fa
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

رفتن به کانال در Telegram
916
مشترکین
-124 ساعت
+27 روز
-730 روز
آرشیو پست ها
ሰኔ 27/2018 ዓ/ም በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ  ፕሮግራም ከ8 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ  ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀው ወደ ተግባር መገባቱን ተገለፀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የወረዳው የ2018 የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር "ተስፋ እንትከል" በሚል መሪ ቃል በሰፋቶ ቀበሌ  በይፋ ተጀመረ። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን  በወረዳው ከ8 ነጥብ 5 ሚሊዮን የፍራፍሬ፣ የቡና፣ የመኖና የደን ዛፍ ችግኞች ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀው ወደ ተግባር ተገብቷል። በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች ምክንያት የተጎዱ አካባቢዎች በየአመቱ በሚተከሉ ችግኞች እንዲያገግሙ ማድረግ ተችሏል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው በጎርፍ የሚጠረግ ለም አፈር በመከላከል ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ በተጨማሪ ለብዝሃ ሕይወት ምቹ አካባቢ መፍጠራቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም  በወረዳው በዘንድሮ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር  የሚተከሉ ከስምንት ሚሊየን አምስት መቶ ሺህ በላይ ችግኞችን ለመጠበቅ፣ ለመንከባከብና የጽድቀት መጠኑ ከፍ ለማድረግ የተጠናከረ ስራ መስራት ይገባል ብለዋል። አክለውም አቶ ሚፍታ በአረንጓዴ አሻራ ያገገሙ አካባቢዎች የመሬት መሸርሸርን ከመከላከል በተጨማሪ ወጣቶች በንብ ማነብ ተግባር በመሰማራት የኢኮኖሚ አቅማቸውን ማሳደግ ችለዋል። ከመደበኛው የችግኝ ተከላ በተጨማሪ በቀጣይ በሚካሄደው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ ፕሮግራም በርካታ ችግኞችን ለመትከል መታቀዱን ገልፀው በዚህ ተግባር የወረዳው ማህበረሰብ በሙሉ በንቃት መሳተፍ አለበት ብለዋል። በተለይም በአጭር ጊዜ ውስጥ ደርሰው ምርት በመስጠት ለአርሶ አደሩ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ የሚሆኑ የተሻሻሉ የፍራፍሬ ችግኞች በብዛት እንደሚተከሉ አቶ ሚፍታ ተናግረዋል፡፡ በወረዳው ግብርና ጽ/ቤት የተፈጥሮ ሀብት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብድራሂም ሰማን በበኩላቸው የተዘጋጁ ችግኞች ወደ ሁሉም ቀበሌዎች በማሰራጨት የተከላው ስራ መጀመሩን ተናግረዋል። በዘርፉ ተጨባጭ ውጤት ለማስመዝገብ ጽ/ቤቱ  ከወረዳው ደንና አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል።

ሰኔ 27/2018 ዓ/ም የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የበጋ ወራት በጎ ፍቃድ መዝጊያና የክረምት ወራት በጎ ፍቃድ መክፈቻ ንቅናቄ መድረክ በስፋቶ ቀርሳ ቀበሌ እያካሄደ ይገኛል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በወረዳው በክረምት ወራት በሚከናወኑ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ተግባራት በ16 ዘርፎች ከ57ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በማሳተፍ ከ117 በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዷል። በበጎ ፍቃድ አገልግሎቱ በአዲስ ቤት ግንባታ፣ በቤት ጥገናና እድሳት፣ በትምህርት፣በፋይዳ ፣በጤና፣በግብርና ፣ማእድ በማጋራት ፣በአረንጓዴ አሻራ እና በሌሎችም ዘርፎች በትኩረት ይሰራል ትብሏል። በመድረኩ ላይ የጉራጌ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን፣ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን ፣የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብድረሂም ርዳ፣የወረዳው የስራ ኃላፊዎች ፣የአብይና ቴክኒክ  ኮሚቴ አባላትና በጎ ፍቃደኞች ተገኝተዋል።

