1 142
مشترکین
+124 ساعت
+27 روز
+1530 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
سپتامبر '26
سپتامبر '26
+9
در 0 کانالها
اوت '26
+54
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '26
+48
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '26
+40
در 0 کانالها
Get PRO
مه '26
+42
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '26
+28
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '26
+37
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '26
+25
در 1 کانالها
Get PRO
ژانویه '26
+18
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '25
+19
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '25
+28
در 1 کانالها
Get PRO
اکتبر '25
+30
در 1 کانالها
Get PRO
سپتامبر '25
+25
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '25
+33
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '25
+36
در 1 کانالها
Get PRO
ژوئن '25
+18
در 0 کانالها
Get PRO
مه '25
+35
در 1 کانالها
Get PRO
آوریل '25
+36
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '25
+67
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '25
+54
در 1 کانالها
Get PRO
ژانویه '25
+52
در 1 کانالها
Get PRO
دسامبر '24
+45
در 1 کانالها
Get PRO
نوامبر '24
+45
در 1 کانالها
Get PRO
اکتبر '24
+56
در 1 کانالها
Get PRO
سپتامبر '24
+55
در 1 کانالها
Get PRO
اوت '24
+72
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '24
+114
در 2 کانالها
Get PRO
ژوئن '24
+124
در 0 کانالها
Get PRO
مه '24
+58
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '24
+30
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '24
+37
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '24
+39
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '24
+56
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '23
+18
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '23
+263
در 0 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 07 سپتامبر | 0 | |||
| 06 سپتامبر | +2 | |||
| 05 سپتامبر | +4 | |||
| 04 سپتامبر | 0 | |||
| 03 سپتامبر | 0 | |||
| 02 سپتامبر | +3 | |||
| 01 سپتامبر | 0 |
پستهای کانال
| 2 | 216ኛው የለንደን ደርቢ በአርሰናል አሸናፊነት ተጠናቀቀ
ጳጉሜን 1/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) በሦስተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በኢሚሬትስ ቼልሲን ያስተናገደው አርሰናል 2 ለ 1 በማሸነፍ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል።
አዲስ ፈራሚው ሞርጋን ሮጀርስ ጨዋታው በተጀመረ በ2ኛው ደቂቃ ባሰቆጠራት ግብ ቼልሲን ቀዳሚ ቢያደርግም፣ 25ኛው ደቂቃ ላይ ካይ ሃቨርትዝ የአርሰናልን የአቻነት ግብ አስቆጥሮ የመጀመሪያው አጋማሽ 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ተጠናቅቋል።
ሆኖም በሁለተኛው አጋማሽ 50ኛው ደቂቃ ላይ ማርቲን ኦዲጋርድ ያስቆጠራት ግብ አርሰናልን አሸናፊ አድርጋለች።
ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል በሦስት ተከታታይ ድሉ በ9 ነጥብ ከሲቲ በግብ መጠን ተበልጦ ሁለተኛ ላይ ተቀምጧል። ቼልሲ በአንፃሩ በ6 ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል ።
አርሰናል በ4ኛው ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ቀጣይ ቅዳሜ ወደ ስታዲየም ኦፍ ላይት አቅንቶ ሰንደርላንድን ሲገጥም፣ ቼልሲ በተመሳሳይ ቅዳሜ ቀን በስታምፎርድ ብሪጅ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ አዲስ አዳጊውን ሃል ሲቲን ያስተናግዳል።
የተለያዩ ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የማህበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ!
