Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union
رفتن به کانال در Telegram
This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.
نمایش بیشتر4 478
مشترکین
-324 ساعت
+117 روز
+2730 روز
آرشیو پست ها
የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በትላንትናው እለት የጁምዓ ሰላት ሰዓት እንዲስተካከል ለዩኒቨርሲቲው አሳሰበ ።
ደብዳቤው በዋናነት ለዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት ፤ በግልባጭ ለአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት እና ለተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር ባስገባው ደብዳቤ የሐገራችን መንግስት ሙስሊም ሰራተኞች የጁምአ ሰላትን እንዲሳተፉ ለማድረግ የመንግስት መስሪያ ቤቶች አርብ ከ 05፡30 እስከ 07፡30 እንዲዘጉ መመሪያ ያወጣና የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንትን ጨምሮ የዩንቨርስቲው አመራሮች ለመመሪያው መተግበር ቁርጠኛ መሆናቸው የገለጹ ቢሆንም ባለፉት ጊዜያት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በውጤታማነት አለመተግበሩን ጠቅሷል።
የትምህርት ዘመኑ እየተጀመረ በመሆኑ የተማሪዎች ህብረት እና ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ሁሉም የአካዳሚክ መርሃ ግብሮች የጁሙዓ የሰላት ጊዜን በሚመለከት የመንግስት መመሪያዎች መተግበራቸውን እንዲከታተሉና ስህተቶችንም እንዲያርሙ አጥብቆ አሳስቧል።
የህብረቱ ተወካዮች ከተማሪዎች ህብረት ጋር በጉዳዩ ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን የተማሪዎች ህብረትም ጥያቄው ተገቢ መሆኑን በመጥቀስ አፈጻጸሙን እንድሚከታተል ገልጿል።
ዩኒቨርሲቲውም በጉዳዩ ላይ ተወያይቶ ከሳምንት በኋላ ውሳኔ እንደሚሰጥ አሳውቋል።
አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ሙስሊም ተማሪዎች:-
የASTU ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ መረጃ ከመስጠት ጀምሮ በአግባቡ የሚቀበሏችሁንና የሚያስተናግዷችሁን ሙስሊም እህት ወንድሞቻችሁን አዘጋጅቷል::
♢ 0979509258 ••• ሰለሐዲን አብደላህ
♢ 0941232826 ••• ሙሐመድአሚን ጀማል
ለእህቶች:- +251965164385
እህቶች ከላይ በተጠቀሱት ስልክ ቁጥሮችም ጭምር በእህቶች በኩል ያሉ የጀመዓው አስተባባሪዎችን አድራሻ ማግኘት እንደምትችሉ ጀመዓው አሳውቋል::
https://t.me/EHEMSU
ለAASTU (አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ) አዲስ ገቢ ሙስሊም ተማሪዎች:-
በመጀመሪያ ለዚህ ያበቃችሁን አምላካችንን አላህ እያመሰገንን በሚከተሉት አድራሻዎች ስለ ዩኒቨርሲቲው: ጀመዓው እና አጠቃላይ ሁኔታዎች መረጃ ማግኘት እንደምትችሉ እንገልፃለን::
♢ አብዱሰላም ሁሴን --- 0979037273
♢ ፋሩቅ ባህሩ --- 0928988230
♢ አይመን ሁሴን --- 0938807462
♢ ሳሊም አሕመድ --- 0986164265
:- በእህቶች በኩል ያሉ የጀመዓውን ተወካዮች ስልክ ቁጥር ከላይ ከተጠቀሱት ወንድሞች ማግኘት ትችላላችሁ:: አላህ ፍሬያማ እና ራሳችሁን ጠቅማችሁ ኡማውን የምታገለግሉበትን የዩኒቨርሲቲ ሕይዎት ይወፍቃችሁ ዘንድ ዱዓችን ነው::
https://t.me/EHEMSU
ለአርባ ምንጭ ዩንቨርስቲ አዲስ ገቢ ሙስሊም እህት ወንድሞቻችን:-
በመጀመሪያ የአላህ ሰላም እዝነት እና ረድዔት በእናንተ ላይ ይሁን :: ምስጋና ሁሉ ሁሉንም ችግር አልፋችሁ በውጤት ለእዚህ ስኬት እንድትበቁ ላስቻለው ጌታችን አላህ የተገባ ይሁን :: እንደ አንድ ሰውነት ሆነን እንድንደጋገፍ እና እንድንረዳዳ ባስተማሩን አዛኙ ነብይ ላይም የአላህ ውዳሴ እና ሰላም ይስፈን ::
የ የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ሙስሊም እህት ወንድሞቹን በኢስላማዊ ፍቅር እና እንክብካቤ አቅፎ ለመቀበል ዝግጅቱን አጠናቋል :: ስለሆነም እናንተ እህት ወንድሞቻችን ከምንም በላይ ከደም በላይ የሚያጋምደንን የኢስላም እህት ወንድማማችነት በማሰብ ማንኛውም የምትፈልጉትን መረጃ እና እገዛ በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች በኩል ትጠይቁ ዘንድ እንጠይቃለን :
👉AMU Muslim students union
📞 0950805051
👉 Main campus
📞Amir :-0963764285 Andurazaq. shamsu
📞V. Amir:-0967348340 Osama Ali
👉Chamo campus
📞Amir :- 0940020497 abdela ferej
📞V. Amir:-0907568300 Awol mohammed
👉 Sawla campus
📞Amir :- 0988401854 Umar Mokriya
👉Abaya campus
📞Amir:- 0963638759 Mohammed sa'id...
