cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ASD AJ LAH

ካነበብኩት…

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
645
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+467 روز
+5430 روز
توزیع زمان ارسال

در حال بارگیری داده...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
تجزیه و تحلیل انتشار
پست هابازدید ها
به اشتراک گذاشته شده
ديناميک بازديد ها
01
ጠያቂ👉🏻 ላለፉት 21 አመታት በየመንገዱ ዳእዋ ስታደርግ መድከም መሰለቸት ተስፋ መቁረጥ አልገጠመህም? ፈቂ 👉🏻ከአላህ የተሰጠኝ ቅዋ አለ አንድም ቀን እንደዛ አይነት ስሜት ተሰምቶኝ አያውቅም ዳእዋን ስጀምር ሰዎች እናቴ ጋር ሄደው ይህው አንድ ልጅሽ አበደ መንገድ ለመንገድ መልፍለፍ ጀመረልሽ አሏት። እኔም አብሽሪ ይሄ የአንቢያዎችና የነብያቶች ስራ ነው ብዬ አሳመንኳት። አሁን እኔ የሚያሳስበኝ ይሄን ስራ የሚያስቀጥል ተተኪ ትውልድ አለመኖሩ ነው። እኛ ሰዎችን ወደ ሰላም ካልተጣራን ሸይጣን ወደ እሳት ይጣራብናል። አላህ ይዘንልህ‼
10Loading...
02
የበታቻችሁን ተመልከቱ ሲባል ብዙዋችን የምንዞረው ከኛ ይበልጥ ድሃ ወደሆኑ ሰዎች ነው ። አላህ በአንተ ላይ የዋለውን ፀጋ ከመዘንጋት ይመስላል ። ይህ ዝንጋቴ ነው ትክክለኛውን ሹክር እንዳናደርግ የሚያግደን ። እዚሁ መንደር እገሌ የተባለ ሰው በዚህ በሽታ ስለተጠቃ ገንዘብ እንርዳው ሲባል እንመለከታለን ። አላህ በታማሚው ቦታ ስላላደረገን ለማመስገን ሁለቴ ማሰብ የሚፈልግ አይደለም ። ጤና ሐብት መሆኑ የሚገለፅልን ሆስፒታሎች ውስጥ ስናዘወትርና እንዲህ ያሉ መሰል ታካሚዎችን ስንመለከት ነው ፣ ዕድሜ ፀጋ መሆኑ የሚገለፅልን መቃብሮችን ስንዘይር ነው ፣ ከሁሉ በላይ ግን «ዛሬ»ን የመሰለ ስጦታ የለም ። ለዚህም ነው ። ከእንቅልፋችን እንደተነሳን ‹‹ አልሐምዱሊላሂ ለዚ አህያና……›› የምንለው ። አዎ! ትንሿን ሞት አስሙተህ በዚያው ሳታስቀር ህያው ያደረግከን አላህ ሆይ ምስጋና ይገባህ የምንለው ። ቀናችንንም በምስጋና እንድንጀምር የተደረገውም ለዚሁ ነው ። አላህ ‹‹ ዛሬን ›› ሰጥቶሃል ። እርሱ የሚወደው አልያ የማይወደው ማድረግ ግን የኛው ምርጫ ነው ። ከወደደው ጥቅሙ ለኛ ካልወደደው ጉዳቱ ለኛ እንጂ እኛ ቀኑን ሙሉ ብናምፀው አላህን አንጎዳውም ቀኑን ሙሉ ብናመልከው አላህን አንጠቅመው ። ለእኛው ነው ወገን ለእኛው ! አብዱ ረዛቅ
720Loading...
03
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ ⏰#አልዓርቢዓዐ 0️⃣7️⃣ #ዙልቀዓዳ 1️⃣4️⃣4️⃣5️⃣ ሂ
810Loading...
04
ከአሳሳ እስከ ሮቤ፣ ከኮኮሳ እስከ አዳማ ፣ ከአርሲ እስከ ባሌ፣ እስከ ሸገርና ጎንደር ድረስ ጭምር ታሪክ አለን ከዚህ ሰው ጋር፡፡ በተለያዩ ከተሞች እየተዘዋወረ በጎዳና ላይ ደዕዋ ሲያደርግ ታውቁታላታችሁ፡፡ ምንም ማንንም የማይፈራ ሙጃሂድ ነው። ስፒከሩ በተዳጋጋሚ ታስሮበት በየፖሊስ ጣቢያው ሲንከራተትም አጋጥሞኛል፡፡ ከልጅነት እስከ ወጣትነትና ጎልማሳነት ምናልባት እስካዛሬዋ እስከመጨረሻዋ የዱንያ ላይ ቀን ድረስ ሐያቱን በሙሉ በደዕዋ አሳልፏል፡፡ አላረፈም። ኢስላምን ለማድረስ ሁሌ እንደተጓዘ ስለማየው ቤት ይገባ ይሆን ብዬ እጠይቃለሁ ብዙ ጊዜ፡፡ ዛሬ ሻሻመኔ ላይ ድንገት ማረፉን ሰማሁ፡፡ ፈቂ ገለቶ አላህ ይዘንልህ፡፡ ሰው በኖረበት ነገር ላይ ይሞታል፤ በሞተበት ነገር ላይም ይቀሰቀሳል፡፡ ደጋግ ባሮችህ ወዳንተ እየመጡ ነው። አላህ ሆይ! ዐለይከ ረበና ቢሑስኒልኺታሚ እንላለን ። Abx
990Loading...
05
ይህንን ቻሌንጅ ተቀላቀሉ‼ ================== ✍ ይህንን ባለ 15 ገፅ የመንግስትንና የኃይማኖቶችን ግንኙነት በተመለከተ በዝርዝር ያብራራል የተባለለትን አዲሱን ረቂቅ አዋጅ ሶፍት ኮፒ በስልካችሁ ላይ ላለ ሰው ሁሉ፣ በምታገኙት ግሩፕና ቻነል እንዲሁም በማንኛውም ገፅ ላይ በማሰራጨት መረጃው በእያንዳንዱ ሙስሊም እጅ ላይ ደርሶ እንዲያነበው እናድርግ። ለዚህ ረቂቅ አዋጅ ግብዓት ይሆን ዘንድ የቀረበውን ባለ 164 ገፅ ጥናት ማንበብ ለሚፈልግም ሶፍት ኮፒው በዚህ ሊንክ ይገኛል። https://t.me/MuradTadesse/35708 * ሰው ጽሑፉን ዝም ብሎ ቢያነበውም ከላይ ሲመለከታቸው አንቀፆቹ ጤነኛ ሊመስሉት ስለሚችሉ፤ ፍንጭ ይሰጠው ዘንድ ረቂቅ አዋጁ ከኛ ከሙስሊሞች ጋር የሚያጋጩትንና ጥያቄ የሚያጭሩ 15+ ነጥቦች የተጠቀሱበትን ይህንን ጽሑፍም ጨምሩለት። https://t.me/MuradTadesse/35742 ይህንን የአዲሱን ረቂቅ አዋጅ PDF ለሁሉም በማሰራጨት መረጃው እንዲደርሰው እናድርግ። የላ ቻሌንጃችን ይጀመር! አብዛሃኛው ሰው ከጀርባ ምን እየተካሄደ እንዳለ መረጃው የለውም። ጭራሽ አዲስ ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱን ራሱ እንኳን ከመረጃው የራቀው ማኅበረሰብ ሚዲያ ላይ አለን የሚለው ራሱ በበቂ ሁኔታ የሰማ አይመስለኝም። ወሬውን ቢሰማም ዶክመንቱ በተጨባጭ ያልደረሰው ብዙ ነውና ይህንን በማድረግ ግንዛቤ እንፍጠር። የፌዴራሉ መጅሊስም በዚህ ጉዳይ ተቃውሞ ያወጣውን ባለ 4 ገፅ መግለጫ አያይዘን እናሰራጨው። መግለጫው በዚህ ሊንክ ይገኛል። https://t.me/MuradTadesse/35632?single ከተቋማችንም ጎን እንቁም። የላ! ከአሁኑ ይጀመርና ያሰራጨ ሰው ለማነቃቂያ ስክሪን ሹቱን ኮመንት ላይ አስቀምጡት!
