7 050
مشترکین
-124 ساعت
-267 روز
-21830 روز
آرشیو پست ها
7 048
''ክርስቶስ ተንስአ እሙታን ▸ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን ፤ አሰሮ ለሰይጣን አግአዞ ለአዳም ፤ ሰላም ▸ እምይእዜሰ ፤ ኮነ ▸ ፍስሐ ወሰላም''
''ክርስቶስ በታላቅ በኃይልና ስልጣን ከሙታን ተነሳ ፤ ሰይጣንን አሰረው አዳምንም ነጻ አወጣው ፤ ስለዚህም ከእንግዲህ ወዲህ ፍፁም ሰላም እና ደስታ ሆነ''
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ የቻናላችን ቤተሰቦች በሙሉ ፥ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ።
በዓሉ የሰላም የፍቅር እና የአንድነት በዓል ይሁንልን አሜን።
7 048
🕋ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ።
በዓሉ የሰላም ፥ የመተሳሰብ እና የፍቅር እንዲሆን እንመኛለን።🕌
EID MUBARIK - ኢድ ሙባረክ
7 048
ሰበር ዜና‼️
የኢራኑ ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ካሜኔኢ ተገደሉ!
በእስራኤል መገናኛ ብዙኃን ላይ የወጡ ዘገባዎችን ዋቢ በማድረግ ሮይተርስ እንደዘገበው፣ የኢራን ከፍተኛው መሪ አያቶላህ አሊ ካሜኔኢ ህይወት አልፏል።
የሪፖርቱ ምንጮች እንዳመለከቱት፣ የካሜኔኢ አስከሬን መገኘቱ ተነግሯል።
ይህ ዘገባ በአካባቢው ያለውን የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ወደ ከፍተኛ ደረጃ የሚያደርሰው ተብሎ ይጠበቃል።
Via BBC , Aljazeera , Reuters
7 048
መድፈኞቹ ዶሮዋን በገዛ ሜዳዋና በደጋፊዎቿ ፊት 'እያጣጣሙ ሲበሏት አመሹ።
እነሆ የሰሜን ለንደን ሰማይ ስር በቀይና ነጭ ቀለም አሸብርቋል።
አዎ ዛሬ ምሽት የለንደን ንጉስ ማንም ሳይሆን አርሰናል መሆኑን በድጋሚ አስመስክሯል።
ብዙዎች 'አርሰናል ዛሬ ይንሸራተታል፣ የዋንጫው ግስጋሴው እዚህ ጋር ያከትማል' ብለው ቢጠብቁም፤የሚካኤል አርቴታ ልጆች ግን ሜዳው ላይ የታዩት እንደ አንበሳ ተቆጥተው ነበር።
አረሰሰናሎች ቶትነሃምን በገዛ ጎጆው ድባቅ በመምታት፣ ለሲቲና ለሌሎች ተፎካካሪዎቻቸው ግልጽ መልእክት አስተላልፈዋል
ይህ ድል ለአርሰናል ደጋፊዎች ከሶስት ነጥብ በላይ ነ
7 048
ረመዷን ነገ ይጀምራል።
በሳውዲ አረቢያ የረመዳን ወር መግቢያ ጨረቃ በመታየቷ የታላቁና ቅዱሱ የረመዳን ወር ጾም ነገ ረቡዕ ይጀምራል።
7 048
አሜን በሉ ልመርቃችሁ🙏
የጾሙ መጀመሪያ "ዘወረደ" ተብሎ እንደ ተጀመረ፣ ማጠቃለያውም በዓለ ሆሳዕናን በድል አድራጊነት እንድንቀበል፣ ከዚያም የትንሣኤውን ብርሃን ለማየት ፈጣሪ ያብቃን።
አምላካችን እግዚአብሔር ይህንን የተቀደሰ የጾም ወቅት የበረከት፣ የፈውስ እና የኃጢአት ማስተሰሪያ ያድርግልን።
በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ፣ ዐቢይ ጾም የሆድን መታቀብ ብቻ ሳይሆን የነፍስን መታደስ የሚጎናጸፉበት የታላቅ ምስጢር ወቅት ነው።
ይህ ጾም፣ የሰው ልጅ በኃጢአት ጨለማ ውስጥ ወድቆ ከፈጣሪው ተለይቶ በነበረበት ዘመን፣ አምላክ ፍጥረቱን ፍለጋ ያደረገውን የፍቅር ጉዞ የምናስብበት የታሪክ መዝገብ ነው።
ከገነት የተሰደደውን አዳም እንባ ለማበስ፣ የአለማት ጌታ ዙፋኑን ትቶ በምድር የተንከራተተበት፣ የተራበበትና በመጨረሻም በመስቀል ላይ ደሙን ያፈሰሰበት የመስዋዕትነት ምስጢር በዚህ ጾም ውስጥ ተቀብሯል።
በነዚህ 55 ቀናት ውስጥ፣ በአካልም በመንፈስም በመታቀብ፣ በጸሎት እና በምጽዋት በመጽናት፣ ከፈጣሪ ጋር ያለንን ግንኙነት እናድሳለን።
ፈጣሪ ጾሙን የሰላም፣ የፍቅር እና የአንድነት ያድርግልን
እንኳን ለታላቁ የዐቢይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ!
