fa
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

رفتن به کانال در Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

نمایش بیشتر
2 936
مشترکین
-124 ساعت
+3307 روز
+38330 روز
آرشیو پست ها
አሳዛኝ ዜና!!! የፋሽስቱ ኦህደድ ብልፅግና  ወንበር ጠባቂ ሰራዊት በጭካኔ ተግባራቸው ሰይጣንን የሚያስንቁ ወሮ በሎች በራያ ቆቦ ወረዳ 015 ቀበሌ አዋስ  ንፁህ አርሶ አደር በጭካኔ ገደሉ። በቀን 25/10/2018/ዓም በሰሜን ወሎ ዞን በራያ ቆቦ ወረዳ 015 ቀበሌ ልዩ ስሙ አዋስ አቶ ሞላ መኮነን የተባለ ግለሰብ  ከግብርና ስራው ውጭ ምንም የማያውቅ ሰላማዊ አርሶ አደር  ወታደራዊ የደንብ ልብስ አልብሶ፣ ከቤተሰቦቹ ፊት ከመኖሪያ ቤቱ  በአሰቃቂ ሁኔታ በጥይት ደብድቦ መረሸኑ በምንም መስፈርት ተቀባይነት የሌለው የጭካኔ ጥግ ነው። በአማራ ፋኖ ምት የተበሳጨው አገዛዙ ንፁህ አርሶ አደርን ቤተሰብ እያየ የሰው ልጅ ህይወት በጭካኔ  መቅጠፍ ፣ የኦህደድ ብልፅግና  የአማራን ህዝብ የዘር ማጥፋት ፕሮጀክት ዋና ማሳያ ነው ። በተጨማሪ በዚሁ ቀበሌ፣ ምንም የማያውቁ አርሶ አደሮች ላይ የተፈፀመው ድብደባና አፈና ንብረትን ሰብስቦ በእሳት ማቃጠል ፣ አገዛዙ  የአማራን ህዝብ  እንደ ጠላት እያየ መሆኑን በግልጽ አሳይቷል። እንድሁም 90000 ብር (ዘጠና ሽ ብር)፣  ሶስት እስማርት  ስልኮች ፣ ሶስት ፓወር ባንክ፣ ወርቅና የአካባቢወ  ማህበርሰብ   በላቡ ያፈራውን የሱቅ  ሸቀጦችን  በመዝረፍ ህዝባችንን ለማሸማቀቅ የብልፅግናው አገዛዝ ህጋዊ ፍቃድ የሰጠበት መሆኑን በገሀድ ተገንዝበናል። አገዛዙ የሚሄድበት የጥፋት መንገድ ትግሉን ማስቀረት ሳይሆን በከፍተኛ ደረጃ ህዝባችን አቢዎታዊ ችቦ የሚለኩስበት ጊዜ ቅርብ መሆኑን አረጋግጠናል። ያለ ጥፋት፣ ያለ ፍርድ፣ ያለ ሰብአዊ ክብር የሚፈጸም የኃይል እርምጃ የጀግንነት መገለጫ ሳይሆን የፍርሃትና  በታሪክም እንደሚታወቀው  የአባገነኖች የመጨረሻ  የመውደቂያ  ምልክት ነው። በመሆኑም  ፍትህ የራቀው፣ ዜጋ በገዛ ሀገሩ እንደ እንግዳ የሚታደንበት ዘመን ያበቃል!!! የንፁሃን ደም መሬት ላይ ፈሶ አይቀርም!! ታሪክ ሁሉንም ይመዘግባል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ(ቤተ-አማራ) ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሰኔ 28/2018 ዓ.ም

206ኛ ኮ/ር 14ኛ ክ/ጦር የበረሃኛው ጅበላ ሙተራ ሻለቃ በደብረ ማርቆስ አቅራቢያ ሊባኖስ በመሸገው የአድማ በትን ሰራዊት ላይ ኬሊቱ 9:00 በፈፀሙት ጥቃት ጠላትን ሙትና ቁስለኛ ሲሆን፦ - ወታደራ
+1
206ኛ ኮ/ር 14ኛ ክ/ጦር የበረሃኛው ጅበላ ሙተራ ሻለቃ በደብረ ማርቆስ አቅራቢያ ሊባኖስ በመሸገው የአድማ በትን ሰራዊት ላይ ኬሊቱ 9:00 በፈፀሙት ጥቃት ጠላትን ሙትና ቁስለኛ ሲሆን፦ - ወታደራዊ ሻንጣ - የምሽግ ሸራ -የክላሽ አስቃጥላ - የክላሽ ካዘና - ወታደራዊ የዝናብ ልብስ - ኮዳ እና ሌሎች ቁሳቁሶች ማርኳል ። በተመሳሳይ የ206ኛ ኮር አዳኝ ቡድን በደጀን ከተማ በትናትናው ዕለት ከሌሊቱ 7:30 ወደ ሰሜን አቅጣጫ ለግዳጅ በተጠረነፉ ሚኒሻዎች ላይ በፈፀመው የቦምብ ጥቃት 4 የሚደርሱት ሕይወታቸውን ሲያጡ 3 የሚደርሱት ከባድ ቁስለኛ ሁነዋል። ሰኔ/28/2018 ዓ.ም አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ! የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