👉 Kulfo campus
📞Amir :-0944450840. Hayatu....
👉Nechsar campus
📞 Amir :- 0915273321 Mohammed Adem
ወደ ግቢ የምትቀላቀሉ እህቶች የሴት ተወካዮችን በነዚህ ወንድሞች በኩል ማግኘት ትችላላቹ
አርባምንጭ ዩንቨርስቲ የሞሉ ተማሪዎች ቀድመው መረጃ እንዲያገዩ በተለያዩ ግሩፖች ሼር እናድርግ
https://t.me/amumsu1
Repost from AAU - Muslim Students Union
ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ገቢ ሙስሊም እህት ወንድሞቻችን:-
በመጀመሪያ የአላህ ሰላም እዝነት እና ረድዔት በእናንተ ላይ ይሁን :: ምስጋና ሁሉ ሁሉንም ችግር አልፋችሁ በውጤት ለእዚህ ስኬት እንድትበቁ ላስቻለው ጌታችን አላህ የተገባ ይሁን :: እንደ አንድ ሰውነት ሆነን እንድንደጋገፍ እና እንድንረዳዳ ባስተማሩን አዛኙ ነብይ ላይም የአላህ ውዳሴ እና ሰላም ይስፈን ::
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ሙስሊም እህት ወንድሞቹን በኢስላማዊ ፍቅር እና እንክብካቤ አቅፎ ለመቀበል ዝግጅቱን አጠናቋል :: ስለሆነም እናንተ እህት ወንድሞቻችን ከምንም በላይ ከደም በላይ የሚያጋምደንን የኢስላም እህት ወንድማማችነት በማሰብ ማንኛውም የምትፈልጉትን መረጃ እና እገዛ በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች በኩል ትጠይቁ ዘንድ እንጠይቃለን ::
☎️ AAU MUSLIM STUDENTS UNION - 0909524252
Main and FBE Campus
☎️ አብዱረሂም አሚን
ስልክ ፦ +251995477358
☎️ አሊፍ ሀጂ
ስልክ ፦ 0955942642
CTBE (AAiT) (5 Kilo) Campus
☎️ማህፉዝ ነጋሽ - 5 kilo - 0996220264
4 Kilo Campus
☎️ ዘይድ ሳዲቅ - 4kilo - +251992546811
☎️ መስዑድ አሊ -4 kilo +251968645684
Sefere Selam Campus
☎️ አብዱረህማን ወሊዩ -sefere selam +251925025478
☎️Bedhaso -sefere selam +251988358715
Ldeta Campus
☎️ Yusuf Hamid
ስልክ ፦ 0907645390
☎️ Dawud Sultan
ስልክ ፦ 0951023812
ወደ ግቢ የምትቀላቀሉ እህቶች የሴት ተወካዮችን በነዚህ ወንድሞች በኩል ማግኘት እንደምትችሉ ለማሳወቅ እንወዳለን።
https://t.me/aaumsu
ከጁምዓ ቀን የስራ ሰዓት ጋር ተያይዞ ያለው አዋጅ በዚህ ዶክመንት ውስጥ ይገኛል:: በዶክመንቱ ገፅ 86 እና 87 ላይ እንደተቀመጠው አዋጁ ጁምዓ ቀን የስራ ሰዓት ከጧት እስከ 5:30 ከሰዓት ደግሞ ከ8:00 ጀምሮ እንደሆነ ይደነግጋል::
@MohammadamminKassaw
ከAAUMSU ይህንን እንደ ሞዴል ተጠቀሙ:: ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም ሆናችሁ ካምፓሶች or ት/ቤቶች ከጁምዓ ቀን የትምህርት ክፍለ ጊዜ ጋር ተያይዞ ያለውን የሰዓት ስህተት አስተካክሉ:: በሕጉ መሠረት ጁምዓ ቀን የትምህርት ክፍለ ጊዜ ከጧት እስከ 5:30 ከሰዓት ደግሞ ከ8:00 ጀምሮ ነው:: ከ5:30 እስከ 8:00 ባለው ውስጥ ትምህርት የሚሰጡት ከሕግ እና መመሪያ ውጪ ነው:: ይህንን ማስተካከል ደግሞ የራስን መብት ከማስከበር ነው::
