fa
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

رفتن به کانال در Telegram
916
مشترکین
-124 ساعت
+27 روز
-730 روز
آرشیو پست ها
ሐምሌ 01/2018ዓ/ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ  ወረዳ የ2018/19 በጀት ዓመት የደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋዮች የሥራ ግብር አሰባሰብ በይፋ ተጀመሯል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ  ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ከወረዳው ንግድና ገብያ ልማት ጽ/ቤት በመቀናጀት የ2018 የግብር አሰባሰብ ስራ እና የ2019 ንግድ ፈቃድ እድሳት ስራ በዛሬው እለት ተጀምሯል። በእወጃ መርሃ ግብሩ ላይ የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን፣ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን ፣የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳን ጨምሮ የአስተባባሪ አካላት እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ሰኔ 30/2018 ዓ.ም የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ገቢዎች ፅ/ቤት የ2018 የግብር ዘመን ግብር አከፋፈልን ለማሳካት ለባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ገቢዎች ፅ/ቤት የ2018 የግብር ዘመን የደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋዮች ግብር አከፋፈልን በውጤታማነት በአጭር ቀናት ውስጥ ለማስፈጸም ከባለድርሻ አካላት የስራ ስምሪት ተሰጠ። በስምሪቱ ወቅት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን እንደገለጹት ግብርን በወቅቱ መክፈል የወረዳውን የልማት ስራዎች ለማፋጠን ቁልፍ ሚና እንዳለው ገልጸው፤ የንግዱ ማኅበረሰብ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንዲወጣ አሳስበዋል። የገቢ አሰባሰብ ስራውን በከፍተኛ ቅንጅትና ተጠያቂነት ለማከናወን ባለድርሻ አካላት ጋር ልዩ ስምሪት መሰጠቱን ገልጸው ለስራው ስኬት ከባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል። የስራው አፈጻጸም በየቀኑ ከተቋሙ እና ከወረዳው አስተባባሪዎች በጋራ እንደሚገመገም አቶ ሚፋታ አክለው ገልጸዋል። የወረዳው ገቢዎች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ረመዳን ከድር የ2018 የግብር ዘመን እቅድ ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት የግብር አከፋፈል ስራው በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ታቅዶ ወደ ስራ የተገባ መሆኑን ጠቅሰው ግብር ከፋዮ ማህበረሰብ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ግብሩን በመክፈል ከአላስፈላጊ ቅጣትና ወለድ ራሳቸውን እንዲከላከሉ ግንዛቤ እየተፈጠረ ሲሆን ባለድርሻ አካላት በጠንካራ ቅንጅት በጋራ መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በውይይቱ ላይ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን ፣የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳን ጨምሮ የአስተባባሪ አካላት እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ሰኔ 29/2018 ዓ.ም በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር ዓቀፍ የተፍጥሬ ሳይንስ ተማሪዎች ኦረንቴሽን እና ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ሽኝት መርሃ-ግብር በዛሬው ዕለት ተካሂዷል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በወረዳው በተፈጥሮ ሳይንስ እና ማህበራዊ ሳይንስ ቁጥራቸው 321 ተማሪዎች በሀገር ዓቀፍ ፈተና ላይ እንደሚቀመጡ ተገልጿል። የተፍጥሮ ሳይንስ ወንድ=56 ሴት= 49 በድምሩ 96 ተፈታኝ ተማሪዎች በዛሬው እለት ሽኝት ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተደርጎላቸዋል። በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የወረዳው ትምህርት ቤቶች ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየው ኬኔ ለተማሪዎች ኦረንቴሽን አስመልክቶ ዝርዝር ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን በተፍጥሮ ሳይንስ ወንድ=56 ሴት=40 በድምሩ 96 ተፈታኝ ተማሪዎች መኖራቸውን ገልጸዋል። በዘንድሮ ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና በማህበራዊ ሳይንስና በተፈጥሮ ሳይንስ 321 ተማሪዎች እንደሚፈተኑ አቶ አለማየው በኦረንቴሽኑ ላይ ተናግረዋል። በሽኝቱ ወቅት የተገኙት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን ተማሪዎች የወረዳው ህዝብ አምባሳደር መሆናቸውን ተገንዝበው ክልከላ ከተደረገባቸው ጉዳዮች ራሳቸውን በመጠበቅ ጥብቅ ዲሲፕልን በተሞላበት ሁኔታና ከኩረጃ በፀዳ መልኩ ፈተናቸውን በመውሰድ ለውጤታማነት መንቀሳቀስ እንደሚገባቸው ገልጸዋል። ተማሪዎች በስነ ልቦና ዝግጁ በመሆን የፈተናን ደንብ አክብረው በመፈተን የተሻለ ውጤት ማምጣት እንዲችሉ ጠቅሰው መልካም የፈተና ጊዜ እንዲሆንላቸው ምኞታቸውን ገልጸዋል። የተፍጥሮ ሳይንስ ፈተና ከሐምሌ 01/2018 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 03/2018 ዓ.