uz
Feedback
የጥበብ እመቤት 📜

የጥበብ እመቤት 📜

Kanalga Telegram’da o‘tish

╱◥██████◣ │∩│🪟▤│🪟│ ▓▆▇█▓🚪▓█▇ 🍹❤️‍🔥✨🍁𝐖𝐄𝐋𝐂𝐎𝐌𝐄🍁✨ 𝚜𝚞𝚌𝚌𝚎𝚜𝚜 እንኳን ደህና መጡ ወደ የጥበብ እመቤት "ሕይወት ትጠይቃለች፣ ጥበብ ትመልሳለች " https://Wisdomlady

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat belgilanmaganToif belgilanmagan
271
Obunachilar
-124 soatlar
+77 kunlar
+15230 kunlar
Postlar arxiv
#ሞትን ሸሽተህ አታመልጣትም። የባግዳድ ነዋሪ የነበረ አንድ ባለጸጋ በጣም የሚወደው ባሪያውን ወደ ገበያ ይልከዋል፡፡ የተላከው ባሪያ ብዙም ሳይቆይ ላብ በላብ ሆኖ በፍርሀት እየተንቀጠቀጠ ይመለሳል፡፡
#ሞትን ሸሽተህ አታመልጣትም። የባግዳድ ነዋሪ የነበረ አንድ  ባለጸጋ በጣም  የሚወደው ባሪያውን ወደ ገበያ ይልከዋል፡፡ የተላከው ባሪያ ብዙም ሳይቆይ  ላብ በላብ ሆኖ በፍርሀት እየተንቀጠቀጠ ይመለሳል፡፡ ጌታውም ምን እንደሆነ ሲጠይቀው ፦ “አንዲት ሴት በገበያው መሀከል ስትዘዋወር አየሁ፡፡ ቀረብ ብዬ  ሳስተውላት ሞት  ናት፡፡ እሷም ልክ እንዳዬችኝ   በጣቷ የዛቻ ምልክት  አሳየችኝ፡፡ ጌታዬ ሆይ፦ እባክህ ፈረስህን ስጠኝና  ወደ ሳማራ ከተማ ሸሽቼ ሞትን ላምልጣት፡" አለው። ባለፀጋውም ለባሪያው  ፈረሱን ሰጠው፡፡ ባሪያውም ሞትን ሽሽት ወዲያውኑ   ፈረሱ ላይ ወጥቶ  ሽምጥ እየጋለበ ወደ ሳማራ ከተማ ገሰገሰ። ባለፀጋውም የሚያስፈልገውን ነገር ራሱ ለመገብዬት  ከጥቂት  ከቆይታ በኋላ ወደ ገበያ ሄዶ  ሲዘዋወር ሞትን አገኛት፡፡ ሰላምታ ከተለዋወጡ  በኋላም፦ “ቅድም  ባሪያዬ ስታይው  ስለምን አስፈራራሽው?” ሲል ጠየቃት፡፡ ሞትም ፈገግ ብላ፦ “እያስፈራራኹትኮ አይደለም። ዛሬ ማታ ሳማራ ከተማ ላይ ቀጠሮ ስላለን፣ እዚህ ሳየው ተገርሜ ነው” አለችው። ፈጣሪ የቀጠራት ቀን ከደረሰች ሞትን ሸሽተህ አታመልጣትም።ከባግዳድ አመለጥኳት ያልካት ሞት- ቀድሞ ሳማራ ገብታ ትጠብቅሀለች

ኃላፊነት እየተወጣን በምንኖርበት የህይወት ውድድር ውስጥ፣ የገዛ ማንነታችንን እንዳናጣው መጠንቀቅ አለብን። ማሽን ዝም ብሎ ይሰራል፣ የሰው ልጅ ግን መኖርና መደሰት ይገባዋል። 🔥 Don't let t
ኃላፊነት እየተወጣን በምንኖርበት የህይወት ውድድር ውስጥ፣ የገዛ ማንነታችንን እንዳናጣው መጠንቀቅ አለብን። ማሽን ዝም ብሎ ይሰራል፣ የሰው ልጅ ግን መኖርና መደሰት ይገባዋል። 🔥 Don't let the pressure of growing up turn you into a stranger to your own soul. ​ኃላፊነት መሸከም ማለት ራስን መቅበር ማለት አይደለም። በኑሮ ውጥረትና በዕድሜ ግፊት ውስጥ ራስን ማጣት እንደ ትልቅ ስኬት ሊቆጠር አይገባም። Stop confusing being functional with being alive; a machine functions, but a human soul needs to thrive. አሁን ምን ላድርግ?' ብለህ አትጠይቅ አዲስ ህይወት አያስፈልግህም፤ ማድረግ ያለብህ የፈለከውን አሁን ያለህን ህይወት ችላ ማለትን ማቆም ብቻ ነው። 🤝

