ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
رفتن به کانال در Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
نمایش بیشتر2 955
مشترکین
+1424 ساعت
+247 روز
+38330 روز
آرشیو پست ها
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ምንጃርና ከረዩ አውራጃ ነበልባል ክፍለ ጦር ድል ተቀዳጀች
ሰኔ 07/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ/ጠ/ግ/አሳምነው ዕዝ ከሠም ፪ኛ ኮር ነበልባል ክፍለ ጦር የብልፅግናውን ጥምር ጦር እንደ ቅጠል አረገፉት።
ሁለት የነበልባል ክፍለ ጦር ሻለቆች የተሳተፉበት ውጊያ ማለትም መብረቅ ሻለቃ እና መቶ አለቃ አበባው ሻለቃ ፋኖዎች በጥምረት ባደረጉት ገድል የብልፅግናውን ግብስብስ ሠራዊት በ06/10/2018 ከቀኑ 6:00 እስከ ማታ 9:45 ሰዓት በነበረው ፍልሚያ ፋኖዎቹ መብረቃዊ ክንዳቸውን በመሰንዘር እንደ እሳት ሲለበልቡት አምሽተዋል።
መነሻውን ከባልጪ አድርጎ ወደ ኢራንቡቲ ቀበሌ ያቀናውን የሪፐፕሊካን ጥበቃ 5ኛ ክፍለጦር እና በስሩ በጥቅማጥቅም የሰበሰባቸውን ሆድ አደር ሚሊሾች እንዲሁም አዲስ ተጨማሪ ሰራዊት በመያዝ ኢራንቡቲ ቀበሌን እቆጣጠራለሁ ብሎ በመንጋ ቢመጣም በአይበገሬዎቹ ነበልባል ክፍለ ጦር ሠራዊታችን ወደ መጣበት እዲመለስ አድርገውታል።
የሀይል ብልጫ የተወሰደበት የጠላት ሀይል ከ15 በላይ እንደተገደለበት እና ቁጥሩ በውል ያልታወቀ ቁስለኛ በአንቡላንስ ከአራት ጊዜ በላይ ጭኖ እንዳመላለሰ እና የሞተበትን ሀይል በአካባቢው ማህበረሰብ በማስገደድ ለህክምና የምታመላልሰው አንቡላንስ ደርሳ እስክትደርስ 15ቱን እሬሳ እዲያቀብሉት ማስገደዱን የውስጥ መረጃችን አሳውቆናል።
ይህ በእንዲሕ እንዳለ የአፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ ዓፄ አምደ ጽዮን ኮር 7/70 ክፍለጦር አንድ(1) የአገዛዙ ወታደር
=> አንድ(1) ዘመናዊ ስናይፐር መሳሪያ
=> አንድ(1) የደረት ትጥቅ
=> አራት(4) ካዝና በመያዝ ወደ ፋኖ ተቀላቅሏል።
በሌላ የአውደ ውጊያ ቀጠና
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋት አውራጃ አስገራሚ ጀብዶች ተሠርተዋል
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ፩ኛ ኮር 7/ለ70 ክፍለ ጦር ዛሬም እንደ ትላንቱ በጠላት ይዞታዎች ውስጥ ሰርገው በመግባት አስገራሚ ድሎችን ማስመዝገባቸውን ቀጥለውበታል።