763Loading...
06
ከቀድሞ ባለቤቱ የተፋታበትን ከትውልድ መንደሩ የተሰደደበትን ምክንያት ሲያስረዳ ወላህ ያስቀና ነበር። የሁሌም አደራው "ውጡ! ወደ አላህ መንገድ ተጣሩ" የሚል ቃል ብቻ ነበር። ከዚህ ንግግሩ የሚገናኝ ቃልን እንጂ ከአፉ ሌላን ቃል አድምጨ አላውቅም።
970Loading...
07
ይሄ ዛሂድ ይህ መንገደኛ የአላህ ባሪያ አለፈን ሰማሁ😢 ኢናሊላሂ ወኢናኢለይሂ ራጂኡን ! ዱኒያን ለአላህ ብሎ ትቶ በዝህድና የአላህና መልእክተኛውን መልእክት እያስተላሉፉ ኖሮ መሞት ምንኛ መታደል ነው ! እንዳለመታደል ሆኖ ልፋቱን ባናግዘውም ተገቢውን ክብር ባንሰጠውም አላህ ግን አንዱንም መልካም ስራውን ሳያስቀር በብዙ አባዝቶ ትልቅ ደረጃን እንደሚያጎናፅፈው ተስፋ እናደርጋለን ! አላህ ሆይ በራህመትህ ተቀበለው ከዚህች ዱኒያ በበለጠቺዋ ጀነትህም አጣቅመው ! ሰዒድ
970Loading...
08
ወንድማችን ፈቂ ገለቶ አላህ ይዘንለት። በተለይ መርካቶ አካባቢና በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች በአደባባይ ዳዕዋው ይታወቃል። ዛሬ ሻሸመኔ ላይ ወደ አኺራህ መሄዱን ሰማን። አላህ ይዘንለት፤ መልካም ሥራውንም ይቀበለው።
960Loading...
09
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ ⏰ #አሱለሳዒ 0⃣6⃣ #ዙልቀዓዳ  1⃣4⃣4⃣5⃣ ሂ
1110Loading...
10
የአብዛኛው ወጣት ጥያቄ ይመስለኛል... "የቱ ጋር ነው የተሳሳትኩት ፈጣሪዬ??.. ለምን እድገቴ እንዲህ የዘገየ መሰለ?.. የቱ ነገር ነው ከህልሜ ጋር ያለኝን ርቀት ያሰፋብኝ?.. የቱ ልምምዴ?.. የትኛውስ ክፉ ስራዬ ነው መንገዴን ያረዘመው?......" ወጣቱ ይጠይቃል.. አሁን ግን የምር ነው የሚጠይቀው.. መልሱ ደግሞ ለአሁን አጥጋቢ ባይመስለንም እንዳንሰላች.. 🙏 የእውነት ፈጣሪያችን የሻትነውን ሁሉ የሚሰጠበት የራሱ የሆነ ፍፁም ትክክል የሆነ ወቅት አለው.. 😊 'ነገርን ሁሉ ውብ አድርጎ የሰራው በጊዜው ነው አዎ በጊዜው!!.. በእርግጥም እኛም ቀን አለን እሺ አህባቢ 👐❤
1321Loading...
11
نذكركم غزة 🇵🇸💣
1290Loading...
12
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ ⏰ #አልስነይን 0⃣5⃣ #ዙልቀዓዳ 1⃣4⃣4⃣5⃣ ሂ
1220Loading...
13
እንግዳ ሆኘ በተጠራሁበት ቤት ምግብ ሲቀርብ Me:- ባላየ
1330Loading...
14
ኒካህ ለማሰር በ3500 የተከራየሀውን ቤት አልጋ ብቻ ሲሞላው ቤቷን የምታይበት አተያይ😓
1660Loading...
15
📆 #በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ ⏰#አልአሃድ 0⃣4⃣ #ዙልቀዓዳ 1⃣4⃣4⃣5⃣ ሂ
1801Loading...
16
መቃወም ያለብን ከመጽደቁ በፊት ነው። ምክንያቱም ያለአግባብ ሌላ መስዋዕትነት ላለመክፈል! ይህ ማለት ግን ቢጸድቅ ራሱ እንደተለመደው መስዋዕትነት ከፍለን እምነታችንን እናስከብራለን እንጂ አንድ ጊዜ ከጸደቀ የማይነካ ነው ማለት አይደለም። በባሌም በቦሌም እምነታችንን የሚነካን ነገር መጋፈጣችን ላይቀር ነገር፤ አጉል ሌላ ገመድ ጉተታ ውስጥ ባያስገቡን ጥሩ ነው። እነርሱም ያለው ሃገራዊ ተጨባጭ አንሷቸው ሌላ የግጭት ድግስ ባይጠምቁ ይሻላል። ሙስሊም በእምነቱ ስለማይደራደር ከታሪክ ቢማሩ ይሻላል። ♠ ለጉዳዩ አዲስ የሆነ ይህን ጽሑፍ ያንብብ፦ https://t.me/MuradTadesse/35687
1720Loading...
17
Media files
1270Loading...
