cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

መጣጥፍ🖋

ከደመናዉ በታች ሁሉም ያልፋል::

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
261
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-27 عوز
+130 عوز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

"My dream home" - ክፍል 14 የተቀጣጠርንበት ቦታ በአባ ፋንታ ኤልዱን ማግኘታችን እንቆቅልሽ ነበር የሆነብን... ኤልዱ ስታየን "እንደምን ሰነበታችሁ?" ብላ ከመቀመጫዋ ተነሳች... ሰላምታዋን ግራ በተጋባ ስሜት ዉስጥ ሆነን ምላሽ እንኳን ሳንሰጣት አጠገቧ ቁጭ አልን... ምን ተፈጥሮ ነዉ ብለን ልንጠይቃት እንኳ አልደፈርንም ነበር... ከደቂቃዎች ዝምታ የሰፈነበት ጥበቃ በኋላ አባ ሲመጡ ከሩቅ አየናቸዉ... በክብር ተነስተን ተቀበልናቸዉና ቡራኬያቸዉን ተቀብለን ተቀመጥን... "ይቅርታ ልጆቼ አረፈድኩባችሁ... አንድ አስቸኳይ ጉዳይ ገጥሞኝ ነዉ" አሉን በትህትና በተሞላ አንደበት... ከዛ በኋላ በመጀመሪያ በየተራ ሁላችንንም እንደሚያናግሩንና በመጨረሻ ደግሞ በአንድነት በጉዳዩ ላይ እንደምንመክርበት ገልፀዉልን... "ወለተ ሃና አንቺ እዚሁ ቅሪ" ብለዉኝ ዳግሜና ኤልዱን ደግሞ ራቅ ብለዉ ይቀመጡ ዘንድ አዘዟቸዉ... እኔም በሱባኤዉ ወቅት የገጠሙኝን ፈተናዎች, አየኋቸዉ ያልኳቸዉን ህልሞች ሁሉ እየነገርኳቸዉ እሳቸዉም በዛ ወርቃማ አንደበታቸዉ ጠቃሚ ምክሮችን ሲሰጡኝና ስለ ህልሞቼ ፍቺ ሲነግሩኝ ቆዩ... ከነገርኳቸዉ ህልሞቼ መሃል ግን "እርስዎ ለእኔና ለዳግሜ ማህተብ ሲያስሩልን አየሁ" ብዬ ለነገርኳቸዉ ህልም "እህ" ብለዉ ጭንቅላታቸዉን ከመወዝወዝ ዉጪ ፍቺዉን አልነገሩኝም... ከዛ በኋላ ዳግሜንና ኤልዱን በየተራ እስኪያነጋግሯቸዉ ድረስ እኔን ሌላ አባት ጋር ለሌላ ጉዳይ ላኩኝ... ስመለስ ከዳግሜ ጋር ጨርሰዉ ኤልዱን በተራዋ እያነጋገሯት ነበር... ወዲያዉ እንዳዩኝ ግን አንድ ላይ እንድንሰበሰብ ነግረዉን ዙሪያቸዉን ከበን ተቀመጥን... "እንግዲህ ልጆቼ እግዚአብሔር በአንድም በሌላም መንገድ ይናገራል... ልቦናችሁን አብርቶ ይህንን ስርአት እንድፈጥሙ የጠራችሁ... ሱባኤያችንንም በሰላም አስጀምሮ ያስፈጠመን እርሱ እግዚአብሄር ይክበር ይመስገን" "አሜን" ብለን በአንድነት መለስን:: "ሱባኤያችንን እንግዲህ የፈጣሪ ፈቃድ ሆኖ ለ4 ሆነን ጀምረን ፈጥመናል... ይህቺ እህታችሁም እንግዲህ የእህት የወንድሜ ጭንቀት የእኔም ነዉና አብሬያቸዉ ሱባኤ እጀምራለሁ ብላ ተጀምሮ እስኪፈጠም በፀሎቷ ስታስባችሁ ከርማለች" አሉን ወደ ኤልዱ እየጠቆሙ... ይህን ጊዜ የኤልዱ በቦታዉ መገኘት ሁለታችንም ተገለጠልን:: "እንግዲህ ክብር ምስጋና የተገባዉ ፈጣሪያችን ምላሹን አሳዉቋል..." "ለእህታችን ወለተ ሀና "በማህተብ" : ለወንድማችን ክንፈ ሚካኤል ደግሞ "አብሮ በመብላት" እንዲሁም ለእህታችን ፍቅርተ ማርያም ደግሞ " ወለተ ሀና ከእናቷ ቤት ጫማ አድርጋ ስትወጣ" ምሳሌ አድርጎ አሳይቷል...." "እንግዲህ ልጆቼ ፈጣሪ ይሁን ያለዉ ይሰምራል... ይጠናልም... እርሱ ያልፈቀደዉ ደግሞ በተቃራኒዉ አይጠናም... አይሰምርም... ይሄንን ተረድታችሁና አስባችሁ ፈቃዱን ለመጠየቅ እንደመጣችሁ ፈጣሪ ያስባችሁ!" ብለዉ ትንሽ የአርምሞ ምክክር ከራሳቸዉ ጋር ያደርጉ ገቡ... እኔና ዳግሜ በመጨነቅ አይነት እንቁነጠነጣለን... "እንግዲህ ልጆቼ ነገም አይደል መሄጃችሁ?" ሲሉን "አዎ" ብለን በአንድነት መለስንላቸዉ... "እንግዲያዉ እስከነገ ጊዜ ብትሰጡኝ ታዲያ ምናለበት?" አሉን:: ወሽመጣችን ቁርጥ ነበር ያለዉ😭 ምንም እንኳን ምላሻቸዉን ለመስማት ብንጓጓም የእሳቸዉ ነገር ሆኖብን በእሺታ ተቀብለን ወደየበአታችን አመራን:: የነገ ሰዉ ይበለን!! ፀጋ🖋 https://t.me/memoir21
نمایش همه...