ዋና ብሬን ተኳሹን ጨምሮ #5 ሀይሎች ፋኖን ተቀላቀሉ የብልፅግና ካምፕ እየፈራረሰ ነው =========================       .....ሰኔ 28/2018 ዓም  ከአገዛዙ ጋር ወግነው የነበሩ የታጠቁ ሀይሎች የፓራ ኮማንዶ እና የመከላከያ አባላት ከሰዴ እና ከግንደወይን በመውጣት 201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል። 1.መንግስቱ እሱባለው ...ፓራ ኮማንዶ ከሰዴ 2.ሁልጊዜ ዝግጁ ......ፓራኮማንዶ ከሰዴ 3.ዳዊት ሞላ............. መከላከያ ከሰዴ 4.ቸርነት አሳዬ.........ብሬን ተኳሽ 5.ይርጋ ደረጀው ....ሚሊሻ 74 ክ/ጦር መሳሪያ በመያዝ ኛ የተቀላቀሉ ሲሆን በክፍለ ጦር አመራሮችም ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። አሁንም ጊዜው አልረፈደም ወደ ትክክለኛ ማንነታቹህ ተመለሱ የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

ሰበር የድል ዜና ‼️ አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ጀብደኞቹ ልዩ ዘመቻ ንስር ሻለቃ በሸዋሮቢት ከተማ ለሊቱን በጥላት ምሽግ ዘልቀው በመግባት ጥላትን ደምስሰው የተተኳሽ እና መገናኛ ሬዲዎዎችን ሲማርኩ በምሽግ ላይ የበሩት የጥላት ሀይል ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል። የተማረኩ የጥላት ንብረቶች ዝርዝር !! 👉🏾2 የብሬን አፈሙዝ 👉🏾3ሺ የብሬን ተተኳሽ 👉🏾 2-የውጊያ ላይ የሜዳ መነፅር 👉🏾በርከት ያሉ የብሬን ሸንሸሎች 👉🏾የደረት ትጥቅና ከ20 የሚደርሱ የክላሽ ካዝናዎች ተማርከዋል ድል ለአማራ ‼️ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ

+1
ለተከታታይ 5ቀን ድጋፍ እና እንክብከረቤ እየተደረገለት ያለ የመከላከያ ምርኮኞ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ........ሰኔ 27/2018 ዓ.ም የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር ሰኔ 23 2018 ዓ.ም በተደረገ አውደ ውጊያ ሙገር ቻይና ካምፕ በውጊያ ለተማረኩ ለመከላከያ አባላት እየተደረገ ያለ እንክብኬቤ ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 6ቀናት በቂ የሆነ የጤና ክትትል በማድረግ ጉልኮስ በመስጠት አስፈላጊውን የጤና ህክምና እና ድጋፍ እና ክትትል እየተደረገለት ሲሆን የአካባቢው ማህበረሰብ ምግብ በማመላለስ የአማራን ህዝብ አቃፊ ደጋፋ መሆኑን በተግባር እያስመሰከረ ይገኛል። አዲስትውልድ አዲስአስተሳሱብ አዲስ ተስፋ የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201እኛም ኮር ህዝብ ግንኙነት