18
ትኩረት ያልሰጠነው አዲሱ ረቂቅ አዋጅ‼ =========================== (ይህ ጉዳይ ከጸደቀ በኋላ ሌላ ዙሩ በከረረ ትግል ውስጥ ሳንገባ በፊት ከወዲሁ እምነታችንን በማይነካ መልኩ መዘጋጀቱን ማረጋገጥ አለብን!) || ✍ ካስታወሳችሁ ከአንድ ወር በፊት ከተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎችና ከተለያዩ የኃይማኖት ተወካዮች ጋር በተናጠል ውይይት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ በተለይ ከኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አባቶችና ከኛ ከእስልምና ኃይማኖት መሪዎቻችን ጋር ባደረጓቸው ውይይቶች መንግሥት በቅርቡ ኃይማኖትን የተመለከተ ሕግ እንደሚያወጣ መናገራቸው ይታወሳል። በተለይ ከመጅሊስ መሪዎች ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት መስጂዶች የሚያደርጉት የአዛን ጥሪ፣ እንዲሁም በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የሚከናወኑ ቅዳሴና አስተምህሮዎች ሌላውን ሰው ማወክ ስለሌለባቸው አስቡበት በማለት ስለሚወጣው ሕግ ይዘት ፍንጭ ሰጥተው ነበር።  መንግሥትና ሃይማኖት አንዱ በአንዳቸው ተግባርና እንቅስቃሴ ውስጥ ጣልቃ አይገቡም የሚለውን ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌ መሠረት በማድረግ፣ መንግሥት ከኃይማኖት ተቋማት ጋር ያለውን ግንኙነት በግልጽ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ በፍትሕ ሚኒስተር በኩል ተዘጋጅቶ አሁን ላይ በሰላም ሚኒስተር አስተባባሪነት ከተለያዩ አካላት ጋር ውይይት መደረግ ተጀምሯል። ይህ አዲሱ አዋጅ በርካታ ክልከላዎችን የያዘ ሲሆን፤ የሙስሊሞችን በጀማዓህ ሶላት መስገድ፣ የእህቶችን ጂልባብና ኒቃብ መልበስ፣ ጀለቢያ፥ አማኢምና ኮፍያ መልበስና የመሳሰሉትን ለማገድ በር የሚከፍት ህግ ተካቶበታል። የነርሱ እሳቤ የሌላውንም እምነት ተከታይ ኃይማኖታዊ አለባበሱንና በቡድን ማምለክን ስለምንከለክል፤ ሙስሊሞችንም «እናንተን ብቻ ሳይሆን ሌላውንም ነው የከለከልነው!» በሚል ሽፋን በመሞገት መከልከል አስበዋል። እዚህ ላይ ያልገባቸው ነገር የእያንዳንዱ እምነት ዶክትሪን የተለያዬ መሆኑን አለማወቅ ነው። በተለይም የእስልምና እምነት ህግጋት በየትኛውም ታዕምር ቢሆን በሰው ሠራሽ ህግ የሚሻሩ አለመሆናቸውን መረዳት ተስኗቸዋል። እነርሱ ሲጀመር ከፊሎቹ ራቁታቸውን መሄድ ነው የቀራቸው። እንኳን ተከልክለው በፈቃደኝነትም እየተገበሩት አይደለም። ታዲያ እነርሱ ከተዘናጉ እኛም አብረን መታፈን አለብን? በጭራሽ! አይደለም ኢትዮጵያ አዲስ የምታዘጋጀው ህግ፤ የዓለም መንግስታት ተባብረው አዋጅ ቢያወጡ፤ እስልምናችንን ከተቃረነ ማንም አይሰማቸውም። የራሳቸውን እንደፈለጉ ያድርጉ። የኛን ግን እንዳያስቡት። በተጨማሪም 24 ሰዓት በካሴት ሳይቀር ተከፍቶ የሚለቀቅን የቤተ ክርስቲያን ቅዳሴና መዝሙር በቀን 5 ጊዜ 5 ደቂቃ ለማትሞላ አጋጣሚ የሚደረግን የአዛን ጥሪ አወዳድሮ አብሮ ጨፍልቆ ለመከልከል መጋጋጥ በየትም ተሰምቶ አይታወቅም። መንግስት አዛን ከከለከለን በተለይም በዐረቡና በሙስሊሙ ዓለም በኩል ያለውን ግንኙነት እንደሚያበላሽ ጠንቅቆ ይወቀው። በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ የሆነ መከራ እንዲለብስ ነው የሚሆነው። ቀድሞ ከሙስሊሙ ተወካዮችና ምሁራን በኩል የተሰጣቸውን ሃሳብ ወደ ጎን በተመው፤ ይህን ረቂቅ የሚያዘጋጁ አካላት።ሙስሊሙን የሚጨፈልቅ ህግ ማውጣታቸው አላማቸው ምን እንደሆነ ግራ ያጋባል። ባለማወቅ ነው እንዳይባል ቀድሞ መረጃ ተሰጥቷቸዋል፤ ግን ወደ ጎን ብለውት በራሳቸው አካሄድ መሄድን መርጠዋል። በርግጥ ፍትሕ ሚኒስተር ውስጥ እነማን እንደሆኑ እናውቃለን። ከአሁን በፊትም ኡማውን ከወያኔ ጀምሮ ሲጨቁኑ የነበሩ አካላት አሉበት። በአጭሩ እየመጣ ያለው ረቂቅ አዋጅ የእምነት ነፃነትን የሚጋፋና ኃይማኖቶች ከእምነታቸው አስተምህሮ ይልቅ በሃገሪቱ መንግስት ቁጥጥር እንዲዳኙ የሚያደርግ አደገኛ አዝማሚያ ያለው ነውና ከወዲሁ እንዲስተካከል ማድረግ አለብን። እኛ በደፈናው ባልተጻፈ ህግ ሲጨቁኑን የነበረውን ጉዳይ ጽፈው በግልፅ አስተካክለው ይመጣሉ ስንል፤ ጭራሽ በግልፅ ከልክለውና ሌላም ዱብእዳ አክለው መጡ። ማንም አይሰማቸውም! ህዝብ መረጃ ይኑረው። በደንብ መረጃዎችን አንሸራሽሩ። ረቂቅ አዋጁ ነገ ከኃይማኖት ተቋማት ተወካዮች ጋር ውይይት ያደርጋል ተብሏል። እዛም ላይ የኛ ተወካዮች በደንብ ጉዳዩን ያንሱት። አላህ የደነገገው ሸሪዓህ በተራ ሰዎች ህግ በፍፁም አይሻርም፤ አይሻሻልም። ሸሪዓን የሚቃረን ህግ ካለ ራሱ ይቀየር እንጂ ሸሪዓህ አይቀየርም። እኛ ሸሪዓን አልደነገግነውም፤ የደነገገው አላህ ነው። ያልደነገግነውን አናሻሽልም። እነርሱ ግን ረቂቁን ያወጡት ራሳቸው ስለሆኑ ራሳቸው አሻሽለው ይምጡ። Period‼ || t.me/MuradTadesse x.com/MuradTadesse fb.com/MuradTadesseOfficial
1241Loading...
