913
المشتركون
-124 ساعات
+27 أيام
-730 أيام
أرشيف المشاركات
ሰኔ 29/2018 ዓ.ም
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር ዓቀፍ የተፍጥሬ ሳይንስ ተማሪዎች ኦረንቴሽን እና ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ሽኝት መርሃ-ግብር በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በወረዳው በተፈጥሮ ሳይንስ እና ማህበራዊ ሳይንስ ቁጥራቸው 321 ተማሪዎች በሀገር ዓቀፍ ፈተና ላይ እንደሚቀመጡ ተገልጿል።
የተፍጥሮ ሳይንስ ወንድ=56 ሴት= 49 በድምሩ 96 ተፈታኝ ተማሪዎች በዛሬው እለት ሽኝት ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተደርጎላቸዋል።
በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የወረዳው ትምህርት ቤቶች ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየው ኬኔ ለተማሪዎች ኦረንቴሽን አስመልክቶ ዝርዝር ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን በተፍጥሮ ሳይንስ ወንድ=56 ሴት=40 በድምሩ 96 ተፈታኝ ተማሪዎች መኖራቸውን ገልጸዋል።
በዘንድሮ ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና በማህበራዊ ሳይንስና በተፈጥሮ ሳይንስ 321 ተማሪዎች እንደሚፈተኑ አቶ አለማየው በኦረንቴሽኑ ላይ ተናግረዋል።
በሽኝቱ ወቅት የተገኙት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን ተማሪዎች የወረዳው ህዝብ አምባሳደር መሆናቸውን ተገንዝበው ክልከላ ከተደረገባቸው ጉዳዮች ራሳቸውን በመጠበቅ ጥብቅ ዲሲፕልን በተሞላበት ሁኔታና ከኩረጃ በፀዳ መልኩ ፈተናቸውን በመውሰድ ለውጤታማነት መንቀሳቀስ እንደሚገባቸው ገልጸዋል።
ተማሪዎች በስነ ልቦና ዝግጁ በመሆን የፈተናን ደንብ አክብረው በመፈተን የተሻለ ውጤት ማምጣት እንዲችሉ ጠቅሰው መልካም የፈተና ጊዜ እንዲሆንላቸው ምኞታቸውን ገልጸዋል።
የተፍጥሮ ሳይንስ ፈተና ከሐምሌ 01/2018 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 03/2018 ዓ.ም ለተከታታይ 3 ቀናት እንደሚቆይ ከኦረንቴሽኑ ለመረዳት ተችሏል።
መድረኩ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን፣
የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየው ኬኔ፣
የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አህመዲን ሰኢድ፣የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና እድሳት ዳይሬክቶሬት ባለሙያ አቶ ወንድሙ ገብሬ እና የጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ባለሙያ አቶ ደሊል ዘርጋው ተገኝተዋል።
ሰኔ 28/2018 ዓ/ም
በሰቆጣ ቃል ኪዳን ኘሮግራም ድጋፍ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ደነብ ቀበሌ ለሚገኙ አጥቢ እናቶች ምግባቸውን ከጓሯችው እንዲያመርቱ ለማስቻል እየተሰራ መሆኑን የወረዳው ግብርና ልማት ጽ/ቤት ገለጸ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ይህ የተገለጸው በወረዳው በደነብ ቀበሌ በተመረጠ መንደር በሰቆጣ ቃል ኪዳን ኘሮግራም ድጋፍ የተዘጋጃ
የተሻሻለ ምርጥ ዘር አቮካዶ የመትከል መርሃ ግብር በተካሄደበት ወቅት ነው።
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን የሰቆጣ ቃል ኪዳን ኘሮግራም ዋና አላማ ነብሰጡር፣ እናቶች የስርዓተ ምግብ እጥረት ላለባቸው ከሁለት ዓመት በታች ላሉ ህፃናትንና በስርዓተ ምግብ እጥረት እንዳይጎዱ አልሞ እየሠራ ያለ ፕሮግራም መሆኑን ገልጸዋል።
አቶ ሚፋታ አክለውም በቀበሌው የሚገኙ የፕሮግራሙ ተጠቃሚ እናቶች በኘሮግራሙ የሚሰጣቸውን ግብዓት ለታለመለት አላማ በማዋል ልጆቻቸውን ከመቀንጨር ለማዳን በትኩረት መስራት እንዳለባቸው ጠቅሰው የግብርና ተቋም ቀበሌ አመራሮች ጋርበመሆን ጠንካራ ድጋፍና ክትትል ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል።
የወረዳው የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ በበኩላቸው የስርዓት ምግብ መሻሻል የእናቶችን ጤና ፣የልጆችን መቀጨጭና መቀንጨር የሚከላከል እና ጤናማ ትውልድ ለመገንባት ከፍተኛ ድርሻ ያለው ተግባር በመሆኑ ገልጸው ሰቆጣ ቃል ኪዳን ኘሮግራም ድጋፍ ደነብ ቀበሌ በተመረጠ መንድር 50 እናቶች በመለየት የተለያዩ ለጓሮ አትክልት ምርጥ ዘሮች፣ የእንቁላል ዶሮና እናት ፍየሎች ተሰጥቶ አጥቢ እናቶች እያለሙና እየተጠቀሙ ይገኛሉ ያሉት አቶ ከድር መርጋ