መጣጥፍ🖋

ከደመናዉ በታች ሁሉም ያልፋል::

👍 3🙏 1
"My dream home" ክፍል - 13 የአንድ ዓመት ርዝማኔ ከነበረዉ የአንድ ወር ከ15 ቀናት ቆይታ በኋላ ተናፋቂዋ የፍልሰታ ጾም ደረሰች.... አንድ ወር ከ15 ቀኑ እንዴት እንደታለፈ አይነገረንም እንዴ? እያላችሁ እንደነበረ አልጠራጠርም😁 ይኸዉላችሁ ከዳጊ ጋር የተፈጠረ ምንም አዲስ ነገር የለም... በቃ አንድ ወሩን ሁለታችንም በተቻለን መጠን ራሳችንን ገዝተን ትምህርታችን ላይ ለማተኮር እየሞከርን ነበር... በሚያሳዝን ሁኔታ ግን ይህ ሁኔታ ከአንድ ወር በላይ ሊዘልቅ አልቻለም... "ምን አልባት አንድ ላይ መሆን ባንችልስ?" በሚል ፍራቻ ሁለታችንም ተከበን... ቀኑን ሙሉ አብረን መዋል... ሲመሽ ልንለያይ እንደሆነ እያሰብን መሸበር ጀማምሮን ነበር... አዲስ ያመጣነዉ ፀባይ ከኛ አልፎ ለጓደኞቻችን ሳይቀር በግልፅ የሚታይ ነበር... ምን አለፋችሁ የአንድ ሰሞን የጓደኞቻችን መነጋገሪያ ነበርን ነዉ የምላችሁ... ትምህርት አልቆ ባይሆን ኖሮ ሁለታችንም F ደርድረን በተባረርን ነበር.... ዳግሜ ሀምሌ አጋማሽ ላይ በመአረግ ተመርቆ ቤተሰቦቹንም ሆነ እኔን ለማስደሰት በቅቷል... አንድ የመጨረሻ የሚያስመሰግን ነገር የሰራነዉ ምርቃቱን በጥሩ ሁኔታ ማክበር ብቻ ነበር... ከዛ በኋላ ግን ዳግሜ ለስራ ፍለጋ እያለ እኔ ደግሞ "ኤልዱ ጋር ስራ መስራት ጀምሬያለሁ" በሚል ሰበብ ከቤት እየወጣን ፀሀይ እስክትጠልቅ አብረን መዋል....አብረን መጨነቅ ነበር ስራችን... ዳግሜ በቤተሰቦቹ አማካኝነት የሚመጡለትን የስራ እድሎች በይደር እያቆየ "ስራ ልፈልግ" እያለ ጎህ ሳይቀድ ከቤት መዉጣቱ ለቤተሰቦቹ አልተዋጠላቸዉም... ያዉ ኤልዱ በቻለችዉ መጠን ልትሸፋፍንለት ትሞክራለች... እኔም ቢሆን እሷ ጋር 'ስራ' እያልኩ ከቤት እንደምወጣ ስለምታዉቅ... የስራ ድርሻዬን ከመሸፈን አንስቶ... ለአባቴ ሳልኖር እንዳለሁ...እየሰራሁ እንደሆነ እየዋሸችልኝ ከችግር ስታወጣኝ ነበር... እሷ ባትኖር ምን ይዉጠን እንደነበር አላዉቅም... ብቸኛ የምትረዳን እሷና እሷ ብቻ ነች... አንድ ጊዜ እንደዉም ሁኔታችን ግራ ሲገባት ደወለችልኝና "ቆይ እንደዚህ ከተዋደዳችሁ... አብራችሁ መሆን ከፈለጋችሁ... ራሳችሁን ከዚህ በላይ ለምን ታስጨንቃላችሁስ? ትጎዳላችሁስ?..... ያንቺ ወይ የእሱ ቤተሰብ አልከለከለ አብራችሁ መሆን እየቻላችሁ የማትችሉ ይመስል ራሳችሁ ላይ መሰናክል ለምን ትፈጥራላችሁ?" ብላኝ ነበር... የኔ ምስኪን ምን ያህል ከኛ እኩል እንደተጨነቀች የገባኝ ያኔ ነበር.... አያደርስ የለ ያቺ የቀጠርናት ቀን ተቃረበች... እኔና ዳግሜ ወደ ጻድቃኔ ገዳም ለመሄድ ዝግጅታችንን ጀመርን... ይህንን ጊዜ ታዲያ ኤልዱ አብሬያችሁ ካልሄድኩ ብላ ድርቅ አለች... ነገሩ ለእኛ ጥሩ አጋጣሚ ነዉ የፈጠረልን... ዳግሜ ከእህቱ ጋር ወደ ጻድቃኔ ሊሄድ እንደሆነ ቤተሰቡ ሲሰማ በእልልታ መርቆ ነበር የተሸኘዉ "በይ በደንብ አስጠምቂዉ" ከሚል አጭር ማሳሰቢያ ጋር.... እኔም ለአባቴ "ከኤልዱ ጋር ፍልሰታን ገዳም ማሳለፍ እፈልጋለሁ" ነበር ያልኩት... ብዙ አልተቃወመም... "በመንገዳችሁ ተጠንቀቁ" እና ለኤልዱ ደግሞ እንደታላቅነቷ "ልጄን አደራ" የሚል መልዕክት አስተላልፎ ግንባሬን ስሞ ነበር የሸኘኝ.... ጻድቃኔ ስንደርስ ለፍልሰታ 2 ቀናት ይቀሩት ነበር... እናም ይህቺን ጊዜ ሶስታችንም ንስሃ ለመግባትና የንስሃ ሱባዬ ለመያዝ ተጠቀምንባት... አቤት የጊቢዉና የአካባቢዉ ሰላማዊነት ግን ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም... በህይወቴ ተሰምቶኝ የማያዉቅ ሰላምና መረጋጋት ነበር ያገኘሁት... ጧት ከኪዳን መልስ ፀበሌን ተጠምቄ ወደ በአቴ እገባና ከሰአት ለቅዳሴ ከኤልዱ ጋር እወጣለሁ... ከሶስት ቀናት የሱባኤ ቆይታ በኋላ እኔ እና ዳግሜ የመጣንበትን ጉዳይ ለንስሀ አባታችን ተናግረን... የተከበረዉን ምክራቸዉን ተቀብለን... ከአንድ ቀን ረፍት በኋላ ሱባኤዉን እንድንጀምር አሳሰቡን... እኛም በፀሎታቸዉ እንዲያስቡን ጠይቀን... ባዘዙን መሰረት በበነጋዉ ሱባኤያችንን ጀመርን... ነሀሴ 15 አመሻሽ ላይ አባ ባሳሰቡን መሰረት ሁለታችንም ሱባኤያችንን ፈፅመን... አባን ለማግኘት ወደ ተቀጣጠርንበት ቦታ አመራን... በቦታዉ ስንደርስ ግን አባን ሳይሆን ኤልዱን ነበር ያገኘናት.... ፀጋ🖋 https://t.me/memoir21
نمایش همه...