19
የፍትሕ ሚኒስቴር ረቂቅ መመሪያ- ግልፅ ለማድረግ !    የህዝቡ ዝምታ ወይ ጥልቅ ከሆነ ቁጣ ወይ ደግሞ ጥልቅ ከሆነ የግንዛቤ እጥረት ሊሆን ይችላል:: ከቁጣ ከሆነ ይበል የሚያስብል ሆኖ ሲፈነዳ የሚታይ ይሆናል:: ከግንዛቤ እጥረት የመሆን እድሉ ሰፊ ነውና የረቂቅ መመሪያው አንደምታው ምንድን ነው የሚለውን እንደሚከተለው እንመልከት::    አይበለውና ከፀደቀ በየትኛውም የትምህርት ተቋማት ኒቃብ ለብሶ መማር ይከለከላል:: ይህ ከሆነ ለአመታት ሲደረጉ የነበሩ ትግሎች አፈር ከመልበሳቸው ባሻገር የትምህርት ተቋሞቻችን ህጋዊ ስልጣን ኖሯቸው ኒቃቢስቶችን አንቀበልም የማለት ሙሉ ስልጣን ይኖራቸዋል:: "ለምን?" ሲባሉም መመሪያው ስለሚያዝ ነው የሚል ምላሽን ይሰጣሉ:: "ሕገ-መንግስቱስ?" ከተባሉም ውይይት ተደርጎበት ከሕገ-መንግስት ጋር ምንም አይነት መጣረስ እንደሌለበት ታምኖ የፀደቀ ነው የማለት መብቱ አላቸው:: በዚህ ውስጥ ወትሮውንም በትምህርት ስርዓቱ ያልታቀፈው ሙስሊም በዚህ ሳቢያ ይገፋል:: ትምህርትን እየጠላ ከማዕቀፉ በሲስተም ይወጣል::  በሁለተኛ ደረጃ በትምህርት ተቋማት ውስጥ ሶላት በጀመዓ መስገድ ይከለክላል:: ወንድምህ ወይም እህትሽ እየሰገዱ ሄዶ ተከትሎ መስገድ ሊያስቀጣ ማለት ነው:: በዚህም ሂደት ከሚቀጣው ተማሪ ባሻገር በሙስሊሙ ዘንድ የባለቤትነት ስሜት እየጠፋ የትምህርት ስርዓቱን በቋሚነት ችላ የሚልበት ስርዓት ይዘረጋል::    በሌላ አውድ ገልብጠን ስንመለከተው ደግሞ ሰፊ የሆነ እድል እናገኛለን:: መመሪያው አሉታዊ ይዘት ባላቸው አንቀፆች እንደተሞላ የተገለፀ ቢሆንም በረቂቅ ደረጃ ያለ ስለሆነ ከላይ እስከ ታች ያለው የህብረተሰብ ክፍል ተፅዕኖ በመፍጠር ከሕገ-መንግስቱ በማይጣረስ መልኩ እንዲፀድቅ ማድረግ ይቻላል:: በዚያ ሂደት ውስጥ የሃይማኖት ነፃነት መብታችንና ሴኩላሪዝም በአግባቡ እንዲከበሩ ማድረግ ከቻልን እስከ ዛሬ በተለያየ ምክንያት አንዴ ሒጃብ ለበሳችሁ ሌላ ጊዜ ሶላት ሰገዳችሁ እያሉ ሲበጠብጡ የነበሩ ሁሉ ተጠያቂ ይሆናሉ ማለት ነው::    ስለሆነም ችላ ሊባል አይገባም:: የዚህ ትውልድ ትልቁ ሀላፊነት ይህንን ፈተና በድል መወጣት ነው:: ሁሉም ትኩረት ሰጥቶ awareness ከመፍጠር ጀምሮ ባሉት እንቅስቃሴዎች ላይ በመሳተፍ ለዘመናት የጭቃ እሾህ ሆኖ ሲነዘንዘን የነበረውን እንቅፋት ማስወገድ ግድ ይለናል:: @MohammadamminKassaw
1520Loading...
20
―አላህ…የሰዎችን ብሶት አዳማጭ፣ ችግራቸዉን ፈች፣ ለመከራቸው ደራሽ፣ ዕዳቸዉን ከፋይ፣ ጭንቀታቸዉን ተጋሪ፣ ህመማቸዉን ታማሚ፣ ሐዘናቸዉ ተካፋይ፣…ያደረገህ እንደሆን በርግጥም የወደደህ ስለመሆኑ ምልክት ነው። በዚህ ሁኔታህ ላይ የኖርክ እንደሆነ ከፍ እንዳልክ ትኖራለህ» 👤 ኢማም ኢብኑል ቀይም። © ከ AbuSufiyan Albenan ቻናል የተወሰደ t.me/Islamic_Star_team
1673Loading...
21
📆 #በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ ⏰#ሰብት 0️⃣3️⃣ #ዙልቀዓዳ 1️⃣4️⃣4️⃣5️⃣ ሂ
1811Loading...
22
Media files
1882Loading...
23
« ሙትቻ ላሉህ ሰዎች እራስህን ለማስረዳት አትሞክር። ለሞትክባቸው ሰዎች የምታባክነው ጊዜ አይኑርህ። ውበትህ ግለፅ ሲወጣ የመጣ ሁሉ ውበትህን አይቶ ላይሆን ይችላልና በአመዳምነት ዘመንህ ላይ ውበትህ የታያቸውን ጠበቅ አድርገህ ያዝ። ቆንጆ መሆንሽን ከሚያደንቁት የበለጠ የሚያስጠላብሽን ሊያስውቡልሽ የሚጣጣሩትን አትዘንጊ። ቁስልሽን በሰው አትከልዪ። የሚመክሩሽ ሁሉም ከጥቃት አይጠብቁሽም። ጥንቃቄ የብልሆች መንገድ ነው። በጣም ነፃነት በሚሰማሽ ሰው በኩል ስስ ነሽና አትራቆቺ። ዋጋ የምትከፍዪላቸው ከጌታሽ መንገድ እንዳያስቱሽ አስተውዩ! የምወድሽዋ ልብሽን በቀደር አረጋጊ! የምወድህዋ እራስህ ካልወደቅክ አይጥሉህምና በጌታህ ታግዘህ ፅና። መንገዱ ምን እንዳለው አይታወቅምና ሰላም ለልባችሁ! © [አብዱልሀኪም ሰፋ] ❤️❤️❤️اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد صلى الله عليه وآله وصحبه أجمعين ❤️❤️❤️ ልባችን ሰላም የሚያገኝበት፣  በሩቋ ሀገር ያሉትም ከአላህ የሆነ እርዳታ እና ድል የሚያገኙበት፣ ተረጋግተው የድል ሰላት የሚሰግዱበት፣  ለተጨነቁት ወንድሞቻችን ድልን ለታመመ መዳንን፣ ለሞቱት ሸሂድነትን  የሚወፈቁበት፣ በሰለዋት፣ በካህፍ እና በዱዓ የደመቀ እና የተዋበ ጁምዓ ይሁንልን💚💚💚
2393Loading...
