳልሆኑ ታምናለህ።
271
ይመሻል ይነጋል!!!
የከፋው ሰው እንጂ ህግን ያጓደለ፣
ከፈጣሪ እርቆ አድሮ የቀለለ፣
ግዜማ ቁጥር ነው ይመሻል ይነጋል፣
የተፈጥሮ ህጉን ጠብቆ ይጓዛል።
ጥፋቱ የሰው ነው ህግ የተላለፈ፣
በደልን በጉያው ደጋግሞ ያቀፈ።
ግዜ ነው አትበሉ ግዜ ምን አጠፋ?
ሰው እኮ ነው ዛሬም በቢጤው የከፋ።
271
ደግነትህ መቃብርህ እንዳይሆን
ሁል ጊዜ ጥሩ ሰው ለመሆን እምትጥር ከሆነ፣ ክፉዎች በሚበዙበት ዓለም ውስጥ መጥፋትህ አይቀርም።
ዙሪያህ በተኩላዎች ተሞልቶ፣ አንተ ብቻ በግ መሆን አትችልም!
271
" ደልቶት የሚፈግግ "
ተማረ መሰለኝ የማሽላን ዘዴ
ጥርሴ ይስቅ ጀመር እያረረ ሆዴ
የውስጥን ቃጠሎ ጥርስ እያስታመመ
በተስፋ መድሀኒት በፍቅር እያከመ
ህይወት ካልተመራች በችሎ ማለፍ ህግ
ጥቂት ሰው ነበረ ደልቶት የሚፈገግ
271
Fake people don’t earn your trust.
They engineer it.
They learn what you need.
Then become what you trust.
Nothing feels forced.
That’s the strategy.
The most dangerous manipulation never asks for trust.
It makes trust feel inevitable.
Your brain mistakes familiarity for character.
By the time you notice the performance, they already know where you’re weak.
The betrayal didn’t begin when they lied.
It began when you rewarded the act.
💯💯💯
271
የሰው ልጅ ሆድ ብቻ ሳይሆን አእምሮም ተሰጥቶታል። ለውጥ ያለው እምሮና ጊዜ ውስጥ ነው።በጊዜ ውስጥ ያልኖረ ሰው በአእምሮ ብቻ ስኬት ላይ መድረስ አዳጋች ነው። ለውጥ ያለው በአእምሮ እና በአካላዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ነው። በተፈጥሮ ውስጥ ያልተገለጠ ሰው በአእምሮ ውስጥ ብቻ ሊወለድ አይችልም።
271
ህይወት ጥያቄ አይደለችም ጥያቄ እንዳላት አድርጎ ለመመለስ መሞከር አንዱ የሰው ልጅ ስንፍና መገለጫ ነው። ህይወትን በእምነት ይኖሯታል የተዘጋ በር የላትምና ለመክፈት አንድከም። እንቆቅልሽ አይደለችምና ምስጢሯን ለመፍታት አንጣር ህይወትን እንደ አመጣጧ ከመኖር በላይ ታላቅ እምነት የለም።
271
አንዳንድ ጊዜ ልብ የምትፈልገው አንድ ሰው ሳይሆን፣ የራስን ስሜት የሚገልጽ ታሪክ ነው። ህመም፣ ደስታ እና ፍቅር በገጸ-ባህሪያት ህይወት ውስጥ ሲንጸባረቁ። የራስህን ታሪክ እዚህ ታገኘዋለህ።
271
ሕይወት ምንድነው?
Me፦ ሕይወት መኖር ነው። መርጦ ሳይሆን ሁሉንም መኖር። ሐዘን ደስታውን ፤ ማዘን መተከዙን፤ መታመም ደኅንነቱን፤ መጋል መባረዱን፤ ማተኮስ መቀዝቀዙን. . . ሁሉን መኖር ነው።
271
" ቅን ለሆኑ ልቦች ❤ "
ከሃዘን አላቀው ሳቅ ለሚመልሱ፣
ቅን ለሆኑ ሰዎች ፍቅር ለለበሱ፣
በመከራ ወራት ቀድመው ለሚደርሱ፣
ሰው በመሆን ልቀው እንባ " ለሚያብሱ ፣
ፈተናን ተጋርተው ተስፋን ለሚሞሉ፣
ብዙ ነገር ሰጥተው ምንም ለማይሉ፣
ለቅኖች ምሳሌ መሆን ለታደሉ፣
ለክፉዎች ክስረት ፍቅር ለተሞሉ፣
ለሚከፍሉት ዋጋ ለፍቅራቸው ቅኔ፣
ለእነርሱ እድሜ ይሰጥ ተቀንሶ ከእኔ።
271
በዚህ አለም ላይ ስምን በጥሩ ዝና ተክሎ ለማለፍ አንድ ሰው በራሱ ውስጥ መሞት አለበት። የሰው ልጅ በዚህ ምድር ላይ የተፈጠረው ደስታን ብቻ ለመቅመስ ብቻ ሳይሆን ለሰብአዊ ፍጡር ግልገሎትን በመስጠት በማክበር ልቆ ስብዕናውን ሲጋራ ነው።
271
ጠቢቡ እንዲህ አለ "በጨለማ ማየት እችላለሁ አለ" የጠቢቡን አባባል ያልተረዳ ሰነፍ ደግሞ ጠየቀ "በጨለማ ማየት ከቻልህ ታድያ ለምን መብራት ይዘህ ትሄዳለህ" ጠቢቡም ከሰነፍ የሚጠብቀው ጥያቄ ነውና ሳይደነቅ መለሠለት"እንዳንተ ዓይነቱ በጨለማ ማየት የማይችል መጥቶ እንዳይጋጨኝ ነው" አለው።
271
“Stop trying to be less of who you are. Let this time in your life cut you open and drain all of the things that are holding you back.”
