ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
رفتن به کانال در Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
نمایش بیشتر2 936
مشترکین
-124 ساعت
+3307 روز
+38330 روز
آرشیو پست ها
ለፍኖተ ሰላም ከተማ እና ለአካባቢው የተላለፈ ጥብቅ መልዕክት!
ከአፋብን ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 109ኛ ኮር 77ኛ ክፍለጦር ለፍኖተ ሰላም እና አካባቢው ላላችሁ ቁማር ቤቶች ማለትም፦ካርቴላ ቤት፣ቢንጎ ቤት እና ካርታ ቤት ፣ተጫዋቾችና አጫዋቾች በሙሉ የተላለፈ ማስጠንቀቂያ!
ቁማር ፍኖተሰላም ላይ እንደ ህጋዊ ስራ ሆኖ ከተጀመረ ሰነባብቷል ይህ አረመኔው ስርዓት የፍኖተሰላምን ህዝብ በኢኮኖሚና በማህበራዊ ለማሽቆልቆል ያመቸው ዘንድ በውስጡ ባደራጃቸው መረጃወቹ ከተማው ውስጥ የቁማር ህጋዊ ፍቃድ ሰጦ እያሰራ እንደሆን ደርሰንበታል።
ይህንን ስራ በዋነኚነት እየሰራችሁ ያላችሁ የዚህ ስርዓት ምስለኔወች እና ቁማር ቤቶች ስማችሁን በዝርዝር ከመጥቀሳችን በፊት ከዚህ እኩይ ተግባራችሁ በአስቸኳይ እንድታቆሙ ስንል መልክታችንን እናስተላልፋለን።
በመጨረሻም ይህንን መልዕክት ተላልፋችሁ የምትገኙ ከሆና አፋብን ምዕ/አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 109ኛ ኮር 77ኛ ክፍለ ጦር ከባድ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን እናሳውቃለን።
ምንጭ፦ በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 77ኛ ክፍለ ጦር የህዝብ ግንኙነት ክፍል!
የራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር ልዩ የወታደራዊና ፖለቲካዊ አቅም ግንባታ ተሃድሶ መርሃ ግብር አከናወነ!!
ሰኔ 29/2018 ዓ.ም
ተሃድሶ ለወታደር ዘርፈ ብዙ የስኬታማ ወታደራዊ ግንባታ ስራዎች የሚከናወኑበት የወታደራዊ ሳይንስ ክፍል አካል ሲሆን፣ ወታደራዊ ግዳጆችን በመገምገም፣ የአመርና የሰራዊቱን ወቅታዊ የፖለቲካ ግንዛቤ በማሳደግ ህዝባዊነትን የተላበሰ የፋኖ ሰራዊት መገንባትን ራዕይ ያደረገ ለየትኛውም ግዳጅ ብቁ እና በከፍተኛ የሞራል ስንቅ የተሞላ አማራዊ ስነልቦና የተላበሰ ዘመናዊ የአማራ ፋኖ ሰራዊት የማደራጀት ዓላማ አንግቦ የፖለቲካዊና የወታደራዊ ሳይንስ ትምህርቶች በጥምረት በአንድ መድረክ ላይ የሚሰጡበት ዘመናዊ የማታገያ ጥበብ ነው።
የአፋበን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አካል የሆነው ለራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር ከሰኔ 24/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አምሥት(5) ቀናት ልዩ የተሃድሶ መርሀ ግብር ለክፍለጦሩ አመራርና አባላት ሰፊ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ግንባታ በመስጠት የተሳካ የግንባታ መድረክ ማካሄዱን የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ለዕዙ ዜና ክፍል በላከው የግንባር መረጃ አስታውቋል።
በዚሁ የግምገማና የግንባታ መድረክ ላይ በየደረጃው የሚገኙ የድርጅትና የዕዝ አመራሮች በአካል ተገኝተው ለክፍለ ጦሩ አባላት ውጤታማ ስልጠናውን የሰጡ ሲሆን፣ የአፋብን ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ፊትአውራሪ ባዩ አለባቸው እና የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ፋኖ አከበር ስመኘው እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የአሳምነው ዕዝ አመራሮች በተዘጋጀው የተሃድሶ መርሀ ግብር ላይ በአካል ተገኝተው ለራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር አባላትና አመራሮች በቂ ግንዛቤ መስጠታቸውን ኮሩ አክሎ ገልጿል።
