fa
Feedback
ተዋሕዶን እንወቅ።

ተዋሕዶን እንወቅ።

رفتن به کانال در Telegram

አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ ሥረይ ለነ ኲሎ አበሳነ ኢታብአነ ውስተ መንሱት እግዚኦ አድኅነነ እምዕለት እኪት ወባልሐነ ውስተ መንሡት። ✝በከመ ምሕረትከ አምላክነ ወአኮ በከመ አበሳነ✝ የየእለቱን ስንክሳር፥ ውዳሴ ማርያም፥ ጸሎተ አርጋኖን፥ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን፥ የጻድቃንና የሰማዕታትን ገድል፥ የተለያዩ መንፈሳዊ ጥያቄዎችን፥ የድሮ እና አዳዲስ መዝሙራትን የሚያገኙበት ቻናል ነው። ይቀላቀሉን።

نمایش بیشتر
Buy Ad
2 373
مشترکین
+224 ساعت
-77 روز
+630 روز
آرشیو پست ها
ፊልጶስ ሳይጠራኝ ገና ሳልቆም ፊቱ ከበለስ ስር ሳለው ያውቀኛል ከጥንቱ መካሪ አያሻውም ኹሉን ያውቃልና ከሳሽ ኾይ ተመለስ ድንጋዩን ጣልና ኦ ቅዱስ #ናትናኤል ሰአል በእንቲአነ❤️ ዛሬ በዓለ ዕረፍቱ ነው.. በረከቱና ምልጃው አይለየን!

ቃለ እግዚአብሔር [ ትምህርት ] መንፈሳዊ ሕይወት ጊዜና ቦታ የሚወስነው ሳይሆን የሁልጊዜ ኑሮአችንና መታወቂያችን መሆን አለበት። ክርስቲያን በአለባበሱ ፣ በአነጋገሩ ፣ በአካሄዱ ፣ በመልካም ሥራው ከሌሎች መለየት አለበት፡፡ ጥሩ የጸሎት ሕይወት ያለው ክርስቲያን አይወድቅም ቢወድቅም እንኳ ይነሳል፡፡ ነገር ግን ከጸሎት ሕይወትና ከቃለ እግዚአብሔር የተለየ ከሆነ ሕይወቱ ጣዕም አልባ ይሆንበታል ፣ በትንሽ ነገር ይከፋል ፣ በሕይወቱ ተስፋ እስከመቂረጥ ብሎም ሃይማኖቱን እስከመካድ ይደርሳል። በሌላ አገላለጽ ከመንፈሳዊ ሕይወት የተለየ ክርስቲያን እና ከውኃ የተለየ ተክል አንድ ናቸው በመጨረሻ ደርቀው ይቀራሉ። ዘወትር ቃለ እግዚአብሔርን ስናደምጥ (ስንማር) ስለ ሦስት ነገሮች መሆን አለበት። 1. ከዚህ በፊት የማናውቀውን አዲስ ነገር ለማወቅ። 2. ከዚህ በፊት የምናውቀውና ተረስቶ ያለን ነገር ለማስታወስና ሥራ ላይ ለማዋል። 3. የምናውቀውን ግን ትኩረት ያልሰጠነውን ወደ ተግባር ለመለወጥ ነው። ቃለ እግዚአብሔርን ስናደምጥ እነዚህን ሦስት ነገሮች መዘንጋት የለብንም አልያ ግን ጌታችን በወንጌል “ከእግዚአብሔር የሆነ የእግዚአብሔርን ቃል ይሰማል፤ እናንተ ከእግዚአብሔር አይደላችሁምና ስለዚህ አትሰሙም።” /ዮሐ 8፥47/ ብሎ የተናገረው በእኛ ላይ ይፈጸማል። #ለሌሎች_ሼር_ማድረግ_አትዘንጉ
JOIN @Applied_CHRISTIANITY

ነፍሴ የወደደችውን ፈለግሁት፥ ፈለግሁት፤ አላገኘሁትም። — #ክፍል_አንድ ከመጽሐፍ ቅዱስ ለመረዳት ከበድ የሚለው - አስተሳሰባችን ከተበላሸም በመጥፎ መልኩ የምንተረጉመው - አንድ መጽሐፍ አለ፤ መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን። ይኽ መጽሐፍ ከአምስቱ የሰሎሞን የጥበብ መጻሕፍት አንዱ ነው። ሰሎሞን መጽሐፉን ከሌሎቹ መጻሕፍቱ በተለየ መልኩ ክርስቶስን፥ ቤተክርስቲያንንና እመቤታችንን በዘይቤያዊ መንገድ እያቆራኘ ይጽፋል። መጽሐፉን ከማንበባችን በፊት ግን Fr. Zakaria Butros (የCoptic Church ካህን ናቸው፤ በእስልምናው ላይ በመሥራት በስፋት ይታወቃሉ) በመጽሐፉ ዙሪያ ከጻፉት በትንሹ ላስነብባችኹ።
Actually, approaching to the book of Song of the Songs is similar to approaching a flaming tree, flamed with the holy fire that had been seen by prophet Moses, as the lord said to him O Moses, ‛Take your shoes off your feet, for the place where you are standing is a holy ground’ (Acts 7:33) ... So when we approach the book of Song of the Songs, with its sublimity of meanings and symbols, we have to take off the shoes of materialism, and lusty thoughts, and go forward in the holiness of meditation and purity of heart, as: "To the pure, all things are pure; but to those who are defiled and unbelieving, nothing is pure; but both their mind and their conscience are defiled." (Titus 1:15)

