1 324
مشترکین
+224 ساعت
+207 روز
+9630 روز
آرشیو پست ها
ሰላም ለእናንተ ይሁን🙏
6ኛ እና 8ኛ ክፍል ነባር ለማስመዝገብ ስትመጡ
1. የተማሪው ወላጅ እናት ሙሉ ስም
2. የተማሪው ፋይዳ ቁጥር
አስፈላጊ መሆኑን እናሳውቃለን
ከ5ኛ-8ኛ ክፍል የሚሰጠው የክረምት ትምህርት ሰኞ 13/11/2018 ዓ.ም ይጀመራል። ልጆቻችሁን ያላስመዘገባችሁ ወላጆች ትምህርት መማር ጀምረው ማስመዝገብ የምትችሉ ስለሆነ በቀኑ ወደ ት/ቤት እንዲመጡ አድርጉ🙏
መልቀቂያ መውሰድ የምትፈልጉ ወላጆች የምናስተናግደው ከሰኞ 13/11/2018 ዓ.ም እስከ ዓርብ 17/11/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ መሆኑን እናሳውቃለን🙏
ከ6ኛ-8ኛ ክፍል የ2019 ዓ.ም የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ረቡዕ 15/11/2018 ዓ.ም የሚጀመር መሆኑን እናሳውቃለን🙏
የክረምት ት/ት መማር ለተማሪዎች የሚሰጠው ዋና ዋና ጥቅሞች፦
👉 በዓመቱ ውስጥ ያጋጠሙ ድክመቶችን ለማስተካከል እድል ይሰጣል
👉 ዝግጅት ለሚያስፈልጋቸው ትምህርቶች ትኩረት ለመስጠት ያግዛል
👉 አዲስ ትምህርቶችን አስቀድሞ መማር ይቻላል
👉 የመጪው ዓመት የትምህርት ዝግጅት ሸክም ይቀንሳል
👉 በረጅም ዕረፍት ምክንያት የሚፈጠረውን የመርሳት ችግር ይከላከላል
👉 ከስልክ/ከጨዋታ ብቻ ይልቅ ልጆች ከቅርብ ጓደኞቻቸው ልምድ የመለዋወጥ ጠቀሜታ ይሰጣል
👉 የጊዜ አጠቃቀም ልምድ ያሰለጥናል
👉ለብሔራዊ ፈተናዎች ቅድመ ዝግጅት እና የፈተና ልምምዶችን በመስራት ጭንቀትን ይቀንሳል
Repost from Maria Rubatto Catholic School
ለማሪያ ሩባቶ ካቶሊክ ትምህርት ቤት ወላጆች እና አሳዳጊዎች በሙሉ የክረምት ትምህርት ክፍያ በባንክ እንደማይከፈል አውቃችሁ በጥሬ ገንዘብ እንድትከፈሉ በትህትና እናሳውቃለን ።
እንኳን ደስ አለን ደስ አላችሁ🏆
በ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ተፈታኝ ተማሪዎቻችን 100% ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ አልፈዋል🏆🏆🏆
እንኳን ደስ አለን ደስ አላችሁ🏆
በ2018 ዓም የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ተፈታኝ ተማሪዎቻችን 100% ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ አልፈዋል🏆🏆🏆
ለማሪያ ሩባቶ ካቶሊክ ት/ቤት ወላጆች እና አሳዳጊዎች በሙሉ የተማሪዎችን የሰኔ ወር የማጠቃለያ ክፍያ ቀድማችሁ የከፈላችሁትን እያመሰገንን የሰኔ ወር እና ከሰኔ ወር በፊት በተለያየ ምክንያት ያልከፈላችሁ ከፈተና በፊት ከሰኔ 1 እስከ 10 ባለው ጊዜ ከፍላችሁ እንድታነቁ ስንል በትህትና እናሳውቃለን፡፡