መጣጥፍ🖋

ከደመናዉ በታች ሁሉም ያልፋል::

👍 4❤ 2
"My dream home" ክፍል - 12 የዳግሜን ምላሽ ከሰማሁ በኋላ ልቤ በትንሹም ቢሆን ተረጋጋች...ካልተጨበጠ ጥርጣሬ ይልቅ የተረጋገጠ ምላሽን ከጉዳዩ ባለቤት ሰምቶ መገላገል እንዴት ረፍት ይሰጣል መሰላችሁ... "በእርግጥ እኔም እወድሃለሁ..." ብዬ ጀምሬ...ለሱ ያለኝ ስሜት ከመቼ ጀምሮ እንደተጠነሰሰ አንድም ሳላስቀር እተርክለት ገባሁ...ይህ አንዱ ግራ አጋቢ ከሆኑ ባህሪዎቼ መካከል አንዱ ነዉ... እንደምትረዱኝና የኔ ሰዉ መሆናችሁን ካረጋገጥኩ በኋላ የዉስጤን ሁሉ ነዉ የምዘከዝክላችሁ...አንድም የሚቀረኝ ታሪክ የለም...ከፊል ማንነቴን የዉስጤን ሁሉ በጥቂት ደቂቃዎች ወይም ሰአታት አወቃችሁት ማለት አይደል... ብዙ ጊዜ ድብቅ ከሚባሉት ሰዎች መሀል ነኝ... ድብቅነቴ የሚመነጨዉ ግን ሚስጥሬን ለማን ማጋራት እንዳለብኝ ለመምረጥ ከማደርገዉ የበዛ ጥንቃቄ ሳቢያ ነዉ...አንዴ ያ ሚስጥሬን ላጋራችሁ የምችለዉ ሰዉ መሆናችሁን አምኜ ወደ እናንተ ከመጣሁ በኋላ ግን በእኔ ህይወት ዉስጥ ከእናንተ የሚደበቅ ነገር አይኖርም! እስከዚችኛዋ ንግግሬ ድረስ ዳግሜ በተመስጦና ከልብ በመነጨ ደስታ ሲያደምጠኝ ነበር...የአሁኗ ንግግሬ ግን ከመቼዉም በላይ ግር ያሰኘችዉ መሆኗ ከፊቱ ላይ ይነበባል... እንዲህ ነበር ያልኩት "ዳግሜ እኔና አንተ እንዋደድ እንፈላለግ ይሆናል... ነገር ግን የሁለታችን መፈላለግ(መዋደድ) ብቻ አብሮነታችንን አያሰምረዉም!" "ማ...ማለት?" አለኝ እንደምንም ከናፍርቶቹን አላቆ... "ማለቴ እኔ ስላፈቀርኩህ አንተም ስላፈቀርከኝ ብቻ ካንተ ጋር መሆን አልችልም!" "የገንዘብ ጉዳይ ነዉ... ዘንድሮ ተመራቂ ነኝ ታዉቂያለሽ...ስራ በቅርቡ እጀምራለሁ... አሁንም ቢሆን ያንን ያህል ብዙ አይሁን እንጂ የተለያዩ ነገሮችን እየሰራሁ ያጠራቀምኩት ገንዘብ አለ..." "No... No.. No... ዳግሜ እንደዛ አይደለም... እኔ ለማለት የፈለግኩት.... ይኸዉልህ ምን መሰለህ...እ...እኔ ስለ relationship ሳስብ ለተወሰነች ጊዜ ወይ አመታት ዘልቆ የሚያበቃ ጊዜያዊ ነገር አይደለም የማቅደዉ... ማለቴ በፍቅረኝነት ተጀምሮ በትዳር አጋርነት የሚቀጥል አይነት ግንኙነት ነዉ መመስረት የምፈልገዉ... ይሄ ደግሞ ጠንካራ የሆነ መሰረት ያስፈልገዋል...በእኔ እምነት ደግሞ ለአብሮነታችን ስምረት ከኛ መፈላለግ በተጨማሪ/ይበልጥ የፈጣሪ ፈቃድ ያስፈልገናል ብዬ አምናለሁ..." ምን እንደሚለኝ ግራ የተጋባ ይመስላል... "እ...እ...እሺ...በምን መንገድ ነዉ ያ የሚሆነዉ...?" "ያዉ በሀይማኖታችን ስርአት መሰረት ቅድም ለፈፀምነዉ ተግባር ንስሀ እንገባና ከዛ ንሰሀ አባታችንን አማክረን ከዛ ፈጣሪ የሱ በሆነዉ መንገድ እንዲመራን እንጠይቀዋለን... እኔ እንደዚህ አስቤያለሁ..." "እ...ሀሳብሽ ጥሩ ነዉ...ግን ለዚህ ትንሽ የፈጠንን አልመሰለሽም...?" "በእዉነቱ ከሆነ አይመስለኝም...እንዳንተ ሀሳብ ከሆነ 'ይህ ነገር መደረግ ያለበት ወደ ትዳር አለም ለመግባት በተጫጨንበት ጊዜ ነዉ' እያልከኝ ነዉ አይደል ካልተሳሳትኩ?" "አዎ" "እኔ እንደሚመስለኝ ግን ጊዜዉ አሁን ነዉ... ምንም አይነት ነገር ከመጀመራችን በፊት ነዉ የፈጣሪን ጣልቃ ገብነት በመሃላችን ማስገባት ያለብን... ስለሁለታችን አብሮነት ፈቃድ የመጠየቅ ጊዜዉም አሁን ነዉ... እስከ እጮኝነት ጊዜ ድረስ በፈቃዳችን ስንመራ ቆይተን ለጋብቻ እንዲፈቅድልን ብንጠይቀዉ አንዴ እንደምንጋባ ወስነን ከተቀመጥን በኋላ ያንተስ ምላሽ ምንድነዉ ብንለዉ እንዴት ይሆናል?" "እሱስ ልክ ነዉ...ነገሩ አዲስ ስለሆነብኝ ነዉ እንጂ..." "ታዲያ ምን ችግር አለዉ? እኛ እናስጀምረዋ...ደግሞ የአሁኑ ዘመን ልጆች የኋላ ታሪካችንን መለስ ብለን ስለማናይና ስለማንጠይቅ ነዉ እንጂ በእናት በአባቶቻችን ጊዜ ሲደረግ የነበረ ድርጊት ነዉ... " "እሺ ታዲያ ለመቼ እናድርገዉ?" አለኝ... አቤት ይሄኔ እንዴት ደስ እንዳለኝ "አፈቅርሻለሁ" ብሎ ሲነግረኝ ከተሰማኝ ሁለት እጥፍ የሚሆን ደስታና እፎይታ ነዉ የተሰማኝ... ይሄንን ሀሳብ እንዴት እንደማስረዳዉ ምን ያህል ጨንቆኝ እንደነበረ ማን በነገራችሁ.... ቆይ ግን ዳግሜ ምን ያህል ቢወደኝ ነዉ ያልኩትን ሁሉ በእሺታ የተቀበለዉ የሚል የትዕቢት ሀሳብ ተናንቆኝም ነበር... "የአሁኑ ክረምት ነሀሴ ላይ...እንደዉም ለፍልሰታ ለምን አይሆንም...አንተም በወግ በመአረግ ተመርቀህ...እኔም የዚህ አመት ፋይናል ፈተናዬን ጨርሼ ነዉ የሚሆነዉ" "ነሀሴ ግን አልራቀም...?" እዚህ ጋር አልቻልኩም ሳቄ አመለጠኝ... እሱም አብሮኝ ሳቀ...ሲስቅ እንዴት አባቱ ነዉ የሚያምረዉ ባካችሁ... "እንዴ አሁን ሰኔ 17 ላይ ነዉ እኮ ያለነዉ..." "ትንሽ ይርቃል...ግን እሺ ይሁን ምን ይደረጋል...ግን እስከዛ እንዴት ነዉ የምንቀጥለዉ ማለቴ... እንደበፊቱ መመለስ የምንችል ይመስልሻል?" "እሱ ትንሽ የሚከብድ ይመስላል...ግን በምንም አይነት የቅድሙ አይነት ሁኔታ ዉስጥ መገኘት የለብንም..." "እሺ... በእሱ እስማማለሁ...ግን አሁንም እንደ ጓደኛ ሆነን መቀጠል የምንችል አይመስለኝም...አሁን ላይ 'ፍቅረኛ' መሆን እንደማንችል ገብቶኛል...ግን at least 'እጩ ፍቅረኛሞች' መሆን አንችልም?" "እጩ ፍቅረኛሞች?" ብዬ በሳቅ ፈረስኩ...አብረን ሳቅን...አይ ዳጊዬ.... ፀጋ🖋 https://t.me/memoir21
نمایش همه...