ፍቅር ቃል ሳይሆን ሀላፊነት ነው፤ ይህን የሚረዳ ወንድ እዉነተኛ አፍቃሪ ነው❤
ፍቅር ቃል ሳይሆን ሀላፊነት ነው፤ ይህን የሚረዳ ወንድ እዉነተኛ አፍቃሪ ነው❤

" የሰው የእውነት ሀቁ " ግዜ ባይጣደፍ ዘመን ባይገሰግስ፣ ምን ነበር ለጥቂት ልጅነት ቢታገስ፣ እድሜ በቀን ቀመር በዓመታት ሲሰላ፣ የሰው የእውነት ሀቁ ልጅነት ነው ጥላ፣ ክፋት ያልበረዘው ጭንቀት
" የሰው የእውነት ሀቁ " ግዜ ባይጣደፍ ዘመን ባይገሰግስ፣ ምን ነበር ለጥቂት ልጅነት ቢታገስ፣ እድሜ በቀን ቀመር በዓመታት ሲሰላ፣ የሰው የእውነት ሀቁ ልጅነት ነው ጥላ፣ ክፋት ያልበረዘው ጭንቀት ያልከሰሰው፣ ማስመሰል የራቀው እምነት ያልጎደለው፣ ከሁላችን እድሜ አምላክ ቢመዝነው፣ ልጅነት ብቻ ነው የእውነት የተኖረው።

የቱንም ያህል ሰዎችን መውደድ፣ መደገፍ፣ እንዲሁም ጊዜና ልብን መስጠት ብትችልም፤ በጊዜ ሂደት እያንዳንዱ ሰው በራሱ መንገድና አስተሳሰብ እንደሚጓዝ ተረዳ። የእኛ ሰላምና ዋጋ ሙሉ በሙሉ በሌላ ሰው
የቱንም ያህል ሰዎችን መውደድ፣ መደገፍ፣ እንዲሁም ጊዜና ልብን መስጠት ብትችልም፤ በጊዜ ሂደት እያንዳንዱ ሰው በራሱ መንገድና አስተሳሰብ እንደሚጓዝ ተረዳ። የእኛ ሰላምና ዋጋ ሙሉ በሙሉ በሌላ ሰው ህልውና ወይም ምርጫ ላይ የተመሰረተ እንዳልሆነ እወቅ! ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ከእኛ ጋር አብሮ የሚኖረው ብቸኛው ሰው እኛው እራሳችን ብቻ መሆንን ስታውቅ፣ ከሌሎች ጋር እንዴት አብረህ መጓዝ እንዳለብህ ትረዳለህ። መንገድህን ትተው የሚሄዱ ሰዎች የጉዞው አካል እንጂ እራስህን የምታጣበት ምክንያት እንዳልሆኑ ታምናለህ

"የሆነው ሁሉ እንዳለ ሆኖ አሁንም ቢሆን ሰዎች ከስረመሠረታቸው ጥሩዎች ናቸው ብዬ አምናለሁ ፡፡" #አና
"የሆነው ሁሉ እንዳለ ሆኖ አሁንም ቢሆን ሰዎች ከስረመሠረታቸው ጥሩዎች ናቸው ብዬ አምናለሁ ፡፡" #አና

ይመሻል ይነጋል!!! የከፋው ሰው እንጂ ህግን ያጓደለ፣ ከፈጣሪ እርቆ አድሮ የቀለለ፣ ግዜማ ቁጥር ነው ይመሻል ይነጋል፣ የተፈጥሮ ህጉን ጠብቆ ይጓዛል። ጥፋቱ የሰው ነው ህግ የተላለፈ፣ በደልን በጉያ
ይመሻል ይነጋል!!! የከፋው ሰው እንጂ ህግን ያጓደለ፣ ከፈጣሪ እርቆ አድሮ የቀለለ፣ ግዜማ ቁጥር ነው ይመሻል ይነጋል፣ የተፈጥሮ ህጉን ጠብቆ ይጓዛል። ጥፋቱ የሰው ነው ህግ የተላለፈ፣ በደልን በጉያው ደጋግሞ ያቀፈ። ግዜ ነው አትበሉ ግዜ ምን አጠፋ? ሰው እኮ ነው ዛሬም በቢጤው የከፋ።

