ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
رفتن به کانال در Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
نمایش بیشتر2 924
مشترکین
+10524 ساعت
+3357 روز
+33630 روز
آرشیو پست ها
የተለመደ የዝርፊያ ተግባሩን ለመፈፀም የተንቀሳቀሰው የብልፅግና ሰራዊት በ34ኛ ክ/ጦር ተቀጥቅጦ ወደ መጣበት ተመለሰ!!
ነሀሴ 22/2018
በዝርፊያ ላይ የተሰማራው የብልፅግና ሰራዊት የተለመደ የዝርፊያ ተግባሩን ለመፈፀምና የ34ኛ ክ/ጦር ፋኖዎችን አፍናለው ብሎ ቢንቀሳቀስም ነበልባሎቹ የ34ኛ ክ/ጦር ፋኖዎች ብርቱ ክንዳቸውን በማሳየት አስከሬኑን አሸክመው ወደመጣበት መልሰውታል።
አገዛዙ በተለዪዩ አቅጣጫዎቾ የተንቅሳቀሰ ሲሄን ፅድ ማርያም ከተማን ለመውረር የመጣውን የጠላት ኃይል አይደፈሬዎቹ የመብረቁ ሻለቃ ፋኖዎች ከቀኑ 6፡00 ጀምሮ ባደረጉት የማጥቃት ውጊያ 10 የጠላት ኃይል ሲደመሰስ በርካቶች ቁስለኛ ሲሆኑ አስከሬኑንና ቁስለኛውን ተሸክሞ ወደመጣበት ተመልሳል
በሌላ በኩል በታላቅ አምባ እንድሁም ጃማን ለመዝረፍ የመጣው የብልፅግና ሰራዊት የዝርፊያ ተግባሩ ሳይሳካለት እግሬ አውጭኝ ብሎ ፈርጥጧል ።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ
የአፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር ህ/ግንኙነት
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝና የ204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ከፍተኛ አመራሮች በእብናት ወረዳ ከገላ ማጠቢያ ከተማ ህዝብ ጋር ውይይት አካሄደ!
ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም
አፋብን የበላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ እና የ204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ከፍተኛ አመራሮች በእብናት ወረዳ ገላ ማጠቢያ ከተማ በመገኘት ከህዝቡ ጋር አጠቃላይ ወቅታዊ ሁኔታዎችን በተመለከተ ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል።
በዚሁ ህዝባዊ መድረክ ላይ የአፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ዮሐንስ ንጉሱ፣ ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ አርበኛ ሰለሞን አጣናው፣ የዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ጄኔራል ተሾመ አበባው፣ የሎጅስቲክስ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ በላይ ዘለቀ፣ የፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ሀብታሙ ሙላው፣ የልዩ ኦፕሬሽን ምክትል መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ሙሉዬ ደሴ እንዲሁም ሌሎች የኮርና የክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በመድረኩም አደረጃጀትንና አንድነትን ማጠናከር፣ የፋኖን ወቅታዊ የትግል ቁመና፣ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በጥልቀት መገምገም፣ የቀጣይ የፖለቲካና የወታደራዊ ዘመቻዎችን ግብ ማስቀመጥ፣ እንዲሁም ከማህበረሰቡ ጋር ስላለው የደጀንነት አሰላለፍና አጠቃላይ የትግሉ ሂደት በተመለከተ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል። በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የገላ ማጠቢያ ከተማ ነዋሪዎች፣ የማህበረሰብ ተወካዮች፣ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች የጎንደር ፋኖ ወደ አንድነት መምጣቱ ታላቅ ደስታ እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል።
