Yederaw - የደራው
የደራው መጽሔት "ፀሐይ አትጠልቅም!" visit | www.yederaw.com ያግኙን @YederawSupport
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام Yederaw - የደራው
کانال Yederaw - የደራው (@yederaw) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 17 227 مشترک است و جایگاه 4 234 را در دسته موسیقی و رتبه 1 999 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 17 227 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 04 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -663 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -40 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 4.39% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 1.97% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 757 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 340 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 3 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“የደራው መጽሔት "ፀሐይ አትጠልቅም!"
visit | www.yederaw.com
ያግኙን @YederawSupport”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 05 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته موسیقی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 04 سپتامبر | 0 | |||
| 03 سپتامبر | 0 | |||
| 02 سپتامبر | 0 | |||
| 01 سپتامبر | 0 |
| 2 | "My Seed" የተሰኘ የሞባይል ስልክ መተግበሪያ ይፋ ተደረገ!
በማህበራዊ ሚዲያ «ቲቸር ዳኒ» በሚል ስሙ የሚታወቀው መምህር ዳኛቸው ሻምበል፣ ተማሪዎች ባሉበት ቦታ ሆነው በስልካቸው በቀላሉ ትምህርት የሚከታተሉበትን "My Seed" የተሰኘ አዲስ የሞባይል መተግበሪያ ይፋ ማድረጉን ገለጸ።
መተግበሪያው በተለይም ከአምስተኛ እስከ 12ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የተዘጋጀ ሲሆን በገጠርም ሆነ በከተማ የሚገኙ ተማሪዎችን በቴክኖሎጂ ታግዞ እኩል የትምህርት እድል ተጠቃሚ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ገልጿል።
በላይ የተጫነው ይህ መተግበሪያ ተማሪዎች የሀገሪቱን የትምህርት ካሪኩለም መሰረት ያደረጉ ትምህርቶችን አሰልቺ ባልሆነና ልክ እንደ ፊልም የተቃኙ ማራኪ ቪዲዮዎች አማካኝነት እንጅ በማድረግ እንዲማሩ ተደርጎ የተቃኘ ነው።
ከተለመዱት የትምህርት አይነቶች በተጨማሪ የመንፈስ ጥንካሬና አስተሳሰብን የሚያጎለብቱ የማይንደሴት ስልጠናዎችን እንዲሁም ተማሪዎች ወደፊት መሆን የሚፈልጉትን ሙያ እንደ ዶክተር ኢንጂነርና ፓይለት የመሳሰሉትን እንዲረዱ የሚያስችሉ ትምህርቶችን አካቷል።