መጣጥፍ🖋

ከደመናዉ በታች ሁሉም ያልፋል::

❤ 5👍 2
ግዜው 1930ዎቹ ነው። አሜሪካ በከፍተኛ የኢኮኖሚ ቀውስ ተመታለች። ሾል አጥ በዝቷል። ፋብሪካዎች፣ ባንኮች  ከስረው ተዘግተዋል። 13 ሚሊየን ሰዎች ሾል አጥ ሆነዋል። ሚሊየነሮች የነበሩ ከስረው ራሳቸውን እያጠፉ ነው። የኩባንያ ሾል አስኪያጆች ከስራ ተፈናቅለው በመንገድ ዳር ፍራፍሬ እየሸጡ ነበር። በአየሩ ውስጥ ተስፋ መቁረጥ ያንዣብባል። 17 አመቴ ነበር። ፋርማሲ ውስጥ ነበር የምሰራው። ፋርማሲስቱ "የመዝጊያ ሰአታችን ደርሷል" አለ። ትክክል ነበር በህይወቴ ውስጥ ያለውን አስቸጋሪ ነገር ሁሉ የምዘጋበት ግዜ ነበር። አዎ ዛሬ ምቹ ቀን ነው። ወላጆቼ ከከተማ ይወጣሉ። ወንድሜ ደግሞ ጓደኞቹ ጋር ይሄዳል። ቤት ውስጥ ብቻዬን ስለምሆን እቅዴን ያለ ምንም እንቅፋት ለመፈፀም ያስችለኛል። አለም ጨልሞብኛል፤ ተስፋ መቁረጥ እንደ መርግ ተጭኖኛል። ከዚህ በኋላ የምኖርበት ምክንያት የለም። የምኖረው ከቤተሰቦቼ ጋር በአንድ አፓርትመንት ሶስተኛ ፎቅ ላይ ነበር። ድህነት ስለበረታብን በቀዝቃዛው ክረምት ማሞቂያውን መለኮስ እንኳን አልችልም። ገንዘብ ለመቆጠብ መብራቱን በማንፈልግበት ግዜ ማጥፋቱን ማስታወስ ይጠበቅብን ነበር። ከድህነታችን የተነሳ ማንቆርቆሪያ ውስጥ ያለውን ሻይ እስከ መጨረሻው እንጥፍጣፊ ድረስ እንጠቀም ነበር። አሁን ግን ሁሉንም ላመልጥ ነው። አስቀያሚው አፓርትመንታችን ስደርስ እንደጠበቅኩት ባዶ ሆኖ ጠበቀኝ። ወላጆቼም ከከተማ ወጥተዋል። ወንድሜም ጓደኛው ጋር ሄዷል። ላድርገው ያሰብኩትን ነገር የሚያስቆመኝ የለም። የእንቅልፍ እንክብሎቹን ካስቀመጥኩበት አወጣሁ። የማወራርድበት ውስኪም አገኘሁ። እንክብሎቹ ለመስራት ምን ያህል ግዜ ይወስድባቸው ይሆን የሚለውን እያሰብኩ ከውስኪው ጎንጨት አልኩኝ። ይመራል። እንክብሎቹን ለመዋጥ ስዘጋጅ አንድ ድምፅ እንዲህ አለኝ፦ "ምን እያደረግክ ነው?" በድንጋጤ ስዞር እንክብሎቹ ወደቁብኝ ፤ ውስኪው ተደፋብኝ። አባቴ ቆሞ ነበር። "እንደምትጠጣ አላወቅኩም ነበር" "አልሄዳችሁም እንዴ?" "እቃ ረስቼ ነው። ድጋሚ ልጠይቅህ። ምን እየሰራህ ነው?" "ምንም ምንም" "ምን ሆነሃል ሲድኒይ" እንክብሎቹን አየ። "ምን እየሆንክ ነው? እነዚህ ደግሞ ምንድናቸው? " "የእንቅልፍ ኪኒኖች" "ለምን?" "ራሴን ላጠፋ" ፀጥታ ሰፈነ። ከትንሽ ፅሞና በኋላ አባቴ ተናገረ፦ "ደስተኛ አለመሆንህን አላውቅም ነበር" "ልታቆመኝ አትችልም። አሁን ብታቆመኝ ነገ አደርገዋለሁ" ቆሞ ጥቂት ካስተዋለኝ በኋላ "ያንተ ህይወት ነው። የመረጥከውን ማድረግ ትችላለህ። የማትቸኩል ከሆነ ለምን ትንሽ ዞር ዞር አንልም?" አለኝ። ምን እንዳሰበ ገብቶኛል። አባቴ የሽያጭ ሰራተኛ ነው። ያሰብኩትን እንዳላደርግ ሊያሳምነኝ ነው። ይሁን እንጂ አይሳካለትም። ነቅቼበታለሁ። ከአምስት ደቂቃ በኋላ የእግረኛ መንገዱ ላይ ተገኘን። ብርድ ስለሆነ መንገዶቹ ባዶ ናቸው። ከረዥም ዝምታ በኋላ አባቴ እንዲህ አለኝ፦ "ንገረኝ እስኪ ልጄ ራስህን ለማጥፋት ለምን ፈለግክ? " ከየት ልጀምርለት? ከሚሰማኝ የብቸኝነት ስሜት ወይስ ከመጪው ግዜ ጨለማነት። ብዙ ህልሞች ነበሩኝ። ነገር ግን እውነቱ ፋርማሲ ውስጥ ተላላኪ ነኝ። ኮሌጅ መግባት እፈልግ ነበር። ግን ለዛ የሚሆን ገንዘብ የለም። ደራሲ መሆን እፈልግ ነበር። ነገር ግን የፃፍኳቸው በደርዘን የሚቆጠሩ ፅሁፎች ተቀባይነት አላገኙም። "ሲድኒ ደራሲ መሆን እንደምትፈልግ ነግረኸኝ ነበር" "አዎ" "አየህ ህይወት እንደ ልብወለድ ነው። የሚቀጥለውን ገፅ ካልገለጥክ ምን እንደሚፈጠር አታውቅም። በሕይወትም ነገን ካልጠበቅክ ዛሬ ላይ ሆነህ ምን እንደሚፈጠር አታውቅም" "አውቃለሁ አባዬ ምንም አይፈጠርም" ሲድኒ ይህን ይበል እንጂ ራሱን የማጥፋት ሃሳቡን ሰርዞት ነበር። ከዚያ በኋላ አሜሪካ ከገባችበት የኢኮኖሚ ቀውስ አገገመች። ሲድኒ ሼልደንም የተሳካለት ቤስትሴለር ደራሲ ሆነ። በአስራዎቹ እድሜዬ ብዙ ልብወለዶቹን አንብቤያለሁ። ሴል አወቃቀር A ነው። ከልብወለዶቹ መሐል እርቃን፣ አስኳል፣ በሬ ካራጁ፣ የጣፈለግ፣ ከፃረሞት ትንቅንቅ፣ የፍርድ ቀን ዘመቻ፣ ህልምሽን ንገሪኝ፣ ማለዳ ቀትርና ምሽት ይገኙበታል። ⛵️⛵️⛵️ "ማንበብ ፋሽን ነው።" Join us @noahbookdelivery
نمایش همه...
