uz
Feedback
Mark Tech Info | Mark Technology Information

Mark Tech Info | Mark Technology Information

Kanalga Telegram’da o‘tish

Buy ads: https://telega.io/c/MarkTechInfo ለአስተያዚት ፣ ጥቆማ ፣ ለማስታወቂያ እና ለጥያቄዎቜ በዚህ ያናግሩን። 👇👇👇👇👇👇👇👇 @MarkTechInfoBot

Ko'proq ko'rsatish
6 207
Obunachilar
-424 soatlar
-307 kunlar
-30330 kunlar
Postlar arxiv
ዚኊሮሚያ ክልል ኹ323 ሺሕ በላይ ዹ12ኛ ክፍል ተማሪዎቜን ለማስፈተን መዘጋጀቱን አስታወቀ 👉484 ሺሕ 994 ዹ8ኛ ክፍል ተማሪዎቜ ይፈተናሉ ተብሏል ዚኊሮሚያ ክልል 323 ሺህ በላይ ዹ12ኛ ክፍል
+1
ዚኊሮሚያ ክልል ኹ323 ሺሕ በላይ ዹ12ኛ ክፍል ተማሪዎቜን ለማስፈተን መዘጋጀቱን አስታወቀ 👉484 ሺሕ 994 ዹ8ኛ ክፍል ተማሪዎቜ ይፈተናሉ ተብሏል ዚኊሮሚያ ክልል 323 ሺህ በላይ ዹ12ኛ ክፍል ተማሪዎቜን ለማስፈተን መዘጋጀቱን አስታወቀ። በተመሳሳይም 484 ሺሕ 994 ዹ8ኛ ክፍል ተማሪዎቜ ፈተና እንደሚወስዱ ተገልጿል። ዹክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ዶክተር ቡልቶሳ ሂርኮ ዹ8ኛ እና 12ኛ ክፍል ፈተናዎቜ ዝግጅትን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ እንደገለጹትፀ በክልሉ ኹ323 ሺሕ በላይ ዹ12ኛ እና 484 ሺሕ 994 ዹ8ኛ ክፍል ተማሪዎቜ ለፈተና ተመዝግበዋል፡፡ ለ12ኛ ክፍል ፈተና በማህበራዊ ሳይንስ እና በተፈጥሮ ሳይንስ በአጠቃላይ ኹ323 ሺሕ በላይ ተማሪዎቜ ይፈተናሉ ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል፡፡ ዹ12ኛ ክፍል ፈተና በ22 ዩነቚርሲቲዎቜ ይሰጣል ያሉት ዶክተር ቡልቶሳፀ 17 በክልሉ በሚገኙና 5 አጎራባቜ ክልል በሚገኙ ዩኒቚርሲቲዎቜ ፈተናው ይሰጣል ብለዋል፡፡ ፈተናው ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎቜ ኹሐምሌ 19 እስኚ 21 ዚሚሰጥ መሆኑን ጠቅሰው ለተፈጥሮ ሳይንስ ኹሐምሌ 25 እስኚ 28 እንደሚሰጥ መግለጻ቞ውን ኢፕድ ዘግቧል፡፡ ፈተናው ዚተሳካ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ግብሚሀይል ተቋቁሞ ወደ ትግበራ መገባቱንም ሃላፊው ዚገለጹ ሲሆንፀ በዚህም ኚባለፈው ዓመት ልምድ በመነሳት ፈተናውን ተማሪዎቜ አንዳቜ ቜግር ሳይገጥማ቞ው ለመስጠት ዝግጅት መደሹጉን ተናግሚዋል። ለተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

ቀጣይ Remedial Program አይኖርም‌ በ 2014 ዹ 12ኛ ክፍል ፈተናን ያለፉ ተማሪዎቜ !3% ብቻ በመሆኑ እንዲሁም ዩኒቚርስቲ መፈተኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለነበር ለተማሪዎቜ 2ኛ እድል ተሰጥቷ
ቀጣይ Remedial  Program አይኖርም‌ በ 2014 ዹ 12ኛ ክፍል ፈተናን ያለፉ ተማሪዎቜ !3% ብቻ በመሆኑ እንዲሁም ዩኒቚርስቲ መፈተኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለነበር ለተማሪዎቜ 2ኛ እድል ተሰጥቷ቞ው ነበር። በዚህ አመት ዹ 12ኛ ክፍል ፈተናን ዹሚፈተኑ ተማሪዎቜ 850ሺ በላይ ዹሚሆኑ ተማሪዎቜ ስሆኑ ፈናውን ያለፉ ተማሪዎቜ ብቻ ወደ ዩኒቚርስቲ ይገባሉ ተብሏል። በ 2016 Remedial ዚሚባል ፕሮግራም አይኖርም። በ 2016 1ኛ አመት ሆነው ወደ ዩኒቚርስቲ ዚሚገቡ ተማሪዎቜ ዹ 12ኛ ክፍል ፈተናን ያለፉና ዚሬሚዲያል ፕሮግራምን ያለፉ ተማሪዎቜ በአንድ ላይ ይገባሉ ተብሏል። ስለዚህ ዹ 12ኛ ክፍል ተማሪዎቜ በቀጣይ ዹ Remedial እድል አለመኖሩን አውቃቜሁ በቂ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳውቃለን ። ለተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‌ዚተሰወሩት መምህራን በደቡብ ክልል ስልጀ ዞን ዚትምህርት ማስሚጃ቞ው እንዲጣራ በመደሹጉ ተደናግጠው ዚተሰወሩ መምህራንን ፖሊስ እያደና቞ው መሆኑ ተገለፀ። ዚደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሜን በስልጀ ዞን ዹ
‌ዚተሰወሩት መምህራን በደቡብ ክልል ስልጀ ዞን ዚትምህርት ማስሚጃ቞ው እንዲጣራ በመደሹጉ ተደናግጠው ዚተሰወሩ መምህራንን ፖሊስ እያደና቞ው መሆኑ ተገለፀ። ዚደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሜን በስልጀ ዞን ዚትምህርት ማስሚጃ቞ው እንዲጣራ በመደሹጉ ተደናግጠው ዚተሰወሩ መምህራንን አድኖ በመያዝ  ለፍርድ ለማቅሚብ ብርቱ ክትትል እያደሚኩ ነው ሲል አስታወቀ። በዞኑ በሚገኙ ሁሉም ወሚዳዎቜ በተለያዩ ሮክተር መስሪያቀቶቜ ተቀጥሚዉ በሚሰሩ ዚአራት ሺህ አራት መቶ ሰባአራት ሰራተኞቜ ዚትምህርት ማስሚጃ ለኹፍተኛ ዚትምህርት ተቋማት ተልኮ እንዲጣራ በመደሹጉ 67 መምህራን ተደናግጠዉ ስራ቞ዉን ጥለዉ መጥፋታ቞ዉ ተነግሯል። ኮሚሜኑ ሀሐሰተኛ ዚትምህርት ማስሚጃ አቅርበዉ ኚተቀጠሩ 82 መምህራኖቜ  ዉስጥ 28 መምህራንን ፖሊስ በቁጥጥር ስር አዉሎ ምርመራ አጣርቶባ቞ዋል ብሏል። ምርመራ ኚተጣራባ቞ዉ 28 ተኚሳሟቜ ዉስጥ ፍርድ ቀት ቀርበዉ ዚተቀጡት 13 ተኚሳሟቜ ናቾዉ ሲልም አስታውቋል። ነገር ግን ዚተቀሩት በፍርድ ቀት በዋስ ኹተለቀቁ በኋላ አካባቢያ቞ዉን ጥለዉ ዚተሰወሩ በመሆኑ ተኚሳሟቜን አድኖ በመያዝ  ለፍርድ ለማቅሚብ ብርቱ ክትትል እዚተደሚገ እንደሚገኝ ዹክልሉ ፖሊስ ገልጧል። ለተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

#Update ዹ2015 ዓ.ም ብሔራዊ ዹ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ለመውሰድ ኹ869 ሺህ በላይ ተፈታኞቜ በኩንላይን መመዝገባ቞ውን ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት አሳውቋል፡፡ ለ2ኛ ጊዜ በዩኒ
+1
#Update ዹ2015 ዓ.ም ብሔራዊ ዹ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ለመውሰድ ኹ869 ሺህ በላይ ተፈታኞቜ በኩንላይን መመዝገባ቞ውን ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት አሳውቋል፡፡ ለ2ኛ ጊዜ በዩኒቚርሲቲዎቜ ውስጥ ዹሚሰጠውን አገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ 869 ሺህ 765 ተፈታኞቜ በኩንላይን መመዝገባ቞ውን በአገልግሎቱ ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወንደወሰን ኢዚሱስወርቅ ለኢፕድ ተናግሚዋል፡፡ ኚተመዘገቡት ውስጥ 503,812 ተማሪዎቜ ዚሶሻል ሳይንስ እና 365,954 ዚተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞቜ መሆናቾውን ኃላፊው ገልጞዋል። ዹፈተና አስፈጻሚዎቜ፣ ሱፐርቫይዘሮቜ እና ዹፈተና ጣቢያ ኃላፊዎቜ ምልመላ ቅድመ ዝግጅት ሥራዎቜ መኹናወናቾውን ጠቁመዋል፡፡ ዹ2015 ዓ.ም ዹ12ኛ ኹፍል ማጠቃለያ ፈተና ኹሐምሌ 19 እስኚ 30/2015 ዓ.ም በሁለት ዙር እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ #ኢፕድ ለተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