ሰበር ዜና!!! አፋብን ወሎ ቤተ-አምሓራ ሚኒሊክ ዕዝ 106ኛ ኮር 31ኛ ሰንጥቅ ክፍለ ጦር በዳውንት ወረዳ ታላቅ ጀብን ሲቀናጁ፤ወላዶችንና እናቶችን የአገዛዙ ሰራዊቶች በጤና  ጣቢያ ጥቃት ፈፅመውበታቸዋል!!! በዳውንት ወረዳ  የጠላት ሰራዊትን አይቀጡ ቅጣት ሲቀጣ ሲውል የዘወትር የክፋት አ ባህሪውን በአማራ ህዝብ ላይ ፀያፍ ተግባራቱን ፈፅሟል!!! በታች ዳውንት ምድር እንደ ብላጊ ገብስ ሲዎቃ የዋለው የአገዛዙ ወታደር ሞትና ውርደትን ተከናንቧል። በዚህአውድ ውጊያ ከረፋዱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ አመሻሽ 11:30 ድረስ የዘለቀ ሲሆን በርካታ የግላት ሰራዊቶች እስከ ወዳኛው ተሸኜተዋል። የወር ደመወዙን አስቦ የሚቀሳቀሰው የሪፖርት ዘመቻ የስርዓቱ ዘማቾች በዳውንት ወረዳ ሚትና ቁስለኛ ተደርገዋል።  ይህንን ጉዳቱን መቋቋም የተሳነው ስርዓቱ እናቶች ምጥ ተይዘው ካሉበት ጤና ጣቢያ የአገዛዙ ወታደሮች ዘልቀው በመግባት "ወንድ ከሆነ የወለዳችሁት ነፍጠኛና ፋኖ ነው የወላዳችሁት" በማለት ግፍና እንግለትን በጤና ጣቢያ በወሊድ ላይ የሚገኙ እናቶች ላይ ሲፈፅሙ፤የጋል ከሚባል አካባቢ ላይ ከአንድ ግለሰብ 70 ሽህ ብርና ከአንድ ሌላ ግለሰብ ዶሮን በመዝረፍ ወደ ኩርባ ከተማ ዘርፈው ተመልሰዋል።የአማራን ህዝብ እንደ ህዝብ የማጥፋት አላማን አንግቦ የሚቀሳቀሰው ስርዓት  በዚህና በሌላ የጥፋት እንቅስቃሴ ላይ ተግባርን እየፈፀመ ይገኛል። ከጥፋትና ሞት ጠርዝ ላዬ ተንጠልጥሎ የሚገኘው አገዛዙ ተስፋ በመቁረጥ ፀያፍ ድርጊትን በአማራ ህዝብ ላይ እየፈፀሙ ሲገኝ፤የዶሮ ስርቆሽን አጠናክሮ ቀጥሎበታል። መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል ሲል መረጃውን የ106ኛ ኮር ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ ሃላፊ አርበኛ እሸቱ አባተ መረጃውን አድርሷል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሰኔ 27/2018 ዓ/ም

በ201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር ሁለት እጅ እነሴ ወረዳ አስቴሪዮ ታዳጊ ከተማ ከውጊያው ጎን ለጎን 5ኪ.ሜ የጠጠር መንገድ ስራ ተሰርቶ ተጠናቀቀ። ========================= ........ሰ
+9
በ201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር ሁለት እጅ እነሴ ወረዳ አስቴሪዮ ታዳጊ ከተማ ከውጊያው ጎን ለጎን 5ኪ.ሜ የጠጠር መንገድ ስራ ተሰርቶ ተጠናቀቀ። ========================= ........ሰኔ 27/2018ዓ.ም የህዝብ መሰረተ ልማት ስራወች በመከናወን ላይ ይገኛል 54ኛ ክ/ጦር ሁለት ርጅ እነሴ ወረዳ ከአስቴሪዮ ታዳጊ ከተማ እስከ ጎድር ሜዳ ቀበሌ ድረስ ያለውን የጠጠር መንገድ ስራ 12 ኪ.ሜ የሚሸፍን ሲሆን የመጀመሪያ ዙር 5ኪ.ሜ የጠጠር መንግድ ስራ በወረዳው ጊዜያዊ መንግስት አማካኝነት ከሚያገኙት የእለት ገቢ በመቀነስ የህዝባችን ችግር መፍታት አለብን በማለት በዛሬው እለት ተጠናቆ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። የአካባቢው የከተማው ነዋሪወች ከዚህ በፊት ዋልካ መሬት በመሆነ አንዳንድ ግብአቶችን ለማስገባት በንግድስራቸው ላይ ተፅኖ ፈጥሮባቸው የቆየ መሆኑን ገልፀው አሁን ላይ ከከተማ ቀጥታ መኪኖች በመግባት የፈለጉት ቦታ ድረስ እየቀረበላቸው መሆኑን በመናገር ደስታቸውን ገልፀዋል። አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስተስፋ የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

ሰላም፣ ጽናትና ክብር ለእናንተ ይሁን ወገኖቼ! ✊ ​ውድ የትግላችን ደጋፊዎች፣ ኩሩ አማራውያንና ውድ የኢትዮጵያ ልጆች በቅድሚያ ባላችሁበት ቦታ ሁሉ ሰላማችሁ ይብዛልኝ። ​የፊታችንን መስመር እያየን፣ የትግሉን ስልትና የድል ዜናዎችን በየሰከንዱና በየደቂቃው ትኩስ እንደሆኑ ለእናንተ ለማድረስ ሁልጊዜም ዝግጁ ነኝ። ሜዳው ላይ ያለውን እውነተኛ እንቅስቃሴ ሳያመልጥዎት መከታተል ይፈልጋሉ? ​👇 ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን የፌስቡክ ቤተሰባችን ይሁኑ፤ አብረን እንዝለቅ! 👇