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/share/181X2irsqB/
ቴሌግራም፡ https://t.me/bongafm974radiostatio
ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/@bongafm97.4?_t=ZM-90PCjvnnVBz&_r=1
ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/@BongaFM97.4 | 32 |
| 3 | "የሌማት ትሩፋት ስራ የህብረተሰቡን አኗኗር ዘይቤ ቀይሯል"፦ አቶ ሰለሞን ኃይሌ
ጳጉሜን 1/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) የሌማት ትሩፋት ስራ ከተጀመረ ወዲህ የህብረተሰቡ አኗኗር ዘይቤ መቀየሩን በካፋ ዞን የጨታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ኃይሌ ተናገሩ።
በወረዳው ኮላ፣ ቀይና እና ሻካ ቀበሌዎች የሌማት ትሩፋት መረሃ-ግብር አካል የሆነው የሞዴል ዶሮ መንደሮች ተመርቀዋል።
በመረሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ኃይሌ የሌማት ትሩፋት ስራ ከተጀመረ ወድህ የህብረተሰቡ የኑሮ ዘይቤ ተቀይሯል ብለዋል።
በርካታ የመንግስት የልማት ኢኒሼትቮች በአካባቢው እየተተገበሩ መሆናቸውን ጠቁመው አሁን የተመረቁ የዶሮ መንደሮች የዚሁ አካል መሆናቸውን ገልጸዋል።
ለተጨማሪው ......https://www.facebook.com/share/p/17kE8GarAZ/ | 56 |
| 4 | "የሌማት ትሩፋት ስራ የህብረተሰቡን አኗኗር ዘይቤ ቀይሯል"፦ አቶ ሰለሞን ኃይሌ
ጳጉሜን 1/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) የሌማት ትሩፋት ስራ ከተጀመረ ወዲህ የህብረተሰቡ አኗኗር ዘይቤ መቀየሩን በካፋ ዞን የጨታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ኃይሌ ተናገሩ።
በወረዳው ኮላ፣ ቀይና እና ሻካ ቀበሌዎች የሌማት ትሩፋት መረሃ-ግብር አካል የሆነው የሞዴል ዶሮ መንደሮች ተመርቀዋል።
በመረሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ኃይሌ የሌማት ትሩፋት ስራ ከተጀመረ ወድህ የህብረተሰቡ የኑሮ ዘይቤ ተቀይሯል ብለዋል።
በርካታ የመንግስት የልማት ኢኒሼትቮች በአካባቢው እየተተገበሩ መሆናቸውን ጠቁመው አሁን የተመረቁ የዶሮ መንደሮች የዚሁ አካል መሆናቸውን ገልጸዋል።
የሌማት ትሩፋት መረሃ-ግብር ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ማህበረሰቡ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆን ሚናው የጎላ ነው ብለዋል ።
ዘርፉ የእናቶችና ህጻናትን የምግብ ስርዓት በማሻሻል ጤናማ ትውልድ እንዲፈጠር የሚያስችል መሆኑንም አመላክተዋል።
ለተጨማሪው ....https://www.facebook.com/share/p/14xTPMBgzDS/ | 1 |
| 5 | "የሌማት ትሩፋት ስራ የህብረተሰቡን አኗኗር ዘይቤ ቀይሯል"፦ አቶ ሰለሞን ኃይሌ
ጳጉሜን 1/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) የሌማት ትሩፋት ስራ ከተጀመረ ወዲህ የህብረተሰቡ አኗኗር ዘይቤ መቀየሩን በካፋ ዞን የጨታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ኃይሌ ተናገሩ።
በወረዳው ኮላ፣ ቀይና እና ሻካ ቀበሌዎች የሌማት ትሩፋት መረሃ-ግብር አካል የሆነው የሞዴል ዶሮ መንደሮች ተመርቀዋል።
በመረሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ኃይሌ የሌማት ትሩፋት ስራ ከተጀመረ ወድህ የህብረተሰቡ የኑሮ ዘይቤ ተቀይሯል ብለዋል።
በርካታ የመንግስት የልማት ኢኒሼትቮች በአካባቢው እየተተገበሩ መሆናቸውን ጠቁመው አሁን የተመረቁ የዶሮ መንደሮች የዚሁ አካል መሆናቸውን ገልጸዋል።
የሌማት ትሩፋት መረሃ-ግብር ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ማህበረሰቡ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆን ሚናው የጎላ ነው ብለዋል ።
ዘርፉ የእናቶችና ህጻናትን የምግብ ስርዓት በማሻሻል ጤናማ ትውልድ እንዲፈጠር የሚያስችል መሆኑንም አመላክተዋል።
ለተጨማሪው ....https://www.facebook.com/share/p/14xTPMBgzDS/ | 1 |
| 6 | ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ለ"ህንግጫ" በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
ጳጉሜን 1/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ለኮንታ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ "ህንግጫ" በዓልን ምክንያት በማድረግ ለመላው የብሔረሰቡ ተወላጆችና ወዳጆች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው፤ የኮንታ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ በዓል ህዝቡ ከትውልድ ትውልድ ያሸጋገረውን ታሪካዊና ባህላዊ ማንነት፣ ሰላም፣ ፍቅርና አንድነት በማደስ በደስታና በህብረት የሚከበር ታላቅ እሴት መሆኑን ገልጸዋል።
ለተጨማሪው ...... https://www.facebook.com/share/p/1d8F6SuSuD/ | 63 |
| 7 | የጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) መልዕክት
የእመርታ ቀን
አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው!
በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል።
በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን።
ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን።
እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው! | 70 |
| 8 | ጳጉሜን 1
የእምርታ ቀን | 57 |
| 9 | "የቀጣናው ሀገራት በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ለኢትዮጵያ የባሕር በር በማመቻቸት ህልውናቸውን ማረጋገጥ አለባቸው" - ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)
ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) "የቀጣናው ሀገራት በሰላማዊ እና ሀብትን በጋራ በመጠቀም መርህ ለኢትዮጵያ የባሕር በር በማመቻቸት የጋራ ህልውናቸውን ማረጋገጥ አለባቸው" አሉ የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)።
ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ ከቀይ ባሕር ጋር የማይነጣጠል ታሪካዊ ቁርኝት ያላትና የባሕር በር ጥያቄዋም የ130 ሚሊየን ሕዝብ የህልውና አጀንዳ ነው፡፡
ከጥንት ጀምሮ ቀይ ባሕር የኢትዮጵያ ግዛት ወሰን አካል ሆኖ መኖሩን ገልጸው ኢትዮጵያውያን ነጋዴዎችም የራሳቸውን መገበያያ ገንዘብ በመጠቀም በቀይ ባሕር በኩል እስከ ሕንድ ውቅያኖስ ድረስ ይነግዱ እንደነበር እና ከ1950ዎቹ በኋላም አሰብና ምፅዋ የኢትዮጵያ ዋና የባሕር በር ወደቦች ሆነው ማገልገላቸውን አስታውሰዋል።
ሆኖም ህጋዊ መሰረት በሌለው ሁኔታ እንዲሁም ያለ ሕዝብ ይሁንታ እና ያለ በቂ ጥናት ኢትዮጵያ የባሕር በር እንድታጣ መደረጉንም አብራርተዋል።
በባሕር ንግድ በተሳሰረች ዓለም ውስጥ 130 ሚሊየን ሕዝብን ይዞ ያለ ምንም የባሕር መውጫ ረጅም ጉዞ ማሰብ አይቻልም ብለዋል፡፡
ለተጨማሪው ....https://www.facebook.com/share/p/189hp9CHkQ/ | 72 |
| 10 | “የማሽቃሮ በዓል አከባበር ድምቀት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መጥቷል” - አቶ ሰለሞን አየለ
ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) የካፈቾ ዘመን መለወጫ በዓል “ማሽቃሮ” ለረጅም ዓመታት ተቋርጦ ከነበረበት እንደገና መከበር ከጀመረ ወዲህ ከፍተኛ መሻሻል እንደታየበት የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን አየለ ተናገሩ።
ሰብሳቢው በካፋ ምሁራን ማህበር በተዘጋጀው “የባህል መነቃቃት፣ ማህበረሰባዊ ትስስርና አንድነት” በሚል ርዕስ በቦንጋ ከተማ በተካሄደው የባህል ሲምፖዚዬም ላይ ተሳትፈዋል።
አስቸጋሪ ወቅቶች አልፈው የማህበረሰቡን ታሪክና የበዓሉን ታላቅነት በሚመጥን መንገድ እየተከበረ በአሁን ወቅት በዓሉን የዓለም ቅርስ ለማድረግ በሚሰራበት ደረጃ ላይ መደረሱን ተናግረዋል።
የታሪክ ሊቃውንት የፃፏቸውና የጥንት እውነታዎች የማህበረሰቡን ታላቅነት የሚያረጋግጡ በመሆናቸው፤ በዚህ አኳሃን በዓሉን በየዓመቱ ማክበር እንደሚገባ ነው የገለጹት።
በዚህ መድረክ የቀረበውን ጥናታዊ ፅሁፍ መሠረት በማድረግ ይህ በዓል በከፍተኛ ትኩረትና ድምቀት እንዲከበር ለማስቻል አንድነት ወሳኝ ጉዳይ ነው ብለዋል።