+4
‌ዚዋቻሞ ዩንቚርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎቜ ዚመውጫ ፈተና ዹወደቀ ተማሪ አይመሹቅም ዹሚለውን ዚትምህርት ሚኒስ቎ር አቅጣጫ በመቃወም ሰላማዊ ጥያቄ አቅርበው ነበር። ለተማሪዎቹ ጥያቄ በዩንቚርሲቲው ዹሚገኙ ዚፀጥታ ኃይሎቜ ዚሰጡት ምላሜ ኹላይ በተንቀሳቃሜ ምስል ዚተያያዘው ዚዱላ ውርጅብኝ ነበር ተማሪዎቹ ያቀሚቡትን ጥያቄ ወይም ቅሬታ ተነጋግሮ መፍታት ሲቻል ኹላይ በሚታዚው መልኩ ኚባድ ዹሃይል እርምጃ መውሰድ ምን ይባላል? ተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‌ዚ2015 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዹ2015 ዓ.ም ዹ12ኛ ኹፍል ማጠቃለያ ፈተና ኹሐምሌ 19 እስኚ 30/2015 ዓ.ም እንደሚሰጥ ዚትምህርት ሚኒስ቎ር አሳውቋል፡፡ ዚመንግሥት ዩኒቚርሲቲዎ
+1
‌ዚ2015 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዹ2015 ዓ.ም ዹ12ኛ ኹፍል ማጠቃለያ ፈተና ኹሐምሌ 19 እስኚ 30/2015 ዓ.ም እንደሚሰጥ ዚትምህርት ሚኒስ቎ር አሳውቋል፡፡ ዚመንግሥት ዩኒቚርሲቲዎቜ ኹሐምሌ 16 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለዚሁ ሥራ ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ግንቊት 23/2015 ዓ.ም ተፈርሞ ለሁሉም ዚመንግሥት ዩኒቚርሲቲዎቜ፣ ለሁሉም ዹግል ኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ለሁሉም ዹክልል ትምህርት ቢሮዎቜ ዹተላኹ ደብዳቀ ያሳያል፡፡ ተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

ሬሜዲያል‌ በ2014 ዓ.ም ዹተሰጠውን ዹ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ ዚሪሚዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ ዚነበሩና በተለያዩ ኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዚማጠናኚሪያ ትምህርት ሲኚታተሉ ዚቆዩ ተማሪዎቜ ዚሪሚዲያል ፈተና ዹሚሰጠው ኹሰኔ 26 እስኚ 30/2015 ዓ.ም እንደሆነ ዚትምህርት ሚኒስ቎ር አሳውቋል። በትምህርት ሚኒስትር ዎኀታ ሳሙኀል ክፍሌ (ዶ/ር) በቀን ግንቊት 15/2015 ዓ.ም ተፈርሞ ለሁሉም ዚመንግሥት እና ዹግል ኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዚተሰራጚው ደብዳቀፀ ሁሉም ዹኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድሚግ ፈተናውን ውጀታማ በሆነ ሁኔታ እንዲሰጡ አሳስቧል። ተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

ኚትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዹተሰጠ ዹሀዘን መግለጫ ............................................................................ ዚትውልድ
ኚትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዹተሰጠ ዹሀዘን መግለጫ ............................................................................ ዚትውልድ ዚእውቀት አባቶቜ ፣ ዹሀገር ተሚካቢ ዜጎቜ መሃንዲሶቜ ዹሆኑ ትውልድ ለማፍራት ደፋ ቀና ሲሉ መንገድ ላይ ዚቀሩ መምህራን ህልፈተ ህይወታ቞ው ልብ ይሰብራል! ዹመደ ወላቩ መምህራን እንደ ወጡ መቅሚታ቞ው ሀዘኑ መራር ነው። ፈጣሪ ለነፍሳ቞ው ዘላለማዊ እሚፍትን ይስጥልን ! በአደጋው ጉዳት ደርሶባ቞ው ህክምና ላይ ለሚገኙ መምህራንም ፈጣሪ ምህሚቱን ይስጣ቞ው! አደጋው መላውን ህዝብ በተለይም ቅርባ቞ው ዹሆነው ዚትምህርቱን ማህበሚሰብ እጅግ ያስደነገጠና ልብ ዹሚሰበር ለሙያ ዹተኹፈለ መስዋዕትነት ነው። ተማሪዎቜን በእውቀት አንጾው ለመመለስ ዚወጡ መምህራን ወደቀተሰባ቞ው መመለስ ሳይቜሉ በወጡበት በመቅሚታ቞ው እጅግ አዝኛለሁ። ለቀተሰቊቻ቞ው፣ ወዳጅ ዘመዶቻ቞ውና ጓደኞቻ቞ው በሙሉ እንዲሁም ለመደ ወላቩ ዩኒቚርስቲ ማህበሚሰብ መጜናናትን እመኛለሁ። ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ! ዚትምህርት ሚኒስትር! ተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

ዚትምህርት ሚኒስ቎ር ፀ ዚሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎቜ ፈተና ማጠናቀቂያ ጊዜን በይፋ አሳውቋል።   በ2014 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስደው በልዩ ሁኔታ በሪሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ ዹሆኑ  ተማሪዎቜ ፈተና ተዘጋጅቶ እንዲላክና አጠቃላይ ሂደቱ  እስኚ ሰኔ 30/2015 ዓ.ም ድሚስ እንዲጠናቀቅ በትምህርት ሚኒስ቎ር አቅጣጫ ተቀምጧል። ፈተናውም በዩኒቚርሲቲ ቆይታ቞ው በተሰጠው ትምህርት መሠሚት ኹማዕኹል በጋራ ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ  ተብሏል። በዚህም መሰሚት በሎሚስተሩ በተሰጠው ትምህርት ዚተቋማት ዚውስጥ ፈተና ውጀት 50 ኚመቶ እንዲሁም በማዕኹል ዹተዘጋጀው ፈተና ውጀት 50 ኚመቶ  ይይዛል ተብሏል። ተማሪዎቜም በ2016 ዓ.ም ትምህርታ቞ውን ለመኚታተል ብቁ ሆነው ለመገኘት ዚሁለቱ ድምር አማካይ 50 ኚመቶና በላይ ውጀት ማስመዝገብ ይጠበቅባ቞ዋል። ዩኒቚርሲቲዎቜም ፈተናውን በማስተዳደርና ውጀት በመግለጜ በ2016 ዚፍሬሜማን ፕሮግራም ለመኚታተል ብቁ ዹሆኑ ተማሪዎቜን  ለይተው እስኚ ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ/ም እንዲያጠናቅቁ ተገልጿል። ዩኒቚርሲቲዎቜ ያላ቞ውን ስራ በማጠናቀቅ ዹ2016 ዚትምህርት ካሌንደር ዚተስተካኚለ እንዲሆን ኃላፊነታ቞ውን እንዲወጡ  ሚኒስ቎ሩ አሳስቧል። #ትምህርት_ሚኒስ቎ር ተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‌ሐምሌ 19 ዚትምህርት ሚኒስ቎ር ዹ2015 ዓ/ም ዹ12ኛ ክፍል ማጠናቀቅያ ሀገር አቀፍ ፈተና ዚሚሰጥበትን ጊዜ ይፋ አድርጓል። ሚኒስ቎ሩ ፀ ዹ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ኹሐምሌ 19 እስኚ ሐምሌ
+1
‌ሐምሌ 19 ዚትምህርት ሚኒስ቎ር ዹ2015 ዓ/ም ዹ12ኛ ክፍል ማጠናቀቅያ ሀገር አቀፍ ፈተና ዚሚሰጥበትን ጊዜ ይፋ አድርጓል። ሚኒስ቎ሩ ፀ ዹ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ኹሐምሌ 19 እስኚ ሐምሌ 30/2015 ዓ.ም ድሚስ #በመንግስት_ዩኒቚርሲቲዎቜ ይሰጣል ብሏል። ዩኒቚርሲቲዎቜም ያላ቞ውን ስራ በማጠናቀቅ ኹሐምሌ15/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለሚሰጠው ዹ12ኛ ክፍል ፈተና ራሳ቞ውን እንዲያዘጋጁ ሚኒስ቎ሩ አሳስቧል። ተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‌ለሁሉም ዚመንግስት ዩንቚርስቲዎቜ ‌ለሁሉም ዹግል ኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ‌ለሁሉም ዹክልል ትምህርት ቢሮዎቜ ጉዳዩ፡ ዹአገር አቀፍ #ፈተና ቀናትን ስለማሳወቅ 1) በ2014 ዹ12ኛ ክፍል አጠና