የክፍለ ጦሩ ልዩ የኦፕሬሽን ቃኝዎች የፋሺስት አብይ አህመድ ግብስብስ ሰራዊትን ወደ ሚንቀሳቀስበት ቦታ ሰርገው በመግባት የጠላትን እቅድ በማክሸፍ መብረቃዊ ጥቃቶችን ፈፅመዋል።
የሰርጎ ገብ ውጊያ ስምሪቱ በቀን 05/10/2018 ዓ.ም ከለሊቱ 5:00 ሰዓት ላይ ከአጣዬ ተነስቶ ወደ በርግቢ አቅጣጫ እየገሰገሰ በነበረው የጠላት መከላከያ ሰራዊት ላይ የ7ለ70 ክፍለ ጦር ጀግኖች በ06/10/2018 በበርግቢ ቀበሌ እና በይምልዎ መካከል ላይ አድፍጠው በመጠበቅ ከባድ ድንገተኛ ጥቃት ፈፅመዋል። በዚህ እልህ አስጨራሽ የለሊት ውጊያ የጠላት ኃይል ድባቅ በመመታቱ ወደ መጣበት ተገዶ ለማፈግፈግ ተገዷል። በዚሕም ከጠላት ሀይል አራት(4) የተገደሉ ሲሆን የተቀሩት ደግሞ በጽኑ ቆስለው በሕክምና ላይ እንደሚገኙ የውስጥ መረጃዎቻችን ገልፀዋል።
ይህ የድል ጉዞ ሳይቋረጥ በማግስቱ በ07/09/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ላይ ከአጣዬ ከተማ ተነስቶ ወደ አላላ በመጓዝ ላይ በነበረው የሆድ አደር ሚሊሻ ኃይል ላይ ሌላ ስልታዊ ጥቃት ተፈጽሟል። የክፍለ ጦሩ የቁርጥ ቀን ልጆች አራዳ በር ላይ ቀድመው ሰርገው በመግባትና ምሽግ በመያዝ፣ በሚሊሻው ላይ የጀግንነት ክንዳቸውን አሳርፈዋል።በዚህ እልህ አስጨራሽ ውጊያ እንድሪስ የተባለው የጠላት ሚሊሻ መሪ እስከ ግብረ አበሮቹ ሙሉ በሙሉ የተደመሰሰ ሲሆን፣ ካጋጠማቸው ከባድ ሽንፈት የተረፉት 3ቱ (ሦስቱ) ደግሞ በከባድ የመቁሰል አደጋ ምክንያት ሪፈር ተጽፎላቸው በሕይወትና በሞት መካከል ይገኛሉ ሲል መረጃዎቻችን ተናግረዋል።
" ክብር ለጀግኖች ሰማዕታት"
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"
የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
+3
በአሜሪካን ሀገር የፔንሴሌቪያ ምክር ቤት ለአድዋ ድል በሰጠው ታሪካዊ እውቅና ላይ የተሰጠ ምስጋና እና የአቋም መግለጫ!
መርዛማ መሪነት፦ የተንኮለኛ መሪዎች መገለጫዎች"
ብቃት የሌለው እና ተንኮለኛ (ክፉ አሳቢ) መሪዎች የሚፈጽሟቸው ተግባራት የአንድን ተቋም፣ ቡድን ወይም ሀገር ህልውና አደጋ ላይ የሚጥሉ ናቸው። እነዚህ መሪዎች በአብዛኛው በግል ጥቅምና በስልጣን ጥም ስለሚመሩ የሚከተሉትን ዋና ዋና ጎጂ ተግባራትን ይፈጽማሉ፦
1. በሴራ እና በመከፋፈል ማስተዳደር (Divide and Rule)
• ሰዎችን ማጋጨት፦ ተንኮለኛ መሪ በበታቾቹ መካከል እርስ በእርስ ጥርጣሬና አለመተማመን እንዲፈጠር ያደርጋል። ሰዎች አንድ ላይ ከሆኑ እሱን ሊቃወሙት እንደሚችሉ ስለሚሰጋ፣ ወሬ በማውራት እና ወገንተኝነትን በመፍጠር አንድነታቸውን ያጠፋል።