በማህበረሰቡ መሪዎችና በምሁራን መካከል ትብብር፣ መከባበር፣ መደማመጥና የአድነት መንፈስ ይበልጥ መጠናከር እንዳለበት አስተያየት ሰጥተዋል።
የጋራ ሀብት ሆነው በበርካታ አካላት ትብብር የሚከናወኑ ተግባራትን ስኬታማ ለማድረግ አንድነትና መደማመጥ በእጅጉ እንደሚያስፈልግ አፅንኦት ሰጥተዋል።
ማሽቃሮን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ በሁሉም የእውቀት ደረጃና ማህበራዊ መሠረት ላይ የሚገኙ የማህበረሰቡ አባላት በባለቤትነት እንዲሰሩ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ፦ ዮሐንስ ክፍሌ
ፎቶ፦ በረከት ገብረኪዳን | 70 |
| 11 | “ማሽቃሮን በዩኔስኮ የማስመዝገቡ ስራ እውን እንዲሆን መስራት የሁሉም ኃላፊነት ነው” - የካፋ ምሁራን
ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) የካፈቾ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል “ማሽቃሮ”ን በዩኔስኮ የማይዳሰሱ ቅርሶች መዝገብ ለማስፈር በሚከናወኑ ስራዎች ላይ መሳተፍ የሁሉም ኃላፊነት መሆኑን የካፋ ምሁራን ተናገሩ።
የካፋ ምሁራን ማህበር ፕረዝደንት ዘገየ ወልደማርያም (ዶ/ር) “የባህል መነቃቃት፣ ማህበራዊ ትስስር እና አንድነት” በሚል ርዕስ በካፋ ልማት ማህበር በተዘጋጀ የባህል ሲምፖዚዬም ላይ “ማሽቃሮ፡ ሀገር-በቀል ጥበብ ለባህላዊ አስተዳደር፣ ለማህበራዊ ትስስርና አንድነት” በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሁፍ አቅርበዋል።
በጥናታዊ ፅሁፉ ከጥንት ጀምሮ ካፈቾ አዝመራ ላይ በመመሥረት የሚያከብረውን ይህንን በዓል፤ የወቅት ቀመርና የዘመን አቆጣጠር ጥበብ በዝርዝር አቅርበዋል።
ጥናቱ ታላላቅ የካፋ ታሪክ አዋቂዎችን፣ አዛውንቶችን በማካተትና የተለያዩ አካቢዎችን በመዳሰስ የተከናወነ ሲሆን፤ የአሮጌው ዓመት ስራዎች ተገምግመው ለቀጣይ ስራ አቅጣጫ የሚቀመጥበት መሆኑን ተናግረዋል።
ለተጨማሪው ......https://www.facebook.com/share/p/1BwYWVWacP/ | 66 |
| 12 | "የበዓል ገበያ በዋጋም ሆነ በምርት አቅርቦት ተመጣጣኝ ነው" ሸማቾች
ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) የእንቁጣጣሽ በዓል ገበያ በዋጋም ሆነ በምርት አቅርቦት ተመጣጣኝ መሆኑን በቦንጋ ከተማ የቅዳሜ ገበያ ሸማቾች ተናግሩ።
ኢትዮጵያውያን እንደየ-እምነታቸውና ባህላቸው ለበዓል የበሬ ቅርጫ እንዲሁም በግ፣ ፍየል፣ ዶሮ፣ ቅቤ፣ ሽንኩርትና ሌሎች አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን በመሸመት የማክበር ልምድ አላቸው።
በቦንጋ ከተማ ብዙኀኑን የሚያገናኘው የቅዳሜ ገበያ በበዓል ግብይት ደምቆ ውሏል ።
ጣቢያችን ባደረገው ቅኝት የእንቁጣጣሽ በዓል ግብይት ምን እንደሚመስል ተዟዙሮ ቅኝት አድርጓል።
ሲገበያዩ ካገኘናቸው መምህር ህገመንግስት ግዛዎ፣ አቶ ታመነ ታከሌና አቶ አሰፋ ገብረሚካኤል፤ የእንቁጣጣሽ በዓል ግብይት በዋጋም ሆነ በምርት አቅርቦት ተመጣጣኝ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም የበሬ ዋጋ ከ80ሺህ ጀምሮ እየተሸጠ መሆኑን ገልጸው ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር መጠነኛ ቅናሽ ማሳየቱን ሸማቾቹ ጠቁመዋል።
የበግና ፍየል ዋጋ ከባለፈው ዓመት ጋር ስነጻጸር ከ4ሺህ እስከ 5 ሺህ ብር ቅናሽ እንዳለው ተናግረው በቂ አቅርቦት እንዳለም አመላክተዋል ።