🔥 1💔 1
"My dream home" ክፍል - 11 ፈፅሞ ያልጠበኩት ነገር እየተከናወነ ነዉ.... ከመደሰት ይልቅ ፍርሃት ያሸብረኝ ጀምሯል... ግን ይህ ስሜት ከ1 ደቂቃ ሊያልፍ አልቻለም... ልክ አይኖቻችን አንዳቸዉ ላንዳቸዉ ልዩ ሚስጢር ሊያወጉ እየተፈላለጉ እንደነበሩት ሁሉ... አሁን ደግሞ ስራቸዉን ለከናፍርቶቻችን አስረክበዉ በተራቸዉ አሸለቡ... የነበርኩበትን የፍርሃትና የመርበትበት ስሜት የሚያስረሳ የሆነ ምንነቱ ሊገልፁት ከሚችሉት በላይ የሆነ ስሜት ዉጦ ሲያስቀረኝ ይታወቀኛል... እሱ ቆርጧል... አፍኖት የቆየዉን ስሜትና ናፍቆት ለመተንፈስ ቸኩሏል... ለነገሩ እኔም አልከለከልኩትም... የሆነ ሀይል ከዛ ከሰጠምኩበት የህልም የሚመስል አለም መንጭቆ ሲያወጣኝ ይታወቀኛል... ያም ሀይል ራሴን... ዙሪያዬን ሁሉ አስረስቶኝ ከነበረዉ የስሜት ከፍታ በሀይል ገፍትሮ ሲፈጠፍጠኝ...እኔ ዉስጥ የነበረዉ የስሜት መናወጥ ከኔ አልፎ ዳግሜ እስኪሰማዉ ድረስ በጣም ከባድ ነዉጥን አስከተለ... ዳግሜን በሀይል ገፈተርኩት... እጆቹን ከላዬ ላይ ባለማንሳቱ በትንሹ ተፍገምግሞ ሚዛኑን መጠበቅ በመቻሉ ከመዉደቅ ተረፈ... ከዛም ድንጋጤ ባኮለታተፈዉ አንደበት "ም...ምነዉ?" ብሎ ጠየቀኝ... የኔ አባት እኔ ልኮላተፍ... እንዴት እንደሚያሳዝን ብታዩ... ግን ያ ዉስጤን የተቆጣጠረዉ ሀይል ከሀዘኔታ ይልቅ እዉነታን... ትክክለኛነትን ስለፈለገ... "መነጋገር አለብን!" አልኩት ጨከን ብዬ... አዎ መነጋገር ነበረብን... ያ ዉስጤን የሞላዉ...የተቆጣጠረዉ ሀይል...ማንም... ምንም አልነበረም... የራሴዉ ማንነት...የምመራባቸዉና ትክክል ናቸዉ ብዬ የማምንባቸዉ መርሆዎቼ ናቸዉ... የቅድሙ ፍርሃቴም ከዚሁ የመነጨ ነበር... የተሳሳተ ምግባር እንዳልገኝ...የተሳሳተ ዉሳኔ እንዳልወስን... ከእግዚአብሄር መንገድ የሚያወጣ ተግባር ላይ እንዳልገኝ በመስጋቴ ነበር... እነዚህን ሁሉ ስጋቶቼን ወደ ጎን ብዬ... ዳግሜ እንደፈለገዉ ልሆንለት... ያለኝን ላከብርለት ነበር... ግን አልቻልኩም... እዉነታዉ ዛሬ ከራሴ ጋር ተጣልቼ ከሱ ጋር ሰላም ለመሆን ብጥር እንኳን ነገ እራሴንም እሱንም አጥቼ ከሁለት ያጣሁ መሆኔ ነዉ... ሴት ነኝ... አዎ ይህ ክብር...መጠሪያ የሆነ ሴትነቴን ደግሞ አክብሬ ካልያዝኩት የነገ አወዳደቄ የከፋ ይሆናልና... ይህንን እንቁ የሆነ ስጦታ በተገቢዉ መንገድ ጠብቄ ላቆየዉ ግድ ይላል... ዳግሜን ስለማልወደዉ ወይ ደግሞ ከፍቅር ይልክ ክብር አስበልጬ አይደለም... እንደዉም በጣም ስለማፈቅረዉና ክብሯን የጠበቀች መልካምና ተወዳጅ ፍቅረኛ... ከዛም አልፎ ሚስት ልሆንለት ስለምሻ ነዉ እንጂ... ምንም እንኳን በፍቅር ወላፈን እየተንገበገበች ያለች ለጋ ወጣት ብሆንም ግን... ፍቅር ስህተቶችን ለመስራት ምክንያት መሆን እንደማይችል ይልቁንም ንፁህ ፍቅር ወደተቃና የህይወት መስመር የሚመራና በአስተዉሎትና በአንድነት ለጋራ ስኬትና ለተባረከ ጥምረት በአብሮነት የሚጓዙበት የእግዚአብሄር ስጦታ መሆኑን አዉቃለሁ... ለዚህም ስሜታችን እኛን ገዝቶ ድርጊቶቻችንን ከሚወስንልን ይልቅ እኛ ስሜታችንን የመግዛቱን ጥበብ እንድንላበስ በማሰብ ነበር ሁሉንም ያደረኩት... የቤታቸዉ በረንዳ ላይ ወንበር ይዘን ወተን ተቀመጥን...ብርዱ ሀይለኛ ነበር... ዳግሜ የእናቱን ጋቢ አለበሰኝና አጠገቤ መጥቶ ቁጭ አለ... እሱም ብርድ ዉስጡ ድረስ ገብቶ ያንቀጠቅጠዉ ጀምሯል... ወደ እሱ ተጠግቼ ጋቢዉን አብረን እንድንለብስ እጄን ዘረጋሁለት... ብዙ ሳይግደረደር ተቀበለኝ.... "እንነጋገር" ብዬ ጠርቼዉ ከምን እንደምጀምር ራሱ አላዉቅም ነበር... ወይ ነገሮች በራሳቸዉ መንገድ እንዲሄዱ መፍቀድ ነበረብኝ እንዴ(ቅድም የሚፈጠረዉን ዝም ብዬ መከታተል ነበረብኝ?) አይ ይህ ልክ አይመስለኝም...ቅድም በወሰድኩት እርምጃ ልቆጭ አይገባም... እሺ አሁን ምን ብዬ ልጀምር?...እያልኩ ከራሴ ጋር ግብግብ ዉስጥ ስገባ... ቀድሞኝ "እ..." ብሎ ጀመረ... ወይኔ ምን ሊለኝ ይሆን ብዬ ተሳቀቅኩ... "ለቅድሙ ይቅርታ" አይለኝም መሰላችሁ... አሁን በቃ እሱ ጋር ያለዉ ስሜት እኔ ጋር የሌለ መስሎታል... ወይኔ አበቃልኝ... አልኩ በዉስጤ... እሱ እንደሚያስበዉ እንዳልሆነ... እኔም በጣም እንደማፈቅረዉ... እንዴት እንደምነግረዉ ጨነቀኝ... ያዉ ሴትም አይደለሁ...ቀድሜ "አፍቅሬሀለሁ" ማለቱ ከብዶኝ እኮ ነዉ😁 እመብርሃን ከጭንቅ ትገላግለዉ አቦ... እሱ ራሱ "እ...ካየሁሽ ቀን ጀምሮ....ማለቴ በደንብ ካወኩሽና ከተግባባሁሽ ቀን ጀምሮ ላንቺ የተለየ ስሜት አድሮብኛል..." አላለኝም...ቆይ ይሄንን ሁሉ ድፍረት ከየት አመጣዉ? መቼም የልቤ ትርታ ሳይሰማችሁ አልቀረም💓 እኔስ "የተለየ ስሜት ማለት?" አላልኩትም መሰላችሁ... ይሄኔ መልሱ ዘገየብኝ...የእኔም ልብ ተጨነቀች..."እንደ እህቴ ነዉ የማይሽ" ቢለኝ አስብችሁታል💔 "ማለቴ..." አሁን 'ማለቴ'ን ምን አመጣዉ ባካችሁ🤦 "አ...አፈቅርሻለሁ" ሲለኝ አቤት የተሰማኝ እፎይታ...አሁን "እኔም አፈቅርሀለሁ አባትዬ ማለት ሳይሆን...በረጅሙ እፎይይይ.... ማለት ነበር ያሰኘኝ...
