fa
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

رفتن به کانال در Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

نمایش بیشتر
2 955
مشترکین
+1424 ساعت
+247 روز
+38330 روز
آرشیو پست ها
ከሪፎሙ ማግስት ከፍተኛ የዕዝና የኮር አመራሮች በተገኙበት የአፄ ምኒልክ ክፍለጦር ደማቅ የተሃዲሶ መርሃ ግብር በማካሔድ እራሱን ለላቀ ግዳጅ ብቁ ማድረጉን የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ለዕዙ በላከው መረጃ አስታወቀ። አፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በስሩ የሚገኙ ክፍለ ጦሮችን ተከታታይ ጥልቅ ግምገማ በማድረግ ለቀጣይ ግዳጅ በተሻለ ቁመና ላይ ለማብቃት ያለመ የተሃዲሶ መርሃ ግብር እያካሔደ ይገኛል። የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አካል የሆነው ምኒልክ ክፍለጦር ትላንት ሰኔ 02 ቀን 2018ዓ.ም ከፍተኛ የዕዝና የኮር አመራሮች እንዲሁም ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ደማቅ የተሃዲሶ መርሀ ግብር ማካሔዱን ኮሩ የገለፀ ሲሆን በፕሮግራሙ ላይ ወቅቱን የዋጀ የተለያዩ መልዕክቶች ተላልፈዋል። በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ኢንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ ባስተላለፉት መልዕክት "ምኒልክ ክፍለ ጦር የተሰየመችው የዘመኑ የአፍሪካው መሪ የኢትዮጵያው ንጉስ በሆኑት የአድዋው ፊትአውራሪ ምልክት በዳግማዊ ንጉስ አፄ ምኒልክ ስም ሲሆን እኛም የእነዛ ጀግኖች ትላንት የውጭ ወራሪዎችን አከርካሪ ሰብረው የመለሱ፣እምቢ ለባርነት ብለው የተዋደቁ፣ ደማቸውን አፍሰው፣አጥንታቸውን ከስክሰው ነፃነትን ያጎናፀፉን ኩሩ የነፃ ህዝቦች ልጆች ነን ያሉ ሲሆን፣ የአሁኑ ትውልድም በአባቶቹ የጀግንነት መንፈስ የኦሆዴድ መራሹ የውጭ ተላላኪ አማራ ጠል ብልፅግና አንዲሁም ብአዴንን የመሰለ የዘመናችን እንቁላል ቀቃይ የሀገር ውስጥ ተላላኪ ባንዳዎችን አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ታሪካችንን በደማችን የምንፅፍ የምኒልክ ልጆች ነን ብለዋል" አክለውም "ምኒልክ ክፍለ ጦር ልክ እንደ አባቶቻችን በአፄ ምኒልክ ታሪክ፣ በመይሳው ካሳ ዘመን ተሻጋሪ ጀግንነት፣ በአባ ኮስትር በላይ ዘለቀ ታሪክ እንዲሁም የዘመናችን እንቁ የትግሉ ችቦ ለኳሽ በርጋዴር ጄኔራል አሳምነው ፅጌ የጀግንነት መንፈስ የተቃኘ ከጎጥና ከአካባቢ እሳቤ የፀዳ የአማራ ሰራዊት የኢትዮጵያ ተስፋ መሆን አለበት" በማለት በሰራዊቱ ፊት ተገኝተው ወቅታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመርሀ ግብሩ ላይ የክፍለ ጦሩ መስራች የነበረው አርበኛ ሙሴ ሸዋፈራ ለሰራዊቱ ባስተላለፉት መልዕክት "ምኒልክ ክፍለጦር እንደ ስሟ በአምሳለ አባታችን አፄ ምኒልክ አይረሴ ታሪኮችን በመስራት የአማራ ፋኖ ቁመና ይዛችሁ የህዝባችሁ አገልጋይ እንድትሆኑ" ሲሉ አዲስ ለተዋቀረው የክፍለጦሩ አመራሮችና ለሰራዊቱ የአደራ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። በመጨረሻም የተሀዲሶ መርሀ ግብሩ በተለያዩ ኪነ ጠበብ ታጅቦ ቀጣይ የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥ በስኬት መጠናቀቁን በመርሀ ግብሩ ላይ በአካል ተገኝቶ ፕሮግራሙን የተከታተለው የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ከስፍራው ለዕዙ ዜና ክፍል በላከው የግንባር መረጃ አስታውቋል።      ''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት''    ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ       ሰኔ 03/2018ዓ.ም

አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ (፪ኛ) ኮር 16ኛ ልባርጋቸው ሙጨ ክ/ር ግዙፍ 2ኛ ዙር ኮማንዶ የፋኖ ሰራዊት አስመረቀ!!! በትናንትናው እለት ሰኔ 2/2018 ጣና ብርጌድ በመባል የሚታዎቀው አደረጃ
አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ (፪ኛ) ኮር 16ኛ ልባርጋቸው ሙጨ ክ/ር ግዙፍ 2ኛ ዙር ኮማንዶ የፋኖ ሰራዊት አስመረቀ!!! በትናንትናው እለት ሰኔ 2/2018 ጣና ብርጌድ በመባል የሚታዎቀው አደረጃጀት አሁን ላይ ከቀጠናው አቀማመጥ ለግዳጅ በሚያመች መንገድ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በዉል በማጤንና በመምከር ታላቁ አርበኛ ልባርጋቸው ሙጨ ያለመውን ትክክለኛ የመታገያ ሀሳብ ከዳር ለማድረስ ጥልቅ ውይይት በማድረግ የክ/ሩን አደረጃጀት አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ (፪ኛ) ኮር 16ኛ ልባርጋቸው ሙጨ በሚል ስያሜና በስሩ አራት ሬጅመንቶችን በማደራጀት ካጠናቀቀ የሰነባበተ ሲሆን ለወራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ብዙ መሰናክሎችን በማለፍ በተለይ የታላቁ አርበኛ ልባርጋቸው መስዋትነት ሳይበግራቸው እንደ ታጋይ በቁጭት የተሻለ በመስራት አንድ ልቡ ቢሰዋ እሽ ልቡ ይወለዳል በማለት ስልጠናውን በብቃት ማጠናቀቅ ተችሏል ሲል የክ/ሩ የህ /ግ አርበኛ አንደበት አበጀ ገልጿታል። ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!! አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ (፪ኛ) ኮር የህ/ግ ክፍል         ሰኔ 3/2018

ሻንበል መሪው ቲም መሪው እና ብሬን ተኳሹ ወደ ፋኖ 201ኛ ኮር 54ኛ እና 74ኛ ክ/ጦር ተቀላቅለዋል። ◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉ ........ሰኔ 3/2018 ዓ.ም 1.በውቀት በላይ...ዋና ብሬን ተኳሽ 54ኛክ/ጦር 2.አበባው ጌትነት....አድማ ብተና 3.ወንድም በሬ...ፓራኮማንዶ...ቲም መሪ 4.ደጉ ጥጋቡ....የጥምር ጦሩ.. ሻንበል መሪ 5.ብልሀቱ ካሳ..ሚሊሻ74ኛክ/ጦር የገቡ ሲሆን በክፍለ ጦር አመራሮቸ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ለማይረባ እና ሽርፍራፊ ጥቅም ብላቹህ መተኪያ የሌለው ህይወታቹህን አትገበሩ ኑ እራሳቹን አድኑ የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