ደግነትህ መቃብርህ እንዳይሆን ሁል ጊዜ ጥሩ ሰው ለመሆን እምትጥር ከሆነ፣ ክፉዎች በሚበዙበት ዓለም ውስጥ መጥፋትህ አይቀርም። ዙሪያህ በተኩላዎች ተሞልቶ፣ አንተ ብቻ በግ መሆን አትችልም!
ደግነትህ መቃብርህ እንዳይሆን ሁል ጊዜ ጥሩ ሰው ለመሆን እምትጥር ከሆነ፣ ክፉዎች በሚበዙበት ዓለም ውስጥ መጥፋትህ አይቀርም። ዙሪያህ በተኩላዎች ተሞልቶ፣ አንተ ብቻ በግ መሆን አትችልም!

" ደልቶት የሚፈግግ " ተማረ መሰለኝ የማሽላን ዘዴ ጥርሴ ይስቅ ጀመር እያረረ ሆዴ የውስጥን ቃጠሎ ጥርስ እያስታመመ በተስፋ መድሀኒት በፍቅር እያከመ ህይወት ካልተመራች በችሎ ማለፍ ህግ ጥቂት ሰው
" ደልቶት የሚፈግግ " ተማረ መሰለኝ የማሽላን ዘዴ ጥርሴ ይስቅ ጀመር እያረረ ሆዴ የውስጥን ቃጠሎ ጥርስ እያስታመመ በተስፋ መድሀኒት በፍቅር እያከመ ህይወት ካልተመራች በችሎ ማለፍ ህግ ጥቂት ሰው ነበረ ደልቶት የሚፈገግ

Fake people don’t earn your trust. They engineer it. They learn what you need. Then become what you trust. Nothing feels forc
Fake people don’t earn your trust. They engineer it. They learn what you need. Then become what you trust. Nothing feels forced. That’s the strategy. The most dangerous manipulation never asks for trust. It makes trust feel inevitable. Your brain mistakes familiarity for character. By the time you notice the performance, they already know where you’re weak. The betrayal didn’t begin when they lied. It began when you rewarded the act. 💯💯💯

የሰው ልጅ ሆድ ብቻ ሳይሆን አእምሮም ተሰጥቶታል። ለውጥ ያለው እምሮና ጊዜ ውስጥ ነው።በጊዜ ውስጥ ያልኖረ ሰው በአእምሮ ብቻ ስኬት ላይ መድረስ አዳጋች ነው። ለውጥ ያለው በአእምሮ እና በአካላዊ እ
የሰው ልጅ ሆድ ብቻ ሳይሆን አእምሮም ተሰጥቶታል። ለውጥ ያለው እምሮና ጊዜ ውስጥ ነው።በጊዜ ውስጥ  ያልኖረ ሰው በአእምሮ ብቻ ስኬት ላይ መድረስ አዳጋች ነው። ለውጥ ያለው በአእምሮ እና በአካላዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ነው። በተፈጥሮ ውስጥ ያልተገለጠ ሰው በአእምሮ ውስጥ ብቻ ሊወለድ አይችልም።

ህይወት ጥያቄ አይደለችም ጥያቄ እንዳላት አድርጎ ለመመለስ መሞከር አንዱ የሰው ልጅ ስንፍና መገለጫ ነው። ህይወትን በእምነት ይኖሯታል የተዘጋ በር የላትምና ለመክፈት አንድከም። እንቆቅልሽ አይደለችም
ህይወት ጥያቄ  አይደለችም ጥያቄ እንዳላት አድርጎ ለመመለስ  መሞከር  አንዱ የሰው ልጅ ስንፍና መገለጫ ነው። ህይወትን በእምነት ይኖሯታል የተዘጋ በር  የላትምና ለመክፈት አንድከም። እንቆቅልሽ  አይደለችምና ምስጢሯን ለመፍታት አንጣር ህይወትን እንደ አመጣጧ ከመኖር በላይ ታላቅ እምነት የለም።