በመድረኩም ስለ ትግሉ አሁናዊ ሁኔታ፣ ስለ ማህበረሰብ አያያዝ እንዲሁም ስለ ውስጣዊ አንድነት ሰፊና ጥልቅ ውይይት በማድረግ በተለዬ አቀባበል ዓላማና ግብ ተኮር መግባባቶች የተፈጠሩበት የተሳካ መድረክ ሲከናወን ሰንብቷል።
ይህንን ድርጅታዊ የሆነ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ግንባታ ተከትሎ፣ የሰራዊቱን ሞራል ይበልጥ ከፍ ያደረገ ደማቅ የተሃድሶ መርሀ ግብር ሲከናወን፣ ይህን የተግባር ተኮር ስልጠና እስከ ግንባር ምሽጎች ድረስ በመዝለቅ የሰራዊቱ የሞራል ማማ በመሆን የሚታወቁት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ ዘረያዕቆብ ፩ኛ ኮር የናደው ክፍለ ጦር የባህል ቡድን አባላት የፕሮግራሙ ድምቀት ሆነው የተሳተፉበት መርሀ ግብር የተካሔደ ሲሆን፣ በዕለቱም የአማራን ማንነትና ባህል የሚገልጹ ልዩ ልዩ የባህል ጭውውቶችና ክዋኔዎች ቀርበው ለሰራዊቱ አባላት ከማነቃቃት አልፎ ለሰራዊቱ የሞራል ስንቅ በመሆን የተሳካ መድረክ ተከናውኗል።
የስልጠናው ተሳታፊ ከሆኑት የራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር ሰራዊትና አመራሮች በሰጡት አስተያየት፣ ይህ ዓይነቱ ድርጅታዊ ስራና የግንባታ መርሃ ግብር ቀደም ሲል የነበሩ በርካታ ብዥታዎችን ያጠራ መሆኑን በመግለፅ፣ አያይዘውም ይህ መድረክ ቀጣይ ለምናደርገው የተቀናጀ ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግል ምቹ ሁኔታ የፈጠረ ነው፤ ትግላችንም ከተናጠል ወደ ህብረት የተሸጋገረበት በመሆኑ፣ በማንኛውም ሁኔታና ሰዓት ለህልውና ትግሉ የምንከፍለውን መስዋዕትነት በደስታና በሙሉ ልብ እንድንወጣ ያደርገናል ብለዋል።
ራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር የተሰየመበት የጀግናው የራስ አበበ አረጋይ ስም ተራ ስያሜ ብቻ እንዳልሆነ የገለጹት አመራሮቹና አባላቱ፣ የህዝብ ፍቅርንና በፅናት ለዓላማ የሚደረግ ተጋድሎን ከክፍለ ጦሩ የአሁናዊ ህልውና ትግል ጋር በማቆራኘት የስልጠና ቆይታቸውን ከታሪክ ጋር አነፃፅረው ሀሳባቸውን ገልፀዋል።
የራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦርም ከትንሽ የሰው ሃይልና ትጥቅ በመነሳት በከፍተኛ ፍጥነት አሁን ግዙፍ ከሚባሉ ክፍለ ጦሮች ተርታ እንድትሰለፍ ያስቻላት የአመራሮቿ እና ሰራዊቱ የአርበኛው ራስ አበበ አረጋይ የፅናት ፈለግን በመላበስ ሌት ከቀን ተግተው በመስራታቸው መሆኑንም በመድረኩ አስታውሰዋል። ታዋቂው አርበኛ ራስ አበበ አረጋይ በፋሺስት ጣሊያን ወረራ ወቅት የሸዋ አርበኞችን በማስተባበርና በመምራት፣ ለሀገር ሉዓላዊነትና ለህዝብ ነፃነት ያደረጉት ተጋድሎ ዛሬም ለክፍለ ጦሩ አባላት ታላቅ የፅናት ምንጭ መሆኑም ተነስቷል።
በመሆኑም የክፍለ ጦሩ አባላት ትናንት በታሪክ እንደተደረገው ሁሉ፣ ዛሬም ሆነ ነገ ይህንን ታሪካዊ ስም በተግባርና በልዩ ልዩ የጦር ሜዳ ጀብዱዎች እንደሚያስጠሩት በጋራ ቃል በመግባት ለተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው የተሃዲሶ መርሀ ግብር በስኬት ተጠናቋል ሲል የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ገልጿል።
በመጨረሻም የክፍለ ጦሩ አመራሮችና ሰራዊት ስለ ህዝብና ዓላማ፣ ስለ አማራ ታሪክና ፋኖነት እንዲሁም ስለ ድርጅትና ድርጅታዊነት ያላቸውን ግንዛቤ ይበልጥ በማሳደግ፣ ቀጣይ መርህን የተላበሱ አሰራሮችን በማስተካከል ተግተው በመስራት ድርጅቱ ካስቀመጠው ግብ ላይ ለመድረስ ዝግጁ መሆናቸውን በቁርጠኝነት አረጋግጠዋል ሲል ኮሩ በግንባር መረጃው አረጋግጧል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት !
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ እና የአፋብን ምኒልክ ዕዝ ወቅታዊ የጋራ የውይይትና ህዝባዊ መድረኮችን አካሄደ!!
ቀን 29/10/2018 ዓ.ም
በቀነ 28/10/2018 ዓ.ም በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ አፄ ዘረያዕቆብ ፩ኛ ኮር በአፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር ስር ብርጌዶች በተገኙበት በወቅታዊ የጠላት አሰላለፍ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ የክፍለ ጦሩ ዋና ሰብሳቢ ፋኖ አቡሽ ጌታሁን ሰራዊቱን የሚያነቃቃና የሞራል ዝግጁነት እንዲኖረው የሚያደርግ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፣ ሌሎች የክፍለ ጦር አመራሮችም በተመሳሳይ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በዕለቱ የተገኙት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዘመቻ መሪ ፋኖ አሳልፍ ደስታ (ቀጭን) አባት አርበኛው የሰራዊቱ የኋላ ደጀን በመሆን ትግሉን መደገፍና ማታገል እንዳለበት ገልጿል፣ ለዚህም ከወትሮው በተለየ ሁኔታ መዘጋጀት እንደሚገባ አሳስበዋል። የዕለቱ የክብር እንግዳ የነበሩው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዋና መሪ እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ በበኩላቸው በድርጅታዊ አንድነቱ መፈጠር የተሰማውን ደስታ ገልፆ፣ እኛ የአባቶቻችን ልጆች ነን" ካሉ በኋላ ጠላትን የማያዳግም እርምጃ ለመውሰድ ሞትን መፍራት እንደማይገባና ሞትን የማይፈራ ሰራዊት ሁልጊዜም እንደሚያሸንፍ ገልጿል ለዚህም ሁሉም ዝግጁ እንዲሆን ጥሪ አቅርቧል። አባት አርበኞቹም በበኩላቸው በተደረገው የማነቃቃትና ጠላትን በጋራ የመመከት ውይይት እንዲሁም በታየው የወትሮ ዝግጁነት ፕሮግራም እጅግ መደሰታቸውን አስታውቀዋል።
በሌላ ዜና ከቀን 27-28/10/2018 ለተከታታይ ሁለት ቀን በግሼ ራቤል ወረዳ በጎልታ መዘራዝር ቀበሌ ከሁለቱም እዞች (ከአፋብን ምኒልክ እዝ እና ከአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ) የተወጣጡ አመራሮች የተገኙበት ህዝባዊ መድረክ ተካሂዷል። ከ700 በላይ የህዝብ ቁጥር የተገኘበትና ከእስልምናም ከክርስትናም የሃይማኖት አባቶች የተሳተፉበት ይህ ስብሰባ በጸሎት ተጀምሮ በጸሎት ተጠናቋል። በመድረኩ ማጠቃለያ ላይም ከማህበረሰቡና ከአመራሩ የተገኙ ጥንካሬዎችን በማስቀጠልና ያሉትን ክፍተቶች በመሙላት ከዚህ በላይ በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ ተደርሶ ስብሰባው በሰላም ተጠናቋል።
የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት ዓሳምነው ዕዝ ህዝብ ግኑኝነት መምሪያ
+2
የሚሰጣቸውን ግዳጅ ለመፈፀም መዘጋጀታቸውን የባሶሊበን ወረዳ አርበኞች ተናገሩ
ሰኔ 28/2018 ዓ.ም
""""""""""""""""""""""""""“"""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር በባሶሊበን ወረዳ የነበሩ ዘራፊዎችን ከቀጠናው ከ አፀዳ በኋላ ከማህበረሰብ ክፍሎች ጋር እየተወያየ ይገኛል። ከደብረ ማርቆስ የጁቤ በሚወስደው አውራ ጎዳና ከጠላት ጋር በመነጋገር ዝርፊያ ሲፈፅሙ በነበሩ ዘራፊዎች ላይ የተቀናጀ ዘመቻ ያደረገው 34ኛ ክ/ጦር ቀጠናውን ከአጥፊዎች በማላቀቅ የህዝብ ደህንነት እየጠበቀ ነው።