√ሰላም የተከበራችሁ የትግላችን ደጋፊዎች በሙሉ  ትግላችን  ድርጅቱ በፈለገው  አቅጣጫ እየተጓዘ ቢሆንም  የትግል ዋና ሞተሩ የሰው ሃይል መሆኑ  ይታወቃል  በአለማችን ትልልቅ የጦር ሰራዊት የግነቡት ሀገራት የሰው ሃይል በማሰልጠን በማደረጃት በማስታጠቅ ነው   የአማራ ፋኖ አደረጃጀቱን እያሻሻለ መምጣቱ  ለሁላችንም ግልፅ ነው!! አሁን በክልላችን በርካታ ምልስ ሰራዊት እንዳለ የውስጥ አርበኞች መረጃ በየዕለቱ ይደርሰናል በዚህም መሰረት  በምኒልክ ዕዝ ቀጠና (50000ሺ ) አምሳ ሺ  ምልስ ሰራዊት ፣ በአሳምነው ዕዝ (36000) ሰላሳ ስድስት  ሺ ፣በቴዎድሮስ ዕዝ  (60000) ስልሳ ሺ ፣ በበላይ ዕዝ (52 000) አምሳ ሁለት  ሺ ምልስ ሰራዊት  እንዳለ አጣርተናል  ስለዚህ ሀገር እየተደፈረ ህዝብ እየተሰቃየ የውትድርናን ሙያ ይዘህ እቤትህ ቁጭ ያልክ  ወታደር  እንዴት አስቻለህ ትናት ከባድማ እስከ ጦረና ግባር ከሀገር ውስጥ ሶማሊያ ከኦጋደን በረሃ እስከ ከሶማሊያ ሞቋድሾ  ከዚያም አልፎ እስከ ሱዳን  በርሃ ድረስ  የከፈልነውን  መስዋትነት ሁላችሁም ታውቃላችሁ  ታዲያ ዛሬ የአማራ ህዝብ  እንደ ህዝብ የሞት አዋጅ ታውጆብን  በጅምላ እየተቀበርን  በጅምላ እየታረድን  እንደነገድ  ሊያጠፉን ቦታና ጊዜ  እየጠበቁ  ባሉበት ስዓት  እንዴት አስችሏችሁ በህዝባችሁ ላይ ልባችሁ ጨክኖ እጅና አግራችሁን አጥፋችሁ ቤታችሁን ዘግታችሁ  መቀመጥን መረጣችሁ  ትናትን ያወራነው ዛሬ በህይወት ስላለን ነው  ነገ በህይወት ካለን  ስለቀጣዩ  ታሪክ  እናወራ ይሆናል! ግን በህይወት እስካለን  በቻልነው  ሙያ ለህዝባችን  ባሪያ ሆነን  እንታገል  ህዝባችንን  እንዳን  እርስታችንን እንጠብቅ  እኔ የምታገለው  የአማራን ህዝብ ጥቅም አሳልፎ ለመሸጥ አይደለም ወይም በህዝባችን ቁማር  ለመቆመር  አይደለም  አማራ  ያለማንም ጣልቃ ገብነት በእራሱ በአብራኩ ልጆች  ወደ ክብሩ  በነፃነት እንዲመለስ ነው  እንደ ባለፈው  ሁለተኛ/ሶስተኛ  ወገን  ሆነን እንደ ብአዴን አሽከር/ተለጣፊ ለመሆን  አይደለም። √ ሁላችንም  ብዙ በደል ደርሱብን ያውቃል ወታደር ቤት እያለን ያንን ሁሉ መከራ አልፈን እዚህ ደርሰናል!  ህይወት እራሷ ፈተና ነች ግን ፅናት ያስፈልጋታል! በርግጥ ትግሉ አልጋ በአልጋ  አይደለም ብዙ ውጣ ውረድ አለ ከዚያ ካሳለፍነው ህይወት አይበልጥም!   ፋኖ ላይ ለህዝብህ ስትል የምከፍለው መስዋት ውስጥህ እየረካ መንፈስህ እየታደሰ  ሞትህ  የፃዲቅ ሞት ቁስልህ የውሻ ቁስል  እንደሆነ  እያወክ  ከጀርባህ  ብዙ  አባት ፣እናት ፣እህት ፣ወንድም ስላለህ  ደስ እያለህ ትታገላለህ! ስለዚህ ወንድሞቸ  በአልቧልታ ውሬ ሳትወናበዱ  ኑ ከህዝባችሁ ጋር ታረቁ  አባት ለልጁ ይቅር ይላል  ትግላችን መሪር ነው ! አሁንም አረፈዱም  ወደ ቀልባችሁ ተመልሱና ወደ እኛ  መጥታችሁ የትግላችን አጋር የህዝባችሁ እምባ አባሽ ፣የእኛ የወንድሞቻችሁ  መከታ ፣ የጠላታችሁ መርዶ እንድትሆኑ እንሻለን! ወደ ትግሉ ለመቀላቀል የምትፈልጉ ወንድሞቸ  በሙሉ በራችን ከፍት ነው  እኔም ሆኑ ጓዶቸ እናተን ለመቀበል ዝግጁ ነን! ስለአፄ ቴዎድሮስ  ጀግንነት ከተነገረው አንድ ልበላችሁ! "ቋራ ላይ ሆኖ ክንፉ ሲያገሳ    የመይሳው ልጅ ቢጨመር ካሳ    ግብፅን  ጨነቀው ነፍሱን  ረሳ     እንኳን ጤነኛው ሬሳው. ፈሳ!" ፋኖ የአማራ ህዝብ የመዳኛ መንገድ! ፋኖ ያሸንፋል  አማራነት ወይ ሞት! ጆሲ __