ዶሮ እንደየ መጠኑ ከ1ሺህ 500 ብር ጀምሮ እየተሸጠ መሆኑን ተናግረው ሽንኩርትና ሌሎች ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እየተሸጡ ናቸው ብለዋል ።
ከዚህ በፊት በበዓላት ወቅት ይታይ የነበረው የዋጋ ጭማሪ በቅዳሜ ገበያ አልተስተዋለም ያሉት ሸማቾቹ፣ ይልቁንም እንደ ሽንኩርት ያሉ ምርቶችን ከሳምንታት በፊት በነበረው ዋጋ መሸመታቸውን ገልፀዋል።
በመጨረሻም አዲሱ ዓመት የሰላምና ደስታ እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል ።
በሀብታሙ ኃይሌ | 73 |
| 13 | “የካፋን ተፈጥሯዊና ሰው-ሰራሽ ሀብቶች ለመጠቀም የምሁራን አንድነት ያስፈልጋል” - የካፋ ምሁራን ማህበር
ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) “የካፋን የተፈጥሮና ሰው-ሰራሽ ሀብቶችን፣ የታሪክና የባህል እሴቶችን በአግባቡ ለመጠቀም የምሁራንን አንድነት ማጠናከር እንደሚገባ የካፋ ምሁራን ማህበር ገለጸ።
“የባህል መነቃቃት፣ ማህበራዊ ትስስር እና አንድነት” በሚል ርዕስ በማህበሩ የተዘጋጀ የባህል ሲምፖዚዬም በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው።
የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ መምህርና የካፋ ምሁራን ማህበር ምክትል ፕረዝደንት ያሬድ አያሌው (ዶ/ር) ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር በጥንት የካፋ ነገስታት ባህል መሠረት በዓመቱ የተከናወኑ ተግባራትን ለመገምገም በሚያስችል መልኩ መድረኩ መዘጋጀቱ ፈይዳ እንዳለው ገልጸዋል።
ለተጨማሪው .....https://www.facebook.com/share/p/19BQ4bnku6/ | 75 |
| 14 | ተመድ የአፍሪካን ትክክለኛ ስፋት የሚያሳይ አዲስ የዓለም ካርታ አፀደቀ
ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4)፦ የተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባኤ የአህጉራትንና የሀገራትን ትክክለኛ የመሬት ስፋት የሚወክል አዲስ የዓለም ካርታ ለመጠቀም የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ በከፍተኛ ድጋፍ አጽድቋል።
የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት እና ባሃማስ በጋራ ባቀረቡት “ካርታውን ማስተካከል” በሚለው ታሪካዊ የውሳኔ ሃሳብ ላይ 164 ሀገራት ሲደግፉ፣ ስድስት ሀገራት ድምፅ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
አሜሪካ ብቻ ደግሞ ይህንን ውሳኔ ተቃውማለች።
ይህ ውሳኔ በአውሮፓውያኑ 1569 በአውሮፓዊው ኬፕቶግራፈር ጄራርደስ መርኬተር የተሠራውን እና ለዘመናት አፍሪካን፣ ላቲን አሜሪካንና ደቡብ እስያን አነስተኛ አድርጎ ሲያሳይ የነበረውን “መርኬተር ፕሮጀክሽን” የካርታ አሰራር በመቀየር በምትኩ ትክክለኛውን የመሬት ስፋት የሚያሳየውን “ኢኳል ኤርዝ ፕሮጀክሽን” እንዲተካ የሚያደርግ ነው።
ለተጨማሪው .....https://www.facebook.com/share/p/1FDbEnfyXs/ | 72 |
| 15 | "የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ሥራን በእውቀትና በቴክኖሎጂ ታግዞ ለማከናወን አስችሎናል"-ሰልጣኞች
