Mark Tech Info | Mark Technology Information
رفتن به کانال در Telegram
Buy ads: https://telega.io/c/MarkTechInfo ለአስተያየት ፣ ጥቆማ ፣ ለማስታወቂያ እና ለጥያቄዎች በዚህ ያናግሩን። 👇👇👇👇👇👇👇👇 @MarkTechInfoBot
نمایش بیشتر6 210
مشترکین
-424 ساعت
-307 روز
-30330 روز
آرشیو پست ها
የኦሮሚያ ክልል ከ323 ሺሕ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለማስፈተን መዘጋጀቱን አስታወቀ
👉484 ሺሕ 994 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ይፈተናሉ ተብሏል
የኦሮሚያ ክልል 323 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለማስፈተን መዘጋጀቱን አስታወቀ። በተመሳሳይም 484 ሺሕ 994 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና እንደሚወስዱ ተገልጿል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ዶክተር ቡልቶሳ ሂርኮ የ8ኛ እና 12ኛ ክፍል ፈተናዎች ዝግጅትን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፤ በክልሉ ከ323 ሺሕ በላይ የ12ኛ እና 484 ሺሕ 994 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ለፈተና ተመዝግበዋል፡፡
ለ12ኛ ክፍል ፈተና በማህበራዊ ሳይንስ እና በተፈጥሮ ሳይንስ በአጠቃላይ ከ323 ሺሕ በላይ ተማሪዎች ይፈተናሉ ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል፡፡
የ12ኛ ክፍል ፈተና በ22 ዩነቨርሲቲዎች ይሰጣል ያሉት ዶክተር ቡልቶሳ፤ 17 በክልሉ በሚገኙና 5 አጎራባች ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ፈተናው ይሰጣል ብለዋል፡፡
ፈተናው ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ከሐምሌ 19 እስከ 21 የሚሰጥ መሆኑን ጠቅሰው ለተፈጥሮ ሳይንስ ከሐምሌ 25 እስከ 28 እንደሚሰጥ መግለጻቸውን ኢፕድ ዘግቧል፡፡
ፈተናው የተሳካ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ግብረሀይል ተቋቁሞ ወደ ትግበራ መገባቱንም ሃላፊው የገለጹ ሲሆን፤ በዚህም ከባለፈው ዓመት ልምድ በመነሳት ፈተናውን ተማሪዎች አንዳች ችግር ሳይገጥማቸው ለመስጠት ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል።
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
ቀጣይ Remedial Program አይኖርም‼️
በ 2014 የ 12ኛ ክፍል ፈተናን ያለፉ ተማሪዎች !3% ብቻ በመሆኑ እንዲሁም ዩኒቨርስቲ መፈተኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለነበር ለተማሪዎች 2ኛ እድል ተሰጥቷቸው ነበር።
በዚህ አመት የ 12ኛ ክፍል ፈተናን የሚፈተኑ ተማሪዎች 850ሺ በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች ስሆኑ ፈናውን ያለፉ ተማሪዎች ብቻ ወደ ዩኒቨርስቲ ይገባሉ ተብሏል።
በ 2016 Remedial የሚባል ፕሮግራም አይኖርም። በ 2016 1ኛ አመት ሆነው ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ተማሪዎች የ 12ኛ ክፍል ፈተናን ያለፉና የሬሚዲያል ፕሮግራምን ያለፉ ተማሪዎች በአንድ ላይ ይገባሉ ተብሏል።
ስለዚህ የ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በቀጣይ የ Remedial እድል አለመኖሩን አውቃችሁ በቂ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳውቃለን ።
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️የተሰወሩት መምህራን
በደቡብ ክልል ስልጤ ዞን የትምህርት ማስረጃቸው እንዲጣራ በመደረጉ ተደናግጠው የተሰወሩ መምህራንን ፖሊስ እያደናቸው መሆኑ ተገለፀ።
የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በስልጤ ዞን የትምህርት ማስረጃቸው እንዲጣራ በመደረጉ ተደናግጠው የተሰወሩ መምህራንን አድኖ በመያዝ ለፍርድ ለማቅረብ ብርቱ ክትትል እያደረኩ ነው ሲል አስታወቀ።
በዞኑ በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች በተለያዩ ሴክተር መስሪያቤቶች ተቀጥረዉ በሚሰሩ የአራት ሺህ አራት መቶ ሰባአራት ሰራተኞች የትምህርት ማስረጃ ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተልኮ እንዲጣራ በመደረጉ 67 መምህራን ተደናግጠዉ ስራቸዉን ጥለዉ መጥፋታቸዉ ተነግሯል።
ኮሚሽኑ ሀሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ አቅርበዉ ከተቀጠሩ 82 መምህራኖች ዉስጥ 28 መምህራንን ፖሊስ በቁጥጥር ስር አዉሎ ምርመራ አጣርቶባቸዋል ብሏል። ምርመራ ከተጣራባቸዉ 28 ተከሳሾች ዉስጥ ፍርድ ቤት ቀርበዉ የተቀጡት 13 ተከሳሾች ናቸዉ ሲልም አስታውቋል።
ነገር ግን የተቀሩት በፍርድ ቤት በዋስ ከተለቀቁ በኋላ አካባቢያቸዉን ጥለዉ የተሰወሩ በመሆኑ ተከሳሾችን አድኖ በመያዝ ለፍርድ ለማቅረብ ብርቱ ክትትል እየተደረገ እንደሚገኝ የክልሉ ፖሊስ ገልጧል።
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