ትግሉን ህዝባዊ መሰረቱን ጠብቆ እንዲጓዝ አጥብቆ ሲሰራ የነበረው 206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር በአለፉት ወራቶች በደጀን፣ አወባል፣ አነደድ፣ ባሶሊበን ወረዳዎች በነበሩ ሰፊ ህዝባዊ መድረኮች ከህዝብ ጋር ምክክር ማድረጉ ይታወሳል ። በተየያዘም ክ/ጦሩ ከባሶሊበን ወረዳ አርበኞች ጋር በድርጅታዊ ተልዕኮዎች ዙሪያ ምክክር አድርጓል።
በንቅናቄ መድረኩ ሰፊ ሕዝባዊ ተሳትፎ የታየበት ሲሆን አርበኞች የሚሰጣቸውን ማንኛውንም ግዳጅ በብቃል ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ህዝባዊነት ለሁንተናዊ ትግል የሚያደርገውን አስተዋጽኦ እንረዳለን ያሉት አርበኞች ክ/ጦሩ በቀጠናው የፈፀማቸውን የህግ ማስከበር ዘመቻ አድንቀው የትግሉን ፍፃሜ በድል ለመቋጨት በሚደረገው ተጋድሎ ከሰራዊቱ ጎን እንደሚሰለፉ አረጋግጠዋል።
አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ!
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
አሳዛኝ ዜና
የኦሮሙማ አገዛዝ በዳባት ወረዳ ከአንድ ሙሉ ቤተሰብ ላይ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ፈፅሟል።
የ208ኛ ኮር በተለያዩ ግንባሮችና ስትራቴጂካዊ ቦታዎች እያስመዘገበ የሚገኘውን ታሪካዊ ድሎች አጠናክሮ ቀጥሏል። ከሰሞኑ በተለያዩ አውደ ውጊያዎች የፋኖን ክንድ መቋቋም ያቃተው የገዢው ሥርዓት የጦር ኃይል ከፍተኛ ምትና ኪሳራ የደረሰበት ሲሆን በዛሬው ዕለትም ውጊያው በከፍተኛ ሁኔታ ቀጥሏል። በጫርቢጣ፣ በጠበረት አቦ እና በጥንጫየ በኩል የገባው የጠላት ኃይል በ208ኛ ኮር ልዩ ልዩ የጦር አሃዶች እየተመታና እየተቀጠቀጠ የሚገኝ ሲሆን የፋኖ ስምሪትም በአካባቢው የበላይነትን በመያዝ የጠላትን እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ እየገታው ይገኛል።
ይሁን እንጂ በጦር ሜዳ ሽንፈትን ያስተናገደው የጠላት ኃይል የተለመደው የብቀላ እርምጃውን በንጹሃን ዜጎች ላይ አሳርፏል። ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር ዞን በዳባት ወረዳ ልዩ ስሙ "13" በተባለው አካባቢ በተደረገው ከባድ ውጊያ የፋኖን ክንድ መቋቋም ያቃተው ይኸው የገዢው ሥርዓት ግሪሳ ጦር መከላከያ የሌላቸውን ንጹሃን አርሶ አደሮች ላይ ያነጣጠረ ጭፍጨፋ ፈጽሟል። በተለይም "ዘና ጎዴ ማርያም" በተባለችው ልዩ ቦታ 19 ወንድ ገበሬዎችን እና 2 ሴቶችን ጨምሮ በአጠቃላይ 21 ንጹሃንን በአሰቃቂ ሁኔታ ረሽኖ አልፏል።
ይህን የጭካኔ ድርጊት ይበልጥ አሳዛኝና ለየት የሚያደርገው የአንድ አባወራ አባላትን ለይቶ ማጥፋቱ ነው። በዚህ የሰሞኑ እረሸና ጫቅሉ አማረ፣ አምባቸው አማረ፣ ሞላ አማረ እና ደስታ አማረ የተባሉ አራት ወንድማማቾች በአንድ ላይ የተገደሉ ሲሆን በተጨማሪም የአምባቸው አማረ እና የደስታ አማረ ልጆች ጭምር ተለይተው ተረሽነዋል። በአጠቃላይ ከአንድ ቤተሰብ ብቻ ከ8 በላይ አባላት በጠላት የጭካኔ በትር ያለጥፋታቸው ተቀጥፈዋል። ይህ የጠላት የሰሞኑ ግፍና ሰቅጣጭ ድርጊት የፋኖን ኃይል ይበልጥ የሚያስቆጣና ለህልውና ለፍትህ ለነፃነት የሚደረገውን ትግል የሚያፋጥን መሆኑን እናሳውቃለን።
✅ድል ለአማራ ህዝብ!!!