አንዳንድ ጊዜ ልብ የምትፈልገው አንድ ሰው ሳይሆን፣ የራስን ስሜት የሚገልጽ ታሪክ ነው። ህመም፣ ደስታ እና ፍቅር በገጸ-ባህሪያት ህይወት ውስጥ ሲንጸባረቁ። የራስህን ታሪክ እዚህ ታገኘዋለህ።
አንዳንድ ጊዜ ልብ የምትፈልገው አንድ ሰው ሳይሆን፣ የራስን ስሜት የሚገልጽ ታሪክ ነው። ህመም፣ ደስታ እና ፍቅር በገጸ-ባህሪያት ህይወት ውስጥ ሲንጸባረቁ። የራስህን ታሪክ እዚህ ታገኘዋለህ።

ሕይወት ምንድነው? Me፦ ሕይወት መኖር ነው። መርጦ ሳይሆን ሁሉንም መኖር። ሐዘን ደስታውን ፤ ማዘን መተከዙን፤ መታመም ደኅንነቱን፤ መጋል መባረዱን፤ ማተኮስ መቀዝቀዙን. . . ሁሉን መኖር ነው።
ሕይወት ምንድነው? Me፦ ሕይወት መኖር ነው። መርጦ ሳይሆን ሁሉንም መኖር። ሐዘን ደስታውን ፤ ማዘን መተከዙን፤ መታመም ደኅንነቱን፤ መጋል መባረዱን፤ ማተኮስ መቀዝቀዙን. . . ሁሉን መኖር ነው።

" ቅን ለሆኑ ልቦች ❤ " ከሃዘን አላቀው ሳቅ ለሚመልሱ፣ ቅን ለሆኑ ሰዎች ፍቅር ለለበሱ፣ በመከራ ወራት ቀድመው ለሚደርሱ፣ ሰው በመሆን ልቀው እንባ " ለሚያብሱ ፣ ፈተናን ተጋርተው ተስፋን ለሚሞሉ
" ቅን ለሆኑ ልቦች ❤ " ከሃዘን አላቀው ሳቅ ለሚመልሱ፣ ቅን ለሆኑ ሰዎች ፍቅር ለለበሱ፣ በመከራ ወራት ቀድመው ለሚደርሱ፣ ሰው በመሆን ልቀው እንባ " ለሚያብሱ ፣ ፈተናን ተጋርተው ተስፋን ለሚሞሉ፣ ብዙ ነገር ሰጥተው ምንም ለማይሉ፣ ለቅኖች ምሳሌ መሆን ለታደሉ፣ ለክፉዎች ክስረት ፍቅር ለተሞሉ፣ ለሚከፍሉት ዋጋ ለፍቅራቸው ቅኔ፣ ለእነርሱ እድሜ ይሰጥ ተቀንሶ ከእኔ።

በዚህ አለም ላይ ስምን በጥሩ ዝና ተክሎ ለማለፍ አንድ ሰው በራሱ ውስጥ መሞት አለበት። የሰው ልጅ በዚህ ምድር ላይ የተፈጠረው ደስታን ብቻ ለመቅመስ ብቻ ሳይሆን ለሰብአዊ ፍጡር ግልገሎትን በመስጠት
በዚህ አለም ላይ ስምን በጥሩ ዝና ተክሎ ለማለፍ አንድ ሰው በራሱ ውስጥ መሞት አለበት። የሰው ልጅ በዚህ ምድር ላይ የተፈጠረው  ደስታን ብቻ ለመቅመስ ብቻ ሳይሆን ለሰብአዊ ፍጡር ግልገሎትን በመስጠት በማክበር ልቆ ስብዕናውን ሲጋራ ነው።

ጠቢቡ እንዲህ አለ "በጨለማ ማየት እችላለሁ አለ" የጠቢቡን አባባል ያልተረዳ ሰነፍ ደግሞ ጠየቀ "በጨለማ ማየት ከቻልህ ታድያ ለምን መብራት ይዘህ ትሄዳለህ" ጠቢቡም ከሰነፍ የሚጠብቀው ጥያቄ ነውና
ጠቢቡ እንዲህ አለ "በጨለማ ማየት እችላለሁ አለ" የጠቢቡን አባባል ያልተረዳ ሰነፍ ደግሞ ጠየቀ "በጨለማ ማየት ከቻልህ ታድያ ለምን መብራት ይዘህ ትሄዳለህ" ጠቢቡም ከሰነፍ የሚጠብቀው ጥያቄ ነውና ሳይደነቅ መለሠለት"እንዳንተ ዓይነቱ በጨለማ ማየት የማይችል መጥቶ እንዳይጋጨኝ ነው" አለው።

“Stop trying to be less of who you are. Let this time in your life cut you open and drain all of the things that are holding
Stop trying to be less of who you are. Let this time in your life cut you open and drain all of the things that are holding you back.”