ተራሮቹ ሁልጊዜም ፅናተኞች ናቸው። ነገር ግን ዝምታቸው የጀግኖችን ደምና የባንዳዎችን ክህደት አምቆ የያዘ ሚስጥራዊ ሳጥን ነው። ታሪካችን የሚጀምረው አንጸባራቂው የለማ አዝመራ በነፈሰ ቁጥር፣ ልቡ በጥቅም በሚወዘወዘው በአንዱ የውስጥ ሰው ቤት ውስጥ ነው። ካሜራው ከተራራው ወርዶ አንዲት ጥንታዊት የሳር ጎጆ ላይ ያርፋል። በጎጆው ውስጥ አንዲት የሸክላ ማሰሮ በከሰል እሳት ላይ ትንተከተካለች። በዚህም አንድ ​አረጋዊው አባ መላኩ ጠቆር ያለውን ጋቢያቸውን በትከሻቸው ላይ እያማረጡ፣ ከፊታቸው ለተቀመጠው ወጣት ልጃቸው ለአሰፋ በትኩረት ይመለከቱታል። አሰፋ አይኖቹ እረፍት የላቸውም። በእጆቹ የወርቅ ሳንቲሞችን ያገላብጣል፤ ፊቱ ላይ ግን የፍርሃትና የስግብግብነት ጥላ ያንጸባርቃል።​አባ መላኩ፦ ድምፃቸው በጥበብና በክብደት ተሞልቶ አሰፋ… ልጄ ሆይ! ይሄ እጅህ ላይ ያለው ወርቅ የትናንት እንጀራህ እንዳልሆነ አውቃለሁ። ይሄ ወርቅ የዛሬው ወገንህ የነገው የሞት ደብዳቤ ነው ይለዋል። ​አሰፋ፦ ከተቀመጠበት ብድግ ብሎ፣ በቁጣ አባባ! እናንተ ሁልጊዜ ስለ ሀገርና ስለ ክብር ታወራላችሁ! ሀገር ምን በላች? ክብር ምን አጠጣች? ከውጭ የመጡት ሰዎች እኮ እኔን የዚህ አካባቢ አስተዳዳሪ ሊያደርጉኝ ቃል ገብተውልኛል። እኔ ባልመራቸው ሌላ ሰው መርቶ ያሳያቸዋል። እኔ መብላት ካለብኝ፣ ለምን አሁን አልበላም? ​አባ መላኩ፦ በትካዜ ራሳቸውን እየነቀነቁ አየህ… አሰፋ። እኛን የመጣብን ጠላት ሊያጠፋን አይችልም ነበር። ምክንያቱም እኛ ይሄን ገደል፣ ይሄን ተራራ፣ ይሄን ጫካ ጠንቅቀን እናውቀዋለን። ጠላት ግን መሬቱንም ሰማዩንም አያውቀውም። ጠላት አይኑ እውር ነበር። ነገር ግን ያ አሳፋሪ ታሪክ የተጻፈው... አንተና መሰሎችህ ሆዳችሁን ለማርካት ጥቅማጥቅም ፍለጋ ስትሉ የጠላት አይን ሆናችሁ ስትመሩት ነው። የአማራ ባንዳ እራሱ ሆዳም አማራ መሆኑን ስታይ ነው የውስጥ ቁስሉ የሚደማው። የውጪው ጠላትማ በሩን አንኳክቶ ይገባል፤ በሩን የከፈትከው ግን አንተ የውስጡ ሰው ነህ! ​አሰፋ፦ ፊቱ እየተለዋወጠ እኔ ወንድሞቼን አሳልፌ አልሰጠሁም! እኔማ... የራሴን እድል ነው የሞከርኩት። ​አባ መላኩ፦ ከመቀመጫቸው ተነስተው ወደ አሰፋ እየተጠጉ፣ አይን አይኑን እያዩ እድልህን ሳይሆን ክብሩን የጠበቀውን ማኅበረሰብህን ነው የሸጥከው! ታሪክ ነገ የአንተን ስም በወርቅ ሳይሆን በጥቁር ቀለም ነው የሚጽፈው። ጠላት ለአንተ የሰጠህ ወርቅ አንተን ለማክበር ሳይሆን፣ አንተን ተጠቅሞ ወንድሞችህን ካረደ በኋላ አንተንም እንደ በግ አርዶ ለመጣል ነው። ለባንዳ የሚሆን ክብር የትም ሀገር የለም! ​ካሜሪው ከአረጋዊው አባ መላኩ አይን ወጥቶ፣ ውጭ ወዳለው ጨለማ ተራራ ይወጣል። ድንገተኛ የነፋስ ጩኸትና የሩቅ የተኩስ ድምፅ ይሰማል። እናም ምን ልላችሁ መሰላችሁ እውነት ነው… ታሪክ ዛሬም ድረስ ይመሰክራል። የአንድ ማኅበረሰብ ትልቁ ጠላት ከሩቅ የመጣው ወራሪ ሳይሆን፣ በመካከሉ በቀለ የተፈጠረ፣ ለጊዜያዊ ጥቅም ሲል የሕዝቡን ደምና ትግል አሳልፎ የሚሸጠው "የውስጥ ሆዳም" ነው። ​ነገር ግን ታሪክ ባንዳዎችን ይረሳቸዋል፤ ወይም ደግሞ በውርደት ስማቸውን ያነሳዋል። ጽናትና እውነተኛነት ግን ለዘላለም እንደ ተራሮቹ ይኖራሉ። ​ ንቃት... የውስጥ ክህደትን የሚያክሽፍ ታላቅ ጋሻ ነው! #Dawit #Amhara ከንጉስች መንደር