#Update
የ2015 ዓ.ም ብሔራዊ የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ለመውሰድ ከ869 ሺህ በላይ ተፈታኞች በኦንላይን መመዝገባቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል፡፡
ለ2ኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠውን አገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ 869 ሺህ 765 ተፈታኞች በኦንላይን መመዝገባቸውን በአገልግሎቱ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወንደወሰን ኢየሱስወርቅ ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡
ከተመዘገቡት ውስጥ 503,812 ተማሪዎች የሶሻል ሳይንስ እና 365,954 የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች መሆናቸውን ኃላፊው ገልጸዋል።
የፈተና አስፈጻሚዎች፣ ሱፐርቫይዘሮች እና የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች ምልመላ ቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30/2015 ዓ.ም በሁለት ዙር እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ #ኢፕድ
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️የዋቻሞ ዩንቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና የወደቀ ተማሪ አይመረቅም የሚለውን የትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ በመቃወም ሰላማዊ ጥያቄ አቅርበው ነበር።
ለተማሪዎቹ ጥያቄ በዩንቨርሲቲው የሚገኙ የፀጥታ ኃይሎች የሰጡት ምላሽ ከላይ በተንቀሳቃሽ ምስል የተያያዘው የዱላ ውርጅብኝ ነበር
ተማሪዎቹ ያቀረቡትን ጥያቄ ወይም ቅሬታ ተነጋግሮ መፍታት ሲቻል ከላይ በሚታየው መልኩ ከባድ የሃይል እርምጃ መውሰድ ምን ይባላል?
ተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30/2015 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ከሐምሌ 16 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለዚሁ ሥራ ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ግንቦት 23/2015 ዓ.ም ተፈርሞ ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች፣ ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ለሁሉም የክልል ትምህርት ቢሮዎች የተላከ ደብዳቤ ያሳያል፡፡
ተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
ሬሜዲያል‼️
በ2014 ዓ.ም የተሰጠውን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ የሪሚዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ የነበሩና በተለያዩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የማጠናከሪያ ትምህርት ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች የሪሚዲያል ፈተና የሚሰጠው ከሰኔ 26 እስከ 30/2015 ዓ.ም እንደሆነ የትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
በትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በቀን ግንቦት 15/2015 ዓ.ም ተፈርሞ ለሁሉም የመንግሥት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተሰራጨው ደብዳቤ፤ ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ፈተናውን ውጤታማ በሆነ ሁኔታ እንዲሰጡ አሳስቧል።
ተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
ከትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተሰጠ የሀዘን መግለጫ
............................................................................
የትውልድ የእውቀት አባቶች ፣ የሀገር ተረካቢ ዜጎች መሃንዲሶች የሆኑ ትውልድ ለማፍራት ደፋ ቀና ሲሉ መንገድ ላይ የቀሩ መምህራን ህልፈተ ህይወታቸው ልብ ይሰብራል!
የመደ ወላቦ መምህራን እንደ ወጡ መቅረታቸው ሀዘኑ መራር ነው። ፈጣሪ ለነፍሳቸው ዘላለማዊ እረፍትን ይስጥልን !
በአደጋው ጉዳት ደርሶባቸው ህክምና ላይ ለሚገኙ መምህራንም ፈጣሪ ምህረቱን ይስጣቸው!
አደጋው መላውን ህዝብ በተለይም ቅርባቸው የሆነው የትምህርቱን ማህበረሰብ እጅግ ያስደነገጠና ልብ የሚሰበር ለሙያ የተከፈለ መስዋዕትነት ነው።
ተማሪዎችን በእውቀት አንጸው ለመመለስ የወጡ መምህራን ወደቤተሰባቸው መመለስ ሳይችሉ በወጡበት በመቅረታቸው እጅግ አዝኛለሁ።
ለቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸውና ጓደኞቻቸው በሙሉ እንዲሁም ለመደ ወላቦ ዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ መጽናናትን እመኛለሁ።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ!