ለተሰው ቤተሰቦች ነፍሳቸውን በአፀደገነት ያሳርፍልን
የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከአውደ ውጊያ ጎን ለጎን የህዝብን ሰብል የመሰብሰብ ስኬት እያከናወነ ይገኛል!!
የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ምክትል ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ኢሳያስ ደመቀ፣ በግንባር ከሚያደርገው ወታደራዊ አመራር ጎን ለጎን የፋኖ አናብስትን በማስተባበር የአካባቢውን ማህበረሰብ ሰብል የመሰብሰብ ስራ በስፋት እያከናወነ ይገኛል።
የአብይ አህመድ ወራሪ ሰራዊት የአማራን ህዝብ ህልውና ለማጥፋትና በረሃብ ለመቅጣት በማለም፣ የደረሰውን አዝመራ በታንክና በሞርተር እየደበደበ እያቃጠለ እንደሚገኝ ይታወቃል። ይህንን የጥፋት ቀጠና ለመከላከልና የህዝቡን የኑሮ ዋስትና ለመጠበቅ፣ የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ምከትል ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ኢሳያስ ደመቀ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም የፋኖ አባላት በየደቂቃው ከጠላት ጋር እየተፋለሙ፣ በትርፍ ሰዓታቸው ግን ማጭድ ይዘው የገበሬውን ሰብል በመሰብሰብ ላይ ይገኛሉ።
በዚህም የአማራ ልጅ ፋኖ ህዝብ ነው፣ ህዝቡ ደግሞ ፋኖ ነው። ጠላት ህዝባችንን ከምድር ገፅ ለማጥፋት እንዲሁም በረሃብ ለመጨረስ የከፈተውን የኢኮኖሚና የሥነ-ልቦና ጦርነት የምንቀለብሰው በደማችን ብቻ ሳይሆን በላባችንም ጭምር ነው ሲሆን
በአሁኑ ወቅት በዕዙ ስር የሚገኙ የፋኖ አናብስት በሚንቀሳቀሱባቸው ቀጠናዎች ሁሉ የደረሱ ሰብሎችን ፈጥኖ በመሰብሰብ ለህዝቡ እፎይታን እየሰጡ ይገኛሉ።
እኛ የምንዋጋው ህዝባችን እንዲኖር ነው" ይላሉ በስፍራው የሚገኙት ተዋጊዎች። "ሰብሉ ህልውናችን ነው፤ ጠላት ሊያጠፋው የሞከረውን እኛ በደማችንና በላባችን እንጠብቀዋለን። ፍቅርን፣ ጀግንነትንና ሰብአዊነትን አጣምሮ የያዘው ሸዋ ጠቅላይ ግዛት የአሳምነው ዕዝ፣ በአውደ ውጊያው ብቻ ሳይሆን በህዝብ ፍቅርም የማይረሳ ታሪክ እየሰራ የወርቅ ማዕበል የመሰለው የማህበረሰብ ሰብል በመስብሰብ የፋኖና የህዝብ አንድነት መሆኑን ያረጋገጠና አንደኛው ምዕራፍ ነው።
ሰኔ 28/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ
ክፍለ ጦሩ በሚያስተዳድራቸው ቀጠናዎች የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍል ጋር ህዝባዊ ውይይቶች እየተካሄዱ ነው።
64ኛ ክ/ጦር ሰኔ 28/2018 ዓ.ም
~~~~~~~
የ64ኛ ክ/ጦር፣ የእነማይ ወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች እና በተገኙበት በእነማይ ወረዳ የቀብሃና ቀበሌ ህዝባዊ ውይይት አካሂደዋል።
በህዝባዊ ውይይት መድረኩ ለተገኙት የማህበረሰብ ክፍል የአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ያለበት ወቅታዊ ሁኔታ ሰፊ ግንዛቤ በመስጠት በቀበሌ ጊ/መንግስት አመራሮች የፍትህ አሰጣጥ የቀበሌ መልካም አስተዳደር የፀጥታ ጉዳይ፣ ህገ ወጥ የኦል መሬት ማስከበር የፋይናንስ እና ሎጀስቲክ አሰባሰብ በተመለከተ ውይይት በማድረግ በመገምገም ለቀበሌ ጊ/መንግስት አመራሮች አቅጣጫ ተሰጥቷል።