አፕሊኬሽኑ በአሁኑ ወቅት በአማርኛ ቋንቋ አገልግሎት መስጠት የጀመረ ሲሆን ወደፊትም እያንዳንዱ ተማሪ በአፍ መፈቻ ቋንቋው እንዲማር ለማስቻል በሌሎች አራት የሀገር ውስጥ ቋንቋዎች ተደራሽ ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
አፕሊኬሽኑን ተጠቃሚ ለማድረግ በቀረበው እቅድ መሰረት ተማሪዎች በወር 399 ብር ክፍያ በመፈፀም ሁሉንም የትምህርት አይነቶች ማስታወሻዎችንና የልምምድ ጥያቄዎችን ማግኘት ይችላሉ።
በተጨማሪም በኔትወርክ ችግር ምክንያት የዳታ እጥረት እንዳይገጥማቸው ቪዲዮዎችን አንድ ጊዜ ዳውንሎድ በማድረግ ያለ ኢንተርኔት ኮኔክሽን መከታተል የሚችሉበት አሰራር የተዘረጋ ሲሆን በቅርቡም ሙሉ በሙሉ ዳታ በማይስፈልግበት መልኩ አገልግሎቱን ለማስፋፋት እየሰራ መሆኑን መምህር ዳኛቸው አስታውቋል።
ተማሪዎችን ለማበረታታትም በአመቱ መጨረሻ የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተጠቃሚዎችን በልዩ መስፈርት በመምረጥ የመኪና ሽልማት የሚያበረክት "መማር ያሸልማል" የተሰኘ ፕሮግራም ማዘጋጀቱ ተገልጿል።
| 357 |
| 3 | بدون متن... | 323 |
| 4 | ኦርቢክስ ቴክኖሎጂስ የኢትዮጵያን ከተሞች የሚያዘምኑ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ይፋ አደረገ
በኢትዮጵያ ከተሞች እየታየ ያለውን ፈጣን እድገትና የመሰረተ ልማት ስፋት ተከትሎ፣ የዜጎችን የእለት ተእለት ህይወት እና የአገልግሎት አሰጣጥን የሚያቀልሉ አዳዲስ የቴክኖሎጂ መፍትሄዎችን ይዞ መውጣቱን ኦርቢክስ ቴክኖሎጂስ አስታወቀ።
የኦርቢክስ ቴክኖሎጂስ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ስዩም ተስፋዬ እንደገለጹት፣ ድርጅታቸው እንደ ስታርትአፕ ካምፓኒ የዜጎችን እለታዊ እንግልት የሚቀንሱ እና ከተሞችን ዘመናዊ የሚያደርጉ አራት ዋና ዋና የቴክኖሎጂ አሰራሮችን አስተዋውቋል።
እንደ አቶ ስዩም ማብራሪያ፣ የመጀመሪያው የቴክኖሎጂ መፍትሄ የመኪና ማቆሚያ ወይም የፓርኪንግ ችግርን የሚያቃልል ነው። በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባም ሆነ በሌሎች ዋና ዋና ከተሞች የተገነቡ የፓርኪንግ ቦታዎች ቢኖሩም፣ አሽከርካሪዎች በቅጽበት ትክክለኛውን መረጃ ለማግኘት እንደሚቸገሩ ጠቁመዋል።
ኦርቢክስ የሰራው ስርዓት ግን የግል እና የመንግስት የፓርኪንግ ቦታዎችን ወደ አንድ ማዕከላዊ የመረጃ ቋት በማምጣት አሽከርካሪዎች ባሉበት ሆነው ክፍት ቦታዎችን በስልካቸው እንዲያዩ፣ እንዲይዙ እና ያለምንም ሰው ንክኪ በራሳቸው አገልግሎት አግኝተው እንዲወጡ ያስችላቸዋል ብለዋል።
ሌላው ሁለተኛው ስራ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የኃይል መሙያ ወይም የቻርጂንግ ስርዓትን ማዕከላዊ ማድረግ ሲሆን ኢትዮጵያ እስከ 2030 ድረስ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ወደ ስራ ለማስገባት እና በርካታ የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን ለመገንባት ባስቀመጠችው እቅድ መሰረት፣ አገልግሎቱ በተበታተነ መልኩ እንዳይሰጥ "ኦርቢክስ ኢቪ "የተሰኘ የተቀናጀ መተግበሪያ አልምቷል።
አቶ ስዩም አክለውም፣ ይህ ስርዓት ተጠቃሚዎች በአንድ መተግበሪያ ብቻ የትኛውም ቦታ የሚገኝ የኃይል መሙያ ጣቢያን እንዲጠቀሙ ከማድረጉም በላይ፣ የአገሪቱን የኢነርጂ መረጃ ደህንነት በአገር ውስጥ የመረጃ ቋት ውስጥ ጠብቆ ለማቆየት እና የመንግስት አካላት የኃይል ፍጆታውን በአንድ ማዕከል እንዲከታተሉ የሚያስችል እንደሆነ ገልጸዋል።