24
📆 #በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ ⏰ #ጁምዓ 0️⃣2️⃣ #ዙልቀዓዳ 1️⃣4️⃣4️⃣5️⃣ ሂ
2030Loading...
25
በዚህ ሌሊት ስንት ሰው ወደ አኼራ ተሻግሮ ይሆን ? ይህችን ንጋት ሳይታደል ከሞት የተገናኘ ስንት ይሆን ? እኔና አንተ ግን አንግተናል :: እኔና አንቺ ግን አንግተናል :: ለምን ? አላህ ስለፈቀደ ማለት ነው :: ምስጋና ይድረሰው ::: ሁሉም ነገር ለእርሱ "ኩን ፈየኩን!" ነው :: ስለዚህ ባደለህ ንጋት ውስጥ መልካም ነገርን ይወፍቅህ ዘንድ ጠይቀው :: ትላንት ያገኘኸውን አይነት ብቻ ሳይሆን አገኘዋለሁ ብለህ የማታስበውን እንኳ ስጠኝ በለው :: በሩን ደጋግመህ አንኳኳ :: አዕምሮህ አንተ አትችልም ብሎ የሚነግርህን ነገር በሙሉ ጠይቀው :: ምክንያቱም እርሱ የአለማት ጌታ ነው :: እሱ የተዓምራት ሁሉ ባለቤት ነው :: እሱ "ሁን!" ብሎ ነገሮችን ሁሉ እንዲሆኑ የሚያስችል ጌታ ነው :: አላህ በመልካም ነገሮች surprise ያድርጋችሁ ! @aaumsu © اللهم صل وسلم وزد وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد صلى الله عليه وعلى آله وصحبه أجمعين በምድር እና በሰማይ ተወዳጅነትን የምታገኙበት…መልካም ስራቸው ከሚበዛላቸው፣ ጊዜያቸውን በኸይር ከሚያሳልፉት፣ ለወንጀላቸው መሀርታን አግኘተው በጀነት ከሚበሰሩት ሰዎች መሀል የምንሆንበት ወዶ በላካቸው እና  እዝነቱን በእርሳቸው ባሳየን ወዱ ነብያችን የበዛ ሰለዋት ምናወርድበት በሱራህ አልካህፍ በዱዓእ በሰላት በቲላዋ በተሳኩ ምኞቶች በጀባሩ ራህመት የታጀበ የተዋበ ምርጥየ ጁምዐን ተመኘሁ። https://t.me/asdajlahh
7 19563Loading...
26
ደመናው ሲጠቋቁር ነጎድጓዱ ሲያጉረመርም ዝናቡ ሊያለቅስ ሲል ነበር የዐስር ሰላትን ልሰግድ አለምባንክ በሚገኘው ሙስዐብ መስጂድ የታደምኩት። ኢማሙ እያሰገዱን ሰላታችን ካጋመስን ወዲህ ጥቁሩን ደመና መሸከም በቃኝ ያለው ሰማይ ዶፍ ዝናብ ያወርድ ጀመር…ኢማሙ በተረጋጋ መንፈስ ሰላታችን አስጨርሰውን ምእመኑ አዝካሩን በሚያጠናቅቅበት ግዜ ከመስጂዱ አወለ ሰፍ ሁለት እድሜያቸው በሀያዎቹ መጀመርያ ላይ መሆናቸው የሚያስታውቅ ወጣቶች ብድግ ብለው ቁርዐን ይዘው ያካፋፍሉ ጀመር… ይህ አይደለ ትርፍ…ይህን የመሰለ አንድ እንኳን ወጣት እያለ ኢንሻአ አላህ አንወድቅም…አላህ ንግዳቸውን ትርፋማ ያድርገው
2700Loading...
27
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ ⏰#አልኽሚስ 0⃣1⃣ #ዙልቀዓዳ 1⃣4⃣4⃣5⃣ ሂ
2630Loading...
28
#የኔ እይታ 51 አላህ ሲፈልግ..... ህይወታችን ውስጥ በጣም ብዙ ተሳክተው ልናያቸው የምንጓጓላቸው ጉዳዮች አሉን። ጉዳዩን እጅግ በጣም ከመፈለጋችን ብዛት ተሳክቶ ለማየት ብዙ የምንደክምለት፣ አቅመቢስነታችንን አውቀን ሁሉን ቻይ አምላካችንን እርዳታውን የምንለምንለት፣ አቅማችንን ሁሉ አሟጠን ለብዙ አመታት የምንለፋለት፣ሰበባችን ብቻ በቂ እንዳልሆነ በማወቃችን ጉዳዩን ወደጌታችን አስጠግተን ውጤቱን በጉጉት የምንጠብቅለት ከባዱ ሀጃችን! ያ ልባችንን ያስጨነቀው፣ ያ ተሳክቶ ለማየት የምንጓጓለት ፣ ያ የደስታችን መገኛ እንደሆነ ያመንበት ሀጃችን..... ያ ሀጃችንን አላህ ለኛ እንደሚጠቅም እና ጊዜው እንደደረሰ ሲወስን ወደ እኛ የሚመጣበት ፍጥነት ያስገርማል። ሰርፕራይዝ ተደርጋችሁ ታውቃላችሁ? ካወቃችሁ የሚያስደስታችሁ ነገር የናንተን ምንም አይነት ልፋት ሳይፈልግ በሌሎች ልፋት ውስጥ አልፎ እናንተ ጋር ያልተጠበቀ ደስታ ሁኖ ሲመጣ ያለውን ስሜት ምን አልባት በደስታ የሚፈስ እምባችሁ እንጂ ሌላ ምንም አይገልፀውም! ይህ በሰው ሰርፕራይዝ መደረግ የሚፈጥረው ስሜት ነው። ሰርፕራይዝ የሚያደርግህ አላህ ሲሆን የጉዳዩን ትልቀት እና ውበት እንዲሁም ሂወትህ ላይ የሚፈጥረውን ለውጥ አስበው......... አላህ ያ ሀጃህ ላንተ እንደሚጠቅም ከወሰነ እጅን አፍ ላይ በሚያደርግ ፍጥነት ያስደምምሀል። ብቻ እርሱ ይፈልግ ያኔ በ ك እና በ ن መካከል ባሉ ቃላት ብቻ ለአመታት ያስጨነቀህን ጉዳይ ፈፅሞት ታገኘዋለህ።   አላህ እስኪፈልግ ሶብ'ሩ..... @rehimahu @rehimahu ለአስተያየትዎ @rehimahubot
2773Loading...
29
▣ የተማሪዎች ፈተና ራሱ እንደዚህ አይታረምም😁! -------------------------------------------- ®Sαlαh Responds 🎙 ▸ t.me/mahircomp123
2561Loading...