መኃልየ መኃልይን ማንበብ ለሙሴ እንደታየው አይነት በቅዱስ እሳት የሚቃጠል ቁጥቋጦን እንደ መቅረብ ያለ ነው፤ ጌታ ለሙሴ እንዲኽ ሲል እንደተናገረው “የቆምህባት ስፍራ የተቀደሰች ምድር ናትና የእግርህን ጫማ አውልቅ።” (ሐዋ. 7፥33) ... ስለዚኽ እኛም መኃልየ መኃልይን ስናነብ፥ [ያሉትን ጥልቅ ትርጉሞችና ምልክቶችንም ለመረዳት] የmaterialism፥ የዝሙት ሐሳቦችን ጫማ አውልቀን፥ በቅድስና መንፈስ እና በንጹሕ ልብ መኾን አለበት፤ እንዲኽ እንደተጻፈ፦ “ሁሉ ለንጹሖች ንጹሕ ነው፤ ለርኵሳንና ለማያምኑ ግን ንጹሕ የሆነ ምንም የለም፥ ነገር ግን አእምሮአቸውም ሕሊናቸውም ረክሷል።” (ቲቶ 1፥15)
(Fr. Zakaria Butros, The challenges against The book of Song of the Songs And their answers, Introduction.) [materialism ለሚለው የአማርኛ አቻ ቃል አልመጣልኽ አለኝ። ያው ትርጉሙን በትክክል እንዳልተረጎምኹት አውቃለኹ.. እንዲኹ ከምተወው ብዬ ነው።] እሳቸው እንዳሉት ነው፤ የምጨምረው የለኝም። ግን ስለ መጽሐፉ በጥቂቱ ልንገራችኹ። መጽሐፉን የጥንት አባቶችን ትርጉም ሳትይዙ (እንዴት እንደተረጎሙት ሳትረዱ) ባታነቡት እመክራለኹ፤ እናንብበው ካላችኹ ግን ከላይ እንደ ተጻፈው ልባችንን ንጹሕ አድርገን ወደ መጽሐፉ መቅረብ ይገባናል። መጽሐፉ በሴትና በወንድ መካከል ያለ ግንኙነትን ተመሥርቶ የተጻፈ ነው፤ ነገር ግን በውስጡ ያዘለው መልእክት እጅግ ጥልቅ ነው - ከጾታዊ ግንኙነቱ በዘለለ ብዙ ነገሮችን በቅኔያዊ መልኩ ይይዛል። በቤተክርስቲያናችን የቀዳም ስዑር ዕለት ከሚነበቡ መጻሕፍት አንዱ ነው፤ “በዘቢብም አጽናኑኝ፥ በእንኮይ አበረታቱኝ፥ በፍቅሩ ተነድፌ ታምሜያለሁና። ግራው ከራሴ በታች ናት፥ ቀኙም ታቅፈኛለች። እናንተ የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት ሆይ፥ እርሱ እስኪፈልግ ድረስ፥ ፍቅርን እንዳታስነሱትና እንዳታነሣሡት፥ በሚዳቋ በምድረ በዳም ዋላ አምላችኋለሁ።” (2፥5-7) ውዷ ጠፍቷትም ስትፈልገው ነበር። “ከተማይቱን የሚዞሩት ጠባቂዎች አገኙኝ፤ ‛#ነፍሴ_የወደደችውን_አያችሁትን?’ አልኋቸውም። ከእነርሱም ጥቂት እልፍ ብዬ፥ ነፍሴ የወደደችውን አገኘሁት።” (3፥3-4 — ውዷ የተባልነው እኛ ነን በቀጣዩ ክፍል እናየዋለን።) ስለ እመቤታችንም እንዲኽ ሲል ይናገራል፤ “ሙሽራዬ ሆይ፥ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ፥ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ፥ ከአማና ራስ ከሳኔርና ከኤርሞን ራስ፥ ከአንበሶች መኖሪያ ከነብሮችም ተራራ ተመልከች።” (4፥8) ስለ ክርስቶስም “ውዴ #ነጭና_ቀይ ነው፥ ከእልፍ የተመረጠ ነው። ... ” እያለ በትንቢት መነጽር እያየ ይናገራል። (5፥10 — ይኼን ምዕራፍ ሙሉውን በቀጣዮቹ ክፍሎች ስለምናየው ስለ ክርስቶስ የሚናገረውንም በዚያው አብረን እናየዋለን። የተጠቀምኳቸውን መጻሕፍት እንዲኹም የአበውን የዚኽ መጽሐፍ የትርጉም ሥራዎች አስቀምጥላችዃለኹ።) [ክፍል ኹለት ይቀጥላል...]