በሶስተኛ ደረጃ የቀረበው «አይ ሀብ» የተሰኘው የዜጎችና የመንግስት ግንኙነት ማጠናከሪያ መድረክ ሲሆን፣ ነዋሪዎች በመንገድ፣ በኤሌክትሪክ፣ በትራፊክ በድንገተኛ አደጋዎች ላይ የሚያዩአቸውን ችግሮች እና መረጃዎች በስልካቸው ለሚመለከተው የመንግስት አካል በቀጥታ እንዲያደርሱ ያደርጋል።
ስርዓቱ መረጃዎችን በየአካባቢው ክልል በመለየት እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት በመተንተን ለአስፈጻሚ አካላት የሚልክ በመሆኑ፣ ለቀረቡት ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት እና በህዝብና በመንግስት መካከል ያለውን እምነት ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
«ኢትዮ ፓርክስ» የተሰኘው አራተኛው የቴክኖሎጂ ማዕቀፍ፣ በከተሞችና ከከተሞች ውጭ ያሉ የተፈጥሮ፣ የባህል እና የቪዲዮ መዝናኛ ቦታዎችን ዲጂታላይዝ በማድረግ ለአገር ውስጥ እና ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች የሚያቀርብ ነው።
ተጠቃሚዎች የፓርኮችን መረጃ፣ የሚሰጡትን አገልግሎት እና የመግቢያ ክፍያዎችን አስቀድመው በመተግበሪያው በማጠናቀቅ የሚፈልጉትን መዝናኛ በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ።
አቶ ስዩም ተስፋዬ ሲደመድሙ፣ ኦርቢክስ ተራ መተግበሪያ ሳይሆን አጠቃላይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን የሚደግፍ እና ወደፊት ወደ ሌሎች የአፍሪካ አገራት ለማስፋፋት የታቀደ ግዙፍ የቴክኖሎጂ ምህዳር መሆኑን አብራርተዋል።
📸 ከበደ መክብብ | 330 |
| 5 | بدون متن... | 818 |
| 6 | "ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ" እስከ 30 በመቶ የሚደርስ ልዩ የበዓል ቅናሽ ይፋ አደረገ
#Ethiopia | በቀድሞ ስያሜው ያሥሚን ጀማል ኮንስትራክሽን በመባል የሚታወቀውና በግንባታው ዘርፍ አዲስ የጥራትና የፍጥነት መለኪያ ያስቀመጠው ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ መጪውን የ2019 አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ ለደንበኞቹ እስከ 30 በመቶ የሚደርስ ልዩ የበዓል ቅናሽ ማዘጋጀቱን ገልጿል።
የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ኑረዲን መሐመድ በሰጡት መግለጫ በቦሌ አትላስ ሳይት የመሬት ደጋፊ (ሾሪንግ) ሥራ መጠናቀቁን እና በካዛንቺስ ሳይት አምስት የቤዝመንት ደረጃዎች አልቀው ህንፃው ግራውንድ ወለል ላይ መድረሱን ተክቶ አዳዲስ የመኖሪያና የንግድ ፕሮጀክቶችን ለገበያ ማቅረባቸውን አሳውቀዋል።
በዚህም መሠረት ከ55 ካሬ ሜትር ስቱዲዮ እስከ 165 ካሬ ሜትር ባለ 3 መኝታ አፓርትመንቶች እንዲሁም የንግድ ሱቆች በካሬ ሜትር ከብር 80,500 ጀምሮ ለሽያጭ የቀረቡ ሲሆን ይህ ልዩ ቅናሽ እስከ መስከረም 30 ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ ብቻ የሚቆይ ይሆናል።