አክለውም ሁሉንም ኮሮችና ክፍለ ጦሮች በአንድ የጋራ ዕዝ ስር በማደራጀት በጠላት ላይ የተቀናጀ እርምጃ የሚወስድበትን የፖለቲካና የወታደራዊ ስትራቴጂ መንደፍ እንደሚገባ፣ ባለፉት ሂደቶች ከነበሩ የአደረጃጀት ክፍተቶች ተገቢውን ትምህርት በመውሰድ እራስን ለላቀ ግዳጅ ማዘጋጀትና ህዝቡን በቅንነት፣ በታማኝነትና በእውቀት ማገልገል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በመጨረሻም የዕዝና የኮሩ ከፍተኛ አመራሮች ህዝቡ የድርጅቱ መስታወትና ዋና የጀርባ አጥንት መሆኑን በማስመር፣ የታዩ ድክመቶችንና ክፍተቶችን በአስቸኳይ በማረም ከህዝቡ ጋር በሙሉ ቅንጅት ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በተጨማሪም በየግንባሩ የሚከፈለው መራር ተጋድሎ የህዝብን ህልውና፣ ነፃነትና ታሪካዊ ክብር ለማስጠበቅ የሚደረግ መሆኑን በመግለጽ፣ ህዝቡ የገባውን ቃልኪዳን አጽንቶ በመጠበቅ የሚያደርገውን የሎጅስቲክስና የደጀንነት ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን በላይዘለቀ 3ኛ ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሞጣ ከተማ ንፁሀን እና የሀይማኖት አባቶች በብልፅግና አሽከሮች ተረሸኑ
====================
.....ነሐሴ 21/2018 ዓም
የደም ነጋዴው ብልፅግና በተደጋጋሚ ንፁሀንን እና የሀይማኖት አባቶችን በመግደል የእምነት ጦርነት ለማንሳት ያቀደው ብልፅግና አልሳካለት ቢልም አሁንም በተለያዩ አካባቢወች አባቶች እየተመረጡ እየተገደሉ ሲሆን በሞጣ ከተማ በዛሬው እለት ከሌሊቱ 11:00ሰዓት ላይ አስማማው ጌታነህ የተባሉን መነኩሴ የአገዛዙ ወንበር አስጠባቂ ሚልሻ ሞጣ ላይ ማርያም አካባቢ በጥይት መቶ የገደላቸው ሲሆን በዛሬው እለት የቀብር ስነሰርአታቸው ተፈፅሟል።
የአማራ ህዝብን ለማጥፋት ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ አለ የለም የሚለውን እርስ በእርስ ለማጨራረስ ያልፈነቀለው ድንጋይ የለም የውድቀቱ ጊዜ ስለደረሰ ሁሉም የእምነት አባቶች እና ህዝባችን በመቻቻል ሴራውን በማክሸፍ ታላቅነታችን ማሳየት አለብን በማለት መልክታችን እናስተላልፋለን።
አዲስትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ
የአፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
የብልፅግና ስርዓት ውድቀት እና የተቀናጀው የሐሰት ትርክት፦ የብልፅግና ሚስጥራዊ መመሪያ ተጋለጠ!!
የአብይ አህመድ አስተዳደር ከተቻለ የአማራን ህዝብ ሙሉ በሙሉ ከምድር ገጽ የማጥፋት፣ ካልቻለ ደግሞ «በሬ ወለደ» በሚሉ የሐሰት ትርክቶች ህዝብን በቅዠት ውስጥ ለማቆየት በየቀኑ ማኒፌስቶዎችን እየቀረፀ ማዋለድ የዕለት ተዕለት ዋነኛ ተግባሩ አድርጎታል።
ነገር ግን በተግባር እየታየ ያለው እውነታ ከዚህ የተለየ ነው። የአማራ የህዝባዊ እምቢተኝነቱ እና የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆቹን ፋኖዎች የጠነከረ ክንድ የስርዓቱን መዋቅር በመናዱ፣ የአብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ የሆኑት የብአዴን ቅጥረኞች ውሳኔ አጣብቂኝ ውስጥ ወድቀዋል።
በዚህም የስርዓቱ መዋቅር እንደ ሕፃን ልጅ ዳዴ ለማለት እየታገለ ባለበት በዚህ ወቅት፣ በየደረጃው ላለው አመራር አስቸኳይ መመሪያዎችን በማውረድ ላይ ይገኛሉ። በዚህም በመላው አማራ ግዛት የፖለቲካ አቅምን ለማዘመን በሚል ሽፋን ለሁሉም የአካባቢው አመራሮች በመመሪያ መልኩ ወርዶ የነበረው የውስጥ ሚስጥራዊ መረጃና ሰነድ ሙሉ በሙሉ በእጃችን ገብቷል።
ይህ በየቀኑ የሚወጣው የሐሰት ትርክት እና የአመራሩ የውስጥ መደናገጥ የሚያሳየው የስርዓቱን መጨረሻ ሲሆን፣ በመላው አማራ የወረደው ሚስጥራዊ ሰነድ ዝርዝር ነጥቦች እንደሚከተለው ይቀርባሉ፦ ምንጩ #Dave #Amhara
በዲማ ከተማና ደብረፅሞና ቀበሌ 4 ሴቶች ኮሎኔል ፀጋየ ይዞት በገባው ሰራዊት መደፈራቸው ታውቋል!!