የትምህርት ሚኒስትር!
ተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
የትምህርት ሚኒስቴር ፤ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ፈተና ማጠናቀቂያ ጊዜን በይፋ አሳውቋል።
በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስደው በልዩ ሁኔታ በሪሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ የሆኑ ተማሪዎች ፈተና ተዘጋጅቶ እንዲላክና አጠቃላይ ሂደቱ እስከ ሰኔ 30/2015 ዓ.ም ድረስ እንዲጠናቀቅ በትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ ተቀምጧል።
ፈተናውም በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው በተሰጠው ትምህርት መሠረት ከማዕከል በጋራ ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ ተብሏል።
በዚህም መሰረት በሴሚስተሩ በተሰጠው ትምህርት የተቋማት የውስጥ ፈተና ውጤት 50 ከመቶ እንዲሁም በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና ውጤት 50 ከመቶ ይይዛል ተብሏል።
ተማሪዎችም በ2016 ዓ.ም ትምህርታቸውን ለመከታተል ብቁ ሆነው ለመገኘት የሁለቱ ድምር አማካይ 50 ከመቶና በላይ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል።
ዩኒቨርሲቲዎችም ፈተናውን በማስተዳደርና ውጤት በመግለጽ በ2016 የፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ የሆኑ ተማሪዎችን ለይተው እስከ ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ/ም እንዲያጠናቅቁ ተገልጿል።
ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን ስራ በማጠናቀቅ የ2016 የትምህርት ካሌንደር የተስተካከለ እንዲሆን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።
#ትምህርት_ሚኒስቴር
ተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️ሐምሌ 19
የትምህርት ሚኒስቴር የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቅያ ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን ጊዜ ይፋ አድርጓል።
ሚኒስቴሩ ፤ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 30/2015 ዓ.ም ድረስ #በመንግስት_ዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል ብሏል።
ዩኒቨርሲቲዎችም ያላቸውን ስራ በማጠናቀቅ ከሐምሌ15/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።
ተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️ለሁሉም የመንግስት ዩንቨርስቲዎች
‼️ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
‼️ለሁሉም የክልል ትምህርት ቢሮዎች
ጉዳዩ፡ የአገር አቀፍ #ፈተና ቀናትን ስለማሳወቅ
1) በ2014 የ12ኛ ክፍል አጠናቀው ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ የሬሜዲያል ኘሮግራም ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎች ለአንድ ሴሚስተር የተሰጠው ትምህርት በማዕከል የጋራ ፈተና ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ፤ ተቋማት ፈተናውን የማስተዳደር ውጤት የመግለፅና በ2016 ፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ ሆነው የተገኙት (ማለትም በተቋማት የውስጥ ፈተና 50 ከመቶ፣ በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና 50 ከመቶ) ተደምሮ በድምሩ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡቱን እንዲያሳወቁ፣ ይህ አጠቃላይ ሂደት እስከ 👉ሰኔ 30 ቀን ድረስ እንዲጠናቀቅ።
2) በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃንና ባለፉት ዓመታት የህግ መውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡት ተማሪዎች የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የመፈተኛ ማዕከላት ውስጥ ፈተናው 👉ከሐምሌ 3 እስከ 13 ባሉት ቀናት ተሰጥቶ እንዲጠናቀቅ።
3) የ2015 የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና 👉ከሐምሌ 19 እስከ 30 የሚሰጥ ሆኖ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከሐምሌ 15 ቀን ጀምሮ ለዚሁ ሥራ ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ።
በመጨረሻም ከ2016 ጀምሮ የትምህርት ካላንደሩን ሁሉም ተቋማት ፕሮግራሞቻቸውን በዚህ ማዕቀፍ ያስተካክሉ ዘንድ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አሳስበዋል።
ተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መቼ ይሰጣል?