ድርጅቱ ደንበኞቹን ከገበያ የዋጋ ንረት ለመጠበቅ የ"ዋጋ ዋስትና" አሰራር መዘርጋቱን የገለጸ ሲሆን በዚህም መሠረት በግንባታ ወቅት የውጭ ምንዛሬ ጭማሪም ሆነ የቁሳቁስ ዋጋ መወደድ ቢከሰት ደንበኞች በተዋዋሉበት የኢትዮጵያ ብር መጠን ብቻ ክፍያቸውን ፈጽመው በወቅቱ ቤታቸውን የሚያረከቡ ይሆናል።
የሀገር ውስጥ እና የቻይና ባለሙያዎችን በማጣመር አያት፣ ልደታ፣ ቦሌ እና ወዳጅነት ፓርክ ፊትለፊት በርካታ ህንፃዎችን በመገንባት ላይ የሚገኘው ተቋሙ፣ በቀጣዮቹ 10 ዓመታት በሀገሪቱ የሪል ስቴት ዘርፍ ቀዳሚ ከሆኑ ተቋማት ተርታ ለመሰለፍ አልሞ እየሰራ ይገኛል።
በተጨማሪም ድርጅቱ የማኅበረሰብ ተሳትፎ ኃላፊነቱን ለመወጣት በአንድ የበጎ አድራጎት ተቋም እና ለሁለት ትምህርት ቤቶች ለሴት ተማሪዎች የንጽህና መጠበቂያ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
📸 ከበደ መክብብ
#HolidayDiscount #EthiopianNewYear #DiscountsEthiopia #EthiopianNewYear2019 #HouseForSaleAddis #ApartmentForSale | 725 |
| 7 | بدون متن... | 1 140 |
| 8 | ዴልታ ኤስፒኤምዩ አካዳሚ ይፋዊ የምረቃ እና የምስረታ ስነ-ስርዓቱን አካሄደ
#Yederaw I በመዋቢያ እና የውበት ጥበብ (Aesthetics) ዘርፍ ላይ ያተኮረው የዴልታ ኤስፒኤምዩ አካዳሚ (DELTA SPMU ACADEMY) ይፋዊ የምረቃ እና ጋዜጣዊ መግለጫ ተካሄደ።
የዴልታ ኤስቴቲክስ ትሬይኒንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር መስራች እና ዋና ስራ አስፈጻሚ ኤደን ካሳሁን በሰጡት ይፋዊ መግለጫ፣ ተቋሙ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ወጣቶች በተለይም ከዋና ከተማው ውጪ በየክልሎቹና በየገጠራማው አካባቢ ለሚኖሩ ዜጎች ተደራሽ የሚሆን ተግባራዊ እና ዘመናዊ የሙያ ስልጠናዎችን ለመስጠት ራዕይ ሰንቆ ስራ መጀመሩን ገልጸዋል።
በፕሮግራሙ ላይ እንደተገለጸው፣ ተቋሙ በውበት ጥበብ ዘርፍ የሚስተዋለውን የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት ለመቅረፍ እና ወጣቶች የራሳቸውን የስራ እድል እንዲፈጥሩ ለማስቻል ያለመ ነው።
ዋና ስራ አስፈጻሚዋ በማብራሪያቸው “ስራን ለመፈለግ ብቻ ሳይሆን ስራን ለመፍጠር፣ ገቢን ለማግኘት ብቻ ሳይሆን ነጻነትን ለመቀናጀት፣ ክህሎትን ለመማር ብቻ ሳይሆን ህይወትን ለመለወጥ” በሚል መርህ ተቋሙ ወደ ስራ መግባቱን ጠቁመው፣ ዴልታ አካዳሚ ፍጹም ባይሆንም ስህተቶችን እየታረመ እና የአሰራር መንገዶችን እያሻሻለ ከማህበረሰቡ ጋር በቅንነት ለመስራት ቃል መግባቱን አስረድተዋል።
የዴልታ ኤስቴቲክስ ትምህርቱን 80 ፐርሰንት በኦንላይን ሲሆን 20 ፐርሰንት በተግባር ይሰጣል ተብሏል።
በመግለጫው ማጠቃለያ ላይ ተቋሙ ለወደፊት ተማሪዎቹ፣ ለደጋፊዎቹ እና ለሽርክና አጋሮቹ ምስጋናውን ያቀረበ ሲሆን፣ ይህ የምስረታ ታሪክ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ወጣቶች አዲስ የስራ እድል እና የክህሎት በር የሚከፍት መሆኑም ተመልክቷል። በፕሮግራሙ ላይ ላይ የክብር እንግዳ በመሆን የሜሪጆይ መስራች ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፏል። | 1 051 |
| 9 | بدون متن... | 947 |
| 10 | ሊዮስ የምግብ ዘይትና አኩሪ ምርቶች ለ'እኛው ለኛው' የአረጋውያን መርጃ ማዕከል የግማሽ ሚሊዮን ብር ድጋፍ አበረከተ