#ገሊላ_ደምበጫ‼️ ቀን 02/10/2018 ዓ/ም ጀብደኛው 99ኛ ክ/ጦር የጠላትን ቅስም በመስበር ያሰብውን ሳያሳካ ወደመጣበት አስፈርጥጦ መልሶታል። በጀብደኝነታቸው አለም የመሰከረላቸው  ወጣትነታቸውን ለአማራ ሕዝብ የሰጡ በወጣት መሪዎች የበለፀገው 99ኛ ክ/ጦር የጠላትን ቅስም በመስበር ወደ ገሊላ ቀጣና የተንቀሳቀሰውን የብርሃኑ ጁላን ግብስብስ  ሰራዊት ሙቱን እና ቁስለኛውን በቅጡ ሳይሸክፍ  ወደ መጣበት #ደምበጫ ከተማ በአቦሸማኔ ፍጥነት እንዲመለስ አስገድደውታ። ።በዚህ የጠላት እንቅስቃሴ ስረገላ ማርያም ሁለት ሕፃናትን በማቁሰል  የአማራ ጠል ስራውንም አሳይቷል::         ነገሩ እንዲህ ነው ከቀኑ 10 ስዓት ገዳማ ጨለማን ትራስ አድርጎ የደምበጫ ወረዳ ታዳጊ ከተማ የሆነችውን #ገሊላን ለመቆጣጠር መነሻውን ደምበጫ ከተማ በማድረግ  ወደ ገሊላ ተንቀሳቀሰ ነገር ግን  በወጣት የጦር ጠበብቶች  የተሞላው 99ኛ ክ/ጦር በአጭር ጊዜ የመከላከል እና መልሶ የማጥቃት ጥበብን በመጠቀም በጠላት ላይ ፈርጣማ ክንዶቹን አሳረፈ ።ከአባል እስከ አማራር እሳት ሲተፉ አመሹ እንኳን ገሊላን ለመቆጣጠር ይዞት የመጣውን ጓዱን ሳይሸክፍ ወደመጣበት የቀበሮ ጉድጓዱ አስፈረጥጠውታል። በዚህ አውደ ውጊያ በርካታ ሰራዊት ሙት እና ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል ©99ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት! 02/10/2018 ዓ.ም

ፍርድ ቤት ቀረበ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያው Girmaw Ashebir ዛሬ ፍርድ ቤት አቅርበውት ነበር። ግርማ ሰሞኑን በአርሲ ክርስቲያኖች ጉዳይ ባሰማው ድምጽ ምክንያት "በሚዲ
ፍርድ ቤት ቀረበ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያው Girmaw Ashebir ዛሬ ፍርድ ቤት አቅርበውት ነበር። ግርማ ሰሞኑን በአርሲ ክርስቲያኖች ጉዳይ ባሰማው ድምጽ ምክንያት "በሚዲያ ህዝብን ለአመጽ በማነሳሳት" የሚል ክስ ቀርቦበታል። በፍርድ ቤቱም  7 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆበታል። በአርሲው ጭፍጨፋ ጉዳይ እዛው ባህር ዳር ላይ የመንግስት ባለስልጣናት ሳይቀር ማህበራዊ ሚዲያው ላይ ድምጻቸውን ባሰሙበት ሁኔታ ነው ግርማው ለብቻ ተነጥሎ እንዲጠቃ የተደረገው። ዩኒቨርሲቲው ሰሞኑን አዘጋጅቶት በነበረው የሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው የመጻህፍ ምርቃት መርሃ ግብር መድረክ መሪ ነበር !! #አርሲየኦሮቶዶክሳዊያንየደምመሬት

የብልፅግና ሎሌዎች የዘረፋ ዶሴ በዳውንት ወረዳ! ቴዎድሮስ አሰፋ እና ቢትወደድ ገበየሁ በተባሉ የብልፅግና  ሎሌዎች(አመራሮች) በሚሰጥ የማህበረሰብ ዘረፋ በዳውንት ማህበረሰብ ላይ ከባድ ውድመትን ማስከተሉ የውስጥ ቀኘዎች መረጃውን አድርሰውናል። ቴዎድሮስ አሰፋ የወረዳዋ ሰላምና ደህንነት ሀላፊ ሲሆን፣ ቢትወደድ ገበየሁ ደግሞ የሚኒሻ ፅህፈት ቤት ሀላፊ ነው። በዳውንት ወረዳ ከሚኒሻ አባላቶች በሱስና በዳሸቀ ስነ-ምግባር የሚታወቁ አባላቶች ተመልምለውና ተልዕኮ ተሰቷቸው ጨለማን ተገን በማድረግ በኩርባ ከተማ ግለሰቦችን በማፈን ቤተሰቦቻቸውን እንገልባችኋለን በሚል ዛቻ ዘረፋ የፈፀሙ ሲሆን፤ በዚሁ ከተማ ውስጥ ከዚህ ቀደም ከተለያዩ ማህበረሰቦች ከመቶ ሽህ ብር በላይ ታፍነው ዘረፋ ፈፅመዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ሰኔ 01/2018 ዓ/ም  ምሽት ላይ በ09 ቀበሌ ሰንተል ከሚባል ቦታ ላይ የሚኒሻ አባል የሆኑት፦ 1/ ብርሀን ጥላሁን 2/ ይብሬ  የሱፍ 3/ እሱባለው ጎላ 4/ በሪሁን ይቅናው እና ሌሎች