نمایش همه...
👍 4❤ 2
https://t.me/hamster_kombat_Bot/start?startapp=kentId1863971083 Play with me, become cryptoexchange CEO and get a token airdrop! 💸 2k Coins as a first-time gift 🔥 25k Coins if you have Telegram Premium
نمایش همه...
Hamster Kombat

Just for you, we have developed an unrealistically cool application in the clicker genre, and no hamster was harmed! Perform simple tasks that take very little time and get the opportunity to earn money!

"My dream home" ክፍል - 10 "ቤት ብቻዬን ነኝ በነፍስ ድረሺልኝ" ያለችኝ ልጅ ቤቷ ስደርስ ያጋጠመኝ ግን ፈፅሞ የተለየ ነገር ነበር... ቤት ማንም አልነበረም ከእሷና ከዳግም ዉጪ... ለኔ ግን የተነገረኝ ከሷ ዉጪ ማንም ቤት ዉስጥ አለመቅረቱን ሁሉም ተሰብስበዉ መቐለ ለአክስታቸዉ ልጅ ሰርግ እንደሄዱ ነበር... ከስንትና ስንት ሳምንታትና አይገፌ ቀናቶች በኋላ ዳግሜን ሳየዉ ምን እንደተሰማኝ መቼም መገመት አይከብድም... ሽሽቴ ከሱ ነበር... አዎ ከነዛ አንፀባራቂ ብርሃን ከሚረጩ አይኖቹ... ከሚያሳሱት ጉንጮቹ... ከአማላይ ቁመናዉ... ቀልቤን ከሚበትን ተስገምጋሚ ድምፁ... ከዛ ተወዳጅ ዉስጣዊ ማንነቱ.... መራቅ ነበር ሀሳቤ... ከእነዚህ ሁሉ ራሴን አሳጥተዉ ሁሉን ከሚያስረሱኝ ነገሮች ሁሉ መራቅ ነበር የፈለኩት... ለሰሚዉ ግራ እንደሚሆን አዉቃለሁ... ሰዉ የወደደዉን ሌት ከቀን ሊያየዉ ይጓጓል እንጂ እሱን ላለማየትና ከሱ ለመራቅ ይሞክራል ያስብልም ይሆናል... እኔ ግን ተፈትኜ የመዉደቄን እዉነታ መቀበል አቅቶኝ ይሁን ከሱ ፊት የመቆም አቅሜን አጥቼ ባላዉቅም...ስለእሱ ማሰቤንና ማለሜን ያስቀርልኝ ይመስል ከሱ መራቁን መርጬ ነበር... የዛሬዋ የቁርጥ ቀን መጣች እንጂ... ቤታቸዉ ስደርስ ኤልዱ ነበረች የተቀበለችኝ... ዉስጥ ስገባ ግን ባልጠበኩት ሁኔታ ከዳግሜ ጋር ፊት ለፊት ተገጣጠምን... ሁለታችንም ባለንበት ደርቀን ቀረን... ከድንዛዜያችን ሳንነቃ... "ቁጭ በይ እንጂ... ዳጊ ተቀመጪ በላት እንጂ" እያለች ኤልዱ ወደ እኛ መጣች... እንደተፋጠጥን እኔ ቁጭ አልኩ... "ተቀመጥ እንጂ... ምነዉ የምትሄድበት አለ?" አለችዉ መልሳ "እ...እሺ" ብሎ እሱም ተቀመጠ... ለሁለታችንም የማይታመን ክስተት ነበር የሆነብን... ራሴን ለመቆጣጠር የቱንም ያህል ብጥር በየምክንያቱ እሱን ሰረቅ አድርጎ አለማየት አልሆነልኝም ነበር... እሱም እንደዛዉ🙊 ከዛ ያዉ "የሴት እንግዳ..." አይደለ ተረቱ... ኤልዱ ራት ልትሰራ ስትነሳ አብሬያት ተነሳሁ... አንድም ከዳግሜ ጋር ብቻ ሳሎን ዉስጥ መቆየት ስለጨነቀኝ ነበር ካላገዝኩሽ ብዬ ራት ማብሰሉን የተቀላቀልኳት... በእዉነት ግሩም ራት ነበር... ገበታዉ ከፍ ካለ በኋላ... ኤልዱ "ለምን ፊልም አናይም?" አለችን... ተያየንና ሁለታችንም በአንድነት "እሺ" አልናት... ለሱም ሲባል ፈንዲሻ አፈንድሸን... ለስላሳችንን አስመጥተን... ፊልሙን ለማየት ተሰየምን... ከመጀመራችን በፊት "ቆይ አንዴ" ብላ ኤልዱ ተነሳችና ችብስ ከካቻኘ ጋር ይዛ መጣች... "Oww... My favorite snack" አለ ዳግሜ... በግርምት ቀና ብዬ አየሁት... "አንቺም የችብስ አፍቃሪ ነሽ?" አለችኝ... አንገቴን ነቀነኩላት... "I prefer popcorn to chips" አለችና ፈንዲሻዉን ለራሷ ወስዳ ለኛ ችኘሱን አንድ ላይ እንድንበላ ሰጠችን... ምን እሱ ብቻ "ተጠጊልኝ" ብላኝ መሃላቸዉ ከተተችኝ ነዉ የምላችሁ... የሆነ ደስ የሚልም የሚጨንቅም ስሜት ዉስጥ ነበርኩ... ፊልሙ ስለምን እንደነበር ብጠይቁኝ መልሴ "ዝምታ" ብቻ ነዉ... በዛ ላይ መብራቱ ጠፍቶ ስለነበር ዳግሜን በነፃነት ሳየዉ ነበር የምላችሁ... አንዳንዴም እሱም ወደ እኔ ሲዞር ተፋፍረን ስናቀረቅር... አልፎ አልፎ ደግሞ የችኘሱ ላስቲክ ዉስጥ እኩል እጃችን ስንሰድ ደግሞ ደንግጠን ስንተያይ... ብቻ ምን ልበላችሁ ብዙ ነበር ታሪኩ... ፊልሙ ሊያልቅ አካባቢ ኤልዱ እንቅልፏ ተጫጭኗት ስትደገፈኝ ሳላስበዉ ስለነበር ከሶፋዉ ላይ ተፈጥፍጬ ነበር... ማን ይዞ እንዳተረፈኝ ገምቱ... ዳግም ነዋ እንደምትሉ አልጠራጠርም.... ፊልሙ ሲያልቅ እንዳማረብን ወደየመኝታ ቤታችን ገብተን ተኛን... እኔና ኤልዱ ግን አንድ ላይ ነበር የተኛነዉ... ስለ እራሷ, ስለቤተሰቦቼቸዉ ስለ እሷና ዳግሜ አስተዳደግ ስታጫዉተኝ ሌሊቱ ተጋመሰ... በጣሞ ደስ የሚል ጊዜ ነበር... እንደዉም በትንሹ ለምን አላጫዉታችሁም... እሷና ዳግሜ ተወልደዉ ያደጉት እዚሁ አዲስ አበባ አሁን የሚኖሩበት ቤት ዉስጥ መስቀል ፍላወር አካባቢ ነበር... ከዚህ በፊት እንደነገርኳችሁ ኤልዱ የዳግሜ የ2 አመት ታላቁ ናት... ዳግሜ ደግሞ ለእኔ የ1 አመት ታላቄ ነዉ...