#Ethiopia | በምግብ ዘይትና አኩሪ ምርቶች ዝግጅት የሚታወቀው ሊዮስ (Leos)፤ በቢሾፍቱ ከተማ ለሚገኘውና ለሁለት አስርተ ዓመታት በአረጋውያን መርጃነት ለዘለቀው 'እኛው ለኛው' ማዕከል የ500,000 (አምስት መቶ ሺህ) ብር የገንዘብ ድጋፍ አደረገ።
ይህ የድጋፍ መርሀግብር የተከናወነው በግብርናውና በኢንዱስትሪው ዘርፍ ቀዳሚ ተጠቃሽ የሆኑትና የሊዮስ የምግብ ዘይትና ሶያ ምርቶች ባለቤት የነበሩት የመቶ አለቃ ለማ አስፋው መታሰቢያ ፕሮግራም ላይ ነው።
መቶ አለቃ ለማ አስፋው በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ዓለም አቀፍ የዶሮና የእንስሳት መኖ ማምረቻ ድርጅት በመመስረት የሚታወቁ ሲሆን፤ ከዚህም ባሻገር አለማ ፋርምስ (Alema Farms) እና ሊዮስ የምግብ ዘይት ፋብሪካን በመሳሰሉ ግዙፍ ተቋማት አማካኝነት በሀገሪቱ የግብርና ግብዓት እጥረት ላይ ትልቅ መፍትሄ ሲያመጡ የቆዩ ባለራዕይ ነበሩ።
ይህ በስማቸው የተደረገው ድጋፍም ድርጅቱ የእሳቸውን የበጎ አድራጎት አርአያነት ለመከተል ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
በቢሾፍቱ ከተማ በተካሄደው በዚህ ስነ-ስርዓት ላይ የዲቦራ ፋዉንዴሽን መስራችና ባለቤት አቶ አባዱላ ገመዳን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የድርጅቱ አመራሮች ተገኝተዋል።
ሊዮስ የምግብ ዘይትና አኩሪ ምርቶች ድርጅት ጥራት ያለው ምርት ለገበያ ለማቅረብ በጥር 2007 ዓ.ም ተመስርቶ ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል። ድጋፍ የተደረገለት 'እኛው ለኛው' የአረጋውያንና የህጻናት መርጃ ማእከልም ላለፉት 20 ዓመታት በርካታ ወገኖችን ሲረዳ የቆየ አንጋፋ ተቋም ነው። | 864 |
| 11 | بدون متن... | 1 250 |
| 12 | በዘንድሮው የ‘ግራንድ አፍሪካን ረን’ ለዕድለኛ ተሳታፊ ዘመናዊ የቶዮታ መኪና በዕጣ እንደሚቀርብ ተገለፀ
ዘመናዊ መኪና የሚያሸልመው ፤ በሺዎች የሚቆጠሩ የዲያስፖራው ማህበረሰብ አባላት በየዓመቱ የሚሳተፉበት የግራንድ አፍሪካን ረን የ5ኪሜ የመዝናኛ ሩጫ ዝግጅት በመጪው ኦክቶበር በዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ለ8ኛ ዓመት ሊካሄድ መሆኑ ተገለፀ።
እ.አ.አ በኦክቶበር 10 2026 በሚካሄደው ዝግጅት ከሚካፈሉ ተሳታፊዎች መካከል እድለኛ የሆነ ባለዕጣ የ2026 ቶዮታ ኮሮላ መኪና በዝግጅቱ ማጠናቀቂያ ላይ የዕጣ ማውጣት ስነስርዓት ተከናውኖ እንደሚሸለም ታውቋል።
የመኪና ሽልማቱ የዝግጅቱ ቀዳሚ አጋር በሆነው አሌክሳንድሪያ ቶዮታ የተዘጋጅቶ የሚቀርብ እንደሆነ ተገልፆል። እንደሁልጊዜውም በዚህ ዝግጅት ላይ ታላላቅ አትሌቶች እና የኪነጥበብ ባለሞያዎች በክብር እንግድነት እንደሚሳተፉም አዘጋጁ ኖቫ ኮኔክሽንስ የላከው ጋዜጣዊ መግለጫ ይጠቁማል።
"ቅድሚያ ለማህበረሰብ" በሚል መረሃ-ግበር የዝግጅቱ አጋር ሆኖ ለአለፉት 5 ዓመታት የቆየው እና ለቀጣዮቹ ዓመታት በአጋርነት የሚቆየዉ የአሌክሳንደሪያ ቶዮታ የጄነራል ማኔጀር የሆኑት አቶ ያሬድ ማን አለብህ እንደገለፁት፣ ግራንድ አፍሪካ ረን ከሩጫም በላይ ለዳያስፖራው ማህበረሱብ የመገናኛ እና ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች የገንዘብ ማሰባሰቢያ መድረክ ሆኖ የሚያገለግል ከመሆኑም ባሻገር የድርጅታቸው የረጅም ጊዜ ደንበኞቹን ለማመስገን በዝግጅቱ ላይ ሽልማት እንደሚያቀርቡ ገልፀዉ፣ የአሌክሳንደሪያ ቶዮታ ከዳያስፖራው ማህበረስብ ጎን በቀጣይነትምበኣጋርነት እንደሚቆም ጠቁመዋል።