Song of Solomon 5 አማ - መኃልየ መኃልይ 1: እኅቴ ሙሽራዬ ሆይ፥ ወደ ገነቴ ገባሁ፥ ከርቤዬን ከሽቱዬ ጋር ለቀምሁ፥ እንጀራዬን ከማሬ ጋር በላሁ፥ የወይን ጠጄን ከወተቴ ጋር ጠጣሁ። ባልንጀሮቼ ሆይ፥ ብሉ፤ ወዳጄ ሆይ፥ ጠጪ እስክትረኪ ድረስ ጠጪ። 2: እኔ ተኝቻለሁ፥ ልቤ ግን ነቅቶአል፤ የውዴ ቃል ነው፥ እርሱም ደጁን ይመታል እኅቴ፥ ወዳጄ፥ ርግቤ፥ መደምደሚያዬ ሆይ፥ በራሴ ጠል፥ በቈንዳላዬም የሌሊት ነጠብጣብ፡ ሞልቶበታልና ክፈችልኝ።
3: ቀሚሴን አወለቅሁ እንዴት እለብሰዋለሁ? እግሬን ታጠብሁ እንዴት አሳድፈዋለሁ? 4: ውዴ እጁን በቀዳዳ ሰደደ፥ አንጀቴም ስለ እርሱ ታወከ። 5: ለውዴ እከፍትለት ዘንድ ተነሣሁ፤ እጆቼ በደጅ መወርወሪያ ላይ ከርቤን አፈሰሱ፥ ጣቶቼ ፈሳሹን ከርቤ አንጠበጠቡ። 6: ለውዴ ከፈትሁለት፥ ውዴ ግን ፈቀቅ ብሎ አልፎ ነበር። ነፍሴ ከቃሉ የተነሣ ደነገጠች፤ ፈለግሁት፥ አላገኘሁትም፤ ጠራሁት፥ አልመለሰልኝም።
7: ከተማይቱን የሚዞሩት ጠባቂዎች አገኙኝ፤ መቱኝ፥ አቈሰሉኝም፤ ቅጥር ጠባቂዎችም የዓይነ ርግብ መሸፈኛዬን ወሰዱት። 8: እናንተ የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት ሆይ፥ አምላችኋለሁ፤ ውዴን ያገኛችሁት እንደ ሆነ፥ እኔ ከፍቅር የተነሣ መታመሜን ንገሩት። 9: አንቺ በሴቶች ዘንድ የተዋብሽ ሆይ፥ ከሌላ ወዳጅ ይልቅ ውድሽ ማን ነው? ይህን የሚያህል አምለሽናልና፥ ከሌላ ወዳጅ ይልቅ ውድሽ ማን ነው? 10: ውዴ ነጭና ቀይ ነው፥ ከእልፍ የተመረጠ ነው። 11: ራሱ ምዝምዝ ወርቅ ነው፤ ቈንዳላው የተዝረፈረፈ ነው፥ እንደ ቁራ ጥቁረትም ጥቁር ነው። 12: ዓይኖቹ በሙሉ ፈሳሽ አጠገብ እንዳሉ፥ በወተት እንደ ታጠቡ በፈሳሽ ውኃ አጠገብ እንደ ተቀመጡ፥ እንደ ርግቦች ናቸው። 13: ጕንጩና ጕንጩ የሽቱ መደብ፥ እርከን እንዳለበት እንደ ሽቱ አትክልት ናቸው፤ ከንፈሮቹ እንደ አበቦች ናቸው፥ የሚፈስስ ከርቤንም ያንጠበጥባሉ። 14: እጆቹ የቢረሌ ፈርጥ እንዳለበት እንደ ወርቅ ቀለበት ናቸው፤ አካሉ ብልሃተኛ እንደ ሠራው፥ በሰንፔር እንዳጌጠ እንደ ዝሆን ጥርስ ነው። 15: እግሮቹ በምዝምዝ ወርቅ እንደ ተመሠረቱ። እንደ ዕብነ በረድ ምሰሶች ናቸው፤ መልኩ እንደ ሊባኖስና እንደ ዝግባ ዛፍ መልካም ነው። 16: አፉ እጅግ ጣፋጭ ነው፥ እርሱም ፈጽሞ ያማረ፤ ነው እናንተ የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት ሆይ፥ ውዴ ይህ ነው፥ ባልንጀራዬም ይህ ነው። የዚኽን ክፍል ማብራሪያ ነገር እና እንዴት ከኛ ሕይወት ጋር እንደሚገናኝ በተወሰነ መልኩ ለማየት እንሞክራለን፤ ይጠብቁ።

ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ !
ክፍል 1
እንደ ልቤ የተባለው ቅዱስ ዳዊት መዝሙሩን ሲጀምር እንዲህ ይላል። "¹ ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ ፥ በኃጢአተኞች መንገድ ያልቆመ ፥ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ ሰው። ² የእግዚአብሔር ሕግ ብቻ ፈቃዱ የሆነ ፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት የሚያስብ። ³ እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች ፥ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል ፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል። ⁴ ኃጥአን እንዲህ አይደሉም ፥ ነገር ግን ነፋስ ከገጸ ምድር ጠርጎ እንደሚወስደው ትቢያ ናቸው። ⁵ ስለዚህ ዝንጉዎች በፍርድ፥ ኃጢአንም በጻድቃን ምክር አይቆሙም። ⁶ እግዚአብሔር የጻድቃንን መንገድ ያውቃልና ፥ የኃጥአን መንገድ ግን ትጠፋለች። /መዝ 1÷1-6/ ይህ የቅዱስ ዳዊት መዝሙር የጻድቃንንና የኃጥአንን ነገር የሚያስረዳ ነው። በኃጥአን መንገድ ያልቆመ ሰው ንዑድ ፣ ክብር ነው ሲል ተናግሯል። መንገድ ብሎ የተናገረው አራዊቱ ፣ እንስሳቱ ሰው ሁሉ የሚመላለስበትን ሳይሆን ግብራቸውን (ሥራቸውን) ለማመልከት ነው። ኃጥአን የተባሉት ሰርቀው ፣ ቀምተው ፣ አስረው ፣ ቋንጃ ቆርጠው ፣ ነፍስ ገድለው የሚኖሩ ናቸው ፤ ጻድቃን ደግሞ ጾመው ፣ ጸልየው ፣ ሰግደው ፣ መጽውተው የሚኖሩ ናቸው። በዚህ የተነሳ ኃጥአን በጻድቃን ምክር አይቆሙም አለ ምነው እንዲህ አለ ቢሉ የጻድቃን ምክራቸው ኃጥአንን የሚያስጨንቅ ስለሆነ ነው ብለን እንመልሳለን። ምነው የጻድቃን ምክራቸው ለኃጥአን ቢጠቅማቸው እንጂ እንዲት ያስጨንቃቸዋል ከተባለ ፡- አንድ ሲሰርቅ የኖረን ሰው ድንገት አትስረቅ ቢሎት ለእርሱ ሳይሰርቅ መኖር ጭንቅ ይሆንበታል ምክንያቱም የኃጥአን ትልቁ በሽታ ምቾትን መፈለግ ስለሆነ ብዙዎቹ ከምቾታቸው የሚለያቸዋን ምንም አይነት ምክር መስማት አይፈልጉም። በመጨረሻም ኃጥአን ከበደላቸው ፣ ከኃጢአታቸው ሁሉ በንስሐ ባይመለሱ መጨረሻቸው ጥፉት እንደሆነም ቅዱስ ዳዊት በዚህ መዝሙሩ ላይ አጠንክሮ ተናግሯል። [ ሚያዚያ 29 -2017 ] ይቀጥላል... #ለሌሎች_ሼር_ማድረግ_አትዘንጉ
JOIN @Applied_CHRISTIANITY

🔴ለጥያቄዎች መልስ ክፍል 1 "በሃይማኖት ከማትመስለው ሰው ጋር ተሳስሞ ነበር ችግር ይኖረው ይሆን?" #ለሌሎች_አጋሩ !
ለጥያቄ @Tyake_alegn_bot
JOIN @Applied_CHRISTIANITY