በዛሬው እለት የተሻሻለ ምርጥ ዘር አቮካዶ ለእያንዳንዳቸው 12 በማዘጋጀት በጓሮቸው እንዲተክሉ መድረጉን አስታውቀዋል።
በፕሮግራሙ ላይ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን፣የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳን ጨምሮ የአስተባባሪ አካላት እንዲሁም የግብርና ጽ/ቤት አመራሮችና ባለሙያዎች፣የቀበሌው ደጋፊ አመራር እና የደነብ ቀበሌ አመራሮች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ሰኔ 27/2018 ዓ/ም
አመራሩ በምርጫ ተግባር ያሳየው ጠንካራ የስራ አቋም በመደበኛ የልማት ስራዎች በመድገም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተገለጸ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ ወቅታዊና መደበኛ ስራዎችን በልዩ ትኩረትና በላቀ ቁርጠኝነት መምራት በሚያስችል የአመራር ስምሪት ኦረንቴሽን ተሰጥቷል።
በኦረንቴሽን መድረኩ የተገኙት የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን እንዳሉት በምርጫ ወቅት ህዝቡ የሰጠውን ድምፅ በማክበር በቀጣይ በልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎች ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልገናል ብለዋል።
አመራር ሙሉ አቅሙን ተጠቅሞ ተግባራት ማሳካት እንዳለበት በመጠቆም በጠንካራ ዲስፕሊንና ቅንጅት ተግባራት መፈጸም እንዳለበት አሳስበዋል።
ህዝቡ በምርጫ የሰጠንን ድምፅ በስራ በመካስ በፓርቲያችን ላይ ያለውን እምነት ማላቅ ይገባል ብለዋል።
የልማትና የፀጥታ ስራዎች አቀናጅቶ መምራት ይገባል ያሉት አቶ ሸምሱ አመራሩ በቀበሌ ደረጃ የሚያደርገው ድጋፍ በአደረጃጀቶች እንዲፈፀሙ ሊያደርግ እንደሚገብም አስገንዝበዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን በበኩላቸው በፓርቲ መሪነት እየተከናወኑ ያሉ ወቅታዊና መደበኛ ተግባራትን በተሻለ በመደገፍ የተጀመሩ ልማት ስራዎችን በማስቀጠል የህዝብንና መንግስትን በማገናኘት የተቀመጡ የልማት ግቦች እንዲሳኩ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ የሆኑት አቶ አ/ረሂም ርዳ የተሰጡ ተልዕኮዎች በተገቢው በመረዳትና በየደረጃው የሚገኙ የአደረጃጀት ስራዎች ከቤተሰብ እስከ ህብረት በማጠናከር አባላቶች ግንባር ቀደም በማድረግ ለሁለተናዊ ልማት መስራት እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል።
በመድረኩ የወረዳ አመራሮች የተገኙ ሲሆን የቀጣይ የሥራ አቅጣጫ እና ስምሪት በመስጠት መድረክ ተጠናቋል።
ሰኔ 27/2018 ዓ/ም
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም ከ8 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀው ወደ ተግባር መገባቱን ተገለፀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የወረዳው የ2018 የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር "ተስፋ እንትከል" በሚል መሪ ቃል በሰፋቶ ቀበሌ በይፋ ተጀመረ።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን በወረዳው ከ8 ነጥብ 5 ሚሊዮን የፍራፍሬ፣ የቡና፣ የመኖና የደን ዛፍ ችግኞች ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀው ወደ ተግባር ተገብቷል።
በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች ምክንያት የተጎዱ አካባቢዎች በየአመቱ በሚተከሉ ችግኞች እንዲያገግሙ ማድረግ ተችሏል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው በጎርፍ የሚጠረግ ለም አፈር በመከላከል ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ በተጨማሪ ለብዝሃ ሕይወት ምቹ አካባቢ መፍጠራቸውን ገልጸዋል።
በመሆኑም በወረዳው በዘንድሮ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር የሚተከሉ ከስምንት ሚሊየን አምስት መቶ ሺህ በላይ ችግኞችን ለመጠበቅ፣ ለመንከባከብና የጽድቀት መጠኑ ከፍ ለማድረግ
የተጠናከረ ስራ መስራት ይገባል ብለዋል።
አክለውም አቶ ሚፍታ በአረንጓዴ አሻራ ያገገሙ አካባቢዎች የመሬት መሸርሸርን ከመከላከል በተጨማሪ ወጣቶች በንብ ማነብ ተግባር በመሰማራት የኢኮኖሚ አቅማቸውን ማሳደግ ችለዋል።
ከመደበኛው የችግኝ ተከላ በተጨማሪ በቀጣይ በሚካሄደው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ ፕሮግራም በርካታ ችግኞችን ለመትከል መታቀዱን ገልፀው በዚህ ተግባር የወረዳው ማህበረሰብ በሙሉ በንቃት መሳተፍ አለበት ብለዋል።
