fa
Feedback
ተዋሕዶን እንወቅ።

ተዋሕዶን እንወቅ።

رفتن به کانال در Telegram

አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ ሥረይ ለነ ኲሎ አበሳነ ኢታብአነ ውስተ መንሱት እግዚኦ አድኅነነ እምዕለት እኪት ወባልሐነ ውስተ መንሡት። ✝በከመ ምሕረትከ አምላክነ ወአኮ በከመ አበሳነ✝ የየእለቱን ስንክሳር፥ ውዳሴ ማርያም፥ ጸሎተ አርጋኖን፥ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን፥ የጻድቃንና የሰማዕታትን ገድል፥ የተለያዩ መንፈሳዊ ጥያቄዎችን፥ የድሮ እና አዳዲስ መዝሙራትን የሚያገኙበት ቻናል ነው። ይቀላቀሉን።

نمایش بیشتر
Buy Ad
2 369
مشترکین
-124 ساعت
-117 روز
+330 روز
آرشیو پست ها
ዛሬ ማታ ኹለት ሰዓት ከሀያ እንዳትቀሩ! @SSC_KIdme_Gibi_Gubae @SSC_KIdme_Gibi_Gubae

ወደ ቤተክርስቲያን ስትገቡ ምን እያላችሁ ትፀልያላችሁ? እኔ የምለውን ልንገራችሁ ድሮ የሆነ መፅሀፍ ላይ አይቼ ነበር "...ወአንሰ እበዉዕ ቤተከ በምህረትከ ወእሰግድ ውስተ ፅርሐ መቅደስከ በፈሪሆትከ
ወደ ቤተክርስቲያን ስትገቡ ምን እያላችሁ ትፀልያላችሁ? እኔ የምለውን ልንገራችሁ ድሮ የሆነ መፅሀፍ ላይ አይቼ ነበር "...ወአንሰ እበዉዕ ቤተከ በምህረትከ ወእሰግድ ውስተ ፅርሐ መቅደስከ በፈሪሆትከ..." ማለትም “ እኔ ግን በምሕረትህ ብዛት ወደ ቤትህ እገባለሁ፤ አንተን በመፍራት ወደ ቅድስናህ መቅደስ እሰግዳለሁ። ”   መዝሙር 5፥7 ከዛ ደግሞ ውስጥ ገብቼ በመሰዊያው ፊት ስሰግድ እንዲህ እላለሁ "...እስግድ ለከ ክርስቶስ ምስለ አቡከ ሄር ሰማያዊ ወመንፈስከ ቅዱስ ማህየዊ እስመ መፃዕሰ ወአድኀንከኒ..." ማለትም "...ክርስቶስ ሆይ ቸር ከሆነው አባትህ ጋር አዳኝ ከሆነው መንፈስህ ጋር እስግድልሀለሁ መጥተህ አድህነኛልና..." @amlake_birhan

Repost from Dn Eyuel Habtamu
ይህ የብዙ ወጣቶች ጥያቄ ነው ። እግዚአብሔር ከረዳን ዛሬ ማታ 3 : 00 ላይ እንገናኝ ! ማንም እንዳይቀር ... ለ ሰው share እናድርግ !
ይህ የብዙ ወጣቶች ጥያቄ ነው ። እግዚአብሔር ከረዳን ዛሬ ማታ 3 : 00 ላይ እንገናኝ ! ማንም እንዳይቀር ... ለ ሰው share እናድርግ !

«በሕይወትህ ዕድሜ ሁሉ ማንም አይቋቋምህም፤ ከሙሴ ጋር እንደሆንኩ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፤ አልጥልህም፤ አልተውህም።» (መጽሐፈ ኢያሱ 1፥5) ወንድምና እኅቶቻችን ሆይ እግዚአብሔር በሥራችሁ ሁሉ ይቅደ
«በሕይወትህ ዕድሜ ሁሉ ማንም አይቋቋምህም፤ ከሙሴ ጋር እንደሆንኩ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፤ አልጥልህም፤ አልተውህም።» (መጽሐፈ ኢያሱ 1፥5)
ወንድምና እኅቶቻችን ሆይ እግዚአብሔር በሥራችሁ ሁሉ ይቅደም። የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም፥ የቅዱሳን መላዕክት፥ የጻድቃን የሰማዕታት፥ የደናግል የመነኮሳት ምልጃና ጸሎት አይለያችሁ። ይህ ቀን አልፎ ለምርቃታችሁ እግዚአብሔር በሰላም ያድርሰን። ሳትጨናነቁ እግዚአብሔርን አስቀድማችኹ የተቻላችኹን ሥሩ። ጭንቀት ይባስ የምታውቁትን ያስጠፋችኹ ይኾናል እንጂ ምንም አይረባችኹም። #መልካም_ፈተና_ይኹንላችኹ