7 048
መረጃ‼️
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና መቶ በመቶ በበይነ መረብ ይሰጣል - ትምህርት ሚኒስቴር
በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ2018 የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና መቶ በመቶ በበይነ መረብ ለመስጠት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የግማሽ ዓመት አፈፃፀም መድረክ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በዚህ ዓመት የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና መቶ በመቶ በበይነ መረብ እንደሚሰጥ ገልፀዋል።
7 048
ጠ/ሩ ስለ ህዳሴ ግድቡ እውነታ በይፋ ተናግረዋል።
ለህዳሴው ግድብ አንድ ብር ብድርም ሆነ እርዳታ አልተቀበልንም ሲሉ ተናግረዋል።
በዚህም የትራምፕ አሉባልታ ውሸት መሆኑ ታውቋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ዛሬ በፓርላማ እንደተናገሩት ፣ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የፋይናንስ ምንጭን በተመለከተ ለዓመታት ሲነሱ ለነበሩ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
ግድቡ ከአንድም የውጭ ሀገር ወይም ተቋም "አንድ ብር" እርዳታ ሳይጠየቅበትና ሳይወሰድበት፣ በኢትዮጵያ መንግስት እና በህዝቡ የላብ ጠብታ ብቻ እዚህ ደረጃ መድረሱን ገልጸዋል።
7 048
ላስታውሳቹ እንዳትረሱ 5ሺ ብር ለመቀጣት ምን ያህል ዝግጁ ናቹ።
ዛሬ ገበያ ከመውጣታችሁ በፊት ይሄን ፅሁፍ ካላያችሁ ኪሳችሁ ባዶ ሊቀር ይችላል!
ከ2 ሺህ እስከ 5 ሺህ ብር የሚደርስ ቅጣት ዛሬ ተጀምሯል።
ምን እንደተፈጠረ እነግራችኋለሁ፣ እስከመጨረሻው አድምጡኝ።
"የፊስታል አጠቃቀምን ለመቀነስ የወጣውን አዲስ መመሪያ ተከትሎ፣ ከዛሬ ጀምሮ ማንኛውም ሰው ፊስታል ይዞ ሲንቀሳቀስ ከተገኘ ከፍተኛ የገንዘብ ቅጣት ይጠብቀዋል።
መንግስት አካባቢያችንን ከፕላስቲክ ብክለት ለመጠበቅ ጥብቅ ቁጥጥር ጀምሯል።
ስለዚህ ዛሬ ወደ ገበያም ሆነ ወደ ሱቅ ሲሄዱ ፊስታል እንዳትይዙ ተጠንቀቁ፤ ራሳችሁን ከማያስፈልግ ቅጣት ጠብቁ መልዕክቴ ነው።
7 048
ማሳሰቢያ‼️
ከነገ ጀምሮ የፕላስቲክ ፌስታል መጠቀም በህግ ያስቀጣል!
የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ባወጣው መመሪያ መሰረት፣ ከነገ ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ማንኛውንም አይነት ቀጭን የፕላስቲክ ፌስታሎችን መጠቀም፣ ማምረትም ሆነ ማከፋፈል በጥብቅ ተከልክሏል። 🚫
⚠️ ማወቅ ያለባችሁ የቅጣት መጠኖች፡
በእጅ ይዞ ለተገኘ ግለሰብ፡ ከ2,000 እስከ 5,000 ብር ቅጣት። 💸
ለአምራቾች እና ለአከፋፋዮች፡ እስከ
200,000 ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት እና እስከ 5 ዓመት የሚደርስ እስራት። ⚖️
💡 መፍትሄው ምንድነው?