የድል_ዜና የደብረ ኤልያስ ቀስተ ደመና ሻለቃ በወሰደው መብረቃዊ የሌሊት ጥቃት በርካታ የአድማ ብተና፣ የፖሊስና የፓራ ኮማንዶ አባላትን ደምስሷል። ሰኔ 27/10/2018 ዓ.ም በበርካታ ውሽንፍር ውስጥ እየተንሳፈፈ አያሌ ፈተናዎችን በድል እያለፈ፤ ለጠላት የምንጊዜም ምስጢር በመሆን በአማራ ፋኖ ትግል ውስጥ እንደ ንጋት ኮከብ በማንጸባረቅ የትግላችን የማይቀዘቅዝ ሙቀት፣የማይደክም ኃይል፣የማይጠወልግ ውበት በመሆን እየቀጠለ የሚገኘው ታሪካዊውና ዝነኛው የቀስተ ደመና ብርጌድ እንደ እሳት የሚፋጅ ክንዱን በየጊዜው በጠላት ላይ እያሳረፈ ጠላትን እያሽመደመደ ይገኛል። በዛሬው ዕለትም  በማርዘነብ ታዳጊ ከተማ ከሌሊቱ 10:30 በወሰደው መብረቃዊ ጥቃት  የአድማ ብተና ጠርናፊው ሳጅን ሙሉቀንን ጨምሮ በርካታ ቁጥር ያላቸው አድማ ብተና ፣ ፓራ ኮማንዶና የፖሊስ አባላት ሙትና ቁስለኛ ሆነዋል፤ በርካታ ወታደራዊ ቁሳቁሶች ተማርከዋል። በውጊያውም 👉 03 ክላሽኮፍ መሳሪያ የተማረከ 👉 02 ስልክ 👉 11 ካዝና 👉 በርካታ የክላሽ ተተኳሾች 👉 በርካታ ወታደራዊ አልባሳት ማለትም ወታደራዊ ጫማዎች፣ ሚሊተሪዎች፣የዝናብ ልብሶች ወዘት 👉 ከ11 በላይ የተደመሰሰ 👉 ከ10 በላይ የቆሰለ 👉 ሳጅን ሙሉቀን የተባለ ጠርናፊ ፖሊስ 👉 ተሜ ቸኮለ የተባለ ቀንደኛ ባንዳ 👉 አትርስ የተባለ አድማ ብተና 👉 ውብሸት የተባለ ብሬን ተኳሽ ፖሊስ እና ሌሎችም ባንዳዎች ተወግደዋል ሲል ፋኖ ዘመን ባሳዝነው  ገለጿል።

ሰላም ጓዶች እንዴት ናችሁ❓ (ከአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር "ለውስጥ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች" የተላለፈ ወቅታዊ መልዕክት) የተከበራችሁ ውድ የሰራዊታችን የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ሰለምታችን በያላችሁበት የትግል ግንባር ይድረሳችሁ። ውድ ጓዶች❗️ በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር፣ በክፍለጦር እና በሻለቃ የህዝብ ግንኙነት (PR) ክፍል እንዲሁም በየትኛውም የፋኖ ሰራዊት ክፍል ስር ያላችሁ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የፋኖ አባላት በተለይ የቲክታክ (Tik tok) ተጠቃሚዎች አሁን ያለውን ወቅታዊ አጀንዳ በሚገባ በአግባቡ በመጠቀም የብልፅግናው አገዛዝ የእሳት እራት ሊሆኑ የተዘጋጁ ወገኖቻችንን ለመታደግና የአገዛዙን ስውር ገመና በማጋለጥ በየትኛውም ጎራ የህይዎት መስዋዕትነት የሚከፍለውን የአማራ ልጅ ቁጥር በጋራ ነቅተን እንድንታደገው ወቅታዊ የአማራዊ ግዴታ መልዕክታችንን አናስተላልፋለን። የዚሕ ወሳኝ አጀንዳ የተለያዩ ይዘት ነገር ግን ተመሳሳይ መልዕክት ያላቸውን ነጥቦች እንደሚከተለው የምንጠቀም ሲሆን:- ✅1ኛ. በአማራ ክልል ያሉ የፀጥታ ሀይሎች ወደ መከላከያ ሰራዊት ሊጠረነፉ መሆኑን ✅2ኛ. አገዛዙ ሰሜን ሸዋ ብሎ ከሰየመው የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አካል ለልዩ ወታደራዊ ግዳጅ የተመለመሉ የፖሊስና የሚሊሻ አባላትን በተመለከተ በትላንትናው ዕለት ዕዙ ያወጣውን መረጃ በዋቢነት በመጠቀም👇 የነባር ፖሊስ ምልመላ 👉ከደብርሀን = 150 👉ከወረዳዎች = 370 ✅ በድምሩ = 520 የነባር ሚሊሻ ምልመላ 👉ከደብርሀን = 800 👉ከወረዳዎች = 1700 ✅ በድምሩ = 2500 ✍️ጠቅላላ የፖሊስና የሚሊሻ ብዛት = ከ3200 በላይ ወደ ግዚያዊ መሰልጠኛ ማዕከል በመላክ አጠቃላይ እንደ አማራ ክልል ከ50,000 እስከ 60,000 የሚሆኑ የፖሊስና የሚሊሻ አባላት ባለማወቅ ለማይቀረው ግዳጅ እየተመለመሉ መሆኑን በሚገባ በሚዲያ እንድናጋልጥ በድጋሚ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን። ድል ለአማራ ፋኖ!!! ድል ለተገፋው ታላቁ የአማራ ህዝብ!!! ሰኔ 27/2018ዓ.ም