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4)፦ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ሥራቸውን በእውቀት እና በቴክኖሎጂ ታግዘው ለማከናወን እንዳገዛቸው በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የመንግስት ሠራተኞች ገለፁ።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢንሼቲቪ የሆነው የ5 ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና ፕሮግራም የሀገሪቱን የዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር በማፋጠን ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል።
በፕሮግራሙም በዋናነት በሶፍትዌር ልማት፣ በዳታ ትንተና፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ክህሎት እና መሰል የቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይ በማተኮር ለዜጎች ስልጠና እየተሰጠ ነው።
ስልጠናውን በማስመልከት ኢዜአ ያነጋገራቸው በቦንጋ የትምህርት ኮሌጅ የፊዚክስ መምህር ሲሳይ አብደላ፣ መንግስት ባመቻቸው የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በአራቱም ፕሮግራሞች ሰልጥናቸውን አጠናቀው የምስክር ወረቀት መውሰዳቸውን ተናግረዋል።
ይህም ሥራቸውን በቴክኖሎጂ አስደግፈው ለማከናወን ከማገዝ ባለፈ በኦንላይን የራሳቸውን ሥራ ለመስራት ተነሳሽነት እንደፈጠረላቸው ጠቁመዋል።
ለተጨማሪው ........https://www.facebook.com/share/p/19GwQHwAFj/ | 84 |
| 16 | “የቶኪ ቤዓ በዓል ዋነኛ ፋይዳ አብሮነትና አንድነት በማጠናከር በጋራ ጉዳዮች ላይ በሰፊው የመመካከር ዕድል መፍጠሩ ነው” — ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም (ቦንጋ እፍ ኤም 97.4)
የዳውሮ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “ቶኪ ቤዓ” በዓል አካል የሆነው የባህልና ቋንቋ ሲምፖዚዬም በታርጫ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በመድረኩ በክብር እንግድነት ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ክልሉ የበርካታ አኩሪ ባህሎችና ታሪኮች መኖሪያ መሆኑን ገልጸዋል።
ከእነዚህ የማኅበረሰብ ሀብቶች መካከል አንዱ በዳውሮ ብሔረሰብ ዘንድ የሚከበረው የቶኪ ቤዓ በዓል መሆኑን ጠቁመው፤ የበዓሉ ፋይዳ አብሮነትንና አንድነትን በማጎልበት በጋራ ጉዳዮች ላይ የመመካከር ዕድል የሚፈጠር መኾኑን ተናግረዋል።
የተጣሉ የሚታረቁበት፣ የተበደሉ የሚካሱበትና እጅ ላጠራቸው ወገኖች ድጋፍ የሚደረግበት መሆኑን በመጥቀስ፤ ይህን በጎ ባህል በማጠናከር ለሕዝቦች አንድነትና ሁለንተናዊ ዕድገት ማዋል እንደሚገባ ተናግረዋል።
የዳውሮ ብሔርን ዘመን ተሻጋሪ ባህልና ታሪክ ጠብቆ ለትውልድ ለማስተላለፍ መጠነ-ሰፊ የጥናትና ምርምር ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ ገልጸዋል።
የብሔረሰቡ ባህልና ታሪክ የምርምር ማዕከል ግንባታ ከገባበት ውስብስብ ችግር በማውጣት በነቃ የኅብረተሰብ ተሳትፎ ግንባታውን ዳግም በማስጀመር አሁን ላይ በተሻለ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