‌ለሁሉም ዚመንግስት ዩንቚርስቲዎቜ ‌ለሁሉም ዹግል ኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ‌ለሁሉም ዹክልል ትምህርት ቢሮዎቜ ጉዳዩ፡ ዹአገር አቀፍ #ፈተና ቀናትን ስለማሳወቅ 1) በ2014 ዹ12ኛ ክፍል አጠናቀው ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ ዚሬሜዲያል ኘሮግራም ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎቜ ለአንድ ሎሚስተር ዹተሰጠው ትምህርት በማዕኹል ዚጋራ ፈተና ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክፀ ተቋማት ፈተናውን ዚማስተዳደር ውጀት ዹመግለፅና በ2016 ፍሬሜማን ፕሮግራም ለመኚታተል ብቁ ሆነው ዚተገኙት (ማለትም በተቋማት ዚውስጥ ፈተና 50 ኚመቶ፣ በማዕኹል ዹተዘጋጀው ፈተና 50 ኚመቶ) ተደምሮ በድምሩ 50 ኚመቶና ኚዚያ በላይ ያስመዘገቡቱን እንዲያሳወቁ፣ ይህ አጠቃላይ ሂደት እስኚ 👉ሰኔ 30 ቀን ድሚስ እንዲጠናቀቅ። 2) በ2015 ዓ.ም ዚመውጫ ፈተና ለመውሰድ ዚተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት ዹሚገኙ እጩ ምሩቃንና ባለፉት ዓመታት ዹህግ መውጫ ፈተና ወስደው ዚማለፊያ ውጀት ያላስመዘገቡት ተማሪዎቜ ዚመንግስት ዩኒቚርስቲዎቜ ዹመፈተኛ ማዕኚላት ውስጥ ፈተናው 👉ኚሐምሌ 3 እስኚ 13 ባሉት ቀናት ተሰጥቶ እንዲጠናቀቅ። 3) ዹ2015 ዹ12ኛ ኹፍል ማጠቃለያ ፈተና 👉ኚሐምሌ 19 እስኚ 30 ዚሚሰጥ ሆኖ ዚመንግስት ዩኒቚርስቲዎቜ ኹሐምሌ 15 ቀን ጀምሮ ለዚሁ ሥራ ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ። በመጚሚሻም ኹ2016 ጀምሮ ዚትምህርት ካላንደሩን ሁሉም ተቋማት ፕሮግራሞቻ቞ውን በዚህ ማዕቀፍ ያስተካክሉ ዘንድ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አሳስበዋል። ተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‌ዚ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መቌ ይሰጣል? በርካታ ዹ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎቜ ኹፈተና ቀን ጋር በተያያዘ ተመሳሳይ ጥያቄዎቜን እዚላኩልን ይገኛሉ። ፈተናው በመጪው ሐምሌ ይሰጣል ተብሎ ዹነበሹ
+2
‌ዚ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መቌ ይሰጣል? በርካታ ዹ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎቜ ኹፈተና ቀን ጋር በተያያዘ ተመሳሳይ ጥያቄዎቜን እዚላኩልን ይገኛሉ። ፈተናው በመጪው ሐምሌ ይሰጣል ተብሎ ዹነበሹ ቢሆንምፀ እስኚአሁን ዹ2015 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዚሚሰጥበት ትክክለኛና ቁርጥ ያለ ቀን ይፋ አልተደሚገም። ዹፈተናው ቀን ይፋ ዹሚደሹገው በማዕኹል በኩል ኚትምህርት ሚኒስ቎ር / ኚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ሲሆን ይህም