• በቡድን መክፈል፦ ሰራተኞችን ወይም ተከታዮችን "የእኔ መስመር ተከታይ" እና "ተቃዋሚ" በማለት ፈርጆ በመካከላቸው የጥላቻ መንፈስ ይዘራል።
2. ብቃት ያላቸውን ሰዎች ማራቅና ማሳደድ
• የበታችነት ስሜት፦ ተንኮለኛ መሪ እውቀትና ክህሎት ያላቸውን ሰዎች እንደ ስጋት ያያቸዋል። የራሱን ድክመት እንዳያጋልጡበት በመፍራት የተማሩ እና ጠንካራ ሰራተኞችን ወደ ጎን ያገላል።
• አሽቃባጮችን መሰብሰብ፦ በዙሪያው የሚያሰባስበው እውነትን የሚናገሩ ሰዎችን ሳይሆን፣ ስህተቱንም ጭምር "ልክ ነህ" እያሉ የሚያጨበጭቡለትን ደካማና አድርባይ ሰዎችን ነው።
3. ተቋማዊ አሰራርንና ህግን ማፍረስ
• የግል ውሳኔ ማብሰል፦ ተንኮለኛ መሪ ህግና መመሪያን አይከተልም። ተቋማዊ አሰራርን በመጣስ ውሳኔዎችን በግል ፍላጎቱና በስሜቱ ላይ ተመስርቶ ያስተላልፋል።
• ድብቅ አጀንዳ መያዝ፦ ውሳኔዎቹ ግልጽነት የሌላቸው፣ ሚስጥራዊ እና ለግል ወይም ለተወሰኑ ቡድኖች ጥቅም ብቻ ያደሉ ይሆናሉ።
4. ስልጣንን ለበቀል እና ለማስፈራሪያነት መጠቀም
• ማስፈራራትና ጫና መፍጠር፦ ተከታዮቹ ወይም ሰራተኞቹ በሃሳብ ሲለዩት በስልጣኑ ተጠቅሞ ያስፈራራቸዋል፣ ጥቅማ ጥቅማቸውን ይከለክላል፣ ወይም ከስራ ያባርራል።
• በቀልኝነት፦ ትናንሽ ስህተቶችን እንኳን ይቅር ከመስራትና ከመማር ይልቅ፣ ሰዎችን ለመጉዳትና ለመበቀል እንደ ትልቅ አጋጣሚ ይጠቀምባቸዋል።
5. ሃላፊነት አለመውሰድ (ጥፋትን ወደ ሌላ ማዛወር)
• የአውራ ጣት ስልት (Scapegoating)፦ ተንኮለኛ መሪ ስራ ሲበላሽ ወይም ውድቀት ሲያጋጥም መሪነቱን ወስዶ አያስተካክልም። ይልቁንም ጥፋቱን በሙሉ ወደ በታችኞቹ በማላከክ ራሱን ንጹህ ለማድረግ ይሞክራል።
• የሌሎችን ስኬት መስረቅ፦ ቡድኑ ጥሩ ስራ ሲሰራ ግን ውጤቱን የራሱ ብቻ አድርጎ ያቀርባል።
6. አርቆ አሳቢነት ማጣትና በአጭር እይታ መመራት
• ጊዜያዊ ጥቅም ማሳደድ፦ ለረጅም ጊዜ የሚዘልቅ እቅድና ራዕይ የለውም። ዛሬን በሴራና በውሸት ማለፍ ላይ ብቻ ያተኩራል።
• ለልማትና ለለውጥ ዝግ መሆን፦ አዳዲስ ሃሳቦችን እና ተቋማዊ ለውጦችን አይቀበልም። ለውጥ ከመጣ ጥቅሜ ይነካል ብሎ ስለሚሰጋ የቆየውንና ያልሰራውን አሰራር ሙጥኝ ብሎ ይኖራል።
ባጭሩ፦ ተንኮለኛ መሪ የቆመበትን ተቋም የሚያፈርስ፣ የሰዎችን ተነሳሽነት የሚገድል እና በሰላም አብሮ የመስራት ባህልን የሚያጠፋ "መርዛማ መሪ" (Toxic Leader) ነው።
📌📌እርስዎስ ይህ አይነት መሪ ገጥሞዎት ይሆን?? ይለናል አርበኛው ዝመተኛው ገዳይ የምኒልክ ግልገል አርበኛ ኤፍሬም ባዬ
በሸበል በረንታ የሚገኘው የአገዛዙ ቅጥረኛ የሚሊሻ መዋቅር መፈራረሱ እንደቀጠለ ነው!!