30
አዲስ አበባ ላይ ይህንን ባነር ይዘው "ሲሰብኩ" የነበሩ ሰዎችን ፖሊስ እንዳሰራቸው እዚህ መንደር ሲዘዋወር አየሁ። ትምህርቱ ለሀይማኖተኛ አይደለም ለቄሳርም እንደሚያስደነግጥ የሚያስተዛዝብ ነው። የክርስትናው አለም አምላክ "ይቅር ባይነቱን" አክቲቬት ሊያደርገው ዘንድ የሚፈስ ደም ማየት ይፈልጋል። የአንተ ንስሀም ሆነ በጸጸት ከሀጥያትህ መራቅህ እግዚአብሔር እንዲምርህ የሚያደርግ ሚና የላቸውም። ብቻ ደም አቅርብለት እንጅ ስርየቱ ይረጋገጥልሀል። ከዚያ በኃላ የፈለግከውን ሀጥያት ብትሰራም "በጸጋው ድነሀልና" ከልካይ የለብህም። ካንተ ጭምትነት ይልቅ ለእግዚአብሔር የሚፈሰው ደም የበለጠ ያስፈልገዋል። ትምህርቱን ለመቀበል አይደለም ለመስማትም ይረብሻል..! ___ https://t.me/Yahyanuhe
2400Loading...
31
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ ⏰#አልዓርቢዓዐ 2️⃣9️⃣ #ሸዋል 1️⃣4️⃣4️⃣5️⃣ ሂ
2240Loading...
32
አሁንኮ የወደፊት ሚስትህ "የወደፊት ባሌ በእውቀት የበለፀገ: በገንዘብ የሞላለት: መልካም ስነ-ምግባር መታወቂያው የሆነ ሰው ነው::" በሚል ሀሳብ ውስጥ ልትሆን ትችላለች:: አንተም በሀሳብ የወደፊት ሚስቴ "ሲያዟት እሺ የምትል: ለእኔም ሆነ ለቤተሰቤ የማትጎረብጥ: ልጆቼን በዲናቸውም ሆነ በዱንያዊ ነገሮች ኮትኩታ የምታሳድግ ናት::" እያልክ ይሆናል:: ግን አንተ የት ነህ? አንቺስ የት ነሽ? ለዚህ ስብዕና እየተዘጋጃችሁ ነው? ያም ሆነ ይህ የአላህ ሰላም በእናንተ ላይ ይሁንና ደህና እደሩ! @MohammadamminKassaw
2302Loading...
33
ሸዋል ላይ አገባለሁ ብሎ ያቀደውን ጀለስህን ስታስታውስ
2610Loading...
34
| ባህሉል እና ሰይዱና ጁነይድ | * ከእለታት ባንዱ ቀን ... የባግዳዱ 'ጠቢብ-ዕብድ'   ባህሉል እና ሰይዱና ጁነይድ ተገናኙ ... ሰይዱና ጁነይድም ከ'እብደቱ' ባሻገር ያለውን ጤንነት የተገነዘቡ ነበሩና ምክር እና ተግሳፅ ይሰጣቸው ዘንድ ጠየቁት ... ባህሉልም "አንተ እኮ እውቅ አሊም ነህ የኔ ምክር አያሻህም" በማለት መልስ ሰጠ ... ሰይዱና ጁናይድ ግን እንዲመክራቸው አጥብቀው ወተወቱት ... * ባህሉልም ... "እንግዲያውስ ስለ ሶስት ነገሮች እጠይቅህና በትክክል  ከመለስክልኝ ምክር እለግስሀለሁኝ" አለ ... በመቀጠልም "እንዴት መናገር እንዳለብህ ፤ እንዴት መብላት እንዳለብህ እና እንዴት መተኛት እንዳለብህ ታውቃለህን? " ሲሉ ጠየቁት ... ሰይድና ጁነይድም "እነዚህንማ ጠንቅቄ አውቃለሁ ...  ስናገር - በትሁት እና በለዘብተኛ ድምፅ ... ነጥቡ ላይ አተኩሬ እናገራለሁኝ የምናገረውን ሰው ቀልብም ላለመሰበር እጅጉን ተጠንቅቄም አስረዳለሁኝ ፤ ስበላ - በቅድሚያ  እጄን እታጠባለሁኝ ... ከመጀመሬ በፊት ቢስሚላህ ብዬ የአላህን ስም አወሳለሁ ... ስመገብ በአግባቡ አኝካለሁ ስጨርስ ደግሞ አልሃምዱሊላህ እላለሁ ፤ ስተኛ - ከመተኛቴ በፊት ውዱዕ አደርጋለሁ ... ንፁህ ነገር መልበሴን  አረጋግጩ  በሸሃዳ አሳርጋለሁኝ " አሉት * " ጥሩ! አለ ባህሉል ... "የምታወራው ነገር ውሸት ከሆነ በለዘብታ እና በትህትና ማውራትህ ከጥቅሙ ጉዳቱ ይበልጣል ... የንግግር ዋናው ነጥብ ንግግሩ እውነት መሆኑ ላይ ነው ... ስትበላም በተከለከለ እና ሐራም በሆነ ምግብ ላይ የአላህን ስም ማወሳትህ ትርጉም የለውም ... ከሁሉም አስቀድሞ የምትበላው ምግብ ከሐራም ፣ ከየቲም ሀቅ ፣ ቧሏ ከሞተባት ሴት ሀቅ እና ከሰዎች ሀቅ የጠራ መሆኑ ማረጋገጥ ነው ወሳኙ አደብ ... ስትተኛም ቢሆን ልብህ በምቀኝነት ፣በክፋት እና በሙስሊም ወንድምህ ጥላቻ ተሞልቶ ... በውዱዕ እና በመኝታ ዚክሮች ታጅበህ መተኛትህ  ፋይዳ የለውም ... በንፁህ ልብ የተኛ ነው  ሙዕሚን ሆኖ አነጋ የሚባለው ... ገባህ! እነዚህ ናቸው መሰረታዊ ጉዳዬች የተቀሩት የእነዚህ ተከታዬች ናቸው" ሲል የጠቢብ ምክሩን ለገሳቸው * ©Fuad Yasin
2515Loading...
35
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ ⏰ #አሱለሳዒ 2⃣8⃣ #ሸዋል  1⃣4⃣4⃣5⃣ ሂ
1890Loading...
36
ፊልም ነዋ የሚመስል…ይህ በገሀዱ ዐለም በኛዋ ውድ ሀገር ፈለስጢን የተፈፀመ ውድመት ነው። አላህ ብስራቱን ቅርብ ያድርግላቸው
2130Loading...
37
በቀን 3 ጊዜ የምትበሉ ሰዎች ምን አስባችሁ ነው? ሀሰን አል በስሪ (ረህመቱላሂ አለይህ) በቀን 3 ጊዜ ለሚበላ ሰው ቤተሰቦቹ መኖ ቤት ይገንቡለት ብለዋል:: አስቡበት:: ምግብ ቀንሱ:: ለሀገር ኢኮኖሚ እድገትም ሆነ ነፍስ ከአላህ ጋር በሚኖራት ግንኙነት ወደ አላህ ቀረብ እንድትል ትልቅ አስተዋፅዖ አለው:: ሆድ ሲሞላ ጭንቅላት ባዶ ይሆናል ይባልስ የል¿ @MohammadamminKassaw
2151Loading...