በውይይት መድረኩ የተገኙት የማህበረሰብ ክፍል እንደተናገሩት በአማራ ህዝብ ላይ ከፍተኛ የሆነ በደል እና ጭቆና የሚፈፅም የአብይ አህመድ አምባ ገነን አገዛዝ ለመገርሰስ ህዝባችን ከፋኖ ጎን መሆኑን በሰፊው አስረድተዋል።
አድስ ትውልድ፣ አድስ አስተሳሰብ፣ አድስ ተስፋ
ሰኔ 28/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር የእነማይ ወረዳ ጊ/መንግስት የሚዲያ ክፍል ኃላፊ
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ አሃድ የሆነዉ 106ኛ ኮር 22ኛ ክፍለጦር ለአምስተኛ ዙር ሰልጣኝ ፋኖዎች በድምቀት አስመረቀ!!
የአማራን ህዝብ መዋቅራዊ የዘር ማጥፋት እቅድን በመረዳት ሞት የታወጀበትን ህዝብ ለመታደግ ትውልዱን ወታደራዊ እና ወታደራዊ ሳይንስ ስልጠና በማሰልጠን ዘመን ተሻጋሪ ታሪክ ለመስራት ቆርጠው የተነሱት የመቄት ምድር ተርቦች በደማቅ ሆኔታ ሰልጣኝ ፋኖዎችን ለአምስተኛ ዙር በድምቀት አስመርቀዋል።
ነፃነትና ዲሞክራሲ ከአሸባሪዎች ዘንድ አንገትን በመድፋት እንደማይገኙ የተረዱት ትውልዶች ወደ ስልጠና ማዕከል በመግባት የወታደራዊና ፖለቲካዊ ስልጠናቸውን በሙሉ ብቃት በማጠናቀቅ የአማራን ህዝብ ከአደጋና ከጥፋት ለመመከት ቃል ገብተዋል።
ለበርካታ ወራቶች ሲሰለጥኑ የነበሩ ሰልጣኝ ፋኖዎች በምርቃት ስነ-ስርዓት ላይ ለአማራ ህዝብና ለአላማቸው በታማኝነት እስከ ህቅታ እንጠብቃለን ሲሉ ቁርጠኝነታቸውን አሳይተዋል።
በዚህ የምርቃት ስነ-ስርዓት ላይ የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሃላፊ አርበኛ ብርሃን አረጋ "የአማራ ሕዝብ እና ወጣት በዚህ ወሳኝ ወቅት የፓለቲካ እና ወታደራዊ ክህሎቱን ማዳበር እንዲሁም ራሱን ለመንግስትነት ማዘጋጀት አለበት ብለዋል። አርበኛው አያይዞም ለቀጣይ ትልቅ ተልዕኮ መሪውም ተመሪውም ራሱን ማዘጋጀት አለበት" በማለት መልክታቸውን አስተላልፈዋል።
በዚህም ምርቃ ላይ የ106ኛ ኮር ሕዝብ ግንኘነት ሃላፊ አርበኛ መ/ር መኩሪያ አጋዤ "እኛ የትውልድ ስራ ነው የያዝነው በዚህ ወቅት እንደ 106ኛ ኮር ከባድ መስዕዋትነት እየከፈልን ያለንበት ወቅት ቢሆንም ሚስማር ሲመቱት ይጠብቃል እንዲሉ አበው የመሪወቻችንን አላማ ማስቀጠል አለብን ብለዋል።
አርበኛው አክለውም ሰልጣኞች ለዚህ ትግል እና ለአላማቸው ራሳቸውን አሳልፈው እንዲሰጡ እና በፅናት እንደ ጀግኖች እንዲታመኑ አሳስበዋል።
በዚህም የ106ኛ ኮር ም/ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ማረጉ አስፋው ለተመራቂወች ወታደራዊ መምሪያ የሰጡ ሲሆን የፋኖን ትግል ማንኛውም አማራ ዳር ማድረስና ጠብቆ መኖር ተፈጥሯዊና ብሔራዊ ግደታቸው ነው በማለት መልክታቸውን አስተላልፈዋል።
በፕሮግራሙ ላይ የ106ኛ ኮር ከፍተኛ አመራር የሆነችው አርበኚት መቅደስ፣ የ22ኛ ክፍለጦር አዛዥ አርበኛ ክንዱ ሙላው፣ የ22ኛ ክፍለጦር ም/አዛዥ አርበኛ ሞገስ ካሴ እና የ22ኛ ክፍለጦር ዘመቻ መሪ አርበኛ ሰለሞን መልዕክት እንዲሁም ለቀጣይ ተልዕኮ የሚያዘጋጅ አነቃቂ ንግግሮችን አድርገዋል ሲል የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ መረጃዉን አድርሷል!!