በተለይም በአጭር ጊዜ ውስጥ ደርሰው ምርት በመስጠት ለአርሶ አደሩ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ የሚሆኑ የተሻሻሉ የፍራፍሬ ችግኞች በብዛት እንደሚተከሉ አቶ ሚፍታ ተናግረዋል፡፡
በወረዳው ግብርና ጽ/ቤት የተፈጥሮ ሀብት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብድራሂም ሰማን በበኩላቸው የተዘጋጁ ችግኞች ወደ ሁሉም ቀበሌዎች በማሰራጨት የተከላው ስራ መጀመሩን ተናግረዋል።
በዘርፉ ተጨባጭ ውጤት ለማስመዝገብ ጽ/ቤቱ ከወረዳው ደንና አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል።
ሰኔ 27/2018 ዓ/ም
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የበጋ ወራት በጎ ፍቃድ መዝጊያና የክረምት ወራት በጎ ፍቃድ መክፈቻ ንቅናቄ መድረክ በስፋቶ ቀርሳ ቀበሌ እያካሄደ ይገኛል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በወረዳው በክረምት ወራት በሚከናወኑ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ተግባራት በ16 ዘርፎች ከ57ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በማሳተፍ ከ117 በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዷል።
በበጎ ፍቃድ አገልግሎቱ በአዲስ ቤት ግንባታ፣ በቤት ጥገናና እድሳት፣ በትምህርት፣በፋይዳ ፣በጤና፣በግብርና ፣ማእድ በማጋራት ፣በአረንጓዴ አሻራ እና በሌሎችም ዘርፎች በትኩረት ይሰራል ትብሏል።
በመድረኩ ላይ የጉራጌ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን፣ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን ፣የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብድረሂም ርዳ፣የወረዳው የስራ ኃላፊዎች ፣የአብይና ቴክኒክ ኮሚቴ አባላትና በጎ ፍቃደኞች ተገኝተዋል።
ሰኔ 26/2018 ዓ/ም
በሰውና በንብረት ላይ የሚደርሰውን የትራፊክ አደጋ ለመከላከል አሽከርካሪዎች ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸው
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ገለፀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ይህ የተገለጸው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ከወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን ለነባርና ለአዲስ አሽከርካሪዎች አደጋን ተከላክሎ ለማሽከርከር የሚያስችል የቴክኒክና የስነ-ባህሪ የተሀድሶ ስልጠና በዛሬው እለት በተሰጠበት ወቅት ነው።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ዳይሮክትሬት የትምህርት ስልጠና ግንዛቤ ማስጨበጫ ኤክስፐርት አቶ ክፍሌ አሼቦ የስልጠናው ሰነድ ባቀረቡበት ወቅት በአሽከርካሪዎች ከሚስተዋሉ የጥንቃቄ ችግሮችና ለመንገድ ትራፊክ አደጋ መንስኤ ከሆኑት መካከል ለአብነት ያለብቃት ማሽከርከር ፣የተሽከርካሪ ደህንነት ሳያረጋግጡ ማሽከርከር ፣ከተፈቀደ የፍጥነት ወሰን ማለፍ ፣ የመንገድ ትራፊክ ህጎች አለማክበር በዋናነት የሚጠቀሱ በመሆናቸው ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አስገንዝበዋል።
አቶ ክፈሌ አክለውም አሽከርካሪዎች በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ባገኙት ዕውቀት ህብረተሰቡን በተፈቀደው መጠን በመጫን የትራንስፖርት መመሪያና ደንብ ተግባራዊ ማድረግ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
የጉራገ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ የመንገድ ደህንነት አስተባባሪ አቶ መስቀሉ ምርጋ በበኩላቸው በትራፊክ አደጋ ምክንያት በሰውና በንብረት ላይ የሚደርሰውን አደጋ ለመከላከል አሽከርካሪዎች ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው ብለዋል።
በስልጠናው ተሳታፊ አሽከርካሪዎች ስልጠናው እጅግ አስፈላጊና ወቅታዊ በመሆኑ በሚያሽከረክሩበት ወቅትም የበለጠ እንዲጠነቀቁ የሚያደርግ እንደሆነም በአስተያየታቸው ተናግረዋል::
በተጨማሪም በዘርፉ እያጋጠሟቸው ያሉ ማነቆዎች በሰፊው አንስተው እንዲቀረፉ ጠይቀዋል።
በመድረኩም የገዳባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትራንስፖርት መንገድ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊዎችና የመንገድ ደህንነት ባለሞያዎች እንዲሁም የትራፊክ ፖሊስ አባላት እና አሽከርካሪዎች ተገኝተዋል።
በተጨማሪም ደንብ ቁጥር 557/2016 በተዘጋጀ ብሮሸር ለእያንዳንዱ አሽከርካሪ ስርጭት ተደርጓል።