:- ይህ ደግሞ መሆን ያለበት ነገሩ ሁሉ ካለፈ ቡሃላ ሳይሆን ከአሁኑ ትምህርት ሳይጀመር ነው::
@MohammadamminKassaw
+1
የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ዩኒቨርሲቲው በነጭ ሳር ካምፓስ ኒቃቢስት ተማሪዎችን "ኒቃብ ለብሳችሁ ግቢ መግባትም ሆነ ዶርሚተሪ መያዝ አትችሉም!" ማለቱን ተከትሎ ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፅ/ቤት ጥያቄውን አቅርቧል:: መሠል የመብት ጥሰት የሚፈፅሙ አካላትም ተጠያቂ እንዲደረጉ ጠይቋል::
+1
አላህ አላህ!
አይመን ኸይረዲን ••• 579 ከ600ው ••• ከአዲስ አበባ አዲስ ከተማ ትምህርት ቤት !
አላሁ አክበር !
አላሁ አክበር ! !
እንኳን ደስ ያለው !
እንኳን ደስ አለን ! !
@MohammadamminKassaw
ሌላ ጀግና ሌላ ሰቃይ - 585 ከ600ው!
ሁንዳኦል አባስ ቱሬ - የኻሊድ ጓደኛ !
እርሱም የዶዶላ ልጅ ነው ሰዎች:: ምን አይነት ተዓምር ነው በረቢ? ምን አይነት ጀግኖች ናቸው በአላህ?!
አላህ ይጨምርላቸው!
ደስ አሰኙን --- ደስ ያሰኛቸውና !!
@MohammadamminKassaw
ኒቃብ ••• በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የነጭ ሳር ካምፓስ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ኒቃብ ለብሶ መግባትን ተከለከሉ!
አዲስ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ቅዳሜ ጀምሮ መግባት የጀመሩ ሲሆን ኒቃቢስት ተማሪዎችን ኒቃብ ካላወለቃችሁ አትገቡም ዶርሚተሪ አትሰጡም እንደተባሉ ጀመዓው አሳውቋል:: የተማሪዎችንም የመብት ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ እስከመጨረሻው እንደሚታገል ገልፇል::
:- ዩኒቨርሲቲዎች ካለፉት አመታት የመብት ጥያቄዎች መማር አለባቸው:: መሠል ስህተት የሚፈፅሙ የዩኒቨርሲቲ አመራሮችም ተጠያቂ መሆን አለባቸው::
@MohammadamminKassaw
ጥቂት ስለ ትንታጉ ተማሪ ኻሊድ በሺር!
ቁርዓን ሐፊዝም ነው ጎበዝ!
በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ኢንትራንስ ፈተና ከ600ው 591 ያመጣው ኻሊድ በሺር ውልደቱ ቡኖ በደሌ ዞን ውስጥ በምትገኘው ጋቺ ወረዳ ነው:: እስከ 6ኛ ክፍል ድረስ እዚያው ተምሯል:: ቁርዓንን ሸይኽ ዘይኑ ላይ አክትሟል ሀፍዟል:: አባቱ መምህር ናቸው:: በስራም ምክንያት ወደ አርሲ ተዛውረው አሁን እዚያ ናቸው::
@MohammadamminKassaw
እንኳን ደስ አለው !
እንኳን ደስ አለን ! !
ወንድማችን ኻሊድ በሺር ከሁሉም የኢትዮጵያ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከ600 ••• 591 በማምጣት ሰቃይ ሆኗል::
ስለ ስኬቱ ደስ ብሎናል !
አላህ ይባርክለት ! !
+1
ሶላተል- ጀመዓ በቤተ- መንግስት !