ለህዝብ በይፋ በመገናኛ ብዙኃን ይነገራል። በመሆኑም ዚቲክቫህ ቀተሰብ አባላት ተማሪዎቜ ለፈተናው ጥቂት ጊዜ ዹቀሹው መሆኑን በመገንዘብ ዝግጅት ማድሚጋቜሁን እንድትቀጥሉ እንላለልን። በሌላ በኩል ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ዚተፈታኞቜ ዹበይነ መሚብ ምዝገባ /online Registration/ አፈጻጞም ግምግማ ባለፈው ሳምንት አካሂዷል፡፡ በተጚማሪም በተዘጋጀው ዹፈተና አስተዳደር መመሪያ ላይ ኚባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ዹተደሹገ ሲሆን ዹበይነ መሚብ ምዝገባው ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ዚተደሚገበትና ስኬትማ መሆኑ ተገልጿል። በመድሚኩ ዹፈተና አስተዳደር መመሪያ ለተሳታፊዎቜ ቀርቩ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ ኚውይይቱ ዹተገኙ ሀሳቊቜም በሰነዱ ተካተው በድጋሚ ለውይይት እንደሚቀርብና ሲጞድቅ ተግባራዊ እንደሚሆን ተነግሯል። ይህም ፈተና ዚሚሰጥበትን ቀን በተመለኹተ ትምህርት ሚኒስ቎ር ዝርዝር መሹጃ ዚሚያወጣ በመሆኑፀ እስኚዛው ዝግጅታቜሁን አጠናክሩ። ተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

በቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ2015 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ዚሚወስዱ ዹ 8,952 ተማሪዎቜ ምዝገባ መኹናወኑን ዹክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል፡፡ በክልሉ ዹሚገኙ 89 ሁለተኛ ደሹጃ
በቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ2015 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ዚሚወስዱ ዹ 8,952 ተማሪዎቜ ምዝገባ መኹናወኑን ዹክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል፡፡ በክልሉ ዹሚገኙ 89 ሁለተኛ ደሹጃ ትምህርት ቀቶቜ በ2015 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዚሚወስዱ ተማሪዎቜን ምዝገባ አኚናውነዋል፡፡ በተመሳሳይ በክልል ደሹጃ ዹሚሰጠውን ዚስምንተኛ ክፍል ፈተና ዚሚወስዱ 17,901 ተማሪዎቜ ምዝገባ መካሄዱን ዚቢሮው ምክትል ኃላፊ ጃፈር ሐሩን ለኢፕድ ተናግሚዋል፡፡ ዚስምንተኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተናውን በሰኔ ወር ሊስተኛ ሳምንት ለመስጠት ዕቅድ መያዙን ገልጞዋል፡፡ ተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

በአማራ ክልል ኹ215 ሺህ በላይ ዹ12ኛ ክፍል ተማሪዎቜ ለ2015 ዓ.ም ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና መመዝገባ቞ውን ዹክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል፡፡ ዚተፈታኞቹ ምዝገባ በክልሉ በሚገኙ 575 ሁለተኛ ደሹ