#ርዕስ የጴጥሮስ አደራ [ኦርቶዶክሳዊ ሲኒማ]
በቅርብ ቀን !
JOIN @Applied_CHRISTIANITY

🔴 ስለ መልካም ምክር እና ስለ ጥያቄ መጠየቂያ ገጽ አጭር መልዕክት ! #ለጥያቄ @Tyake_alegn_bot “ጠቢብ እነዚህን ከመስማት ጥበብን ይጨምራል፥ አስተዋይም መልካም ምክርን ገንዘቡ ያደርጋል።” |ምሳ 1÷5]
JOIN @Applied_CHRISTIANITY

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፥ በአማን ተንሥአ! እናንተዬ.. ቻናላችንን ከከፈትናት ኹለት ዓመት ኾናት ለካ😁.. ያው ጠፍቻለኹ አውቃለኹ በብዙ በብዙ ምክንያት [ይቅር በሉኝ]🫣 በቅርቡ በአዲስ መልኩ እመለሳለኹ.. እስከዚያው Share እያደረጋችኹ ጠብቁኝ። ደካማው ወንድማችኹን ገብረ ማርያምን በጸሎታችኹ አስቡት።

እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል አደረሳችኹ! “ጌታ በእውነት #ተነሥቷል!” (ሉቃ. 24፥34)

ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት...? “ኢየሱስም መልሶ፦ ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ። ... ዮናስ በዓሣ አንባሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ፥ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል አላቸው።” (ዮሐ. 2፥19፤ ማቴ. 12፥40) ጌታችን በከርሰ መቃብር የቆየው ከዓርብ አስራ አንድ ሰዓት በፊት ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ ነው። ታዲያ ሦስት ቀን ከሦስት ሌሊት በከርሰ መቃብር አደረ ልንል እንችላለን? ይኽን ጥያቄ ለመመለስ የዕብራውያንን የቀን አቆጣጠር መረዳት ያስፈልጋል። በኹለት መንገድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ተደርጎ ሊቆጠር ይችላል። 1. በዕብራውያን አቆጣጠር አንድ ሌሊት የሚጀምረው ከዋዜማው 11 ሰዓት ጀምሮ ነው። ከአስራ አንድ ሰዓቱ በፊት ያሉት ሰዓቶች አንድ ሰዓትም ቢኾን እንደ አንድ መዓልትና ሌሊት ይቆጠራል። ጌታችን ደግሞ የተቀበረው ከአስራ አንድ ሰዓት በፊት ነው - አንድ ቀንና አንድ ሌሊት። ዓርብ ከሠርክ 11:00 ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ሠርክ 11:00 ድረስ - ከዓርብ ጋር ኹለት ቀንና ኹለት ሌሊት። ከላይ እንዳየነው አንድም ሰዓት ቢኾን እንደ አንድ መዓልትና ሌሊት ይቆጠራል፤ ከቅዳሜ ሠርክ 11:00 ጌታችን ከሞት እስከ ተነሣበት መንፈቀ ሌሊት ድረስ - ከዓርብና ከቅዳሜ ጋር በአንድ ላይ - ሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት ኾነ ማለት ነው። 2. ክርስቶስ በፈቃዱ የተሰቀለውና የሞተው በዕለተ ዓርብ ስለኾነ አቆጣጠሩ ከጠዋት 12 ሰዓት ይጀምራል - ከ12 ሰዓት እስከ 6 ሰዓት በምድር ላይ ብርሃን ነበር - አንድ ቀን። ከስድስት እስከ ዘጠኝ ሰዓት ደግሞ በምድር ላይ በምትሐት ያልኾነ እውነተኛ ጨለማ ነበር - አንድ ሌሊት። ከዓርብ ዘጠኝ ሰዓት እስከ 12 ሰዓት እንደገና ቀን ኾኗል - አንድ ቀን። ከማታ 12 ሰዓት እስከ ቅዳሜ ጠዋት 12 ሰዓት - አንድ ሌሊት። ከቅዳሜ ጠዋት እስከ ማታ እና ከማታ እስከ መንፈቀ ሌሊት - ከዓርብ ጠዋት ጀምሮ - ሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት ይኾናል።
ነፍሴን ደግሞ አነሣት ዘንድ አኖራለሁና ስለዚህ አብ ይወደኛል። እኔ በፈቃዴ አኖራታለሁ እንጂ ከእኔ ማንም አይወስዳትም። ላኖራት ሥልጣን አለኝ ደግሞም ላነሣት ሥልጣን አለኝ።” (ዮሐ. 10፥17-18)


አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ? ሊያርዱት ሲወስዱት እንደማይናገር በግ ከዕለተ ኃሙስ ማታ ጀምሮ ‛ተፈጸመ’ እስከሚልበት ጊዜ ድረስ ብዙውን ጊዜ ገዢውን ጲላጦስን እስከሚያስገርመው ድረስ ዝም ያለው ጌታ መናገር ባለበት ሰዓት ግን ዝም አላለም። በዕጸ መስቀል (በንግሥናው ዙፋን) ላይ ሳለ ከተናገራቸው የፍቅር ቃላት አንዱ ‛ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ’ (ከላይ ርዕስ ያደረግነውን) ነው። ይኽን ቃል የተናገረው ጌታ ስለ ኹለት ነገር ነው (ሌሎችም አሉ ግን ለዛሬ ኹለቱን እንይ)። 1. የመጀመሪያው አይሁድ እንዲያስተውሉ የተናገረው ቃል ነው። በጥንት ዘመን መጻሕፍት የሚቀመጡት በጥቅልል መልክ ነበር፤ እያንዳንዱ ጥቅልል ደግሞ የሚታወቀው በሚጀምርበት የመጀመሪያው ሐረግ ነበር። የመዝሙር 21 መታወቂያ ደግሞ ‛ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ’ የሚለው ነበር። ያ መዝሙር ደግሞ ጌታ በዕለተ ዓርብ የተቀበለውን መከራ የሚያሳይ፥ ክርስቶስ መሢሁ መኾኑን የሚገልጽ ነው፤ አይሁድ ያንን አስተውለው ወደ ልቡናቸው እንዲመለሱ “በታላቅ ድምጽ ጮኸ።”
Psalms 22 አማ - መዝሙር 7: የሚያዩኝ ሁሉ ይላገዱብኛል፤ ራሳቸውን እየነቀነቁ በከንፈሮቻቸው እንዲህ ይላሉ፦ 8: “በእግዚአብሔር ተማመነ፥ እርሱንም ያድነው፤ ቢወድደውስ ያድነው።” 12: ብዙ በሬዎች ከበቡኝ፥ የሰቡትም ፍሪዳዎች ያዙኝ፤ ... 13: እንደ ነጣቂና እንደሚጮኽ አንበሳ በላዬ አፋቸውን ከፈቱ። 15: ኃይሌ እንደ ገል ደረቀ፥ በጕሮሮዬም ምላሴ ተጣጋ፥ ወደ ሞትም አሸዋ አወረድኸኝ። 16: ብዙ ውሾች ከብበውኛልና፤ የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ፤ እጆቼንና እግሮቼን ቸነከሩኝ። 17: አጥንቶቼ ሁሉ ተቈጠሩ፤ እነርሱም አዩኝ ተመለከቱኝም። 18: ልብሶቼን ለራሳቸው ተከፋፈሉ፥ በቀሚሴም ላይ ዕጣ ተጣጣሉ።
2. ኹለተኛው ምክንያት ከአዳም ጀምሮ እስከ ክርስቶስ መምጣት ድረስ ለ5500 ዓመታት የአዳም ልጆች በሙሉ ሲጮኹት የነበሩትን ጩኸት ለኛ ቤዛ (ምትክ) ሊኾነን የመጣው ጌታ በነርሱ ቦታ ኾኖ የጮኸልን ጩኸት ነው። ኃሙስ ማታ “በምድር ላይ እንደሚወርድ እንደ ደም ነጠብጣብ” እስኪወርደው ድረስ የተጨነቀው ጭንቀት የአዳም ልጆች በምድርም ከዚያም በሲዖል የተጨነቁትን ጭንቀት በነርሱ ቦታ ኾኖ በመጨነቁ የወረደው ነው። በሌሎችም ቦታዎች የምናገኛቸው ክርስቶስ “ ‛ዕሩቅ ብእሲ - ሰው ብቻ’ ነው” የሚሉ የሚመስሉ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችንም በዚኽ መልኩ መረዳት አለብን። በብሉይ ብዙ ነቢያት ጌታ በመስቀል የተናገረውን ሐሳብ የያዙ ብዙ ቃላትን ተናግረዋል፤ “እጅኽን ስደድልን ... አድነን ... ” እያሉ የጌታን መምጣት በጉጉት ጠብቀዋል (ምንም እንኳን እግዚአብሔር ከነርሱ ጋር ቢኾንም ዓለም በኃጢአት ተመልታ ስለነበር ‛ጽድቃቸው እንደ መርገም ጨርቅ’ ኾኖባቸው ነበር)። ጌታም በነሱ ቦታ ኾኖ የነሱን ጩኸት ጮኾላቸዋል።
“ጲላጦስም ደግሞ ጽሕፈት ጽፎ በመስቀሉ ላይ አኖረው፤ ጽሕፈቱም፦ የአይሁድ ንጉሥ የናዝሬቱ ኢየሱስ የሚል ነበረ።” (ዮሐ. 19፥19)
እንበለ ደዌ ወሕማም፥ እንበለ ፃማ ወድካም፥ አመ ከመ ዮም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ ለብርሃነ ትንሣኤሁ እግዚአብሔር በፍስሓ ወበሰላም!