ከነገ ጀምሮ ለገበያም ሆነ ለማንኛውም ጉዳይ በፌስታል ፋንታ የጨርቅ ከረጢቶችን ወይም እንደገና ጥቅም ላይ የሚውሉ ቦርሳዎችን እንዲጠቀሙ ይመከራል።
ወዳጅ ዘመድዎ ሳይታወቅበት ተቀጥቶ እንዳይቸገር አሁኑኑ Share በማድረግ መረጃው እንዲደርሳቸው ያድርጉ! 🙏
ለበለጠ መረጃና አዳዲስ ዜናዎች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ፡
7 048
ቲክቶከሩ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰማ‼️
ሴት እህቶችን ወደ መዝናኛ ቦታዎች በመውሰድ፣በሚጠጡት መጠጥ ውስጥ አደንዛዥ ዕጽ በመጨመር፣
.ያልተገባ ድርጊት እንዲፈጽሙ በማድረግና በምስል በመቅረጽ፣
ምስሉን በማህበራዊ ሚዲያ በማሰራጨት ወንጀል እንደተጠረጠረ ፖሊስ አስታውቋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ከሀገሪቱ ባህልና እሴት ውጪ የሆኑ ተግባራትን ሲፈጽም የነበረውን ንጉሰ ዳዊት (ግብዳው) የተባለ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።
7 048
ሴኔጋል የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ሆነች‼️
በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አስተናጋጇን ሞሮኮ በማሸነፍ ሴኔጋል ዋንጫውን አንስታለች።
ምሽት 4 ሰዓት ላይ በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ ሴኔጋል በተጨማሪ ሰዓት ባስቆጠረችው ብቸኛ ግብ የዋንጫ ባለቤት ሆናለች።
የሴኔጋልን የድል ግብ ፓፔ ጉዬ ከመረብ አሳርፏል።
7 048
ተፈፀመ‼️
የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ‼️
በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ ያለውና በሁለገብ የፈጠራ ብቃቱ የሚታወቀው አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ፣ ዛሬ ጥር 10 ቀን 2018 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በክብር አርፏል።
7 048
አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ባደረበት ህመም በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ኢቢኤስ ቴሌቪዥን ገለጸ።
አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ በቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢነት፣ በተዋናይነትና በሌሎች የጥበብ ስራዎቹ በኪነ ጥበቡ ቤተሰብ ዘንድ ይታወቃል።
ሁለገቡ አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ለበርካታ ዓመታት በኢቢኤስ ቴሌቪዥን የሚተላለፈውን የቤተሰብ ጨዋታ ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ በመሆን እያገለገለ ነበር።
አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ በፊልም እና በቴአትር ስራዎቹ እጅግ ተወዳጅ የነበረ ሲሆን፤ ሲቲ ቦይስ፣ ሳልነግራት፣ ያንቺው ሌባ 2፣ ኤፍቢአይ፣ ሚስተር ኤክስ፣ ቾምቤ እና ሌሎችም ድንቅ ብቃቱን ያሳየባቸው ፊልሞች ናቸው።
ፍሬሽ ማን ከህዝብ ጋር ያስተዋወቀው የቴአትር ስራው ነው።
አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ባለትዳርና የ3 ልጆች አባት ነበር።
7 048
ፈርኦኖቹ ተደረማመሱ።
የአንፊልድን ሜዳ ያንቀጠቀጡ የሞ ሳላ እግሮች በሞሮኮ ምድር ሳይጠበቁ ዝለዋል።
የአባይን ውሀ እየጠጡ ያደጉት ፈርኦኖቹ ግብፆች በሴኔጋል የቁርጥ ቀን ልጅ በጥቁር አልማዙ በ sedio mane ብትንትናቸው ወቷል።
ከግማሽ ፍፃሜው የካይሮ ትኬታቸው የቆረጡት ፈርኦኖቹ የውድድሩ አሳዛኝ ተሸናፊ ሆነዋል።
የማኔው ሴኔጋል ለፍፃሜው ጨዋታ ከወዲሁ ትኬታቸው ቆርጠዋል ማለፋቸውም በይፋ አረጋግጠዋል።
ሴኔጋል ሀገር በደስታ እየተናወጠች ትገኛለች።
7 048
ሰበር አስደሳች መረጃ ‼️
ትብብራቹ አንድነታቹ በመጨረሻም ፍሬ አፍርትዋል።
Popular electronics በይፋ 1 million ገብተዋል።
በታድያ ብዙሀኑ ማህበረሰብ ቻለንጁን ላስጀመረው አዶናይ ምስጋናቸው እያቀረቡ ሲሆን።
ይህ እንዲሳካ ለተባበራቹ ሁላቹም ታላቅ ምስጋና ይገባችኋል።
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