38
Media files
1960Loading...
39
ማን ያውቃል በሕይወትህ ፈጽሞ ያላሰብከው መልካም ነገር ሊፈፀም ጫፍ ደርሶ ይሆናል። አትመለሰ፣ ተስፋ አትቁረጥ። ABX @MohammadamminKassaw
2132Loading...
40
ከሶፍ ውጭ ለብቻ መቆም ~ ሶፍ ሳይሞላ ለብቻ መቆም ክልክል ነው። ነብያችን ﷺ እንዲህ ይላሉ፦ እንዲህ ብለዋል፦ لا تصح صلاة المنفرد خلف الصف "ከሶፍ ኋላ ተነጥሎ ለሚሰግድ ሰው ሶላት የለውም።" [አሕመድ፡ 15862] ስለዚህ:- 1- ሶፍ ያልሞላ ከሆነ ለብቻ መቆም በጥብቅ የተከለከለ ነው። 2- ሶፉ የሞላ ከሆነ፣ ዘርዘር ብለው በመሰለፋቸው ሳያስቸግር የሚያስገባው ክፍተት ካገኘ አጠጋግቶ ይግባ። 3- የሚያስገባው ክፍተት ከሌለ ብቻውን ቆሞ ይሰግዳል። አላህ እንዲህ ይላል፦ { فَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ مَا ٱسۡتَطَعۡتُمۡ } "አላህንም የቻላችሁትን የክል ፍሩት።" [አተጋቡን፡ 16] ከዚህ ውጭ ሶፍ ላይ ያለን ሰው ወደ ኋላ መሳብ አይቻልም። ምክንያቱም ይህንን የሚደግፍ ሶሒሕ ማስረጃ የለምና። በዚህ ላይ የሚጠቀሰውም ሐዲሥ ደካማ ነው። በዚያ ላይ ከሶፍ አውጥቶ ወደ ኋላ መጎተት ጥፋቶች አሉበት። * ሰውን መወስወስ አለበት። * የሚሳበውን ሰው የተሻለ ደረጃ ካለው ፊተኛው ሶፍ ዝቅ ማድረግ አለበት። * የፊተኛው ሶፍ ላይ ክፍተት መፍጠር አለበት። ይህም በጥብቅ የተከለከለ ነው። አዋቂው አላህ ነው። = የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor
2321Loading...
ጠያቂ👉🏻 ላለፉት 21 አመታት በየመንገዱ ዳእዋ ስታደርግ መድከም መሰለቸት ተስፋ መቁረጥ አልገጠመህም? ፈቂ 👉🏻ከአላህ የተሰጠኝ ቅዋ አለ አንድም ቀን እንደዛ አይነት ስሜት ተሰምቶኝ አያውቅም ዳእዋን ስጀምር ሰዎች እናቴ ጋር ሄደው ይህው አንድ ልጅሽ አበደ መንገድ ለመንገድ መልፍለፍ ጀመረልሽ አሏት። እኔም አብሽሪ ይሄ የአንቢያዎችና የነብያቶች ስራ ነው ብዬ አሳመንኳት። አሁን እኔ የሚያሳስበኝ ይሄን ስራ የሚያስቀጥል ተተኪ ትውልድ አለመኖሩ ነው። እኛ ሰዎችን ወደ ሰላም ካልተጣራን ሸይጣን ወደ እሳት ይጣራብናል። አላህ ይዘንልህ‼
نمایش همه...
የበታቻችሁን ተመልከቱ ሲባል ብዙዋችን የምንዞረው ከኛ ይበልጥ ድሃ ወደሆኑ ሰዎች ነው ። አላህ በአንተ ላይ የዋለውን ፀጋ ከመዘንጋት ይመስላል ። ይህ ዝንጋቴ ነው ትክክለኛውን ሹክር እንዳናደርግ የሚያግደን ። እዚሁ መንደር እገሌ የተባለ ሰው በዚህ በሽታ ስለተጠቃ ገንዘብ እንርዳው ሲባል እንመለከታለን ። አላህ በታማሚው ቦታ ስላላደረገን ለማመስገን ሁለቴ ማሰብ የሚፈልግ አይደለም ። ጤና ሐብት መሆኑ የሚገለፅልን ሆስፒታሎች ውስጥ ስናዘወትርና እንዲህ ያሉ መሰል ታካሚዎችን ስንመለከት ነው ፣ ዕድሜ ፀጋ መሆኑ የሚገለፅልን መቃብሮችን ስንዘይር ነው ፣ ከሁሉ በላይ ግን «ዛሬ»ን የመሰለ ስጦታ የለም ። ለዚህም ነው ። ከእንቅልፋችን እንደተነሳን ‹‹ አልሐምዱሊላሂ ለዚ አህያና……›› የምንለው ። አዎ! ትንሿን ሞት አስሙተህ በዚያው ሳታስቀር ህያው ያደረግከን አላህ ሆይ ምስጋና ይገባህ የምንለው ። ቀናችንንም በምስጋና እንድንጀምር የተደረገውም ለዚሁ ነው ። አላህ ‹‹ ዛሬን ›› ሰጥቶሃል ። እርሱ የሚወደው አልያ የማይወደው ማድረግ ግን የኛው ምርጫ ነው ። ከወደደው ጥቅሙ ለኛ ካልወደደው ጉዳቱ ለኛ እንጂ እኛ ቀኑን ሙሉ ብናምፀው አላህን አንጎዳውም ቀኑን ሙሉ ብናመልከው አላህን አንጠቅመው ። ለእኛው ነው ወገን ለእኛው ! አብዱ ረዛቅ
نمایش همه...
2
Photo unavailableShow in Telegram
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ ⏰#አልዓርቢዓዐ 0️⃣7️⃣ #ዙልቀዓዳ 1️⃣4️⃣4️⃣5️⃣ ሂ
نمایش همه...