በሰሙነ ሕማማት ይህንን አድርጉ!ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ እንደጻፉት እንኳን አደረሳችሁ! ሰሙነ ሕማማት አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ሁሉ ቤዛ ሆኖ ተላልፎ መሰጠቱን የምናስታውስበት ሳምንት ነው። ይህንን ምክንያት በማድረግ የሥርዓት ለውጥ ሲደረግ ሲመለከቱ ግራ የሚጋቡና ሥርዓተ አምልኮውን በሚገባ ከመከታተል ይልቅ ሥርዓት የጣሱ እየመሰላቸው የሚጨነቁ ስላሉ ልናደርገው የሚገባንን እጽፍላችኋለሁ። 🔘1.  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ብሎ ፊትንና መላ ሰውነትን በትዕምርተ መስቀል {በመስቀል ምልክት} ማማተብ አይከለከልም። ከካህን እጅ ቡራኬ አንቀበልም በካህኑ እጅ ያለውን መስቀል አንሳለምምና ማማተብም የለብንም በሚል ፍልስፍና ካልሆነ ማማተብ ክልክል ነው ተብሎ የተጻፈበት ቦታ የለምና። 🔘2. የሚከለከል ጸሎት የሌለ መሆኑን አውቃችሁ ያስለመዳችሁትን ጸሎት በትጋት ጸልዩ። መሥዋዕት ካለመሠዋታችን ቅዳሴ ካለመቀደሳችን በቀር በዚህ ሳምንት ከብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ጀምሮእስከ ሊቃውንት ድርሳናት ድረስ በቤተ ክርስቲያን የማይጸለይ ጸሎት የለምና። 🔘3. ሰላምታ መስጠት ከጸሎተ ሐሙስ ዕለት በቀር አልተከለከለም፤ እሱም ቢሆን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በይሁዳ ሰላምታ ተላልፎ መሰጠቱን ለማስተዎስ እንጅ ሌላ የተለየ ምክንያት ስለሌለው በመርሳት ወይም በሌላ ከድፍረት በተለየ ምክንያት ሰላምታ ያቀረበላችሁን ሰው ልታስደነግጡና ትልቅ ኃጢአት እንደሠራ አድርጋችሁ ልታስጨንቁት አይገባም። 🔘4. “በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ” ብሎ መጻሕፍትን ማንበብ ወይም ሌላ ሥራን መጀመር ይቻላል። ስመ እግዚአብሔር መጥራት የምንከለከልበት ጊዜ መቸም የለምና። 🔘5. የጌታችንን ሕማሙንና ሞቱን የሚያስታውሱ መጻሕፍትን በማንበብና በመስማት ጊዜአችንን መወሰን ይገባናል። 🔘6. በዚህ ሳምንት ተድላ ደስታን ሲያደርጉ መገኘት ከአይሁድ ጋር እንደ መተባበር የሚያስቆጥር ስለሆነ አብዝቶ በመብላትና በመጠጣት፣ ያማረውንና ጌጠኛውን ልብስ በመልበስ፣ ባልና ሚስት በምንጣፍ በመገናኘት እንዲሁም በልዩ ልዩ ምክንያት ከምናደርጋቸው ተድላ ደስታዎች መራቅ ይገባናል። ቅዱሳን በዘመናቸው ሁሉ ባሰቡት ጊዜ የሚያስጨንቃቸውን የክርስቶስን መከራ እያሰብን ለጥቂት ጊዜም እንኳን ቢሆን የክርስቶስን መከራ በሰውነታችን ማሰብ ይገባናል። የተቻለው እንደ ጴጥሮስ የራሱን ኃጢአት እያሰበ እንደ ማርያም መግደላዊት የክርስቶስን ሞት እያዘከረ ሊያለቅስ ይገባዋል። በወዲያኛው ዓለም ከማልቀስ የሚያድነን ዛሬ የራሳችንን ኃጢአት አስበን የክርስቶስን ሞት አዘክረን የምናለቅሰው ለቅሶ ነው እንጅ ዛሬ ከተደሰትን ደስታችንን በዚህ ዓለም ማድረጋችን አይደለምን? 🔘7. በተቻለን መጠን በቤተ ክርስቲያን መዋል ይገባናል፤ ሕማማተ መስቀልን የሚያስታውሱ መጻሕፍት የሚነበቡበት ሳምንት ስለሆነ ነው። ነገር ግን በልዩ ልዩ ምክንያት በቤተ ክርስቲያን መዋል እንኳን ባይቻላችሁ ባላችሁበት ቦታ ሁናችሁ እየዋሻችሁ በሐሰት የከሰሱትን፣ እየቀማችሁ ልብሱን የገፈፉትን፣ ሰው እየደበደባችሁ በጅራፍ የገረፉትን፣ በወንድሞቻችሁና በእኅቶቻችሁ ላይ እየፈረዳችሁ በክርስቶስ ላይ የፈረዱበትን፣ በሰዎች ላይ እየተዘባበታችሁ የተዘባበቱበትን፣ በሳቅና በሽንገላ ሰውን እየሸነገላችሁ ሽንገላ በተሞላበት ሰላምታ ጌታውንና መምህሩን አሳልፎ የሰጠ ይሁዳን ልትመስሉ አይገባም። ይልቁንም በአይሁድ እጅ ተላልፎ ቢሰጥም ንጹሓ ባሕርይ መሆኑን በማመን እስከ ቀራንዮ የተከተሉትን ደቀመዛሙርት ልትመስሉ ይገባል። እግራችሁ በመቅደሱ ውስጥ ባይቆምም ልባችሁን ከመቅደስ ልታወጡት አይገባም። እያዘናችሁ ባላችሁበት ቦታ ዋሉ። 🔘8. በቤታችሁም ሆነ በቤተ ክርስቲያን አብዝታችሁ ስገዱ። ስለሁላችንም ቤዛ የሚሆን ክርስቶስ በፊታችን መስቀል ተሸክሞ ሲወድቅ እያያችሁት ትቆማላችሁን? አይሁድ ገፍተውት አንድ ጊዜ ወደ ምድር በወደቀ ጊዜ ለወደቀው መውደቅ ዘመናችንን ሙሉ ብንወድቅ ብንነሣ ውለታ መክፈል እንችል ይመስላችኋል? ቅዱሳን ሳያቋርጡ ሲሰግዱ የሚኖሩት ክርስቶስ በፊታቸው በአይሁድ እጅ እየተገፋ መስቀሉን እንደተሸከመ ሲወድቅ በዓይነ ሕሊናቸው ስለሚያዩት ነው። በስንክሳር ተጽፎ የምናገኘው ዜና ሞታቸው እየሰገዱ ሳሉ ሞት ነፍሳቸውን ከሥጋቸው ለይቶ እንደሚወስዳትና ለስገደት ታጥቀው እንደተንበረከኩ እንደሚገኙ ይነግረናል። የተሰቀለውን ክርስቶስን የሚያስብ ሰው ለሰውነቱ ዕረፍትን አይሻም። 🔘9. ከሁሉም ሰው ጋር ፍቅርን አድርጉ። ሰውን ለመውደድ ምክንያት አታብጁ። ክርስቶስ አሳልፎ የሰጠውን ይሁዳን “ወዳጄ” ብሎ ሲጠራው አትሰሙትም? እግዚአብሔርን አንተን ያለ ምክንያት እንደ ወደደህ አንተም ያለ ምክንያት ሰውን መውደድ ልመድ። ክርስቶስ አንተን ጠላቱ ሆነህ ሳለ ፍቅርን ካላጎደለብህ ለጠላትህ ፍቅርን አታጉድልበት። ክርስቶስ ይሁዳን ‘’ወዳጀ’’ ብሎ ከጠራው አንተም ይሁዳዎችህን ወዳጀ ብለህ ጥራቸው። አውቃለሁ ጠላትን መውደድ መራራ ሐሞትን ከመጠጣት በላይ መራራ ነው። ነገር ግን እኔም ለይሁዳዎቻችን ፍቅርን እንስጥ ማለቴ መራራ ሐሞት የጠጣ ክርስቶስን እንድንመስለው ነው። 🔘10. ለሁሉም መስጠት በምትችሉት መጠን ስጡ እንጅ አትቀበሉ። ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነውና በመስጠታችሁ ብፁዓን ተብለው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገቡት ትቆጠራላችሁ። ምናልባትም የምትሰጡት ገንዘብ ባይኖራችሁ ገንዘብ ለሰጧችሁ ባለጠጎች የምትሰጡት ጸሎት ሊኖራችሁ ይገባል። ከምንጊዜውም የበለጠውን ስጦታ የተቀበልንበት ሳምንት መሆኑን እያሰባችሁ አንዳች የምትሰጡት ሥጋዊም ሆነ መንፈሳዊ ስጦታ የሌላችሁ ባዶዎች እንዳትሆኑ ተጠንቀቁ። ከሁሉ በላይ የሆነውን ስጦታ የጌታን ሥጋና ደም እነሆ ተቀብለናል።      ክርስቶስ መድኃኒነ መጽአ ወሐመ በእንቲአነ ወበሕማማቲሁ ቤዘወነ! ©️ስምዐኮነ መልአከ https://t.me/Tsegasilase ለአስተያየትዎ 👉 @Tsegasilasebot