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
ሰኔ 28/2018ዓ.ም
በአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝባዊ እና የወታደራዊ ወቅቱን ያገናዘበ ሰፊ ውይይት ተካሄደ!
በአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት በአሳምነው ዕዝ ስር በሚተዳደሩ ቀጠናዎች፣ የዕዝ የህዝብ አስተዳድር መምሪያ አርበኛ ኤፍሪም ባዩ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በሰፊው ህዝባዊ ውይይት ተኣሔደ። ውይይቱ የተካሄደው በመንዝ እና ግሼ አውራጃ፣ የመዝ ቀያ ገብረኤል ወረዳ 013 ቀበሌ በዚህ ህዝባዊ መድረክ ላይ ሶስት ዋና ዋና አጀንዳዎች ተነስተው ጥልቅ ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን፣ ዝርዝሩ እንደሚከተለው ቀርቧል፡-
1. የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ውጤት መቃወም፦ በውይይቱ ላይ ተሳታፊዎቹ "የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ማጭበርበር የተሞላበት፣ ለሀገርም ሆነ ለህዝብ ታማኝነት የሌለው ነው" ሲሉ ኮንነዋል። የአሁኑ ገዥ አካል "ተመረጥኩ" የሚለው በውሸት እና በማጭበርበር መሆኑን አመራሮቹና ህዝቡ በጋራ አንስተዋል።
2. የአማራ የህልውና ትግል ወቅታዊ ሁኔታ፦የአማራ ህልውና ትግል በአሁኑ ወቅት የደረሰበትን ከፍተኛ ደረጃ በተመለከተ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን፣ ትግሉ ወደፊት የሚሻቸውን ስትራቴጂዎችና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስመልከት ሰፊ ምክክር ተደርጓል።
3. የሽግግርና የጊዜያዊ አስተዳደር ምስረታ ግምገማ፦ የብልፅግናን መዋቅር በማፍረስ፣ በአካባቢው በፋኖ ሊመራ የሚችል ጊዜያዊ መንግስት መመስረቱ የሚታወስ መሆኑን የጠቀሱት አመራሮቹ፣ የነበሩትን አሰራሮች በመገምገም በቀጣይ ህዝቡን በተሻለ ሁኔታ እንዴት ማስተዳደር እንደሚቻልና መዋቅሩን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል።
በዚህም በኮር ምኒሊክ ክፍለጦር የተሰጠ የስነ-ልቦና ግንባታ በሌላ በኩል፣ በአምደፄዎን ኮር ምኒሊክ ክፍለጦር ሁለተኛ ሻለቃ ስር ለሚገኙ አመራሮችና ሰራዊት አባላት ያነጣጠረ ተመሳሳይ የውይይትና የልማት መድረክ ተካሂዷል ። በዚህ ወታደራዊ መድረክ ላይ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፡- የመሪነት ባህሪ ግንባታ፦ ለአመራሩና ለሰራዊቱ በስነ-ምግባር፣ በስነ-ልቦና እና በመሪነት ባህሪያት ዙሪያ ጠንካራ ግብዓትና ተሰጥቷል።የትግሉ ወቅታዊ ቁመና፦ በትጥቅ ትግሉ በኩል እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶችና ትግሉ የደረሰበት ደረጃ ላይ ግምገማ ተደርጓል። የድርጅት አስፈላጊነት፦ ጠንካራ ድርጅታዊ መዋቅር መኖሩ ለትግሉ ስኬት ያለውን ወሳኝ ሚና በተመለከተ ለሰራዊቱ ሰፊ ግንባታ ተካሂዷል።
ሰኔ 28/2018 ዓ.ም
አሳዛኝ ዜና!!!