👍 1
ከአሳሳ እስከ ሮቤ፣ ከኮኮሳ እስከ አዳማ ፣ ከአርሲ እስከ ባሌ፣ እስከ ሸገርና ጎንደር ድረስ ጭምር ታሪክ አለን ከዚህ ሰው ጋር፡፡ በተለያዩ ከተሞች እየተዘዋወረ በጎዳና ላይ ደዕዋ ሲያደርግ ታውቁታላታችሁ፡፡ ምንም ማንንም የማይፈራ ሙጃሂድ ነው። ስፒከሩ በተዳጋጋሚ ታስሮበት በየፖሊስ ጣቢያው ሲንከራተትም አጋጥሞኛል፡፡ ከልጅነት እስከ ወጣትነትና ጎልማሳነት ምናልባት እስካዛሬዋ እስከመጨረሻዋ የዱንያ ላይ ቀን ድረስ ሐያቱን በሙሉ በደዕዋ አሳልፏል፡፡ አላረፈም። ኢስላምን ለማድረስ ሁሌ እንደተጓዘ ስለማየው ቤት ይገባ ይሆን ብዬ እጠይቃለሁ ብዙ ጊዜ፡፡ ዛሬ ሻሻመኔ ላይ ድንገት ማረፉን ሰማሁ፡፡ ፈቂ ገለቶ አላህ ይዘንልህ፡፡ ሰው በኖረበት ነገር ላይ ይሞታል፤ በሞተበት ነገር ላይም ይቀሰቀሳል፡፡ ደጋግ ባሮችህ ወዳንተ እየመጡ ነው። አላህ ሆይ! ዐለይከ ረበና ቢሑስኒልኺታሚ እንላለን ። Abx
نمایش همه...
ይህንን ቻሌንጅ ተቀላቀሉ‼ ================== ✍ ይህንን ባለ 15 ገፅ የመንግስትንና የኃይማኖቶችን ግንኙነት በተመለከተ በዝርዝር ያብራራል የተባለለትን አዲሱን ረቂቅ አዋጅ ሶፍት ኮፒ በስልካችሁ ላይ ላለ ሰው ሁሉ፣ በምታገኙት ግሩፕና ቻነል እንዲሁም በማንኛውም ገፅ ላይ በማሰራጨት መረጃው በእያንዳንዱ ሙስሊም እጅ ላይ ደርሶ እንዲያነበው እናድርግ። ለዚህ ረቂቅ አዋጅ ግብዓት ይሆን ዘንድ የቀረበውን ባለ 164 ገፅ ጥናት ማንበብ ለሚፈልግም ሶፍት ኮፒው በዚህ ሊንክ ይገኛል። https://t.me/MuradTadesse/35708 * ሰው ጽሑፉን ዝም ብሎ ቢያነበውም ከላይ ሲመለከታቸው አንቀፆቹ ጤነኛ ሊመስሉት ስለሚችሉ፤ ፍንጭ ይሰጠው ዘንድ ረቂቅ አዋጁ ከኛ ከሙስሊሞች ጋር የሚያጋጩትንና ጥያቄ የሚያጭሩ 15+ ነጥቦች የተጠቀሱበትን ይህንን ጽሑፍም ጨምሩለት። https://t.me/MuradTadesse/35742 ይህንን የአዲሱን ረቂቅ አዋጅ PDF ለሁሉም በማሰራጨት መረጃው እንዲደርሰው እናድርግ። የላ ቻሌንጃችን ይጀመር! አብዛሃኛው ሰው ከጀርባ ምን እየተካሄደ እንዳለ መረጃው የለውም። ጭራሽ አዲስ ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱን ራሱ እንኳን ከመረጃው የራቀው ማኅበረሰብ ሚዲያ ላይ አለን የሚለው ራሱ በበቂ ሁኔታ የሰማ አይመስለኝም። ወሬውን ቢሰማም ዶክመንቱ በተጨባጭ ያልደረሰው ብዙ ነውና ይህንን በማድረግ ግንዛቤ እንፍጠር። የፌዴራሉ መጅሊስም በዚህ ጉዳይ ተቃውሞ ያወጣውን ባለ 4 ገፅ መግለጫ አያይዘን እናሰራጨው። መግለጫው በዚህ ሊንክ ይገኛል። https://t.me/MuradTadesse/35632?single ከተቋማችንም ጎን እንቁም። የላ! ከአሁኑ ይጀመርና ያሰራጨ ሰው ለማነቃቂያ ስክሪን ሹቱን ኮመንት ላይ አስቀምጡት!
نمایش همه...
ከቀድሞ ባለቤቱ የተፋታበትን ከትውልድ መንደሩ የተሰደደበትን ምክንያት ሲያስረዳ ወላህ ያስቀና ነበር። የሁሌም አደራው "ውጡ! ወደ አላህ መንገድ ተጣሩ" የሚል ቃል ብቻ ነበር። ከዚህ ንግግሩ የሚገናኝ ቃልን እንጂ ከአፉ ሌላን ቃል አድምጨ አላውቅም።
نمایش همه...
ይሄ ዛሂድ ይህ መንገደኛ የአላህ ባሪያ አለፈን ሰማሁ😢 ኢናሊላሂ ወኢናኢለይሂ ራጂኡን ! ዱኒያን ለአላህ ብሎ ትቶ በዝህድና የአላህና መልእክተኛውን መልእክት እያስተላሉፉ ኖሮ መሞት ምንኛ መታደል ነው ! እንዳለመታደል ሆኖ ልፋቱን ባናግዘውም ተገቢውን ክብር ባንሰጠውም አላህ ግን አንዱንም መልካም ስራውን ሳያስቀር በብዙ አባዝቶ ትልቅ ደረጃን እንደሚያጎናፅፈው ተስፋ እናደርጋለን ! አላህ ሆይ በራህመትህ ተቀበለው ከዚህች ዱኒያ በበለጠቺዋ ጀነትህም አጣቅመው ! ሰዒድ
نمایش همه...
😢 2👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
ወንድማችን ፈቂ ገለቶ አላህ ይዘንለት። በተለይ መርካቶ አካባቢና በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች በአደባባይ ዳዕዋው ይታወቃል። ዛሬ ሻሸመኔ ላይ ወደ አኺራህ መሄዱን ሰማን። አላህ ይዘንለት፤ መልካም ሥራውንም ይቀበለው።
نمایش همه...
😢 2
Photo unavailableShow in Telegram
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ ⏰ #አሱለሳዒ 0⃣6⃣ #ዙልቀዓዳ  1⃣4⃣4⃣5⃣ ሂ
نمایش همه...
የአብዛኛው ወጣት ጥያቄ ይመስለኛል... "የቱ ጋር ነው የተሳሳትኩት ፈጣሪዬ??.. ለምን እድገቴ እንዲህ የዘገየ መሰለ?.. የቱ ነገር ነው ከህልሜ ጋር ያለኝን ርቀት ያሰፋብኝ?.. የቱ ልምምዴ?.. የትኛውስ ክፉ ስራዬ ነው መንገዴን ያረዘመው?......" ወጣቱ ይጠይቃል.. አሁን ግን የምር ነው የሚጠይቀው.. መልሱ ደግሞ ለአሁን አጥጋቢ ባይመስለንም እንዳንሰላች.. 🙏 የእውነት ፈጣሪያችን የሻትነውን ሁሉ የሚሰጠበት የራሱ የሆነ ፍፁም ትክክል የሆነ ወቅት አለው.. 😊 'ነገርን ሁሉ ውብ አድርጎ የሰራው በጊዜው ነው አዎ በጊዜው!!.. በእርግጥም እኛም ቀን አለን እሺ አህባቢ 👐❤
نمایش همه...