#ሰሙነ_ሕማማት እንበለ ደዌ ወሕማም፥ እንበለ ፃማ ወድካም፥ አመ ከመ ዮም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ ለብርሃነ ትንሣኤሁ እግዚአብሔር በፍስሓ ወበሰላም! ያለ ደዌና ያለ ሕማም፥ ያለ ፃማና ያለ ድካም እግዚአብሔር ለትንሣኤው ብርሃን እንደ ዛሬ ቀን በደስታና በፍቅር በአንድነት ያድርሰን፤ ያድርሳችሁ!

#ሆሳዕና_በአርያም “አቤቱ እባክህ አሁን አድን፥ አቤቱ እባክህ አሁን አቅና፥ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው፡፡” (መዝ. 117፥25)
+2
#ሆሳዕና_በአርያምአቤቱ እባክህ አሁን አድን፥ አቤቱ እባክህ አሁን አቅና፥ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው፡፡” (መዝ. 117፥25)

0064835110101 አሐዱ ባንክ
+1
0064835110101 አሐዱ ባንክ

#ከስንክሳር_ገጾች - መጋቢት 29 በዓለ ጽንሰት ይህች ቀን ለቤተ ክርስቲያን በእጅጉ ልዩ ናት። በዓመቱ ከሚከበሩ በዓላትም አንደኛውን ሥፍራ ትይዛለች። በዚህ ዕለት አምላካችን እግዚአብሔር:- 1. ሰማይና ምድርን ፈጠረ። (ዘፍ. 1፥1) 2. በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት በድንግል ማርያም ማኅፀን አደረ (ተጸነሰ)። በዓሉም በዓለ ትስብእት ይባላል። አምላክ ሰው፥ ሰው አምላክ የሆነበት ማለት ነው። (ሉቃ. 1፥26) 3. የክብር ባለቤት መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ። (ማቴ. 28፥1፤ ማር. 16፥1፤ ሉቃ. 24፥1፤ ዮሐ. 20፥1) 4. ጌታችን ዳግመኛ ለፍርድ በዚሕች ቀን ይመጣል። (ማቴ. 24፥1) በነዚህ ታላላቅና ድርብርብ በዓላት ምክንያት ቀኑ ርዕሰ በዓላት (የበዓላት ራስ)፥ በኩረ በዓላት እየተባለም ይጠራል። ቸሩ እግዚአብሔር ዓለምን ከመፍጠሩ፥ ከጽንሰቱ፥ ልደቱና ትንሣኤው በረከትን ይክፈለን። በጌትነቱም ሲመጣ በርሕራሔው ያስበን።
መጋቢት 29 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ በዓላት
1. ጥንተ ዕለተ ፍጥረት (ዓለም የተፈጠረችበት) 2. በዓለ ትስብእት (የጌታችን ጽንሰቱ) 3. ጥንተ በዓለ ትንሣኤ 4. ዳግም ምጽዐት 5. ቅድስት ማርያም መግደላዊት 6. ቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያ 7. ቅዱሳት አንስት (ትንሣኤውን የሰበኩ) 8. ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ (ጽንሰታ) 9. አብርሃ ወአጽብሐ (ጽንሰታቸው) 10. ቅዱስ ኢያሱ ነቢይ (ጽንሰቱ) 11. ቅዱስ ላሊበላ (ጽንሰቱ) 12. አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (ጽንሰታቸው)
ወርኃዊ በዓላት
1. የፈጣሪያችንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት 2. ቅድስት አርሴማ ድንግል 3. ቅዱስ ጴጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት 4. ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ 5. ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ (ጻድቅና ሰማዕት)

#ኒቆዲሞስ — አይሁድን ፈርቶ በሌሊት ከጌታችን ይማር የነበረው ባዕለ ጸጋ፥ ባለ ስልጣንና የአይሁድ አለቃ - በኋላ ፍርሃቱን ጥሎ የጌታውን ሥጋ ከመስቀል አውርዶ በአዲስ መቃብር ያስቀመጠ፥ በሦስቱም
+2
#ኒቆዲሞስ — አይሁድን ፈርቶ በሌሊት ከጌታችን ይማር የነበረው ባዕለ ጸጋ፥ ባለ ስልጣንና የአይሁድ አለቃ - በኋላ ፍርሃቱን ጥሎ የጌታውን ሥጋ ከመስቀል አውርዶ በአዲስ መቃብር ያስቀመጠ፥ በሦስቱም የክርስትና ደረጃዎች (ወጣኒ፥ ማዕከላዊ፥ ፍጹማዊ) ያለፈ ክርስቲያን። “አስቀድሞ በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ መጣ። [የአርማትያሱ ዮሴፍና ኒቆዲሞስም] የኢየሱስንም ሥጋ ወስደው እንደ አይሁድ አገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር ልብስ ከፈኑት።” (ዮሐ. 19፥39-40)