64ኛ ክ/ጦር ነሀሴ 21/2018 ዓ.ም
~~
ከጄኔራል ከሶፊያ በክሪን ትዛዝ የተቀበለው ኮሎኔር ፀጋየ የ64ኛ ክ/ጦር የፋኖ ሰራዊትን አልሞ ተኩሶ መግደልና ማቁሰል ያልቻለው በእነማይ ወረዳ ዲማ ከተማና እና ደብረፅሞና ቀበሌዎች የሚኖሩ ኖሪዎች ላይ ከፍተኛ ዝሪፊያ፣ ውድመትና ፆታዊ ጥቃት እየፈፀመ ይገኛል።
በዲማ ከተማ ሰፍሮ ከሚገኘው የሚሊሻ አባል ውስጥ እህቷን እና የእህቷን ልጅ የሆነችውን ሚሊሻ ሰጣርጌ ጋርዴ ወይራ ቀበሌ ተወላጅ በመሳረያ በማንገራገር መድፈሩን ተርጋግጦል። ከዚህ በፊት ይህ ሚሊሻ ሴት ደፍሮ ብዙ ዓመት መታሰሩ ተረጋግጦል። ኮሎኔል ፀጋየ በዲማና አካባቢው ማህበረሰብ ላይ ወረራ ለመፈፀም ይዞት የመጠውን ወራሪ ሀይል 8 ግዜ የማጥቃት ሙከራ ቢያደርግም ጀግኖቹ የበላይ ዘለቀ ልጅች የጠላትን ሰራዊት ግንባር ግንባሩን በመብሳት በዲማ ከተማ የሚገኙ መንገዶች ላይ የጠላት አስከሬን ከምረውታል።
የአገዛዙ ስራዊት በዲማ፣ ደብረ ጽሞና ቀበሌ የ64ኛ ክ/ጦር የፋኖ ከባላትን አፀዳለሁ በሚል ቅዤት የጥንታዊ ዲማ ጊዮረጊስ ገዳማን አውድሟል። የዲማ ቅዱስ ጊዮረጊስ ገዳምና በዙሪያ የሚገኙ ቤተክርስቲያንን ምሽግ በማድረግ የቅዳሴ ስርዓትና መሰል ሀይማኖታዊ አገልግሎት እንዲቋረጥ አድርጓል። በገዳሙ ውስጥ የሚገኙ መነኮሳትን አቁስሏል አንገላቷል። ይሁንና በጥንታዊ ገዳም ዲማ ጊዮረጊስ ገዳምና ቤተክርስቲያን የጦር ምሽግ ከማድረጉ ባሻገር በገዳማቱና በአካባቢው የሚገኙ ቤተክርስቲያን ዙሪያ በርካታ አስነዋሪ ተግባር እየሰራ ይገኛል። በዲማ ከተማ የህዝብ ሃብትና ንብረት ከተዘረፍባቸው ንፁሃን ኗሪዎች ውስጥ ቀጥቂቱ:-
1ኛ.አቶ አንዳርጌ መኮነን = ከ100 ኩንታል በላይ
2ኛ. አቶ መልካሙ ጋሸው= 25 ኩንታል ጤፍ
3ኛ. አቶ ልብሞኝ የስጋት= ሙሉ የቤት እቃ
4ኛ. አቶ አዱኛ= 22 ኩንታል ጤፍ
5ኛ.አቶ ዋሌ አበበ= ሙሉ የቤት እቃ የተጫነ
6ኛ. ወ/ሮ ዘርፌ ታርክ= የምግብ ቤት እቃ ሙሉ የወደመ
7ኛ. አቶ አለማየሁ ፈንታ= የቤት እቃ በሙሉ የተጫነ
8ኛ.ወ/ሮ እታቱ ቁርስ ቤት = የቤቱን ሙሉ ውድመት
9ኛ. አቶ ሸገው መዝገቡ = 1 ሱቅ በሙሉ የወደመ
10ኛ. አቶ ጎሹ መኩርያው = ሙሉ የቤት እቃ የተጫነ