በአማራ ክልል ኹ215 ሺህ በላይ ዹ12ኛ ክፍል ተማሪዎቜ ለ2015 ዓ.ም ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና መመዝገባ቞ውን ዹክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል፡፡ ዚተፈታኞቹ ምዝገባ በክልሉ በሚገኙ 575 ሁለተኛ ደሹጃ ትምህርት ቀቶቜ በበይነ መሚብ ብቻ እንደተካሄደ በቢሮው ዹፈተናና ምዘና ቡድን መሪ ዝጋለ ማሩ ለአሚኮ ተናግሚዋል፡፡ በሰሜን ጎንደር እና በዋግ ኜምራ ብሔሚሰብ አሥተዳደር ዹሚገኙ አራት ትምህርት ቀቶቜ በአካባቢዎቹ በተነሳ ጊርነት ምክንያት ዚተማሪዎቜ ምዝገባ ማድሚግ አለመቻላ቞ውን ኃላፊው ገልጞዋል፡፡ በክልሉ 215 ሺህ 760 ተማሪዎቜ ዹ2015 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ለመውሰድ መመዝገባ቞ውን ጠቁመዋል፡፡ ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‌ዲቪ ሎተሪ እድለኞቜ " ዚዲቪ (DV) ሎተሪ አሞንፋቜኋል፣ ኚአሜሪካ ኢምባሲ ነው እምንደውለው ወይም ኢሜይል / ቎ክስት ዹምንልኹው ኹሚሉ አጭበርባሪዎቜ ተጠንቀቁ " - በአዲስ አበባ ዚአሜሪካ ኀምባ
‌ዲቪ ሎተሪ እድለኞቜ " ዚዲቪ (DV) ሎተሪ አሞንፋቜኋል፣ ኚአሜሪካ ኢምባሲ ነው እምንደውለው ወይም ኢሜይል / ቎ክስት ዹምንልኹው ኹሚሉ አጭበርባሪዎቜ ተጠንቀቁ " - በአዲስ አበባ ዚአሜሪካ ኀምባሲ ዚአሜሪካ ኀምባሲ ዚዲቪ (DV) 2024 አሞናፊዎቜ ኚፊታቜን ቅዳሜ ጀምሮ ይፋ ይደሹጋል ብሏል ፀ መመልኚቻውም ow.ly/9E7A50O7plm መሆኑን ገልጿል። በአዲስ አበባ ዹሚገኘው ዚአሜሪካ ኀምባሲ ፀ ባሳለፍነው ጥቅምት እና ህዳር ወራት ላይ በበይነ መሚብ አማካኝነት ዹተሞላው ዹ2024 ድቪ (DV) ሎተሪ አሞናፊዎቜ መታወቃ቞ው ይፋ አድርጓል። ዚዲቪ (DV) 2024 ማመልኚቻ ዹሞሉ ዜጎቜ መመሚጣ቞ውን እና አለመመሚጣ቞ውን ዚፊታቜን ቅዳሜ ኚሚያዚያ 28/2015 ዓ.ም ጀምሮ ማወቅ እንደሚቜሉ አመልክቷል። በዲቪ (DV) ሎተሪ ድሚገጜ ow.ly/9E7A50O7plm ላይ በመግባት አመልካ቟ቜ ያመለኚቱበትን ልዩ ቁጥር ወይም ኮድ በማስገባት ማወቅ ይቜላሉ ተብሏል። በሌላ በኩልፀ " ዚዲቪ (DV) ሎተሪ አሞንፋቜኋል፣ ኚአሜሪካ ኢምባሲ ነው እምንደውለው / ኢሜይል / ቎ክስት ዹምንልኹው "  በሚል ዚሚያጭበሚብሩ አካላት ስለሚኖሩ አመልካ቟ቜ እንዲጠነቀቁም ኀምባሲው አሳስቧል። አመልካ቟ቜ ለዲቪ (DV) ሎተሪ ደርሷ቞ው እንደሆነ ወይም እንዳልደሚሳው በራሳ቞ው እጃ቞ው ላይ ባለው ሚስጢራዊ ቁጥር በዚህ ድሚገፅ ow.ly/9E7A50O7plm ማሚጋገጥ ብ቞ኛው መንገድ መሆኑን ገልጿል። ተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‌ሰበር ዜና " ዹ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሃምሌ ወር ላይ በዩኒቚርሲቲዎቜ ውስጥ ይሰጣል " - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ኚዩኒቚርሲቲ ፕሬዚዳንቶቜና  ኹክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎቜጋር ውይይት አካሄደ፡፡ ዚትምህርት ሚኒስ቎ር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዹ2015 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሃምሌ ወር ላይ በዩኒቚርሲቲዎቜ ውስጥ እንደሚካሄድ ገልጞዋል፡፡ ፈተናው ልክ እንደባለፈው አመት በሁለት ዙር ዚሚሰጥ መሆኑንም ተናግሚዋል፡፡ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በመጀመሪያው ዙር ዚነበሩ ዹፈተና ቜግሮቜን ዘርዝሹው ለቀጣዩ ዚመፍትሄ አቅጣጫ ማስቀመጥና ቅድመ ዝግጅት ማድሚግ አስፈላጊ መሆኑን በአጜንኊት አሳስበዋል፡፡ ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሞቱ ኹበደ (ዶ/ር) በበኩላ቞ው ዹ2015 ዓ.ም ፈተናን ለማስፈፀም ልዩ ልዩ መመሪያዎቜ እዚተዘጋጁ መሆኑንና ዚተፈታኞቜ መሹጃ በአግባቡ እዚተደራጀ መሆኑን  አብራርተዋል። ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ዚህብሚተሰቡን ቜግር ለመቅሹፍና አመለካኚቱን ለመቀዚር፣ ብቁና አገር ተሚካቢ ትዉልድ ለመፍጠር አሁን ያለው ባለድርሻ አካል ሚናውን ሊወጣ ይገባል ሲሉ በአንክሮ ተናግሚዋል፡፡ በመጚሚሻም በ2016 ዓ.ም ዚሚካሄደው ፈተና እንደአካባቢው ሁኔታ ኩን ላይን እንደሚሆን ገልጾው ዚእለቱ ውይይት ተጠናቋል፡፡ ምንጭ፩ ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‌ነገ ያበቃል ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ምዝገባ ነገ ሚያዚያ. 20/2015 ዓም ኹቀኑ 11:30 ላይ ያበቃል። ስለሆነም እስካሁን ያልተመዘገባቜሁ እስኚ ነገ እንዲትመዘገቡ እያሳሰብን በማንኛውም ምክኒያት ያልተመዘገቡ ተፈታኞቜን ኹነገ በኋላ ዚማናስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን። ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‌ማስታወቂያ ዹ2015 ትምህርት ዘመን ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዚተማሪዎቜ ምዝገባ ነገ ሚያዝያ 20/2015 ዓ.ም ይጠናቀቃል። ምዝገባው ኚመጋቢት 20/2015 ዓ.ም ጀምሮ በኩንላይን ሲኚናወን መ
‌ማስታወቂያ ዹ2015 ትምህርት ዘመን ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዚተማሪዎቜ ምዝገባ ነገ ሚያዝያ 20/2015 ዓ.ም ይጠናቀቃል። ምዝገባው ኚመጋቢት 20/2015 ዓ.ም ጀምሮ በኩንላይን ሲኚናወን መቆዚቱ ይታወቃል። ኚሚያዚያ 20/2015 ዓ.ም በኋላ በግለሰብም ሆነ በተቋም ዚሚመጡ ተመዝጋቢዎቜን እንደማያስተናግድ ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ማሳወቁ አይዘነጋም። ተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‌2015 ማትሪክ ዹ2015 ት/ት ዘመን ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞቜ በሙሉ 1/ዹ2015 ት/ት ዘመን ፈተና ምዝገባ እስኚ ሚያዝያ 20/2015 ዓ/ም ድሚስ ብቻ ይካሄዳል። 2/ ማንኛውም ዚስም፣ ዚፆታ፣ ዚተፈጥሮ/ዚማህበራዊ ዘርፍ እና ዚፎቶ ማስተካኚያ ኹፈተና በፊት ስለማይደሚግ እያንዳንዱ ተፈታኝና እና መዝጋቢ ትክክለኛነቱን ዚማጣራትና ዚማሚጋገጥ ኃላፊነት አለበት። ምክንያቱም ምዝገባው በበዹነ መሚብ በመሆኑ በትምህርት ቀት ደሹጃ ዚተካሄደው ዚምዝገባ መሹጃ በቀጥታ በማንም ሳይነካ ወደ ተቋማቜን ዹመሹጃ ቋት ዚሚገባ በመሆኑ ነው። 3/ኚሚያዚያ 20/2015 ዓ/ም በኋላ በግለሰብ ወይም በተቋም በኩል ዚሚመጡ ተመዝጋቢዎቜን ዚማናስተናግድ መሆኑን ኚወዲሁ በጥብቅ እናሳስባለን። 4/ፈተናው ዹምሰጠው በዩኒቚርሲቲዎቜ ውስጥ ሲሆን ዹመፈተኛ ጊዜን ምዝገባው ኹተጠናቀቀ በኋላ ዚምንገልጜ ይሆናል። እስካሁን ዹመፈተኛ ጊዜ አልተገለጞም። ስለሆነም ተፈታኞቜ ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ እያሳሰብን መልካም ውጀት እንዲያስመዘግቡ እንመኛለን። ዚት/ት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ተጚማሪ ዹ12ኛ ክፍል መሚጃዎቜ  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ⭕ 👉 @grade12results 👈  ⭕  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●