ለአገር መከላከያ ሠራዊት፤ ለክልል ሚሊሻዎች እና ለአካባቢ ታጣቂ አባላት በሙሉ፤ ይህ መልእክት የሚላክላችሁ በኢትዮጵያችን ሰማይ ስር እየተፈጠረ ያለውን መራራ እውነታ በመገንዘብ የደም መፋሰሱን ለማስቆም እና አገሪቱን ከአደጋ ለመታደግ ያለንን የጋራ ኃላፊነት በማስታወስ ነው። ላለፉት ዓመታት በትግራይ ጀምሮ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች እየተካሄደ ያለው የእርስ በእርስ ጦርነት ዋነኛ አስፈጻሚዎች እና ተጠቂዎች እናንተ ናችሁ። እናንተ ለአገር ሉዓላዊነትና ለሕዝብ ደህንነት የተቋቋማችሁ ሕዝባዊ አደራ የተጣለባችሁ ታላላቅ ኃይሎች ናችሁ፤ ሆኖም ዛሬ ላይ የፖለቲካ ሴራዎች አድምቀውና ለጠባብ የሥልጣን ፍላጎት ተጠቅመው ወንድም ወንድሙን የሚገድልበት እናት ልጇን የምታጣበት እና የአገር መሠረት የሚናጋበት አሳዛኝ ምዕራፍ ላይ ደርሰናል። ይህ በገዥው ፓርቲ የፖለቲካ ሴራ የተጠመደው የጦርነት ቀለበት አገርን የሚበትን እንጂ አገርን የሚገነባ አይደለም። ስርአቱ የአንድ ግለሰብ አምባገነንነት እውን ለማድረግ በሕዝብ ስቃይና በድሃ ልጆች ደም እየተጫወተ መሆኑን መገንዘብ አለባችሁ። አገዛዙ ከሕዝብ ብቻ ሳይሆን ከራሱ መዋቅር ጭምር ቅቡልነቱን ያጣ በመላው ኢትዮጵያውያን የተጠላ በመሆኑ ብቻውን የቀረና ተዳክሞ ለመውደቅ እየተንገዳገደ ያለ ስርአት ነው። እየወደቀ ላለ መጥፎ አገዛዝ መሞትም ሆነ መግደል በታሪክ ተወቃሺ የሚያደርግ የታሪክ ጠባሳ ስለሆነ ሳይመሽ በአንድነት ቁመን አገራችንንና ሕዝባችንን እናድን። እናንተም ደመ ከልብ አትሁኑ አገዛዙ ብታልቁ ደንታ ባይኖረውም ቤተሰቦቻችሁና ወገናችሁ በሕይወት ትፈልጋችኋለች። በመሆኑም ከእንግዲህ የፖለቲካ ጨዋታ መጠቀሚያ መሆናችሁን ትታችሁ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያንገበግበውን ስቃይ በመረዳት በጠመንጃ ሳይሆን በህሊናችሁ በማሰብ ከሕዝባችሁ ጎን እንድትቆሙ ጥሪ እናቀርባለን። እናንተ የሕዝብ ልጆች እንደሆናችሁና የሕዝብ እንባ መሆናችሁ ማንም ሊክደው የማይችል እውነት ነው። በሌላ በኩል ፋኖ እንደ ህዝባዊ ትግል ከስሜታዊነት እና ከጥፋት ዑደት ወጥቶ ይህንን ኃይል በሥልት ወደ ሕዝባዊ ትግሉ ለማምጣት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን በመስራት ለሚመጡ አባላት የደኅንነት ዋስትና በመስጠት የጦር መሣሪያቸውን ጥለው ለሕዝብ የሚቆሙትን እንደ ወንድም በመቀበል እንዲሁም በጦርነት አሸናፊ ከመሆን ይልቅ የጠላትን ሰራዊት በሃሳብ እና በክብር በማሸነፍ ትጥቅ ሳይፈቱ ወደ ሕዝብ ወገን እንዲመጡ የማግባባት ስራን እንደ ዋና የትግል ስልት መጠቀም ይኖርበታል። በተጨማሪም ሁለቱም ወገኖች የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም ቀዳሚ አጀንዳ በማድረግ የደም መፋሰስን የሚገታ የሰላም ድልድይ በመገንባት፤ የጋራ ጠላታችን ድህነት አለመግባባት እና የውጭ ጣልቃ ገብነት መሆኑን በመገንዘብ አቅማችንን ለአገር ልማት እና ለሕዝብ አንድነት በማዋል ለትውልድ የሚተርፍ ታሪክ መስራት ይገባናል። የኢትዮጵያ ድኅነት የሚረጋገጠው በመሣሪያ ኃይል ሳይሆን በመተማመን እና ወንድማማችነትን በገነባ አንድነት ነው። ዛሬ የምትወስዱት ውሳኔ የአገራችንን ነገ ዕጣ ፈንታ ይወስናል፤ ሰላም እና ፍትሕ ከሚሹ የሕዝብ አደራዎች ጋር እንድትቆሙ፣ እንዲሁም ለዚህ ትግል መሠረት የሆኑ አካላት ይህንን ሰፊ የዕርቀ ሰላም እና የመቀላቀል ስልት በትኩረት እንዲያከናውኑ በአጽንኦት እናሳስባለን። አገራችን ከዘመናት የእርስ በእርስ ጦርነት ተላቃ በእኩልነት እና በፍትሕ የምትተዳደርበትን ቀን ለማየት የጋራ አሻራችንን እናኑር። ኑ ከህብዝ ጋር እንቁም! የራስን ህዝብ መግደል ከውጭ ወረራ የማይተናነስ ክህደት ነው! ከወንድማችሁ #ታጋይየህዝብልጅ ከአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ

ከአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር የተሰጠ አስቸኳይ መግለጫ!! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር በኤፍራታ ግድም ወርዳ አጣዬ ከተማ ኗሪ የሆኑት​ን የአማራን ሕዝብ ህልውና አደጋ ላይ ለመጣል ታሪካዊ ማንነቱን ለማስለወጥ የሚሸረቡ ሴራዎች ከቀን ወደ ቀን እየተባባሱ መምጣታቸውን ክፍለ ጦራችን በቅርብ እየተከታተለ ይገኛል። በሽመልስ አብዲሳ የሚመራው በአማራ ክልል የኦሮሞ ልዩ ዞን በኦነግ ሽኔ ስም መዋቅራዊ በሆነ መንገድ አጣየ (ኤፌሶን) ከተማን ለ 13 ጊእዜ አቃጥሎ ለቁጥር የሚከብዱ የአማራ ተወላጆችን በግፍ ጨፍጭፎ ሙሉ ንብረት አውድሞ የቁም እንስሳቶችን ዘርፎ መሸሽ የማችሉ አይነ በስሮችን እና አቅመደካሞችን ከነ ሂወታቸው ባዶ ቤት ውስጥ አቃጥሎ በአለም ላይ ያልተሰራ ግፍ የተፈጸመባት አጣዬ(ኤፌሶን) ከተማን ይሄው ሀይል ድጋሚ ለአደገኛ የዘር ፍጅት እና ወረራ እየተዘጋጀ ባለበት ሁኔታ የአጣዬ ከተማን እያስተዳደሩ ያሉ ሆዳም አማራ ካድሬወች አብይ አህመድ የአማራን ህዝብ ለማፈናቀል ለማጥፋት የሚጠቀምበትን የኮሊደር ልማት ሰበብ የኦሮሚያን ባንዲራ በአስፋልት ደር በመቀባት ኗሪውን እያለማመዱት ይገኛሉ። የአብይ አህመድ ብልፅግና መራሹ ስርዓት በመጀመሪያ የአጣዬ ከተማና አካባቢዋን በኃይል በማውደም፣ ቀጥሎም ለብልጽግና ሥርዓት ታማኝ የሆኑና ለነሱ የሚታዘዙ የአማራ ተወላጆችን በይስሙላ የአመራርነት ቦታዎች ላይ አስቀምጧል። በአሁኑ ወቅት ደግሞ የአካባቢውን ሕዝብ በማንገላታት፣ በማስፈራራትና በማፈናቀል፣ የኦሮሚያ ባንዲራ ብቻ የሚውለበለብበት ልዩ "ኮሪደር" ለመፍጠር ሌሊትና ቀን እየተሰራ መሆኑ የሚታወቅ ሃቅ ነው። ​ስለሆነም የሽዋ ጠቅላ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር የሚከተሉትን ጥብቅ መመሪያዎችና ወታደራዊ ውሳኔዎችን ያስተላልፋል፡- ​፩. ለአጣዬ ከተማና አካባቢው የብልፅግና አመራሮች የተሰጠ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ፦​ይህንን የታሪካዊ ስፍራዎችን የማስለወጥና የማንነት ቅሚያ ሴራ በአስቸኳይ የማያስቆም ማንኛውም የአጣዬ ከተማና አካባቢው የብልፅግና አመራር፣ በታሪክና በሕዝብ ፊት ተጠያቂ መሆኑ ማቆሚያ የለውም። ይህንን ፀረ-አማራ ድርጊት የማታቆሙ ከሆነ፣ ክፍለ ጦራችን የብልፅግና ወንበር አስጠባቂ የጥፋት ኃይሎች ላይ የሚወስደውን ዓይነት እጅግ የጠነከረና የማያወላውል ወታደራዊ እርምጃ በእናንተም ላይ ለመውሰድ የሚገደድ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን። ​፪. ለአካባቢው የፖሊስና ሚሊሻ አባላት የተሰጠ ጥሪ፦ ​በየቀጠናው የምትገኙ የብልፅግና የፖሊስና የሚሊሻ አባላት ሆይ! የዐቢይ አህመድ መንግስትና የክልሉ አስተዳደር እናንተን ከመከላከያ ጋር ግንባር ድረስ በመውሰድ ማገዶ ሊያደርጋችሁ ግልፅና ቀጭን ትዕዛዝ አውርዷል። ይህንን የአማራን ሕዝብ ለማጥፋትና እናንተን ለመጨረስ የወረደውን የጥፋት ትዕዛዝ ተቀብሎ የሚሄድ አንድም ኃይል ሊኖር አይገባም። ​የወገኖቻችሁን ደም ለሚያፈስና እናንተን ለሚማግድ የጥፋት ሥርዓት ከመታዘዝ መሣሪያችሁን ይዛችሁ በአስቸኳይ ወደ ወገኖቻችሁ ወደ ጀግናው የአማራ ፋኖ እንድትቀላቀሉ ወታደራዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ፫. የአጣዬ(ኤፌሶን) እና ለአካባቢው ቆራጥ ወጣት የተላለፈ ጥሪ ​አጣዬ የጽናትና የጀግንነት ምድር ናት! ዛሬ በማንነታችን ላይ ያንዣበበውና ታሪካዊቷን ከተማችን ህዝባችንን ሊያጠፋ የቆረጠው የአብይ አህመድ የብልግና መራሹ ስርዓት ከምንጊዜውም በላይ ከባድ የህልውና አደጋ ደቅኖብናል። ይህ የመጣው ጠላት ዝም ብሎ የሚያልፍ ሳይሆን፣ ማንነታችንን ሊያጠፋና የወደፊት ተስፋችንን ሙሉ በሙሉ ሊበላ እና ሊያጠፋ ነው። ይህንን አውዳሚ ኃይል በትዕግስት መመልከት ራስን ለባርነት አሳልፎ መስጠት ነው። ​ያንዣበበውን አደጋ መመከትና ማስቆም የሚቻለው በአንድነት ስንቆም ብቻ ነው። ወጣትነት ጉልበት ነው፤ የለውጥ ኃይል ነው። ይህንን ጉልበት ወገንን ከጥፋት ለማዳን ማዋል የዛሬው ትውልድ የማይታለፍ የታሪክ አደራ ነው! ​ስለሆነም የአጣዬ ወጣት የሚከተሉትን ተግባራት በአስቸኳይ እንዲያከናውን በክፍለ ጦራችን ስም ጥሪ አናቀርባለን። በአስቸኳይ በየአካባቢው በጥብቅ መደራጀት፤ የተደራጀ ኃይል የማይበገር ነውና ​ከፋኖ ጋር መሰለፍ በግንባርም ሆነ በደጀንነት ከፋኖ ጎን በጽናት መቆም፤ ማሸነፍ የሚቻለው እጅ ለእጅ ተያይዞ በመሰለፍ ብቻ ነው። ​የነገን ተስፋ ማረጋገጥ ዛሬ የምንከፍለው መስዋዕትነት የነገውን ነፃነታችንንና ሰላማችንን የሚያረጋግጥ ብቸኛው መንገድ ነው። በመጨረሻም ​በኤፍራታ ግድም ወርዳ አጣዬ ዙሪያ የምትገኙ ከሊቅ እስከ ደቂቅ በውጭም በውስጥም የምትኖሩ የአማራዊያን ! ታሪክ በአንተ ትከሻ ላይ ወድቋል። ዝምታህ ጠላትን ያበረታል፤ መነሳትህ ግን ህዝብህን ይታደጋል። አሁኑኑ ተደራጅ! ከፋኖ ወንድሞችህ ጎን ቁም! ይሄንን ሊበላህና ሊያጠፋህ የመጣውን የአብይ አህመድ አረመኔያዊ ሰርዓት በጋራ መክተን እናስቆመው! "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!!!" "ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!!! ሰኔ 27/2018 ዓ/ም አፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሰባት ለሰባ ክፈለ ጦር!