አሁን ይሄ ከማወራዉ ታሪክ ጋር ምን አገናኘዉ ሆ... ዳግሜና ኤልዱ ሌላ ታላቅ ወንድም አላቸዉ... አቤሴሎም ይባላል ኤልዱ እንደነገረችኝ ከሆነ አሁን ዉጪ ነዉ የሚኖረዉ... ብዙ የልጅነት ጊዜያቸዉን አብረዉ ያሳለፉት ኤልዱና ዳግሜ ነበሩ ይህም የሆነበት ምክንያት አቤሴሎም ብዙ ጊዜዉን አያቶቹ ቤት እየሄደ ያሳልፍ ስለነበር ነዉ:: አሁን ኤልዱ የ24 አመት ቆንጅዬ ወጣት ወቷታል... ዳግሜ ደግሞ የ22 አመት ጎረምሳ... እሷ የኮሌጅ ት/ቷን ጨርሳ የራሷን ንግድ እያንቀሳቀሰች ያለች ብርቱ ሴት ስትሆን... ዳግሜ ደግሞ የ4ኛ አመት የኮሌጅ ተመራቂ ተማሪ ነዉ... ይህንን እንኳን ቀድሜ አዉቃለዉ... ጓደኛዬ የምትማርበት ኮሌጅ ተማሪ እኮ ነዉ... ያን ሰበበኛ ፎቶዉን ከሷዉ ስልክ ላይ አይቼም አይደል እንዴ እንዲህ ቀልቤን መሰብሰብ እስኪሳነኝ ድረስ እንደቆሎ ተበትኜ የቀረሁት... ለካስ የእኔና የዳግሜን ትዉዉቅ በቅጡ ነግሬያችሁ አላዉቅም... እስኪ ለማንም ያልነገርኩትን ሚስጥሬን ዛሬ ልዘክዝክላችሁ.... ይኸዉላችሁ አንድ የተባረከች/የተረገመች ቅዳሜ (እስከዛሬ አትገባኝም) የጓደኛዬ ኮሌጅ በሲኒየር ተማሪዎችና በአዲስ ገቢ ተማሪዎች(ፍሬሾች) መሃል የልምድ ልዉዉጥ ብሎ ከየዲፓርትመንቱ 2 ተማሪዎች ተመርጠዉ ስብሰባ ይጠራል... በዚህ አጋጣሚ ታዲያ ጓደኛዬ ከCS ዳግሜ ደግሞ ከMgt ዲፓርትመንት ተወክለዉ ሄደዉ ነበር... ከዛ የመዝጊያ ስነስርአቱ ላይ ፎቶ አብረዉ ተነሱ እላችኋለሁ... እኔም የሱን ፎቶ ከጓደኛዬ የፎቶ ማህደር ዉስጥ በማየቴ ነበር ላዉቀዉ የቻልኩት... እሱ እኔን ከነመፈጠሬ ራሱ በማያዉቅበት ዘመን እኔ ከስሙ ጀምሮ ስለእሱ ማወቅ እስከምችለዉ ድረስ ከጓደኛዬ በቂ መረጃ አሰባስብ ነበር ነዉ የምላችሁ... ከዛ በኋላ... እሱን ባወኩት በ9 ወሬ... እኔ ብቻ ሳልሆን እሱም ሊያዉቀኝ በቃ... በርግጥ ጥሩ አጋጣሚ አልነበረም... አባቴ ሆስፒታል ተኝቶ ለህይወቱ ሲያጣጥር የነበረበት ወቅት ነበር... የአባቴን ሆስፒታል መግባት ሰምቼ ራሴን ስቼ ስወድቅ ደግፎ... ተሸክሞ ወደ መኪናቸዉ ያደረሰኝም እሱ ነበር(ከዘቢብ በደረሰኝ መረጃ መሰረት)... ከዛ በኋላ እንግዲህ ያዉ የምታዉቁት ነዉ ከሱ አልፎ ከጓደኞቹ ጋር እና ከቤተሰቦቹ ጋር ወዳጅ ሆኜ መቅረቴ የማይካድ ነዉ... ሌሊት ላይ ያለ ወትሮዬ ነቃሁ... መጀመሪያ ላይ ቤቱ ስለተቀየረብኝ መስሎኝ ነበር... ብዙ ጊዜ ሌሎች ሰዎች ቤት በእንግድነት ስንሄድ እንቅልፍ እንቢ የሚለን ሰዎች አለን.... ተሳሳትኩ? እኔ ብቻ ነኝ እንዴ እንዲህ የሚያደርገኝ ቆይ? ሰአቱን ሳይ 9:15 ይላል... ጉሮሮዬ ደርቋል የሆነ የሚያርሰዉ ነገር ይፈልጋል... ለምን እንደሆነ ሳስታዉስ ለካ ማታ ብዙ ጨዉ የበዛባቸዉ ምግቦች በልተን ነበር... ዉሃ ጥሙን መቋቋም ሲያቅተኝ ዉሃ ፍለጋ ወደ ኪችን አመራሁ... እንቅልፍ ባቦዘዘዉ እይታ ፍሪጁን እየከፈተ ያለ ሰዉ ያየሁ መሰለኝ... አይኔን አሻሽቼ ለማየት እየሞከርኩ ቀስ ብዬ ተጠጋሁ.... ዳግም ነበር... "ዉሃ ትፈልጊያለሽ?" አለኝ
نمایش همه...
👍 1
ራሴን በአዎንታ ነቀነኩለት... ዉስጤ ግን "እንዴት አወቀ?...ደግሞ በተመሳሳይ ሰአት እንዴት ዉሃ ሊጠማን ቻለ?" እና በመሳሰሉት ጥያቄዎች ሲተረማመስ ነበር... የታጠበ ብርጭቆ ለመፈለግ ዙሪያዉን ሲያማትር እሱ በእጁ ከያዘዉ ዉጪ ሌላ አጣ... "ቆይ ከብፌ ዉስጥ ላምጣልሽ" ሲለኝ ምን እንዳክለፈለፈኝ አላዉቅም "ችግር የለዉም በሱዉ እጠጣለሁ" አልኩት በእጁ ወደያዘዉ ብርጭቆ እየጠቆምኩ... ከዛ? ከዛማ ምን ልበላችሁ ዉሃዉን ቀድቶልኝ እየጠጣሁ እያለ ወደ እኔ ቀስ እያለ ሲቀርብ ያታወቀኛል... በትንታ እዛዉ ድፍት እንዳልል እየተጠነቀቅኩ ዉሃዉን በዝግታ እየጠጣሁ የሚያደርገዉን እከታተል ገባሁ... በስተመጨረሻም አጠገቤ ሲደርስ ይታወቀኛል... አሁንም በዝግታ ከፀጉሬ ላይ ተንሸራቶ ወርዶ ሊወድቅ የነበረዉን ሻሽ ወደ ቦታዉ መልሶ ሲያስርልኝ ይታወቀኛል... ከዛ አሁንም በዝግታ ሲጠጋኝ የሞቀዉ ትንፋሹ ግንባሬን ሲገርፈዉ በሰመመን ዉስጥ ሆኜ ይሰማኛል... ምን እሱ ብቻ ግንባሬን ሳመኝ...ጉንጬን ደገመኝ... አሁንም አላረፈም ወደ አንገቴ ወረደ... ይህንን ጊዜ ብርጭቆዉ ከእጄ አመለጠ ግን ከየት መጣ ሳይባል የሱ እጅ ከስር ቀለበዉ... ቀልቦም አስቀመጠዉ... በድንጋጤ እና በፍርሃትም ጭምር ቀና ብዬ አየሁት... የሱ አይኖች ግን የድል አድራጊነት በሚመስል መልኩ ከወትሯቸዉ በበለጠ ሲያንፀባርቁ አየሁ... ዛሬ ቆርጧል አልኩ... አዎ ዛሬ ወደኋላ የለም... እኔ ብመለስ እንኳን እሱ አይመለስም.... ፀጋ 🖋 https://t.me/memoir21
نمایش همه...