ግብረአበሮች በመሆን ግለሰቦችን ከመኖሪያ ቤታቸው በመግባት አፍነው በመውሰድ ሰባዊና አካላዊ ጉዳት ሲፈፅሙባቸው፤ በንብረታቸው ላይ ደግሞ ዘረፋ ፈፅመዋል። በ07 ቀበሌ የማህበረሰቡን ቤት በሩን ሰብሮ በመግባት በርካታ የማህበረሰብን ንብረትና ገንዘብ ዘርፈው ወደ ኩርባ ከተማ ለአለቆቻቸው የዘረፉትን ገንዘብ አስረክበዋል። ይሄንን ፀያፍ ተልዕኮ የሰጧቸው አመራሮች ሲሆኑ እነዚህ አካላቶች የሚኒሻ ፅህፈት ቤት  ሀላፊ በሆነው በቢትወደድ እና የወረዳዋ ሰላምና ደህንነት በሆነው በቴዎድሮስ አሰፋ ተልዕኮ እየሰጡ የወረዳዋን ማህበረሰብ ከዘረፋ እስከ አካላዊ ጉዳት እየፈፀሙባቸው  ይገኛሉ።ከዚህ ቀደም ከወለጋ ያመጡት ሽፍታ በፋኖዎች እርምጃ እንደተወሰደበት የሚታወቅ ሲሆን በዚህ ሰዓት ከሚኒሻ አባላቶች መልምለው ተልዕኮ በመስጠት እኩይ ተግባርን እና ሎሌያዊ ባህሪያቸውን እየፈፀሙ ይገኛል። ወንጀለኞቹ የጊዜ ጉዳይ እንጅ ግፉዓን ስንዝር አይሻገሯትም። የአማራ ህዝብም ነፃ ይወጣል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሰኔ 01/2018ዓ.ም

የአገዛዙ 11ኛ ዕዝ 90ኛ ክፍለ ጦር የሰራዊት አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው ምኒልክ ዕዝን ተቀላቀሉ!! ሰሞኑን በማደናገሪያ ምርጫ ሰበብ በወሎ ቤተ አማራ ምዕራብ ወሎ ግንባሮች ከባድ የሆነ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ የደረሰበት 11እዝ 104ኛ ኮር 90ኛ ክፍለ ጦር  የሰራዊት አባላት ሲሆኑ ከነዚህም መካከል ድሽቃ ተኳሹን ጨምሮ 5 አባሎች ከነሙሉ ትጥቃቸዉ አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክፍለ ጦር አትሮንስ ሻለቃን ተቀላቅለዋል። እነዚህ የሰራዊት አባላትም  የብልፅግናዉ ስርዓትን በመፀየፍ  ከነሙሉ ትጠቃቸዉ በትናንትናው ዕለት ማለትም ሰኔ 1/2018 ዓ.ም አትሮንስ ሻለቃን የተቀላቀሉ ሲሆን አባሎቹ ሲመጡ የምኒልክ ዕዝ የ105ኛ የኮር አመራር እና የክፍለ ጦር አመራሮች ደማቅ አቀባበል አድርገዉላቸዋል። የመከላከያ አባሎቹም ፋኖ እያደረገላቸዉ ያለዉን እንክብካቤ በጣም እንዳስደሰታቸዉ ገልፀዉ አሁንም የብልፅግናን ወንበር ለማስጠበቅ ስትሉ ዳግም እማትገኝ ዉድ ህይወታቹህን ሳትገብሩ በየ ቀጠናቹህ ወደሚገኝ የፋኖ አደረጃጀት በመዉጥት ተቀላቀሉ ሲሉ ላልወጡ የሰራዊት ጓዶቻቸዉ ጥሪ አስተላልፈዋል። ፋኖ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ መብረቃዊ ጥቃት ከመፈፀም ባለፈ በስቦ ማስከዳትም ደማቅ ድል እየተቀዳጀ ይገኛል ሲል የ105ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን  መምሪያ!! ሰኔ 2/2018ዓ.ም

ቀን 02/10/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነዉ ዕዝ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦር ፪ኛ ሻለቃ በሰራችው ድንቅ ና ልዩ የከተማ ውስጥ ኦፕሬሽን ካለምንም የተኩስ ልውውጥ የአገዛዙን የሚሊሻ ሻንበል መሪ ከነ ሙሉ ትጥቁ ጋማውን አንጠልጥላ በድል ተመልሳለች። የነጎድጓድ ክፍለ ጦር 2ኛ ሻለቃ ትናንት ሰኔ 01/2018 ዓ/ም ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት ገደማ ላይ በደብረ ብርሃን ከተማ ዙሪያ በሚገኘው በሲያደብርናዋዩ ወረዳ ስር ልዩ ስሙ አንጨቆረር ከተማ ድረስ ዘልቃ በመግባት በወሰደችው የተጠና ልዩ ኦፕሬሽን የአገዛዙን ወንበር አስጠባቂ ሚሊሻ ሻምበል መሪ የሆነውን መካሻ አግደው በጋሻው የሚባለውን ባንዳ ሚሊሻ ከነሙሉ ትጥቁ ስታወጣ አቶ መካሻ አግደው በበኩላቸው ይሕንን ብለዋ፡ ፋኖ እደመብረቅ ድንገት ከፊቴ ሲበራብኝ የእምነታቸውና የታማኝነታቸው ልክ ገብቶኛል ስለሆነም በአገዛዙ እንደኔ የተታለላችሁ አድማ ብተና ና ሚሊሻወች አገዛዙ አያዋጣም እኔ አረጋግጫለሁ ስለዚሕ እናተም ተረዱና ወደ ፋኖ ተቀላቀሉ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የፋኖ አናብስቶቹም ይሕንን ሲሉ መልዕታቸውን አስተላልፈዋል ፡ ከአገዛዙ ጎን የተሠለፋችሁ ሁሉ እኛ ስራችን ነውና ከዚሕ ብትማሩ ይበጃችኋል ብለዋል ። በሌላ ዜና የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር ንጉስ ሳህለ ሥላሴ ክፍለጦር የተሀድሶ መርሀግብር አካሒደዋል። በዚሕ መርሃግብር የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሰብሳቢ አርበኛ እንጂነር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ፡ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ፖለቲካ መምሪያ ሃላፊ አርበኛ ዶ/ር ታደሰን እና ሌሎች የዕዝ፣የኮር እና የክፍለጦር አመራሮችን ጨምሮ የክፍለ ጦሩ ሰራዊት በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል። እንዲሁም ከክፍለጦር አመራሮች ለተነሱ ጥያቄዎች በየደረጃው በሚገኙ አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ የተሠጠበት ሲሆን ሠራዊቱም ከዛሬዋ ሰዓት ጀምሮ ለቀጣይ ድርጅታዊ ግዳጆች ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ክብር ለትግሉ ሠማዕታት ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!!! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሰኔ 02/2018 ዓ/ም

የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር አፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር የተሀድሶ ፕሮግራም አካኼደ!! ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ​አንጋፋው አፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር የተሰጠውን ድርጅታዊ ግዳጅ በስኬት አጠናቆ ከተመለሰ በኋላ ሰፊ የተሀድሶ መርሀግብር አካሄደ። ​በዚህ የተሀድሶ መርሀግብር ላይ የአምሃራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አመራር፣የ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አመራሮች ፣ የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ኮር አመራሮች እና የዓፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር አመራሮች በተገኙበት ወቅታዊ ዝግጁነትንና ቀጣይ የትግል አቅጣጫዎችን በተመለከተ ግምገማና ውይይት አድርጎል። ​ክፍለ ጦሩ፡ በቅርቡ አገዛዙ ያካሄደውን "የጨረባ ምርጫ" ለማስፈጸም