የዚኽን ቀጣይ ክፍል ከሰሞኑ እለቃለኹ.. እያጋራችኹ ጠብቁኝ።

እንዴት እሱ እንዲኽ ያደርጋል ብለኽ ከፈረድክ፥ እንዴት እንዲኽ እንዳረገ እስኪ ገባኽ ትፈተናለኽ!” እንዲኽ ተብሎ በመጽሐፍ ተጽፏልና፦
እንዳይፈረድባችሁ #አትፍረዱ፤ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና፥ በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ #ይሰፈርባችኋል። አትኰንኑ አትኰነኑምም። ይቅር በሉ ይቅርም ትባላላችሁ።

Repost from Dn Eyuel Habtamu
ሰላም እንዴት አመሻችሁ ተወዳጆች ዛሬ ረፈድ አድርገን 3 : 30 እንጀምራለን ። የመጨረሻ ቀን ስለሆነ ሰብሰብ በሉ ☺️

🫴...እንድንቀበለው [እንድንቆርብ] መጥቶ ስንቴ 'እስመ ሃያል' እያልን መለስነው፣ ይቀበሉኛል ብሎ ወጥቶ ስንት ዘመን ሙሉ ሳንቀበለው መለስነው 🤲...ሳንቀበለው ለመለስነው ዘመን ይቅር ይበለን 🤲
"ሚስጥረ ቁርባን” ከ ዲ/ን እያሱ መስፍን (መራኁት)ጋር ቅዳሜ ምሽት 3 ሰአት ላይ https://t.me/yetewahdotmhrt

Repost from ዛ አንቀጽ
ዛሬ ዕለተ አርብ ነው !! ጾማችን ተመልሳልናለች እንዳስለመድን ዕለተ አርብን የቸሩ መድኃኔዓለምን ሕማሙን ፤ ስለእኛ የተቀበለውን ሞት እያሰብን በጾም እንውላለን ፥ ፍቅሩን እንዘክራለን!! ዛ አንቀጽ
ዛሬ ዕለተ አርብ ነው !! ጾማችን ተመልሳልናለች እንዳስለመድን ዕለተ አርብን የቸሩ መድኃኔዓለምን ሕማሙን ፤ ስለእኛ የተቀበለውን ሞት እያሰብን በጾም እንውላለን ፥ ፍቅሩን እንዘክራለን!! ዛ አንቀጽ የእግዚአብሔር ደጅ ናት ላለፉት ወራት በነጻ መድኃኔዓለም ክርስቶስን ለሚሻ ልብ ሁሉ የሚያጽናኑ ፥ የሚያረጋጉ ፥ የሚያንጹና የጌታን ውለታ የሚያስታውሱ አገልግሎቶችን ሲያኬያሂድ ቆይቷል። በተለይም ዕለተ አርብን በልዩነት እንደ አባታችን መባዓ ጽዮን በጾምና በበጎ ቸርነት ስንዘክር ቆይተናል እንደ ጌታ ፍቃድም በተሰጠን መክሊትም እንደ ጻድቁ አባታችን መባዓ ጽዮን ቸሩ መድኃኔዓለምን ልናገልግል አስበናል። ጾም የነፍስን ቁስል ትፈውሳለችና ከእንግዲህ ዕለተ አርብን ወገባችንን ጠበቅ አርገን ታጥቀን እየጾምን ፥ የምግባችንን ወጪ ለተቸገሩና ለሚያስፈልጋቸው እርዳታ እየሰጠን በክርስቶስ አንድ መሆናችንን እንሰብካለን። ጌታ ሆይ ከፍቅርህ እንድንደርስ እርዳን ፥ አንተን ደስ ከማያሰን ነገር ሁሉ እንድንለይ መለየቱን ስጠን የበረታን ውለን አክፍለን ፥ ያልሆነልን ፀሐይ እስክትጠልቅ ቆይተን ፥ አልያ እስከ 11 ፥ ያልቻለ እስከ 9 ፥ የታመመ እስከ 6 ጹመን የምንለምንህን ልመናችንን አንተ ስማን ፥ በእኛ ላይ ያለህን ቅዱስ ፍቃድህን ግለጽልን !! አንተ በመጽሐፍ መከራዬን በዕለተ አርብ ያሰበ እጣው ክፍሉ ከእኔ ጋር ነው ብለሃልና ። “እግዚአብሔርን በመፍራት ተገዙለት ለእርሱ መገዛትም ደስ ያሰኛችሁ። እግዚአብሔር ቸር ምሕረቱም ለዘላለም ፣ እውነቱም ለልጅ ልጅ ነው ። እኛስ ሕዝቡ የመሰማሪያው በጎች ነን ፥ ወደ ደጁ በመገዛት፣ ወደ አደባባዮችም በምስጋና ግቡ ፤ ጾምን እንጹም፤ ጓደኞቻችንን እናፍቅር፤ እርስ በርሳችንም እንፋቀር" ቅዱስ ያሬድ