የመዝናኛ ሩጫው ዋና አዘጋጅ የሆኑት ዶክተር ጋሻው አብዛ ዝግጅቱ ከአንድ ቀን የ5 ኪሜ የቤተሰብ ሩጫነት የበለጠ ፋይዳ ያለው መርሀግብር መሆኑን ጠቁመው፤ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያንን ብሎም አፍሪካዊያንን በማቀራርብ ረገድ ጉልህ ሚና እንዳለው ገልፀዋል።
የመኪና ስጦታዉ ለአንድ ዕድለኛ ከሚያበረክተው እገዝ ጎን ለጎን የዕጣ ማውጣቱ ሂደት በዝግጅቱ ቀን አዝናኝ እና አጓጊ ሆኖ እንዲከናውን እየተሰራበት መሆኑንም አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡
የዘንድሮው ለ4ኛ ጊዜ በስጦታነት የሚቀረብ የቶዮታ መኪና ነው። የግራንድ አፍሪካ ረን ምዝገባ በዝግጅቱ ድረ-ገፅ www.africanrun.com ላይ ከሰኔ ወር መጀመሪያ አንስቶ እንደሚጀመር አዘጋጆቹ አያይዘው አንስተዋል። | 979 |
| 13 | ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ የቤት እጥረትን ለመቅረፍ አዳዲስ የሪል እስቴት ፕሮጀክቶችን ይፋ አደረገ
#Yederaw | ከኮንስትራክሽን ዘርፍ ወደ ሪል እስቴት አልሚነት የተሸጋገረው ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ፣ በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ የሚስተዋለውን ከፍተኛ የመኖሪያ ቤት እጥረት በዘላቂነት ለማቃለል ሰፊ እንቅስቃሴ መጀመሩን አስታወቀ።
ኩባንያው ከዚህ ቀደም በመስቀል ፍላወር እና በቄራ አካባቢዎች የገነባቸውን ዘመናዊ አፓርትመንቶች አጠናቆ ለባለቤቶቹ ማስረከቡ የሚታወስ ሲሆን፤ በዛሬው ዕለት ደግሞ በቦሌ አትላስ አካባቢ በ1,496 ካሬ ሜትር መሬት ላይ ያሳነፀውን ባለ 15 ወለል ዘመናዊ አፓርትመንት በይፋ ለገበያ ማቅረቡን አብስሯል።
በዚሁ የቦሌ አትላስ ፕሮጀክት የከተማዋን ነዋሪዎች የተለያየ ፍላጎትና አቅም ያማከሉ፣ ከ80 እስከ 165 ካሬ ሜትር ስፋት ያላቸው ባለ አንድ እና ባለ ሦስት መኝታ ቤቶች ተካተውበታል።
የኩባንያው የልማት ራዕይ በዚህ ብቻ አላበቃም፤ በካዛንቺስ አካባቢ ለንግድ እና ለመኖሪያ አገልግሎት የሚውል ባለ 19 ወለል ግዙፍ ሕንፃ በመገንባት ላይ ይገኛል። በተጨማሪም በአደይ አበባ (ሳሪስ) አካባቢ ሰፊ የመኖሪያ መንደር ለመገንባት የሚያስችለውን የቅድመ ዝግጅት ሥራ ማጠናቀቁን የገለጸው ድርጅቱ፣ ለዚህም ይረዳው ዘንድ የጎህ ፕሮፐርቲ ኮርፖሬሽንን 80 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ መግዛቱን አሳውቋል።
እነዚህ ተከታታይ እና ግዙፍ ፕሮጀክቶች፣ ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ያካበተውን ሰፊ ልምድ ወደ ቤት ልማት በማሸጋገር የብዙ ዜጎችን የቤት ባለቤት የመሆን ሕልም ዕውን ለማድረግ እንዲሁም በከተማዋ ያለውን የቤት አቅርቦትና ፍላጎት አለመመጣጠን ለማጥበብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ በሽያጭ መርሐግብሩ ላይ ተገልጿል።
#ኮምፓስ_ፕሮፐርቲስ #ሪል_እስቴት #አዲስ_አበባ #መኖሪያ_ቤት #ኢትዮጵያ #CompassProperties #AddisAbaba #RealEstateEthiopia | 1 218 |
| 14 | بدون متن... | 1 047 |
| 15 | የኢትዮጵያን ገጽታ ለዓለም የሚያስተዋውቅ ታላቅ የዲጂታል ዘመቻ ይፋ ሆነ