ንቅረብ ለመድኃኒተ ሕይወት ✍ ኪዳን ዘኢየሱስ እንደ ጻፈው ኢየሱስ የሕይወት እንጀራ ነው፤ ኢየሱስ የሕይወት መጠጥ ነው። ለሥጋችን ምግብና ውኃ ሳንሰጥ አንድ ቀን እንኳን መቆየት የሚከብደን ኾነን ሳለ ነፍሳችንን ለምን እናስርባለን? ለምንስ እናስጠማለን? የክርስቶስ ሥጋና ደም ለሥጋችን፥ ለነፍሳችን፥ ለመንፈሳችን ቅድስና እና ሕይወት የተሰጠ ዘለዓለማዊ ምግብ ነው። ምነው እኛ ግን መራባችንን ያላወቅን ረሃብተኞች ኾንን? ለምንስ የሕይወት መድኃኒት ከኾነው ጌታ ራቅን? ዳዊት በመዝሙር ቃል “ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ ነፍሴም ወደ አንተ ትናፍቃለች” እያለ የነፍሱን ጥም ሊያረካለት ወደ ሚችለው ጌታ ያማትራል፤ ለነፍስ ሕይወት የሚኾነውን ውኃ ሊሰጥ የሚችለው ጌታ ብቻ መኾኑን ያውቃልና። እኛ ግን ነፍሳችን ሕይወትን ናፍቃ ተጠምታ ሳለ ወደ ሕይወት መድኃኒት ላለመቅረብ ምክንያት እንደረድራለን፤ ‛መጀመሪያ ሕይወት ይኑረኝ፥ ኃጢአትን ላቁም’ እንላለን። የሕይወትን መድኃኒት ሳንቀበል በራሳችን ሕይወት የለንም፤ ለኃጢአት ሥርየት የተሰጠውን፥ ኃጢአትን የሚያስተወውን #መድኃኒት ሳንቀበል ከኃጢአት ልንላቀቅ ከቶ አንችልም! ክርስቲያኖች ሆይ፥ በነፍሳችን አንቀልድ። የያዝነው ሕይወት ነው። በነፍሳችን ላይ ቁማር አንጫወት ነፍሳችን ከእኛ ሳትወሰድ በፊት “ወደ ሕይወት መድኃኒት እንቅረብ፤ ጸጋ ኾኖ የተሰጠንን ቅድሳት (ሥጋውና ደሙን) በእግዚአብሔር ጥበብ እንቀበል።” (ቅዳሴ እግዚእ)

#ከስንክሳር_ገጾች አንድ ቅዱስ - መጋቢት 27 ታላቁ ቅዱስ መቃርስ ቅዱስ መቃርስ የ5ኛው መቶ ክ/ዘመን ሰው ሲሆን የቅዱስ ቄርሎስና የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ተከታይ ነው። ከሕይወቱ ማማርና ከቅድስናው መሥመር የተነሳ አበው አመስግነውት አይጠግቡም። ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት “ጻድቅ እንደ ዘንባባ ያፈራል” እንዳለው። (መዝ. 91) ዳግመኛ "ወይከውን ከመ ዕጽ እንተ ትክልት ኀበ ሙሐዘ ማይ" (መዝ. 1፥3) እንዳለው ቅዱስ መቃርስ እጅግ ብዙ ትሩፋቶችን አፍርቷል። ከሁሉ አስቀድሞ በበረሐ ኗሪ ከሆነበት ቀን ጀምሮ ስለ ጌታ ፍቅር እንባው እንደ ዥረት እየፈሰሰ። ራሱን በብረት ዘንግ ይመታ ነበር። ቃው በምትባል ሃገር ዻዻስ ሆኖ በተሾመ ጊዜም ተጋድሎውን አልቀነሰም። ዻዻስ ቢሆንም የሚለብሰው የበርሃዋን ደበሎ ነው። ከብቅዓቱ የተነሳ የሕዝቡ ኃጢአት በግንባራቸው ላይ ተጽፎ እየታየው ስለ ወገኖቹ ያለቅስ ነበረ። በቤተ መቅደስ ውስጥ ቆሞ አንጀቱ ቅጥል እስኪል ድረስም ያለቅስ ነበር። ሁልጊዜ ሲቀድስ ጌታችንን ከመላእክቱ ጋር ያየው ነበር። አንድ ቀንም ጌታ ቅዱስ መቃርስን “ዻዻሱ ሆይ ሕዝቡን ገስጻቸው። ብትገስጻቸውና ባይሰሙህ እዳው በእነርሱ ላይ ነው” አለው። ቅዱስ መቃርስም ሕዝቡ ከኃጢአታቸው ይመለሱ ዘንድ ይመክራቸው፥ ይለምንላቸውም ነበር። ከዚህ ሁሉ በኋላ በጉባኤ ኬልቄዶን (ጉባኤ አብዳን) 636 ዻዻሳት ንጉሡን ፈርተው ሃይማኖታቸውን ሲክዱ ቅዱሳኑ ዲዮስቆሮስና መቃርስ “ተዋሐዶን አንክድም” በማለታቸው ዘበቱባቸው። ብዙ አሰቃይተውም ወደ ጋግራ ደሴት አሳደዷቸው። ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ጋግራ ውስጥ ሲሞት ቅዱስ መቃርስ ወደ እስክንድርያ ተመልሶ ሕዝቡን ሲመክር ያዙት። ከመሬት ላይ ጥለውም እየደጋገሙ ኩላሊቱን ረገጡት። ከመከራው ብዛትም በዚህች ቀን ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ። ቅዱሱ ሙታንን ማስነሳትን ጨምሮ ብዙ ተአምራትን ሠርቷል። መድኃኔ ዓለም ከወዳጆቹ ጸጋ ክብርን ያድለን።
መጋቢት 27 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1. ቅዱስ ዮሐንስ (ፍቁረ እግዚእ) 2. ቅዱሳት አንስት (ከእግረ መስቀሉ ያልተለዩ) 3. ቅዱሳን ባልንጀሮች (በጌታ ስቅለት ጊዜ ከሞት የተነሱ) 4. ቅዱሳን ዮሴፍና ኒቆዲሞስ 5. ታላቁ ቅዱስ መቃርስ (የመነኮሳት አለቃ - ዕለተ ዕረፍቱ ነው።) 6. ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት (የኢትዮዽያ ንጉሥ) 7. ቅዱስ ዕፀ መስቀል 
ወርኃዊ በዓላት
1. አቡነ መብዐ ፅዮን ጻድቅ 2. ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት 3. ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ 4. ቅዱስ ቢፋሞን ጻድቅና ሰማዕት፥