በርካታ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ከፈተና ቀን ጋር በተያያዘ ተመሳሳይ ጥያቄዎችን እየላኩልን ይገኛሉ።
ፈተናው በመጪው ሐምሌ ይሰጣል ተብሎ የነበረ ቢሆንም፤ እስከአሁን የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ትክክለኛና ቁርጥ ያለ ቀን ይፋ አልተደረገም።
የፈተናው ቀን ይፋ የሚደረገው በማዕከል በኩል ከትምህርት ሚኒስቴር / ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ሲሆን ይህም ለህዝብ በይፋ በመገናኛ ብዙኃን ይነገራል።
በመሆኑም የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ተማሪዎች ለፈተናው ጥቂት ጊዜ የቀረው መሆኑን በመገንዘብ ዝግጅት ማድረጋችሁን እንድትቀጥሉ እንላለልን።
በሌላ በኩል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና የተፈታኞች የበይነ መረብ ምዝገባ /online Registration/ አፈጻጸም ግምግማ ባለፈው ሳምንት አካሂዷል፡፡
በተጨማሪም በተዘጋጀው የፈተና አስተዳደር መመሪያ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን የበይነ መረብ ምዝገባው ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ የተደረገበትና ስኬትማ መሆኑ ተገልጿል።
በመድረኩ የፈተና አስተዳደር መመሪያ ለተሳታፊዎች ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ ከውይይቱ የተገኙ ሀሳቦችም በሰነዱ ተካተው በድጋሚ ለውይይት እንደሚቀርብና ሲጸድቅ ተግባራዊ እንደሚሆን ተነግሯል።
ይህም ፈተና የሚሰጥበትን ቀን በተመለከተ ትምህርት ሚኒስቴር ዝርዝር መረጃ የሚያወጣ በመሆኑ፤ እስከዛው ዝግጅታችሁን አጠናክሩ።
ተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ የ 8,952 ተማሪዎች ምዝገባ መከናወኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል፡፡
በክልሉ የሚገኙ 89 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን ምዝገባ አከናውነዋል፡፡
በተመሳሳይ በክልል ደረጃ የሚሰጠውን የስምንተኛ ክፍል ፈተና የሚወስዱ 17,901 ተማሪዎች ምዝገባ መካሄዱን የቢሮው ምክትል ኃላፊ ጃፈር ሐሩን ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡
የስምንተኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተናውን በሰኔ ወር ሦስተኛ ሳምንት ለመስጠት ዕቅድ መያዙን ገልጸዋል፡፡
ተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
በአማራ ክልል ከ215 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለ2015 ዓ.ም ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና መመዝገባቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል፡፡
የተፈታኞቹ ምዝገባ በክልሉ በሚገኙ 575 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በበይነ መረብ ብቻ እንደተካሄደ በቢሮው የፈተናና ምዘና ቡድን መሪ ዝጋለ ማሩ ለአሚኮ ተናግረዋል፡፡
በሰሜን ጎንደር እና በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር የሚገኙ አራት ትምህርት ቤቶች በአካባቢዎቹ በተነሳ ጦርነት ምክንያት የተማሪዎች ምዝገባ ማድረግ አለመቻላቸውን ኃላፊው ገልጸዋል፡፡
በክልሉ 215 ሺህ 760 ተማሪዎች የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ለመውሰድ መመዝገባቸውን ጠቁመዋል፡፡
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
ተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️ዲቪ ሎተሪ እድለኞች
" የዲቪ (DV) ሎተሪ አሸንፋችኋል፣ ከአሜሪካ ኢምባሲ ነው እምንደውለው ወይም ኢሜይል / ቴክስት የምንልከው ከሚሉ አጭበርባሪዎች ተጠንቀቁ " - በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ
የአሜሪካ ኤምባሲ የዲቪ (DV) 2024 አሸናፊዎች ከፊታችን ቅዳሜ ጀምሮ ይፋ ይደረጋል ብሏል ፤ መመልከቻውም ow.ly/9E7A50O7plm መሆኑን ገልጿል።
በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ፤ ባሳለፍነው ጥቅምት እና ህዳር ወራት ላይ በበይነ መረብ አማካኝነት የተሞላው የ2024 ድቪ (DV) ሎተሪ አሸናፊዎች መታወቃቸው ይፋ አድርጓል።
የዲቪ (DV) 2024 ማመልከቻ የሞሉ ዜጎች መመረጣቸውን እና አለመመረጣቸውን የፊታችን ቅዳሜ ከሚያዚያ 28/2015 ዓ.ም ጀምሮ ማወቅ እንደሚችሉ አመልክቷል።
በዲቪ (DV) ሎተሪ ድረገጽ ow.ly/9E7A50O7plm ላይ በመግባት አመልካቾች ያመለከቱበትን ልዩ ቁጥር ወይም ኮድ በማስገባት ማወቅ ይችላሉ ተብሏል።
በሌላ በኩል፤ " የዲቪ (DV) ሎተሪ አሸንፋችኋል፣ ከአሜሪካ ኢምባሲ ነው እምንደውለው / ኢሜይል / ቴክስት የምንልከው " በሚል የሚያጭበረብሩ አካላት ስለሚኖሩ አመልካቾች እንዲጠነቀቁም ኤምባሲው አሳስቧል።