ሙሉውን ለማንበብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://www.facebook.com/share/p/19FW3gCwhe/ | 92 |
| 17 | “አዲሱ ዓመት በየቤቱ ሙሉ ጤና፣ እልልታና በረከት የሚሞላበት እንዲሆን ከልቤ እመኛለሁ” - አቶ ማስረሻ በላቸው
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4)
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ-መስተዳድና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ለዳውሮ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል “ቶኪ ቤዓ” የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።
“ቶኪ ቤዓ” የንጉስ ሃላላ ልጆች ዘመንን ለትውልድ ቀምረው ከማሻገር ባለፈ ታሪካዊ ማንነታቸውንና የጥንታዊ ስልጣኔ መፍለቂያ ህዝቦች መሆናቸውን ለዓለም ደምቀውና ተውበው የሚያሳዩበት ብሔራዊ ቀናቸው ነው ብለዋል።
አዲሱ ዓመት የማህበረሰቡ አንድነት፣ መከባበርና አብሮነት ይበልጥ የሚጠነክርበት፣ የተጀመሩ የልማት ስራዎች የሚሳኩበት በየመስኩ የተያዙ እቅዶች የሚፈጸሙበት እንዲሆን ተመኝተዋል።
አዲሱ ዓመት በየቤቱ ሙሉ ጤና፣ እልልታና በረከት የሚሞላበት እንዲሆን ከልቤ እመኛለሁ ሲሉ መልዕክታቸውን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አስተላልፈዋል።
የዳውሮ ህዝብ ድንቅ ባህል፣ የእንግዳ ተቀባይነት፣ የአብሮነት እሴትና ታሪክ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ ለክልላችን ብሎም ለሀገራችን ውበትና ጥንካሬ መሆኑ የሚቀጥልበት መልካም አዲስ ዓመት እንዲሆንልን እመኛለሁ ብለዋል።
የተለያዩ ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የማህበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ!
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/share/181X2irsqB/
ቴሌግራም፡ https://t.me/bongafm974radiostatio
ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/@bongafm97.4?_t=ZM-90PCjvnnVBz&_r=1
ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/@BongaFM97.4 | 71 |
| 18 | “እንደ ቶኪ ቤዓ ያሉ ባህላዊ ዕሴቶቻችን የአብሮነታችን መሰናሰኛ ከመሆን ባሻገር ለዘላቂ ሰላምና ልማት ጽኑ መሠረት ናቸው” - አቶ ፍቅሬ አማን
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4)
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን፣ ለዳውሮ ብሔር የዘመን መለወጫ “ቶኪ ቤዓ” በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።
በመልዕክታቸው በዓሉ የቀደሙ አባቶች የነበራቸውን ጥንታዊ የከዋክብትና የጨረቃ ዑደትን መነሻ ያደረገ፣ የዘመን አቆጣጠር እውቀት፣ ባሕላዊ ዕሴቶችና ትውፊታዊ ክዋኔዎችን አጣጥሞ የያዘ ውብ በዓል ነው ብለዋል።
አሮጌውን ዓመት በሰላም፣ በጤናና በደስታ ላሳለፈው ፈጣሪ ምስጋና የሚቀርብበት፣ መጪው አዲስ ዓመት ደግሞ የሰላም፣ የፍቅር፣ የምርታማነትና የብልጽግና ዘመን እንዲሆን የጋራ መልካም ምኞትና ጸሎት የሚደረግበት በዓል መሆኑን ገልጸዋል።