አዲሶቹ የመጅሊስ አመራሮች በቤተ- መንግስት የጀመዓ ሶላት ሲሰግዱ የሚያሳይ ፎቶ ነው ••• ይህ እንግዲህ ዛሬ የሆነ ነው !
ትምህርት ቤት የሚከለክሉትስ? ትምህርት ቤት እንከለከላለን ብለው የማይከተሉትስ?
ልጆች ሆይ:- አባቶቻችሁን ምሳሌ አድርጋችሁ ስገዱ ••• መብታችሁ ነውና
ት/ቤቶች ሆይ:- ቤተ- መንግስቱን ምሳሌ አድርጋችሁ ተማሪዎች ሲሰግዱ ለመከልከል አትሞክሩ ••• መብታቸውን ማክበር ግዴታችሁ ነውና
@MohammadamminKassaw
ስራ --- አካውንቲንግ ፍሬሽ ተመራቂ!
ቦታ:- አዲስ አበባ
CVያችሁን @MOHAMMADAMMINM ላኩልኝ::
@MohammadamminKassaw
ዲላ ዩኒቨርሲቲ በኒቃብ ጉዳይ ጥቁር ታሪክ ያለው ግቢ ነበር ••• በ2016 ዓ.ል 60 ገደማ ተማሪዎች በኒቃብ ጉዳይ ከትምህርታቸው ተሰናክለዋል ••• ከዚያም ቡሃላ አልፎ አልፎ መሠል ትንኮሳዎች እየተፈፀሙ ተማሪዎችም ችለው እያለፉ 2017 ዓ.ል ደረሰ ••• በዚህም አመት ዩኒቨርሲቲው "ከኒቃባችሁ እና ከትምህርታችሁ ምረጡ!" - በሚል ያልሆነ ምርጫ ሊያስመርጣቸው ሞከረ:: ተማሪዎቹም "ኒቃቡም ትምህርቱም ምርጫዎቻችን ሳይሆኑ ግዴታዎቻችን ናቸው!" - ብለው ወደ ትግል ገቡ:: ስለ መብታቸው ሲሉ ከዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ አልፈው ዞን ክልል ፌደራል ማሰኑ:: እምቢኝ ተብለው ከግቢ ሲባረሩም እምቢኝ ብለው ለ10 ቀናት ከትምህርት ምግብ እና ዶርም ተከልክለው ከመስጂድ ተጠለሉ:: በስተመጨረሻም በአላህ ፈቃድ መብታቸውን አስጠብቀው ተባረውበት ወደነበረው ግቢ በክብር ገቡ::
ይህ በሙስሊም ተማሪዎች ሰላማዊ የመብት ጥያቄ ሂደት ውስጥ በተምሳሌትነት ከሚጠቀሱት ነው:: ይህንንም እውቅና በመስጠት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ባካሄደው 4ኛ አመት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የምስክር ወረቀት ሰጥቷል::
አባጅፋር (ረህመቱላሂ ዐለይሂ) ጅማ በእርሳቸው እስክትታወቅ ድረስ የፍትሕ: የጀግንነት እና የጥበብ ተምሳሌት ነበሩ:: ከተማቸው ጅማም እንዲሁ በተመሳሳይ:: ሆኖም አባጅፋር ባፀኗት ከተማ የአባጅፋር ልጅ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ መሠረታዊ ሐይማኖታዊ መብታቸው ተገፎ ለአመታት ዘልቀው ነበር:: ሙስሊም ሴት ተማሪዎች የሐይማኖት መገለጫቸው የሆነውን ኒቃብ ለብሰው መማር ተከልክለው ነበር:: ሙስሊም ወንድ ተማሪዎች ጀለብያ እና አማኢማ ለብሰው መማር ይከለከሉ ነበር::
ሆኖም የዚህ ትውልድ ልጆች ••• ሊበቃ ሊያበቃ ይገባል ብለው በ2017 ዓ.ል በወርሐ ረመዳን ስለ መብታቸው ጠይቀው ታገሉ ••• በስተመጨረሻም ለአመታት ሲፈፀም የነበረውን የመብት ጥሰት አስቁመው መብታቸውን አስከበሩ::
ይህንንም የጅማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ትግል የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት እውቅና በመስጠት ባካሄደው 4ተኛ አመት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ የምስክር ወረቀት ሰጥቷል!