አመልካቾች ለዲቪ (DV) ሎተሪ ደርሷቸው እንደሆነ ወይም እንዳልደረሳው በራሳቸው እጃቸው ላይ ባለው ሚስጢራዊ ቁጥር በዚህ ድረገፅ ow.ly/9E7A50O7plm ማረጋገጥ ብቸኛው መንገድ መሆኑን ገልጿል።
ተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️ሰበር ዜና
" የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሃምሌ ወር ላይ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል " - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶችና ከክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችጋር ውይይት አካሄደ፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሃምሌ ወር ላይ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚካሄድ ገልጸዋል፡፡
ፈተናው ልክ እንደባለፈው አመት በሁለት ዙር የሚሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በመጀመሪያው ዙር የነበሩ የፈተና ችግሮችን ዘርዝረው ለቀጣዩ የመፍትሄ አቅጣጫ ማስቀመጥና ቅድመ ዝግጅት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት አሳስበዋል፡፡
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በበኩላቸው የ2015 ዓ.ም ፈተናን ለማስፈፀም ልዩ ልዩ መመሪያዎች እየተዘጋጁ መሆኑንና የተፈታኞች መረጃ በአግባቡ እየተደራጀ መሆኑን አብራርተዋል።
ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የህብረተሰቡን ችግር ለመቅረፍና አመለካከቱን ለመቀየር፣ ብቁና አገር ተረካቢ ትዉልድ ለመፍጠር አሁን ያለው ባለድርሻ አካል ሚናውን ሊወጣ ይገባል ሲሉ በአንክሮ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም በ2016 ዓ.ም የሚካሄደው ፈተና እንደአካባቢው ሁኔታ ኦን ላይን እንደሚሆን ገልጸው የእለቱ ውይይት ተጠናቋል፡፡
ምንጭ፦ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
ተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️ነገ ያበቃል
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ምዝገባ ነገ ሚያዚያ. 20/2015 ዓም ከቀኑ 11:30 ላይ ያበቃል።
ስለሆነም እስካሁን ያልተመዘገባችሁ እስከ ነገ እንዲትመዘገቡ እያሳሰብን በማንኛውም ምክኒያት ያልተመዘገቡ ተፈታኞችን ከነገ በኋላ የማናስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
ተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️ማስታወቂያ
የ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የተማሪዎች ምዝገባ ነገ ሚያዝያ 20/2015 ዓ.ም ይጠናቀቃል።
ምዝገባው ከመጋቢት 20/2015 ዓ.ም ጀምሮ በኦንላይን ሲከናወን መቆየቱ ይታወቃል።
ከሚያዚያ 20/2015 ዓ.ም በኋላ በግለሰብም ሆነ በተቋም የሚመጡ ተመዝጋቢዎችን እንደማያስተናግድ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ማሳወቁ አይዘነጋም።
ተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️2015 ማትሪክ
የ2015 ት/ት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች በሙሉ
1/የ2015 ት/ት ዘመን ፈተና ምዝገባ እስከ ሚያዝያ 20/2015 ዓ/ም ድረስ ብቻ ይካሄዳል።
2/ ማንኛውም የስም፣ የፆታ፣ የተፈጥሮ/የማህበራዊ ዘርፍ እና የፎቶ ማስተካከያ ከፈተና በፊት ስለማይደረግ እያንዳንዱ ተፈታኝና እና መዝጋቢ ትክክለኛነቱን የማጣራትና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት። ምክንያቱም ምዝገባው በበየነ መረብ በመሆኑ በትምህርት ቤት ደረጃ የተካሄደው የምዝገባ መረጃ በቀጥታ በማንም ሳይነካ ወደ ተቋማችን የመረጃ ቋት የሚገባ በመሆኑ ነው።
3/ከሚያዚያ 20/2015 ዓ/ም በኋላ በግለሰብ ወይም በተቋም በኩል የሚመጡ ተመዝጋቢዎችን የማናስተናግድ መሆኑን ከወዲሁ በጥብቅ እናሳስባለን።
4/ፈተናው የምሰጠው በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ሲሆን የመፈተኛ ጊዜን ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኋላ የምንገልጽ ይሆናል። እስካሁን የመፈተኛ ጊዜ አልተገለጸም።
ስለሆነም ተፈታኞች ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ እያሳሰብን መልካም ውጤት እንዲያስመዘግቡ እንመኛለን።
የት/ት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
ተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 @grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