የተሸረቡ ሴራዎችን ለማክሸፍ በተለያዩ ግንባሮች በቆራጥነት በመሰማራት ሕዝባዊና ድርጅታዊ ግዴታውን በላቀ ድል መወጣቱን በውይይቱ ላይ የነሳ ሲሆን ፡ ክፍለጦሩ ከመቼውም በላይ ራሱን በማሻሻል ድርጅታዊ ተልዕኮችን በመቀበልና ግዳጅን በመወጣት ለወጣለት ለአማራ ሕዝብ በቁርጠኝነት የቆመ ና አርአያ መሆን የሚችል ግዙፍና ጠንካራ እዲሁም ልበ ሙሉ ጦር ነው ሲል የክፍለ ጦሩ ዋና መሪ አርበኛ አቡሽ ገልፀዋል። የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዋና ዘመቻ መምሪያ ሃላፊ አርበኛ አሳልፍ ደስታ(ቀጭን) በበኩላቸው ክፍለ ጦሩ ልክ እንደ አማራ የፅንዓት ምልክት ነው ብለዋል። በሌላ በኩል የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሃብት አሠባሰብ መምሪያ ሃላፊ አርበኛ አበበ ፀጋዬ "ክፍለ ጦሩ" ልክ እንደ ዓፄ ይኩኑ አምላክ " ታማኝ" ነው ብለዋል። ​በፕሮግራሙ ማጠቃለያ ላይ ክፍለ ጦሩ ባደረገው በዚህ የተሀድሶ መድረክ ይበልጥ ተጠናክሮና ተደራጅቶ በመምጣት የአማራ ሕዝብ የጣለበትን አደራ ለመወጣትና የትግሉ ሠማዕታት የሠጡት አደራ ለመወጣት በቀጣዩ ማንኛውም ዓይነት የድርጅት ግዳጆች ለመወጣት ሙሉ ዝግጁነቱን አረጋግጧል። ​✊ "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!!!" ​💪 "ሕልውናችን በተባበረ ክንዳችን!" ​ሰኔ 01/2018 ዓ.ም አፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግኑኝነት መምሪያ

የኔታ በትረ ማርያም አበባው ታሰሩ።   የኔታ በትረ ማርያም አበባው በኢትዮጵያ  ቤተ ክርስቲያን ብርቱ አገልጋይ ናቸው። እጅግ ሰላማዊ ናቸው። ለምን ታሰሩ? ስለ አርሲ ክርስቲያኖች ፍጅት ለምን ትጽፋለህ ሊሆን ይችላል። በተለይም በማኅበራዊ ሚዲያና በተለያዩ የትምህርት መድረኮች ላይ ሰፊ የወንጌልና የሃይማኖት ትምህርት የሚያስተምሩ መምህርና የሊቃውንት ትምህርትን በቀላል መንገድ የሚያስረዱ ዘመኑን የዋጁ ናቸው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሚገኙትን የጉባኤ ቤት ትምህርቶችን ለምዕመናን በቀላሉ ተደራሽ አድርገዋል። የተለያዩ ጥናታዊ ጽሑፎችን፣ የጥያቄና መልስ መርሐ ግብሮችን፣ እንዲሁም እንደ "የሥነ ፍጥረት ትምህርት" እና  መሰል መጻሕፍትንና ጽሑፎችን በዲጂታል ፎርማት በማዘጋጀት በነጻ አሰራጭተዋል። በቤተ ክርስቲያኒቱ ዶግማና ቀኖና ዙሪያ የሚነሱ ጥያቄዎችንና ወቅታዊ የፕሮቴስታንት ተሐድሶአዊ እሳቤን በሊቃውንት ትርጓሜ መሠረት ምላሽ በመስጠት ይታወቃሉ። ሊቁ ያዘጋጁት መጻሕፍት 1)"ኦርቶዶክሳዊ ተዋሥኦ  ቅጽ 1  እና 2" በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የሚነሱ ልዩ ልዩ ጥያቄዎችንና ኦርቶዶክሳዊ ምላሾቻቸውን በጥልቀት የያዘ መጽሐፋቸው ነው። በተጨማሪ በመጻሕፍተ ሊቃውንት፣ በመጻሕፍተ መነኰሳት እንዲሁም በሐዋርያት የሥርዓት መጻሕፍት ላይ ለተነሡ ጥያቄዎችና አሻሚ ሐሳቦች ሰፊ ማብራሪያና ምላሽ የሚሰጥ ነው። 2)"ነገረ ማርያም በሊቃውንት" የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ዘለዓለማዊ ድንግልና፣ ንጽሕና እና የነገረ ማርያም ትምህርትን መጻሕፍትን አጣቅሶ በመተንተን ለመናፍቃን ምላሽ የሰጡበት መጽሐፍ ነው። 3)መሠረታዊ የግእዝ ቋንቋ መማሪያ የታሰሩት/የታገቱት ጎንደር ከተማ ነው።