Repost from Dn Eyuel Habtamu
ነገ ማታ በዛ ብለን እንገናኝ ! እግዚአብሔር ሰላም ያገናኘን 🙏
ነገ ማታ በዛ ብለን እንገናኝ ! እግዚአብሔር ሰላም ያገናኘን 🙏

በዚኽ ቪዲዮ ለመመለስ ከተሞከሩ ጥያቄዎች መሐል 00:16 እግዚአብሔር ኃጢአቴን ይቅር ይለኝ ይኾን? 00:43 ንስሐ የገባኹበትን ኃጢአት ደግሜ ብሠራውስ? 00:58 “ዕድሜዬ ለንስሐ አልደረሰም” 01:11 “ነገ ንስሐ እገባለኹ” 01:26 የንስሐ አባቴ ቢናገሩብኝስ? 01:52 ንስሐ ከገባኹ በኋላስ ማድረግ ያለብኝ ሌላ ነገር አለ? ❝መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና፥ ንስሐ ግቡ!❞ (ማቴ. 4፥17)

Repost from Dn Eyuel Habtamu
ነገ ማታ 3 : 00 ጌታ ቢወድ እና ቢፈቅድ ብንኖርም ! ቻናሉን እናሳድገው ወገን ይሄ ትልቅ ነገር ነው ። እንዴት ነው ሀሳባችሁ ? comment 👇
ነገ ማታ 3 : 00 ጌታ ቢወድ እና ቢፈቅድ ብንኖርም ! ቻናሉን እናሳድገው ወገን ይሄ ትልቅ ነገር ነው ። እንዴት ነው ሀሳባችሁ ? comment 👇

አንድ ወንድሜ በውስጥ መስመር የላከልኝ ነው.. ከተቻላችኹ በገንዘብ ካልኾነላችኹ በጸሎትና በማጋራት እንተባበረው። ሰላም ወንድሜ እንደምን አለህ ዲ/ን ዓምደብርሃን አባላለሁ የወሎ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ አመት ተማሪ ነኝ ወንድም እባክህን እርዳታህን እፈልጋለሁ በቻልከው አቅም አግዘኝ ወንድሜ እባክህን ትልቅ ችግር ውስጥ ገብቼ ነው ነገሩ እንዴት መሰለህ ከጓደኞች ጋር ስራ ለመስራት ብር ከልጆች ተበድሬ ስራ እጀምራለሁ ነገር ግን ባልጠበቁት መልኩ አብሬያቸው የምንሰራ ልጆች ካዱኝ አሁን ደሞ ብር የተበደርኳቸው ልጆች አምጣ እያሉኝ ነው ለቤተሰብ እንዳልደውል ባሁን ሰአት እናቴ ያለ አባት ሁለት ልጆችን እያሳደገች ለኔ በወር 1000 2000 ብር እራሱ እምትልክልኝ ተቸግራ ነው በዚህ ሰአት ደሞ ከጊቢ መውጫ ሰአት ስለሆነ ለትራንስፓርት እየተባለ ብዙ ወጪ ይበዛል የተበደርኩት ብር ደሞ በጣም ብዙ ነው ስልኬን እራሱ አሽጦኛል ወንድም አዛኜን እየዋሸሁህ አይደለም በምትችለው አቅም እርዳኝ በጣም ጭንቀት ውስጥ ነኝ ስርቆት እራሱ አስቤ ዲያቆን ሆኜ ህሊናዬን ሸጬ ይህን ማድረግ ከባድ ነው እባክህን ወንድሜ በምታምነው አምላክ  የምታውቃቸውን ሰዎች አስተባብረህ የሆነ ነገር እርዱኝ በፈጣሪ አሁን ከጊቢ ለመውጣት አንድ ሳምንት ነው የቀረን እባክህን የምጠይቀው ባጣ ነው ወደ አንተ የመጣሁት እባክህን ወንድሜ ተረዳኝ ወንድሜ የምደግመው [ውዳሴ ማርያም] [ኪዳን] መርገም ይሁንብኝ እየዋሸሁህ አይደለም ከቻልክ በዚህ ደውልልኝ 0965125075  ዓምደብርሃን ከተማ አመሰግናለሁ🙏

ለዚኽም ቻናል መጠቀም ትችላላችኹ🤗

Repost from አረቦን
A reflection on logos from Emmaus. https://youtu.be/UUMefAlbwCU?si=LrLk9QvAwx_HupMH

ፊልጶስ ሳይጠራኝ ገና ሳልቆም ፊቱ ከበለስ ስር ሳለው ያውቀኛል ከጥንቱ መካሪ አያሻውም ኹሉን ያውቃልና ከሳሽ ኾይ ተመለስ ድንጋዩን ጣልና ኦ ቅዱስ #ናትናኤል ሰአል በእንቲአነ❤️ ዛሬ በዓለ ዕረፍቱ ነው.. በረከቱና ምልጃው አይለየን!