11ኛ. ወ/ሮ ማናየሽ ታዴ = ሙሉ ሱቅ ውድመት
13ኛ.አቶ አዩ ስራብዙ= 60 ኩንታል ጤፍ የተጫነ
14ኛ.አቶ አምታተው ሙሉ የቤት እቃ
15ኛ.አቶ ንጹሕ ሙለጌታ
16ኛ.አቶ አንዳርጌ መኮንን
17ኛ.አቶ የሽዋስ
18ኛ.መሪጌታ ኑርልኝ
✍️በደብረ ፅሞና ቀበሌ የወደመና የተዘረፍ ሀብት ንብረት ውስጥ በጥቂቱ:-
1ኛ.አቶ በለጠ ሙንየ= 4ኩታል ጤፍ ፣ 1ኩታል ስንዴ
2ኛ.አቶ ከፌ ገሬ = የሱቅ ሸቀጥና መጠጥ
3ኛ. አቶ እንቻል እያለ= 3ኩታል ጤፍና የቤት እቃ ወድሞበታል
4ኛ. አቶሰዋለ መኩ= 50ሽ ብር
5ኛ. አቶ ታምሬ አስቻለ= ብፌ፣ ቴልቪዥንና አልባሳት
6ኛ.አቶ አበቡ ነጮ= የሱቅ ሸቀጥ
7ኛ. አቶ ብዙነህ ደጉ= ሸቀጥ
8ኛ. አቶ ውዱ ይበልጣል= ሸቀጥ
9ኛ. አቶ ሙሉ= ሸቀጥ
10ኛ. አቶ ግብረአብ ጫኔ= 1ማፋፊያ ጤፍ፣ 1 ማፋፊያ፣ ሽብራ ፣1ማፋፊያ ዱቄት፣ 1ከረጢት የአፈር ማዳበሪያና አልባሳት የተዘረፈ
11ኛ. አቶ ሙሉጌታ ጫኔ= 21 ኩንታልና 24 ማፋፊያ ጤፍ፣ 6 ኩታል ሽብራ፣ 1 ኩታል አብሽ፣ 2.5 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ፣ ሙሉ የቤት እቃ ምግብ አልባሳት የተዘረፈና የወደመ፤ ባደራ የተቀመጠ 1ማፋፊያ ጓያ፣ 1ኩታል ስንዴ የቤተ ክርስቲያን፣ የዲማ ነጋዴዎች ያስቀመጡት ሽኩርት፣ ሰንዴና መሰል ንብረቶች በሙሉ የተዘረፈና የወደመ ቤቱም ባሁኑ ሰአት አገዛዙ እንደካምፕ እየተጠቀሙበት ይገኛል።
በዲማ ከተማ በተደረገው ተጋሃሎ ጠላት ማረኩት ብሎ ያቀረባቸው አልጋ ቴሌቪዥን፣ ፍራሾች መሰል ንብረቶች ከዚህ በፊት ያቃጠለዉ የፍቅር እስከ መቃብር ተዋንያኖች ንብረት መሆኑንና አገዛዙ በዝርፊያ የወሰዳቸዉ እንጅ የፋኖ ንብረ አለመሆናቸውን እናሳውቃለን።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስቸሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ፣
ነሀሴ 21/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
ከሰም ፪ኛ ኮር የቡልጋ እና የነበልባል ክፍለ ጦሮች በጋራ በፈጸሙት የደፈጣ ጥቃት በአገዛዙ ጦር ላይ ከፍተኛ ምት አደረሱ!!
ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ከሠም ፪ኛ ኮር ቡልጋ ክፍለ ጦር እና ነበልባል ክፍለ ጦር የተቀናጀና ከፍተኛ መናበብ የተሞላበት አሰደማሚ የደፈጣ ጥቃት በአገዛዙ ጥምር ጦር ላይ ድል ተቀዳጅተዋል።
የአገዛዙ የልዩ ዘመቻ አየር ወለድ 105ኛ ክፍለ ጦር የመከላከያ ሰራዊት አዲስ ምልምል ወታደሮችንና ሬሽን ለማቀበል መነሻውን በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ አረርቲ ከተማ በማድረግ ወደ ቡልጋ ክፍለ ጦር አቅጣጫ ተንቀሳቅሶ ነበር። በሌላ በኩል ደግሞ ከመተህ ብላ ከተማ ተጨማሪ ኃይል ሊቀበለው እንቅስቃሴ አድርጎ በነበረ ኃይል ላይ ነው።
ነገር ግን ቀድመው መረጃውን ያገኙት የቡልጋ ክፍለ ጦር የፋኖ አናብስት ልዩ ቦታቸው ከተሬ፣ ጉራምባ እና ሜጢ ድልድይ በተባሉ ስፍራዎች ጥብቅ ደፈጣ ዘርግተው በመጠበቅ፣ የጠላት ኃይል ወደ ወጥመዱ እንደገባ መብረቃዊ ጥቃት ፈጽመውበታል።
በዚህም የአገዛዙን ፀረ -ህዝብ ኃይል እንደ ቅጠል በማራገፍ በርካታ ሙትና ቁስለኛ አድርገውታል። ያላሰበውና ያልጠበቀው ከባድ ምት የደረሰበት የአገዛዙ ጦር፣ ሙትና ቁስለኛውን እየጎተተ አስፋልቱን የደም ጎርፍ በማድረግ ወደ መተህ ብላ ከተማ ለመመለስ የተገደደ ሲሆን፣ የአካባቢው ጤና ጣቢያም በሙትና ቁስለኞች መጨናነቁን ከውስጥ የተገኙ መረጃዎች ያረጋግጣሉ።
በተመሳሳይ አቅጣጫ ከምንጃር ተንቀሳቅሶ የነበረውን የአገዛዙን ኃይል ደግሞ የቡልጋ ክፍለ ጦር አባላት ለነበልባል ክፍለ ጦር አሳልፈው በመስጠት፣ የነበልባል ክፍለ ጦር ቃኝና መሃንዲስ "ነብሮ" ሻለቃ ከሌሊቱ 7:00 ሰዓት ገደማ አሮጌ ምንጃር በተባለ ስፍራ ላይ በብቃት ተቀብሎታል። የ"ነብሮ" ሻለቃ በሌሊቱ የጨረቃና ከዋክብት ብርሃን ታጅበው፣ ብሬንና ስናይፐርን አጣመረው ባካሄዱት ጥቃት ጠላትን በሚገባው ቋንቋ ሲያነጋግሩት አድረዋል።
በዚህ የተቀናጀ ጥቃት ምክንያት የአገዛዙ የልዩ ዘመቻ 105ኛ ክፍለ ጦር አባላት ከፍተኛ ድንጋጤ፣ ውጥረትና የፍርሃት ቆፈን ውስጥ መውደቃቸው የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ገልጿል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
+1
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ኢንጂነር ቅጣው እጅጉ ንስር በለሳ ክፍለ ጦር ከተውጣጡ የብርጌድ አሀዶች በአመዱት ከተማ በጠላት ላይ ከፍተኛ ድል ተቀዳጅቷል።
ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም
የጠላት ኃይል ከየኋላ ወደ አርባያ ከተማ እንቅስቃሴ ያደረገው ጠላት ላይ ወታደራዊ ገዥ ቦታዎችን በመያዝ ከፍተኛ ኪሳራ አድርሰውበታል ።
የጠላት ኃይል አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቶ ወደ መጣበት የኋላ መመለስ እንኳን ሳይችል ቀርቶ ለመፈርጠጥ ተገዷል።
በዚህ አውደ ውጊያ በጠላት ኃይል ላይ በርካታ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ ለማድረስ የተቻለ ሲሆን 20 የጠላት ኃይል ሲደመስስ ከ15 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ከባድና ቀላል ጉዳት አስተናግዷል ሲል መረጃውን ያደረሰን የክፍለ ጦሩ ህዝብ ግንኙነት ነው።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን በላይዘለቀ 3ኛ ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
+2
ሰበር የድል ዜና የአፋብን፤ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፤206ኛ ኮር/የ14ኛ ክ/ጦር አካል የሆነችው የእሳት ነበልባሏ የበረኸኛው ጅበላ ሙተራ ሻለቃ ድል ተቀዳጀች!!!
ዛሬ በቀን 21/12/2018ዓ,ም ከሌሊቱ 8:00ስዓት በተጠና ኦፕሬሺን በደብረኤልያስ ወረዳ ልዩቦታው አበሸም በተባለ ት/ቤት መሺጎ በነበረው የአብይ አህመድ ዙፋን አስጠባቂ የአድማብተና የሚሊሻ አባላት ላይ መብረቃዊ! ጥቃት በማድረስ ሙትና ቁስለኛ ማድርግ ተችሏል::
ተችሏል ::
በኦፕሬሺኑ የተገኙ ድሎች:-
👉በእጅ የተማረከ=አንድ ሚሊሻ
👉 ኮሪያ ክላሺ =አንድ
👉ሲሶክላሲ =አንድ
👉በርካታ ተተኳሺ
👉በርካታ ወታደራዊ ሻጣ
👉ለጊዜውበቁጥር ያልታወቀ የድማ ብተና እና ሚሊሻ አባል ሙትናቁስለኛ ማድረግ ተችሏል::
ነሃሴ 21/12/2018አዓ,ም
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳስብ!!አዲስ ተስፋ የአፋብን፤ቴዎድሮ2ኛ ዕዝ/206ኛ ኮር/የ14ኛክ/ጦር ህዝብግንኙነት መምሪያ
+2
የንስሩ አርበኛ የቁርጥ ቀን ልጅ እና የህዝብ ፍቅር! እኔ በታሪክና በውጊያ ሜዳ በርካታ የቆረጡ የአማራ ጀግኖችን አውቃለሁ፤ ለወገናቸው ዋጋ የከፈሉ ህያው ስሞችንም አጠናለሁ።
ነገር ግን ከእነዚህ ሁሉ መካከል እንደ ንስር ከተራራ ተወርውሮ ጠላትን የሚያስበርድ፣ በውጊያ ስልቱ ወደር የሌለው አንድ ልዩ የአማራ ልጅ አፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ምክትል ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ኢሳይያስ ደመቀ ነው!