64ኛ ክ/ጦር ሰኔ 06/2018 ዓ.ም
መንገሻ ጎቻው ፖራ ኮማንዶ ወይንየ ቀበሌ ተወላጅ ሲሆን አንድ ኮሪያ ክላሽ ከ40 ጥይት እና የደረት ትጥቅ በመያዝ በሸበል በረንታ የዕድውሃ ከተማ ከሚገኘው የአገዛዙ አረመ* ኔዊ ኃይል በአካባቢው የሚገኝ ማህበረሰብ ላይ እያካሄደ ያለውን ዝርፊያ እና ጭቆና በመቃወም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ከእነ ሙሉ ትጥቁ ተቀላቅሏል።
በሌላ መረጃ በእነማይ ወረዳ ማህበረብረሃን ቀበሌ የሚገኘው የአገዛዙ ኃይል ከፋኖ ሐይሎችን ጋር መፋለም ሲያቅተው በስር-እየሱስ ቀበሌ የጤና ተቋምን እና የአካባቢው ማህበረሰብ የቤት በር በመስበር የቤት እቃቸውን በመዝረፋ እና በማውደም የቀረውን የቤት ዕቃ በመጫን አረመኔዊ ተግባሩን ዛሬም አሳይቷል።
የአብይ አህመድ አገዛዝ በቢቸና እና የዕድውሃ ከተማ የሚኖሩ ነጋዴዎች እና የመንግስት ሰራተኞች ላይ ከፍተኛ ዝርፊ እየፈፀመ ይገኛል። በአገዛዙ ከፍተኛ ዝርፊ ከተፈፀመባቸው ነጋዴዎች እና የመንግስት ተቋማት ውስጥ:-
✍️ከግል ክሊኒኮች 50.000 ብር
✍️ከሆቴል 25.000 ብር
✍️ከሱቅ 2,000 ብር
✍️የጭነት ሲኖ ተሽከረካሪዎች 10.000 ብር
✍️የህዝብ ማመላለሻ 5,000 ብር
✍️የመንግስት ሰራተኛ ከ10.000.ብር እስከ 20,000 ብር ከ10.000 ብር በታች ደሞዝ የሚበሉ ከሆነ 2,000 ብር ከደሞዛቸው እንዲነሳ ተወስኖል።
✍️የጤና ባለሙያዎች የአዳር ብር (ዱቲ) የ7 ወር ደሞዝ እንዳልተከፈለ እና በአስገዳጅ ሁኔታ እያሰሩ እንደሆነ ተረጋግጦል።
✍️ከባጃጅ ሹፊሮች 1,000 ብር እንዲከፍል ትዛዝ ከተሰጠ በሆላ ካልከፈለ ከ2,000 ብር እስከ 3,000 ብር በአስገዳጅ ሁኔታ እንዲከፍሉ ይደረጋሉ። በዚህም የተነሳ በሁለቱም ወረዳ የሚገኙ የከተማ ኖሪዎች አገዛዙ እየፈፀመባቸው ባለውን ዝርፊያ መማረራቸውን ከውስጥ መረጃ ምንጮቻችን አረጋግጠናል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ሰኔ 06/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
ማፍረስ፣ መናድ እንደቀጠለ ነው!!!