ም ለተከታታይ 3 ቀናት እንደሚቆይ ከኦረንቴሽኑ ለመረዳት ተችሏል። መድረኩ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን፣ የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየው ኬኔ፣ የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አህመዲን ሰኢድ፣የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና እድሳት ዳይሬክቶሬት ባለሙያ አቶ ወንድሙ ገብሬ እና የጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ባለሙያ አቶ ደሊል ዘርጋው ተገኝተዋል።

ሰኔ 28/2018 ዓ/ም በሰቆጣ ቃል ኪዳን ኘሮግራም ድጋፍ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ደነብ ቀበሌ ለሚገኙ አጥቢ እናቶች ምግባቸውን ከጓሯችው እንዲያመርቱ ለማስቻል እየተሰራ መሆኑን የወረዳው ግብርና ልማት ጽ/ቤት ገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ይህ የተገለጸው በወረዳው በደነብ ቀበሌ በተመረጠ መንደር በሰቆጣ ቃል ኪዳን ኘሮግራም ድጋፍ የተዘጋጃ የተሻሻለ ምርጥ ዘር አቮካዶ የመትከል መርሃ ግብር በተካሄደበት ወቅት ነው። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን የሰቆጣ ቃል ኪዳን ኘሮግራም ዋና አላማ ነብሰጡር፣ እናቶች የስርዓተ ምግብ እጥረት ላለባቸው ከሁለት ዓመት በታች ላሉ ህፃናትንና በስርዓተ ምግብ እጥረት እንዳይጎዱ አልሞ እየሠራ ያለ ፕሮግራም መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ሚፋታ አክለውም በቀበሌው የሚገኙ የፕሮግራሙ ተጠቃሚ እናቶች በኘሮግራሙ የሚሰጣቸውን ግብዓት ለታለመለት አላማ በማዋል ልጆቻቸውን ከመቀንጨር ለማዳን በትኩረት መስራት እንዳለባቸው ጠቅሰው  የግብርና ተቋም ቀበሌ አመራሮች ጋርበመሆን ጠንካራ ድጋፍና ክትትል ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል። የወረዳው የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ በበኩላቸው የስርዓት ምግብ መሻሻል የእናቶችን ጤና ፣የልጆችን መቀጨጭና መቀንጨር የሚከላከል እና ጤናማ ትውልድ ለመገንባት ከፍተኛ ድርሻ ያለው ተግባር በመሆኑ ገልጸው ሰቆጣ ቃል ኪዳን ኘሮግራም ድጋፍ ደነብ ቀበሌ በተመረጠ መንድር 50 እናቶች በመለየት የተለያዩ ለጓሮ አትክልት ምርጥ ዘሮች፣ የእንቁላል ዶሮና እናት ፍየሎች ተሰጥቶ አጥቢ እናቶች  እያለሙና እየተጠቀሙ ይገኛሉ ያሉት አቶ ከድር መርጋ በዛሬው እለት የተሻሻለ ምርጥ ዘር አቮካዶ ለእያንዳንዳቸው 12 በማዘጋጀት በጓሮቸው እንዲተክሉ መድረጉን አስታውቀዋል። በፕሮግራሙ ላይ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን፣የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳን ጨምሮ የአስተባባሪ አካላት እንዲሁም የግብርና ጽ/ቤት አመራሮችና ባለሙያዎች፣የቀበሌው ደጋፊ አመራር እና የደነብ ቀበሌ አመራሮች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ሰኔ 27/2018 ዓ/ም አመራሩ በምርጫ ተግባር ያሳየው ጠንካራ የስራ አቋም በመደበኛ የልማት ስራዎች በመድገም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ ወቅታዊና መደበኛ ስራዎችን በልዩ ትኩረትና በላቀ ቁርጠኝነት መምራት በሚያስችል የአመራር ስምሪት ኦረንቴሽን ተሰጥቷል። በኦረንቴሽን መድረኩ የተገኙት የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን እንዳሉት በምርጫ ወቅት ህዝቡ የሰጠውን ድምፅ በማክበር በቀጣይ በልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎች ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልገናል ብለዋል። አመራር ሙሉ አቅሙን ተጠቅሞ ተግባራት ማሳካት እንዳለበት በመጠቆም በጠንካራ ዲስፕሊንና ቅንጅት ተግባራት መፈጸም እንዳለበት አሳስበዋል። ህዝቡ በምርጫ የሰጠንን ድምፅ በስራ በመካስ በፓርቲያችን ላይ ያለውን እምነት ማላቅ ይገባል ብለዋል። የልማትና የፀጥታ ስራዎች አቀናጅቶ መምራት ይገባል ያሉት አቶ ሸምሱ አመራሩ በቀበሌ ደረጃ የሚያደርገው ድጋፍ በአደረጃጀቶች እንዲፈፀሙ ሊያደርግ እንደሚገብም አስገንዝበዋል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን በበኩላቸው በፓርቲ መሪነት እየተከናወኑ ያሉ ወቅታዊና መደበኛ ተግባራትን በተሻለ በመደገፍ የተጀመሩ ልማት ስራዎችን በማስቀጠል የህዝብንና መንግስትን በማገናኘት የተቀመጡ የልማት ግቦች እንዲሳኩ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ የሆኑት አቶ አ/ረሂም ርዳ የተሰጡ ተልዕኮዎች በተገቢው በመረዳትና በየደረጃው የሚገኙ የአደረጃጀት ስራዎች ከቤተሰብ እስከ ህብረት በማጠናከር አባላቶች ግንባር ቀደም በማድረግ ለሁለተናዊ ልማት መስራት እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል። በመድረኩ የወረዳ አመራሮች የተገኙ ሲሆን የቀጣይ የሥራ አቅጣጫ እና ስምሪት በመስጠት መድረክ ተጠናቋል።