ምርጥ አዛዥነትና የጦር ሜዳ ብቃት፦ አርበኛ ኢሳይያስን ልዩ የሚያደርገው በጦር ሜዳ ያለው የብረት ያህል የጠነከረ ጀግንነቱ ብቻ አይደለም። ፈጣን ውሳኔ የመስጠት ብቃቱና የውጊያ ስልቱ ከታችኛው ተራ ሰራዊት እስከ ከፍተኛ አመራሩ ድረስ ሙሉ አክብሮትና ታዛዥነትን አትርፎለታል።
❤️ኢሱ ልብ የሚነካው የህፃናት ስስት፦ ከወታደራዊ ግርማ ሞገሱ ይልቅ ግን ስሜትን የሚያንቀሳቅሰው የእሱና የህዝቡ ግንኙነት ነው! በተለይም የአማራ ህፃናት እሱን ሲያዩ የሚያሳዩት የስስት፣ የኩራት እና የአድናቆት አስተያየት የሰውን ልብ ይነካል፤ ህፃናቱ የሚያዩት እንደ ወታደራዊ አዛዥ ብቻ ሳይሆን፣ ከፊት የሚቆምላቸው ታላቅ ወንድማቸው አድርገው ነው።
✨ የነገዋ የወታደራዊና የኢትዮጵያ ታላቅ ጀነራል አርበኛ ኢሳይያስ ደመቀ! ሰናይ ሌሊት ይሁንላችሁ ወዳጆቼ! #Dave #Amhara
በምስራቅ ወለጋ ጊዳ ወረዳ አንዶዴ ድቾ ቀበሌ በቢዛሞ ፋኖ ሽንፈት የተከናነበው የገዳ ኮማንዶ ለእምነታቸው የመነኑ ቀሳውስት፣ ቆሞስና ሴቶችን በግፍ ረሽኗል።
በአንዶዴ ድቾ ስላሴ ቤተክርስቲያን ኪዳን በማድረስ ላይ የሚገኙት በግፍ ከተረሸኑት መካከል ቆሞስ አባ ታደሠ መኮንን ይገኙበታል።
ቆሞስ አባ ታደሠ መኮንን በጊዳ ወረዳ ሀገረ ስብከት አንዶዴ ስላሴ ለአካባቢው ማህበረሰብ በመልካም አስተምሮና እኔ የስላሴ ባሪያ ነኝ በማለት፤ ለስላሴ ግልጋሎት ኪዳን ከሚቋረጥ በክብር መስዋት እመርጣለሁ አንጂ ስጋየን ለሚገል አህዛብ እምነቴን አጸናለሁ በማለት በቆረቆሩትና ስላሴ ቤተክርስቲያን ውስጥ በጨካኞች ተገለዋል።
ወንድማለም መንፈሳዊ አባቴ ነፍስዎን በአጸደ ገነት ያሳርፍልን በረከትዎ ይደርብን።
በሰዴ ወረዳ የቆሎ ተማሪወች እና ህዝቡ ላይ በምሽት ቤት በማስከፈት ዝርፊያ እና ጥቃት ተፈፀመባቸው።
========================
.........ነሐሴ20/2018 ዓ.ም
የከሰረዉ እና በውድቀት ጎዳና ላይ ያለው የብልፅግና ስርዓት አማራ ጠልነቱን በይፋ በድሮን እና በከባድ መሳሪያ መከራዉን እያበዛ የሚችለዉን ሁሉ እያደረገ ይገኛል።
የፋኖን በትር መቆቋም ያቃተዉ ሆድ አደሩ እራሱን ጠልቶ ለአብይ የሚያሽቃብጠዉ የብልፅግና ሚሊሻ እና የፖሊስ አመራር ሰዴ ከተማ ዉስጥ ሌሊት እየተቀሳቀሰ በጨለማ ጭብል በመልበስ ከንፁሀን ማህበረሰብ ቤት እያስከፈተ መዝረፉን ቀጥሏል ።
ማለትም ነሐሴ18/2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 2:00 ሰዓት ላይ ዉዱ ከሚባል ባለሱቅ በቀዳዳ ብር የወሰዱ ሲሆን አንድ የቆሎ ተማሪ 1.ኤልያስ አለህኝ የተባለ ደግሞ ቤት ክፈት ብለዉ ሊዘርፉት ሲሞክሩ አልከፍትም ሲላቸዉ በጥይት መተዉታል እና ሌላም በርካታ ነጋዴወች በዚህ መልኩ ገንዘብ እየተዘረፉ ስለሆነ እና ወጣትም ሊያፍሱ ስለሆነ የሰዴ ወረዳ ማህበረሰቦች ከእንዲህ አይነት ሌባ እና ቀማኛ ስርዓት እራሳቹህን እንድጠብቁ ስንል የጥንቃቄ መልክታችን እናሳዉቃለን።
የ201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦር የሰዴ ወረዳ ጊ/መንግስት አስተዳደር ሚዲያ እና ህ/ግንኙነት ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም
ድል ለአማራ ፋኖ ክብር በጀግንነት ለተሰዉ ሰማእታት
አዲስ ትዉልድ፣ አዲስ ተስፋ አዲስ፣ አስተሳሰብ