አፋብን ላስታ ጄ/ል አሳምነው ፅጌ የጠላትን ሰራዊት ከውጊያ ባሻገር ለምን ዋጋ እንደሚከፍሉ ቆም ብለው በማሰብ ከራሳቸው ጋር የታረቁ ከህዝብ የህዝብ የሆኑ ወንድሞቻችንን አረፈዳችሁ ብለን ሳንቆጣ፣ ሳናገራግር ስቀን በክብር ተቀብለናቸዋል።
አባቶቻችን ከምዓራብ እቅጣጫ ነአኩተለአብ በር፣ በስተምስራቅ አቦ መሳለሚያ፣ በስተደቡብ መካነ-ልዕልት፣ በስተሰሜን መዳጌ ሲደርሱ ከበቅሎአቸው ወርደው፣ ጫማቸውን አውልቀው ስለቦታው ቅድስና እና ክብር ሲሉ የማይሆኑለት አልነበረም።
የአቢይ አህመድ አገዛዝ አምርሮ የሚጠላውን ህዝብ እና እምነት ለማርከስ አቢይ አህመድ የግራኝ አህመድ የግብር ልጅ ነውና ከአባቱ በላይ ጨክኖ የቅዱስ ላሊበላ ውብ እና ብርቅዬ ቤተመቅደሶችን በከባድ መሳሪያ ተኩሶ መታቸው፣ ታንክ ነዳባቸው። ይህንን ግፉን እያደር የተረዱ ከድሃ ልጆች ተውጣጥተው ለዚህ እርኩስ ሰው መንበር ሲባል የውሻ ሞት ይብቃ ብለው የነቁ ሙሉ ትጥቃቸውን በመያዝ ወደ እናት የአማራ ህዝብ እቅፍ በሰላም መጥተዋል።
#ፋኖነት ግፍን ተቃውመህ ፍትህና ርትዕት የምትገዛበት ከወርቅ የከበረ የማዕዘን ድንጋይ ነው!!!
#ድል ለፋኖ!!!
አፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር በስሩ ላሉ የክፍለጦርና የሻለቃ PR መሰረታዊ የICT ክህሎት ስልጠና ለተከታታይ ቀናት ሰጥቶ አጠናቀቀ።
፻ አለቃ ክብርት ገረመው የ 6ኛ ዕዝ 602ኛ ኮር 32ኛ ክ/ጦር ሀለተኛ ሬጅመንት የሻምበል ሁለት አዛዥ 206ኛ ኮር14ኛ ክ/ጦር ንጉስ ተክለሃይማኖት ሻለቃ ተቀላቀለ።
( 206ኛ ኮር) ሰኔ 6/2018 ዓ.ም
================================
የአረመኔው ሰርዊት ምንም አይነት የመዋጋት ብቃትና ፍላጎት ባለመኖሩ ከምመራት ሻምበል 23 አባላት ከድተዋል ያለ ሲሆን ከ206ኛ ኮር 14ኛ ክ/ጦር የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጋር ቆይታ አድርጓል።
ሰራዊቱ ሴቶችን አስገድዶ እንዲደፍር ካድሬዎች በአካል ተገኝተው ያበረታታሉ ያለ ሲሆን የአረመኔው ሰራዊት በንፁሐን ላይ በተለይም በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚደርሰውን የአስገድዶ መድፈር ፆታዊ ጥቃት የስናን ወረዳ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ባወቀ በሰራዊቱ መካከል ተግኝቶ ሲያበረታታ እንደነበር ለአብነት ገልጿል።
የወንበዴዎችን ምር*ጫ ተከትሎ ማብራሪ የሰጠው ፻ አለቃ ክብረት ገረመው የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከ3 በላይ ምር*ጫ ካርድ በመውሰድ ግንቦት 22 እና 23 በተደረገው ማጭበርበር ተሳታፊ ይሁኑ እንጂ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ከደብረ ማርቆስ ከተማ ጀምሮ በሁሉም ቀጠናዎች ከፍተኛ ውጊያ በመደረጉ ምንም አይነት ምር*ጫ አለመደረጉን አስታውቋል ።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከሠም ፪ኛ ኮር ሀይለማርያም ማሞ ክፍለ ጦር በሀገረማርያም ቀጠና በአገዛዙ የሚሊሻ ና የፖሊሥ ኃይል ላይ ድል ተቀዳጀ።