ቶኪ ቤዓ የሥራ ባሕልን የሚያበረታታ፣ አትረፍርፎ ማምረትና ጠግቦ መብላትን፣ የማካፈል ባህልን የሚያላምድ እንዲሁም የሀገረሰብ ጥበባትንና አብሮነትን ያቀናጀ በዓል እንደሆነ ተናግረዋል።
ሙሉውን ለማንበብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://www.facebook.com/share/p/1Di6LCkrHt/ | 53 |
| 19 | ርዕሰ-መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ለዳውሮ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል “ቶኪ በዓ” የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4)
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ለክልሉ ሕዝቦችና ለመላው ኢትዮጵያውያን በሙሉ ለዳውሮ ብሔር የዘመን መለወጫ “ቶኪ በዓ” በዓል እንኳን አደረሳችሁ፣ አደረሰን! ብለዋል።
ርዕሰ-መስተዳድሩ እንደገለጹት፤ “ቶኪ በዓ” የዳውሮ ብሔር ዘመን ተሻጋሪ የምስጋና፣ የአሮጌውን ዓመት በሠላም ሽኝቶ አዲሱን ዓመት በአዲስ በተስፋ የመቀበያ የሰላምና የአንድነት መገለጫ በዓል ነው።
በዓሉ የተጣሉ የሚታረቁበት፣ ወዳጅና ዘመድ በፍቅር የሚመራረቁበት፣ አባቶች መጪው ዓመት የሰላም፣ የፍቅርና የጥጋብ እንዲሆን የሚመርቁበት እንዲሁም ልጆች በከፍተኛ ናፍቆት የሚጠብቁት የብሔሩ ታላቅ ባህላዊ ዕሴት መሆኑን አብራርተዋል።
አክለውም ይህንን ድንቅ ባህላዊና ታሪካዊ በዓል ጠብቆ፣ አልምቶና ማኅበራዊ ዕሴቱን ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በመጨረሻም ርዕሰ-መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነትና የአብሮነት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል ሲል የክልሉ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ዘግቧል። | 67 |
| 20 | ማሽቃሮ፣ ነፃነትና ሴትነት
(በዮሐንስ ክፍሌ)
ማሽቃሮ የካፋ ህዝብ የእኩልነት፣ የነፃነትና የምስጋና ታላቅ የምድር ላይ ድምቀት ነው። ይህ ኩሩ ህዝብ በርካታ ውብ ባህሎችና እሴቶች አሉት። ከነዚህም መካከል ማሽቃሮ—የዘመን መለወጫና የምስጋና በዓል የህዝቡን መንፈሳዊነት፣ ነፃነት፣ ማህበራዊ አንድነትና የመከባበር ባህል በግልጽ የሚያሳይ ልዩ ህያው ቅርስ ነው።
ማሽቃሮ አሮጌውን ዓመት በሠላም አሳልፎ ለአዲሱ ያደረሰን ፈጣሪ የማመስገኛ፣ ያለፉትን አፈፃፀሞች የመገምገሚያ፣ የወደፊቱን ዕቅድ የመንደፊያ እንዲሁም ማህበረሰባዊ ፍቅርና እኩልነት የሚታደስበት ታላቅ መድረክ ነው።
በካፈቾዎች ዘንድ የሴቶች እኩልነትና ነፃነት ከጥንት ጀምሮ በዘመነ እሳቤ የሚገመገም መሆኑን ማሽቃሮ ያረጋግጣል። በካፋ ባህልና ታሪክ ውስጥ ሴቶች ያላቸው ቦታ በውበትና በክብር የተቃኘ ነው። ይህ አመለካከት ጥንት ከነበረው የካፋ ንጉሳዊ አስተዳደር ስርዓት ጀምሮ ለሴቶች ይሰጥ የነበረውን ከፍተኛ ስፍራ የሚያንፀባርቅ ነው።
በብሔሩ ባህል ሴት የቤተሰብም ሆነ የማህበረሰብ መሰረት፣ የፍቅርና የደስታ ምንጭ ተደርጋ ትወሰዳለች። ዛሬ ዓለም የሴቶችን የእኩልነት ጉዳይ የክርክር አጀንዳ አድርጎ ዘልቋል። ካፈቾዎች ግን ጥንትም ሴቶችን በአደባባይ አድምቀው የሚያሳዩበት እሴት ነበራቸው—አላቸውም።
ተጨማሪውን ለማንበብ .....https://www.facebook.com/share/p/18Ew6oWynP/ | 70 |