።።።..ሰበር ዜና 1ብሬን 15የነፍስ ወከፍ መሳሪያ እና በርካታ ተተኳሽ ገቢ ተደርጓል። የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር የአባይ ሸለቆ ተርቦች አዳራቸውን ታምር ሰርተዋል። =====
+1
።።።..ሰበር ዜና 1ብሬን 15የነፍስ ወከፍ መሳሪያ እና በርካታ ተተኳሽ ገቢ ተደርጓል። የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር የአባይ ሸለቆ ተርቦች አዳራቸውን ታምር ሰርተዋል። ========================== .....ሰኔ 27/2018 ዓ.ም ከመርጡለ ማርያም ከተማ ዙሪያ ተከማችቶ የነበረውን የሚሊሻ ካምፕ ላይ ድንገተኛ ጥቃት በመፈፀም በርካታወችን ሙት ፣ ቁስለኛና ምርኮ አድርገውታል። በዚህም ከ20 በላይ የአብይ ወንበር አስጠባቂ ወደ ላይኛው ሲሸኝ ከሞት የተረፈው ከካምፕ ወጥቶ እግሩ ወደመራው ሲበታተን ሁለቱ መማረክ ተችሏል ። በተደረገው ሰልታዊ ማጥቃት 5 ባንዳ ቆስሎ ሆስፒታል የገባ ሲሆን 01ብሬን እና 15 የነብስ ወከፍ መሳሪያ እና በርካታ ተተኳሽ ጥይት ጋር ገቢ ሆኗል። ወደማይቀረው ከተሸኙት ሚሊሻወች ውስጥም ፦ ◍አስራት ዳምጤ ◍ ልዑል የተንካባው ◍ገብሩ አልማው ምክትል ሻለቃ ◍እንዳለው ጌትነት ◍ አልማው ባየ ◍አዲሱ የእነባው ◍ሹሙ ◍ መርሻ አሞኘ ◍መሰረት ምስጋን ◍ ሀብቴ ◍መሰረት ያለው ◍ገነት ተሜ እና መሰረት ደባልቄ ጥቂቶቹ ናቸው። 👉 አሁንም አልረፈደም የደም ግብር ነጋዴው አብይ አህመድ በሚጠራው የጦርነት ድግስ ውስጥ እየገባችሁ የምትማገዱ የብልፅግና ፍርፋሪ ለቃቃሚወች የአማራ ፋኖ ይቅር ባይ ነውና በይቅርታ ወደ ቤተሰባችሁ ተቀላቀሉ በማለት አሁንምጥሪ እናቀርብላቹሀለን ነብሰ በላው የአባይ ሸለቆ ተናዳፊ ተርብ ስራ ጀምሯል🔥🔥🔥🔥 የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር ይበልጣል ጥሩነህ የእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ጊ/መንግስት ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን

አማራ የህልውና አደጋ የተጋረጠበት ህዝብ ብቻ ሳይሆን እየጠፋ ያለ ህዝብ ነው። እኛ ደግሞ የዚህ እየጠፋ ያለ ህዝብ ልጆች ነን ስለዚህ ይህን ህዝብ ማሰልጠን፣ማደራጀት፣ማስታጠቅ እና ማንቃት መብት ሳይሆን አማራዊ ግዴታችን ስለሆነ ይህንን የማይፈልግ /በራሱ መንገድ ባርነትን እና ውርደትን የመረጠን ህዝብ ደግሞ የመጨረሻ እጣፈንታው ምን ሊሆን እንደሚችል እርግጠኛ ሆኖ መናገር አይከብድም። ይህን ህዝብ  ነፃ ለማውጣት ደግሞ ብቸኛ አማራጩ ከአለት የጠነከረ እንደብረት ምሰሶ ቀጥ ያለ በመጣ በሔደው እማይናወጥ ጠንካራ የሆነ አማራን እሚመጥን በመተማመን ላይ የተመሰረተ ድርጅት መፍጠር የግድ ይላል ይህ ደርጅት የአማራን ህዝብ ከሌሎች ወንድም ህዝቦች እሚያስበልጥ ወይም እሚያሳንስ ሳይሆን የህዝብን ሰላም እና ጥቅም በዘላቂነት ለማረጋገጥ እሚያስችል መሆን ይኖርበታል። የእኛ አንድነት የማያወላዳ፣የማያሻማ ፣የጥንካሪያችን እና የአሸናፊነታችን ቁልፍ ምስጢር ነው ። የትግል ስልታችንን እና የትግል መስመራችንን የአማራን ህዝብ ባህልን፣ሀይማኖትን፣ቋንቋን እና ሌሎች ሁነቶችን ያማከለ ሊሆን ይገባል።  አንድነታችንን የጠላ ሁሉ የአማራ ህዝብ ታሪካዊ ጠላት እንደሆነ እራሱን በማሳመን ነገ ለሚደርስበት የታሪክ ክስ እና ፍርድ ከወዲሁ መልሱን እያዘጋጀ እንዲጠብቀን ለማሳሰብ እወዳለሁ። በዚህ የህልውና ትግል ውስጥ የአንዱ መጠንከር ለሌላው አቅምና ጉልበት እንጂ ስጋት አይደለም ።    ፊታውራሪ ባዩ አለባቸው አፋብን ዘመቻ መምሪያ ሀላፊ ! በአንድ መድረክ ላይ ከተናገረው የተወሰደ ....