ሰኔ 06/2018ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ
ከሰም ፪ኛ ኮር የኃይለ ማርያም ማሞ ክፍለጦር ሻለቃ አንድ እና የክፍለ ጦር ቃኚና መሃንዲሥ ሻለቆች በጥምረት በሀገረ ማርያም ወረዳ ንፋሥ አምባ ቀበሌ ልዩ ቦታው አሌሊቱ ድልድይ ተበሎ ከሚጠራው ሥፍራ ላይ በአገዛዙ ጥምር ጦር ላይ የፋኖ ሰራዊት ደፈጣ በማድረግ በጠላት ላይ አካላዊና ቁሳዊ ኪሳራ አደረሰ።
ጠላት ሁል ጊዜ እንደለመደው የጥፋት ተልኮውን ለመፈፀም ወደ ንፋስ አምባና ሰኮሩ ቀበሌ መንቀሳቀሱን የደረሳቸው የኃይለ ማርያም ማሞ የምድር ተምዘግዛጊ ጦር የተንቀዠቀዠውን ጠላት ወደ መውደቂያው ጠብቆ በማሥገባት ድንገት ባላሰበው መልኩ መብረቃዊ ጥቃት ሲሰነዘርበት አንድ(1) የሚሊሻ አባል ሲደመሰስ፡ ቀሪ ሁለት ሚሊሻ አካላዊ ጉዳት ደርሶባቸዋል። በተጨማሪ አንድ (1) የፖሊሥ አባል ሥሙ ሳሳሁ የሚባል ከጉልበቱ በታች በነበልባሎቹ ተመቶ ቁስለኛ መሆኑ ታውቋል።
ይህ ዘገባ እስከተጠናቀቀበት ሰዓት ድረስ አውደ ውጊያው እንደቀጠለ ይገኛል። ጠላትም የፋኖ የሀይል ሚዛን ከአቅሙ በላይ በመሆኑ እያፈገፈገና ወደ ኋላ በመመለሥ ላይ ይገኛል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት"
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን "
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
በ2እጅ እነሴ ወረዳ ጥሩሰላም ቀበሌ (አራጢ) ላይ በወቅታዊ ጉዳዮች ከህዝቡ ጋር የክ/ጦር አመራሮች በመገኘት ውይይት ተካሄደ።
^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^
ሰኔ05/2018ዓ.ም
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር በ2እጁ እነሴ ወረዳ ጥሩሰላም ቀበሌ {አራጢ} በጀግኖች የትውልድ ቀዬ የአመራር ውይይት አካሔደ።
የአብይ አህመድ ሰራዊት አራጢን ሲያስብ እንቅልፍ አይተኛም፤ጉልበቱ ይርዳል።
ቀጠናው በአማራ የትግል አብዮት ውስጥ ታሪክ ከሚዘክራቸው የእኔ ተፈራ ደምጤ(ተፌ) እና ሌሎች የትውልድ ቀዬ ነው።
ከ2ኛ ተፈራ ዳምጤ እስከ 54ኛ ክ/ጦር የቀጠለው የቀጠናውን ጀብደኝነት በወትሮው ግለት ማስቀጠል ብሎም ማሻሻል ላይ ከጥሩ ሰላም ቀበሌ ተዋጊ ኃይል ጋር የጋራ ውይይት ተደርጓል።
በቀጠናው የቀበሌ መዋቅርና ህዝባዊ አስተዳደርን ጨምሮ የተገመገመና የወደፊት አቅጣጫ የተቀመጠበት መድረክም ሲሆን
በውይይቱ የህዝባችንን የትግል አረዳድና ቁርጠኝነት የተረዳንበት መድረክ ነበር።
እናደራጃለን ! እንመክራለን! እንፈፅማለን!!
አዲስ ትውለድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!!
አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
የድል ዜና ከወደ ደራ
ሰኔ 06/2018 ዓ.ም
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር በፍቃዱ በላይ ክፍለ ጦር የበረሀው ጀግኖች ትናንት ከማለዳ አንድ(1:00) ሰዓት ከ30 ደቂቃ ጀምረው እስከ ምሽቱ አንድ(1:00) ሰዓት ድረስ በተደረገ እልሕ አስጨራሽ ውጊያ በሰረርኩላ እና በቱቲ ከተሞች መሽጎ በነበረው የአገዛዙ ኃይል ላይ እንደ እሳት እያቃጠሉ ጠንካራ ምት አድርገውበታል። ሆኖም የሥርዓቱ ጅምላ ተጋላቢ ኃይል በመሬት ላይ ሊቀበለው የሚገባውን ታሪካዊ ቅጣት ከጀግኖቹ ክንድ ተመግቧል።
የበረሀው ትንታግ በፍቃዱ በላይ ክፍለጦር አንዲት እሳት የለበሰች ሻለቃ ወደ ሰረርኩላ ከተማ በረገጠችበት ቅጽበት በአገዛዙ ጥርቅም ኃይል ላይ የወሰደችው ፈጣንና መብረቃዊ የማጥቃት ስልት ጠላትን ሙሉ በሙሉ ግራ አጋብቶታል። ከዚሕም የተነሳ ጭንቅ ውስጥ የገባውና መውጫ ያጣው የአገዛዙ ኃይል ጫካ ውስጥ ያደራጀውን ዘራፊውን የ"ሸኔ" ስብስብ ለአጋዥነትና ለሕይወት ማዳኛ የጋበዘ ሲሆን የአናብስቶቹ ክንድ የማይነካ በመሆኑ ነገሩ እዳሠበው ሳይሳካ ቀርርቶበታል።
በመጨረሻም ጠላት የሚያስማርከውን አስማርኮ የጓዶቹን አስከሬን እንኳን ሳይሰበስብ ከተማዋን ጥሎ ወደ ጫካ ፈርጥጧል። ጀግኖቹ የሰረርኩላን ከተማ እስከ ምሽቱ ሁለት(2:00) ሰዓት ሙሉ በሙሉ በቁጥጥራቸው ስር አውለዋታል።
በሌላ በኩል በቱቲ ከተማ በተደረገው አውደ ውጊያ እጅ በአፍ የሚያስጭን ነበር። የቱቲ ከተማ በተናዳፊዎቹ ሻለቆች የባሩድ ጢስ ስትታጠን፣ ባሩዱም ሲቆላ በዋለበት በዚያ አስፈሪ ሰዓት ጠላት ምሽጉን በመነጠቁ ከተማዋን ጥሎ ለመውጣት ተገዷል። የወገን ኃይል ከተማዋን ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር ድላቸውን አጣጥመዋል።
ይሕ በእንዲሕ እንዳለ ጠላት በእውር ድንብርና በፍርሃት ተውጦ ዙ-23 እና ሞርተሮችን እያጮኸ ቢውልም በጀግኖቹ የቦታ ቁጥጥርና በማይበገረው የስነ-ልቦና የበላይነት ግንባሩን ተመትቶ እንደ ቅጠል ሲረግፍ አምሽቶ ፣ በዚህ ደማቅ አውደ ውጊያ የተረጋገጠውና በጀግኖቹ እጅ የገባው የምርኮ ዝርዝር እንደሚከተለው ይፋ ሆኗል፦
➾3 ከፋኖ ከድተው ወደ አገዛዙ ገብተው የነበሩ ባንዳዎች
➾1 የአገዛዙ ካድሬ
➾3 የሚሊሻ አባላት
➾የተማረከ ንብረት ዝርዝር ፦
➾8 ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች
➾4 የወገብ ትጥቅ
➾1 የደረት ትጥቅ
➾6 የእጅ ቦንቦች እና... በርካታ ተተኳሽ ጥይቶች በጀግኖቹ እጅ ገቢ ተደርገዋል።
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!"
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን "
የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
አድሜን እፈልጋለሁ አድሜን መሆን የሚፈልግ እውነተኛውን የአማራ ትግል መምራት የሚችል ሰው ከታች በአለው ሊንክ አውሩን