መጣጥፍ🖋

ከደመናዉ በታች ሁሉም ያልፋል::

👍 3❤ 3
CODE⓵⓷ ROUND ❷ በ30 ዲናር የተሸጠች ሀገር "አባዬ" አለኝ ገና እንቅልፍ ሸለብ ሲያደርገኝ ስለነበረ እየተበሳጨሁ "ምንድነው" አልኩት "1 ዲናር ግን ስንት ብር ነው?" ብሎ ጠየቀኝ። እውነት ግን ስንት ብር ነው እኔንጃ?! የሚያውቅ ሰው ያለም አይመስለኝም፥ አሁን ገበያ ላይ ራሱ አለ? ግን ደግሞ አባት ሆኜ እንዴት አላውቅም እላለሁ?! አውቃለሁም አላውቅምም ሳልል በሆዴ ቴክኖሎጂ ውሎ ይግባ እያልኩ Googleን ጠየኩት "187 ብር ነው" አለኝ ወዳጄ Google፥ ደነገጥኩ። እንደዚህ ውድ ይሆናል ብዬ አልጠበኩማ!! የምንዛሬውን መጠን ከመንገሬ በፊት "ለምንህ ነው የፈለከው ለመሆኑ" አልኩት "የሆነች ፅሁፍ እየፃፍኩ ነበረ" ብሎ አምጥቶ የሆነ ወረቀት አስታቀፈኝ "በ30 ዲናር የተሸጠች ሀገር" ይላል ያልጠበኩት አይነት ጠንከር ያለ ርዕስ ሆነና አስገረመኝ። ስለኢትዮጵያ ሲነሳ እንዴት እንደሚያደርገው ስለማውቅ የፃፈላት ሀገር ኢትዮጵያ መሆኗ አላጠራጠረኝም "ለምን 30 ዲናር??" አልኩት ምናልባት ይሁዳ እየሱስን ከለወጠበት መጠን ጋር መመሳሰሉ አጋጣሚ ይሆን ወይስ ሆን ተብሎ የሆነ መሆኑን ለማወቅ "መግቢያውን ብታነበው እኮ ትረዳው ነበረ" ብሎ ሸራፋ ፈገግታ አሳይቶኝ ቀጠለ "30 ዲናርን እዚህ ጋር የተጠቀምኩት በገንዘቡ መጠን ሳይሆን በተምሳሌት ነው። አየህ 30 ዲናር የዋለው ለመደበኛ ግዢና ሽያጭ ሳይሆን አዳኝ የሆነውን ለአለም ሁሉ የሚተርፈውን ኢየሱስ መለወጫነት ነው።እዚህ ጋር በድፍረት የእየሱስን ባህሪ በተምሳሌት ስለሀገራችን ማድረግ ትችላለህ። ለአለም ሁሉ በተፈጥሮ ሀብቷ በድንቅ አቀማመጧ እና በተስተካከለ አየሯ የምትተርፈውን ሀገር በኋላቀርነት ስትፈረጅ ባህሏ እና የአኗኗር ዘይቤዋ በገዛ ህዝቦቿ ሲጣጣል ስታይ ሁኔታው ይመሳሰልብሀል። የእየሱስ ከሀዲ ይሁዳ ነበረ የኢትዮጵያ ከሀዲዎች ግን እኛ ነን ህዝቦቿ ጉንጯን ስመን መሬቷን እና ሀብቷን እየቆረስን ሸንሽነን ለነጮቹ አሳልፈን የሰጠን። ምናልባት አርብ ላይ አልደረስን ይሆናል ማለቴ ለይቶላት ሀገራችንን አላጣናትም ገና ዛሬ ሀሙስ ላይ ነን ነገ እንደሚቆጨን የሚረዳ ንቃተ ህሊና ሳይኖረን ደጋግመን እየከዳናት ነው። ለዛ ነው አሁን ሀገራችን ያለችበትን ሁኔታ ከመጨረሻው እራት ጋር አመሳስዬው ዋጋዋን 30 ዲናር ያደረኩት" አለኝ ቀጥሎም "የዲናሩንም ዋጋ ተወው ያን ያህል አስፈላጊ አይደለም" ብሎ ጥሎኝ ሄደ ያንጎላጀጀኝንም እንቅልፍ ይዞት ሄደ ቆይ ገና በ15 አመት ምንድነው እንደዚህ መብሰል?! ወይ ጉድ! ግን እድሜ ልካችንን ይሁዳን ስንኮንነው እንዳልኖርን ለካ እኛም ከሀዲዎች ኖረናል?! @gbw_dan
نمایش همه...
❤ 4🔥 1
Repost from Thoughts
ከመጣችበት ታክሲ ወርዳ ልትሻገር ግራ ቀኟን ስትማትር በራሪ መኪናዎቹ አስፈሯት። አንዱ ሲመጣ ይሂድ ብላ ስትጠብቅ... ሌላ ሲመጣ አሁንም ስትጠብቅ... ደቂቃዎች ነጎዱ የመኪናዎቹ ብዛት ደግሞ አልፈው የሚያባሩ አይመስሉም። "እስከ ስንት ሰዓት እዚህ ተገትሬ ልውል ነው?!" ብላ በሆዷ እያጉረመረመች ፊቷ ያለውን አስፋልት ስታየው ከሶስት ሰፋፊ እርምጃዎች አይበልጥም። እንደምንም ራሷን አደፋፍራ ሮጥ ሮጥ ብላ ተሻገረችና ዞራ በግርምት አስፋልቱን ራሷን እየነቀነቀች ተመለከተችው። የራሷን ህይወት መሰላት... ግቧ ላይ እንደማተኮር ችግሮቿ ላይ ስትመሰጥ ግቧን ለመምታት ብዙ ዘመን አቃጠለች። ምናልባትም ትኩረቷን ሰብስባ አላማዋ ላይ ብቻ ብታተኩር ኖሮ ያን ያህል ርቆ አይታያትም ነበረ ማለት ነው። "መገናኛ መገናኛ" የሚል ታክሲ ሲጣራ ስትሰማ ባነነች ደግሞ አሁንም በራሷ አመለካከት ስትመሰጥ ወደፊቷ መባከን ስለሌበት ዳይ! ወደቀጣዩ ታክሲ... ✍nani
نمایش همه...
❤ 1
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.