#Yederaw | የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊ ጸጋዎች፣ ታሪካዊ ቅርሶች እና ዘመናዊ ገጽታ በታዋቂ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች (Influencers) አማካኝነት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ያለመ አዲስ ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ።
"ኢንፍሉዌንሰር ቱር 2026" የተሰኘው ይህ መርሃ ግብር፣ የሀገሪቱን የቱሪዝም ዘርፍ በዲጂታል አማራጮች ለማነቃቃት ታቅዶ የተቀረጸ ነው።
የፕሮጀክቱ ዋና ዋና ዓላማዎች
* ዓለም አቀፍ እውቅና፦ በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚገኙ ታዋቂ ግለሰቦች በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች በመዘዋወር ያዩትን ተጨባጭ እውነት ለተከታዮቻቸው በከፍተኛ ጥራት እንዲያጋሩ ምቹ ሁኔታ መፍጠር።
* ሁለገብ ተሳትፎ፦ መርሃ ግብሩ የቱሪስት መዳረሻዎችን ከማስተዋወቅ ባለፈ፣ የዩኒቨርሲቲ ጉብኝቶችን፣ ማህበረሰብ ተኮር የበጎ አድራጎት ተግባራትን እና ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን ያካትታል።
* የዘርፉን አቅም መገንባት፦ በየክልሉ የሚገኙ አዳዲስ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች ከታዋቂዎቹ ጋር ተቀናጅተው እንዲሰሩ በማድረግ የይዘት ፈጠራ ጥበብን ማሳደግ።
ይህንን ግዙፍ ንቅናቄ በበላይነት የሚመራው ኤን ዜድ ኮሙኒኬሽን (NZ Communication) ሲሆን፣ ድርጅቱ የኢንፍሉዌንሰሮችን አስተዳደር እና የዘመቻ አፈጻጸሙን በኃላፊነት ያከናውናል። በፕሮጀክቱ ላይ የሚሳተፉ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የሀገራቸውን ገጽታ ያለ ምንም ክፍያ በፈቃደኝነት ለማስተዋወቅ መስማማታቸው ተገልጿል።
ኤን ዜድ ኮሙኒኬሽን በሰጠው መግለጫ፣ ፕሮጀክቱን ስኬታማ ለማድረግ ከሚዲያ ተቋማት፣ ከንግድ ድርጅቶች እና ከከተማ መስተዳድሮች ጋር በቅንጅት ለመስራት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል። ይህ እንቅስቃሴ ለሀገራዊ ኩራትና ለኢትዮጵያ የቱሪዝም ዕድገት ትልቅ አዎንታዊ ተፅዕኖ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል። | 1 127 |
| 16 | بدون متن... | 837 |
| 17 | ኪ ሃውሲንግ ለ300 አባላቱ የቤት ዕጣ አወጣ!
#Yederaw | ኪ ሃውሲንግ ፋይናንስ ሶሉሸን መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በጌትፋም ሆቴል ባዘጋጀው ልዩ መርሐግብር ለ300 አዳዲስ አባላቱ የቤት ዕጣ አውጥቷል።
በዕጣው አሸናፊ የሆኑት ቤቶች ስብጥር፦
* 45 ዕድለኞች — ባለ 1 መኝታ
* 105 ዕድለኞች — ባለ 2 መኝታ
* 150 ዕድለኞች — ባለ 3 መኝታ
ስለ አሰራር ሞዴሉ
ተቋሙ "Economies of Scale" በተሰኘው የፋይናንስ ሞዴል አማካኝነት፤ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች በዝቅተኛ ቅድመ-ክፍያ እና በወር ከ2 ሺህ ብር በሚጀምር ቁጠባ የቤት ባለቤት እንዲሆኑ እያስቻለ ይገኛል።