የፋሽስቱ ኦህደድ ብልፅግና ወንበር ጠባቂ ሰራዊት በጭካኔ ተግባራቸው ሰይጣንን የሚያስንቁ ወሮ በሎች በራያ ቆቦ ወረዳ 015 ቀበሌ አዋስ ንፁህ አርሶ አደር በጭካኔ ገደሉ።
በቀን 25/10/2018/ዓም በሰሜን ወሎ ዞን በራያ ቆቦ ወረዳ 015 ቀበሌ ልዩ ስሙ አዋስ አቶ ሞላ መኮነን የተባለ ግለሰብ ከግብርና ስራው ውጭ ምንም የማያውቅ ሰላማዊ አርሶ አደር ወታደራዊ የደንብ ልብስ አልብሶ፣ ከቤተሰቦቹ ፊት ከመኖሪያ ቤቱ በአሰቃቂ ሁኔታ በጥይት ደብድቦ መረሸኑ በምንም መስፈርት ተቀባይነት የሌለው የጭካኔ ጥግ ነው።
በአማራ ፋኖ ምት የተበሳጨው አገዛዙ ንፁህ አርሶ አደርን ቤተሰብ እያየ የሰው ልጅ ህይወት በጭካኔ መቅጠፍ ፣ የኦህደድ ብልፅግና የአማራን ህዝብ የዘር ማጥፋት ፕሮጀክት ዋና ማሳያ ነው ።
በተጨማሪ በዚሁ ቀበሌ፣ ምንም የማያውቁ አርሶ አደሮች ላይ የተፈፀመው ድብደባና አፈና ንብረትን ሰብስቦ በእሳት ማቃጠል ፣ አገዛዙ የአማራን ህዝብ እንደ ጠላት እያየ መሆኑን በግልጽ አሳይቷል።
እንድሁም 90000 ብር (ዘጠና ሽ ብር)፣ ሶስት እስማርት ስልኮች ፣ ሶስት ፓወር ባንክ፣ ወርቅና የአካባቢወ ማህበርሰብ በላቡ ያፈራውን የሱቅ ሸቀጦችን በመዝረፍ ህዝባችንን ለማሸማቀቅ የብልፅግናው አገዛዝ ህጋዊ ፍቃድ የሰጠበት መሆኑን በገሀድ ተገንዝበናል።
አገዛዙ የሚሄድበት የጥፋት መንገድ ትግሉን ማስቀረት ሳይሆን በከፍተኛ ደረጃ ህዝባችን አቢዎታዊ ችቦ የሚለኩስበት ጊዜ ቅርብ መሆኑን አረጋግጠናል።
ያለ ጥፋት፣ ያለ ፍርድ፣ ያለ ሰብአዊ ክብር የሚፈጸም የኃይል እርምጃ የጀግንነት መገለጫ ሳይሆን የፍርሃትና በታሪክም እንደሚታወቀው የአባገነኖች የመጨረሻ የመውደቂያ ምልክት ነው።
በመሆኑም ፍትህ የራቀው፣ ዜጋ በገዛ ሀገሩ እንደ እንግዳ የሚታደንበት ዘመን ያበቃል!!! የንፁሃን ደም መሬት ላይ ፈሶ አይቀርም!! ታሪክ ሁሉንም ይመዘግባል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት"
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ወሎ(ቤተ-አማራ) ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰኔ 28/2018 ዓ.ም