በደሌ ካምፓስ ላይ የነበረውን የሚረሳ ያለ አይመስለኝም ••• በ2017 ዓ.ል በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ከደረሰባቸው የመብት ጥሰቶች መካከል በመቱ ዩኒቨርሲቲ በደሌ ካምፓስ የሚገኙ ሙስሊም ተማሪዎች ይጠቀሳሉ:: ዩኒቨርሲቲው "ወይ ኒቃባችሁን አውልቃችሁ ተማሩ --- ወይ ደግሞ እቃችሁን ሸክፋችሁ ወደ ቤታችሁ ተመለሱ!" የሚልን አማራጭ ለሙተነቂቦች ሲያቀርብ ••• ሁሉም ተማሪ ጁምዓ ቀን "እህቶቻችን ገብተው ካልተማሩ እኛም አንማርም!" በማለት ከበር ላይ ከጧት ጀምሮ እስከ ቀኑ 11:30 ድረስ ቆመው ከብዙ ንግግር ቡሃላ በሰላማዊ መንገድ መብታቸውን አስከብረው ነበር::
ይህ በበደሌ የነበረው የተማሪዎች ጥያቄ ከዚያ ቡሃላ ለነበሩ የመብት ጥያቄዎች ፈርቀዳጅ ነበር ••• የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረትም ይህንን ተምሳሌታዊ ተግባር ባካሄደው 4ተኛ አመት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ እውቅና ሰጥቷል::
መቱ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረትም ተማሪዎቹን በመወከል የእውቅና ምስክር ወረቀቱን ተቀብሏል!
+3
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ተወካዮች በኬንያ በተዘጋጀው የምስራቅ አፍሪካ ተማሪዎች ኮንፈረንስ ላይ ተሳተፉ!
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ረቡዕ:- ነሐሴ 14/2017 ዓ.ል
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ተወካዮች በኬንያዋ ናይሮቢ ለአምስት ቀናት በተካሄደው የምስራቅ አፍሪካ ተማሪዎች ኮንፈረንስ ላይ ተሳታፊ ሆነዋል:: በኮንፈረንሱ የኬንያ: ታንዛኒያ: ሩዋንዳ: ቡሩንዲ እና ኡጋንዳ ተወካዮች የተሳተፉ ሲሆን በተማሪዎቹ መካከል የልምድ ልውውጥ ፕሮግራም ተካሂዷል:: የህብረቱ ተወካዮች ከተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ጀመዓዎች የተወከሉ ሲሆን ለጀመዓዎቻቸው የሚጠቅሙ ልምዶችን ከተለያዩ ሀገራት ጀመዓዎች እንዳገኙ ገልፀዋል::
+1
ሐርቫርድ ዩኒቪርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች አዲስ የመስገጃ ሥፍራ አዘጋጀ ።
በአሜሪካ ማሳቹሴትስ የሚገኘው ሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ፤ ለሙስሊም ተማሪዎች አዲስ የመስገጃ ሥፍራ ማዘጋጀቱን አስታውቋል።
የዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ጋዜጣ ሐርቫርድ ክሪምሰን በድረ ገጽ ባሠራጨው መረጃ መሠረት፣ በማደሪያ ክፍሎችና በጊዜያዊ መስገጃነት በተዘጋጁ ሥፍራዎች ተወስነው የቆዩ ሙስሊም ተማሪዎች ከመስከረም ወር አንስቶ በተዘጋጀላቸው አዲስ መስገጃ ሥፍራ መስገድ ይችላሉ።
ዩኒቨርሲቲው ያሳለፈው ውሳኔ በሙስሊም ተማሪዎች ማኅበራት አድናቆት ተችሮታል። የሐርቫርድ እስላማዊ ማኅበር የውስጥ ግንኙነት ተባባሪ ዳይሬክተር ሻኪራ ዓሊ፤ ዩኒቨርሲቲው ቋሚ የመስገጃ ሥፍራ ማዘጋጀቱ የኀላፊዎችን ቁርጠኝነት ያሳያል ብላለች።
ሙስሊም ተማሪ እንደመሆኔ መጠን ያለ ሐሳብ የመስገጃ ሥፍራ ማግኘቴ እፎይታ የሚሰጥ ስለሆነ እንደ ቀላል ነገር የምወስደው አይደለም ስትል አክላለች።
በሐርቫርድ የሚገኙ ሙስሊም ተማሪዎች እ.አ.አ ከ1995 ጀምሮ የመስገጃ ሥፍራ ችግር እንዳለባቸው ሲገልጹ መቆየታቸው ተዘግቧል። የዩኒቨርሲቲው ሙስሊም ኢማም ዓብዱልረሺድ ለተማሪዎች በላኩት ኢሜይል ለዓመታት ሲነሳ የነበረው ቅሬታ መፈታቱን ገልፀዋል።
@MohammadamminKassaw