ኪ ሃውሲንግ ወደ ገበያ ከገባ ጊዜ ጀምሮ በአዲስ አበባ በሚገኙ 7 ሳይቶች እና በባህር ዳር በሚገኙ 2 ሳይቶች በመቶዎች የሚቆጠሩ አባላቱን የቤት ባለቤት ማድረግ መቻሉ ተገልጿል።
ቀጣይ እቅዶች እና አጠቃላይ እይታ
የተቋሙ አባላት ቁጥር በአሁኑ ወቅት ከ20,000 በላይ የደረሰ ሲሆን፣ በቀጣይም "ኪ መንደር" የተሰኘ ግዙፍ የመኖሪያ መንደር ግንባታ ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው።
ይህ የዕጣ አወጣጥ መርሐግብር የግሉ ዘርፍ በሃገሪቱ የቤት ልማት ላይ ያለውን ጉልህ አሻራ ያሳየና የብዙዎችን ተስፋ ያለመለመ መሆኑን በስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙ ታዛቢዎች መስክረዋል።
#KeyHousing #ኪሃውሲንግ #EthiopiaNews #AddisAbaba #HousingLottery #RealEstateEthiopia #LocalNews #NewsUpdate | 993 |
| 18 | بدون متن... | 925 |
| 19 | ከሩብ ክፍለ ዘመን በላይ በምስል የታተመ የጥበብ ጉዞ፦ የፎቶግራፍ ባለሙያው ሲሳይ ጉዛይ
#Ethiopia | በጥበብ ዓለም ውስጥ የአንድን ሰው ማንነት፣ የአንድን አፍታ ስሜት እና የታሪክን ሂደት በቋሚነት አስሮ ማስቀረት የሚችለው የካሜራ ሌንስ ብቻ ነው።
በዚህ ረገድ ላለፉት 25 ዓመታት ካሜራውን እንደ ብዕር በመጠቀም በኢትዮጵያ የፎቶግራፍ ጥበብ ውስጥ ደማቅ አሻራውን ያሳረፈው ድንቅ ባለሙያ ሲሳይ ጉዛይ ተጠቃሽ ነው።
የ25 ዓመታት የጥበብ አሻራ
ሲሳይ ጉዛይ በፎቶግራፍ ሙያ ውስጥ ለሁለት አስርት ዓመታት ተኩል የዘለቀው ቆይታው፣ ሙያውን ከቴክኒክ ባለፈ ወደ ጥልቅ ስሜት ቀያይሮታል።
በሺዎች የሚቆጠሩ ድንቅ ምስሎችን ለታሪክ ያበረከተው ሲሳይ፣ በተለይም በሰው ልጆች ስሜትና በታላላቅ ሁነቶች ላይ የሚያደርገው ትኩረት ልዩ ያደርገዋል።
ተወዳጅ ሰብዕና እና ሙያዊ ብቃት
ባለሙያው ከሥራው ባለፈ በሰብዕናው "ሰውን አክባሪና በሁሉ ዘንድ ተወዳጅ" በመሆኑ ይታወቃል።
በሥራው ወቅት የሚያሳየው ትህትና እና ከደንበኞቹ ጋር ያለው የቀረበ ግንኙነት፣ በፎቶግራፎቹ ላይ የሚታዩት ሰዎች ነፃ ሆነው የውስጥ ስሜታቸውን እንዲገልጹ ትልቅ ድልድይ ሆኗቸዋል። ይህ ተወዳጅነቱ የብዙዎችን የልብ ወዳጅነት እንዲያተርፍ አስችሎታል።
ታላቅ የፎቶ ኤግዚቢሽን በቅርቡ
ላለፉት 25 ዓመታት የተከማቹ ድንቅ የጥበብ ሥራዎችን ለአይን ለማብቃት እና የፎቶግራፍን ፋይዳ ለማሳየት፣ ሲሳይ ጉዛይ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ታላቅ የፎቶ ኤግዚቢሽን ለማዘጋጀት በከፍተኛ ዝግጅት ላይ ይገኛል።
የአጋርነት ጥሪ
ይህንን ተወዳጅ ፎቶግራፈር በሚያዘጋጀው የፎቶ ኤግዚቢሽን ላይ በሐሳብም ሆነ በሌሎች ድጋፎች ማገዝ ለምትሹ በሚከተለው ስልክ ቁጥር ደውላችሁ ማነጋገር ትችላላችሁ፦
📞 0911 24 58 11
የሲሳይ ጉዛይ የረጅም ዘመን የጥበብ ሥራና የሕይወት ተሞክሮ በኢቢኤስ (EBS) ቴሌቪዥን "ውሎ" ፕሮግራም ላይ ቀርቦ ለተመልካች መቅረቡ የሚታወስ ሲሆን፣ ሙሉ ቆይታውን በYouTube መመልከት ይቻላል።
ሙሉ ቆይታውን በዚህ ሊንክ መመልከት ትችላላችሁ፦
https://youtu.be/4xQRmfGR2xs?si=kzakTLYMKqVoS93V
#getutemesgen #getu #ጌጡ #Ethiopia #Photography #SisayGuzay #PhotoExhibition #Art #Documentary #HistoryInFrames #EBSTV #VisualStorytelling | 1 048 |
| 20 | بدون متن... | 937 |