ሰኔ 26/2018 ዓ/ም በሰውና በንብረት ላይ የሚደርሰውን የትራፊክ አደጋ  ለመከላከል አሽከርካሪዎች ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ገለፀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ይህ የተገለጸው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ከወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን ለነባርና ለአዲስ አሽከርካሪዎች አደጋን ተከላክሎ ለማሽከርከር የሚያስችል የቴክኒክና የስነ-ባህሪ የተሀድሶ ስልጠና  በዛሬው እለት በተሰጠበት ወቅት ነው። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ዳይሮክትሬት የትምህርት ስልጠና ግንዛቤ ማስጨበጫ ኤክስፐርት አቶ ክፍሌ አሼቦ የስልጠናው ሰነድ ባቀረቡበት ወቅት  በአሽከርካሪዎች ከሚስተዋሉ የጥንቃቄ ችግሮችና ለመንገድ ትራፊክ አደጋ መንስኤ ከሆኑት መካከል ለአብነት ያለብቃት ማሽከርከር ፣የተሽከርካሪ ደህንነት ሳያረጋግጡ ማሽከርከር ፣ከተፈቀደ የፍጥነት ወሰን ማለፍ ፣ የመንገድ ትራፊክ ህጎች አለማክበር በዋናነት የሚጠቀሱ በመሆናቸው ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አስገንዝበዋል። አቶ ክፈሌ አ‎ክለውም አሽከርካሪዎች በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ባገኙት ዕውቀት ህብረተሰቡን በተፈቀደው መጠን በመጫን የትራንስፖርት መመሪያና ደንብ ተግባራዊ ማድረግ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የጉራገ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ የመንገድ ደህንነት አስተባባሪ አቶ መስቀሉ ምርጋ በበኩላቸው በትራፊክ አደጋ ምክንያት በሰውና በንብረት ላይ የሚደርሰውን አደጋ  ለመከላከል አሽከርካሪዎች ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው ብለዋል። በስልጠናው ተሳታፊ አሽከርካሪዎች ስልጠናው እጅግ አስፈላጊና ወቅታዊ በመሆኑ በሚያሽከረክሩበት ወቅትም የበለጠ እንዲጠነቀቁ የሚያደርግ እንደሆነም በአስተያየታቸው ተናግረዋል:: ‎ ‎በተጨማሪም በዘርፉ እያጋጠሟቸው ያሉ ማነቆዎች በሰፊው አንስተው እንዲቀረፉ ጠይቀዋል። ‎ ‎በመድረኩም የገዳባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትራንስፖርት መንገድ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊዎችና የመንገድ ደህንነት ባለሞያዎች እንዲሁም የትራፊክ ፖሊስ አባላት እና አሽከርካሪዎች ተገኝተዋል። በተጨማሪም ደንብ ቁጥር 557/2016 በተዘጋጀ ብሮሸር ለእያንዳንዱ አሽከርካሪ ስርጭት ተደርጓል።

ሰኔ 26/2018 ዓ/ም ሀሚሊን ፌስቱላ ኢትዮጵያ ግብረ ሰናይ ድርጅት በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፕሮጀክት ዜሮ ወረዳ በወረዳ ከኢትዮጵያ የማጥፋት ፍኖተ ካርታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በወልቂጤ ከተማ በዛሬው እለት ተካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ሀሚሊን ፌስቱላ ኢትዮጵያ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ለሚገኙ 6 ጤና ጣቢያዎችና በሁሉም ቀበሌዎች ፕሮጀክት ዜሮ ወረዳ በወረዳ ከኢትዮጵያ የማጥፋት ፍኖተ ካርታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በወልቂጤ ከተማ በዛሬው እለት ተካሄዷል። የሀሚሊን ፌስቱላ ኢትዮጵያ ኮርዲኔተር ወ/ሮ ሚስጥር አለባቸው በመርሃ ግብሩ ተገኝተው እንዳሉት ከ63 ዓመታት በፊት በአውስትራሊያዊቷ ፋና ወጊ የቀዶ ጥገና ሐኪም ዶክተር ካትሪን ሃምሊን እና ባለቤቷ ዶ/ር ሬግ ሃምሊን የተመሠረተው ሃምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ እጅግ አሰቃቂ የሆነው የወሊድ ጉዳት ወይም የማሕፀን ፊስቱላ የደረሰባቸውን ኢትዮጵያውያን ሴቶች ለማከም መሆኑን ገልጸዋል። ወ/ሮ ሚስጥር አለባቸው አክለውም ሀምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ ባለፉት 63 አመታት ከ70,000 በላይ የሚሆኑ ለማሕፀን ፊስቱላ የተጋለጡ ኢትዮጵያውያን ሴቶችን ጤና እና ክብር መመለሱን ጠቅሰው ዶ/ር ካትሪን ሃምሊን የፊስቱላ ታካሚን ማከም በፊኛ ላይ ያለውን ቀዳዳ ማከም ብቻ ሳይሆን ሴትን በሙሉ በፍቅር እና በጥንቃቄ ማከም እንደሆነ ሁልጊዜ ያምኑ ስለነበር በሃምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ ከፊስቱላ ጉዳት የሚያገግሙ ሴቶችን የበለጠ ለመደገፍ የማገገሚያ እና የመልሶ ማቋቋም ፕሮግራም በማዘጋጀት የሃምሊን የሕክምና ሞዴል ያቀፈ እና ሴቶች በነጻነት እና በክብር ሕይወታቸውን እንዲመሩ የሚያስችል እንደሆነ ተናግረዋል። ሀሚሊን ፌስቱላ ኢትዮጵያ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ለሚገኙ 6 ጤና ጣቢያዎች ፕሮጀክት ዜሮ ወረዳ በወረዳ ከኢትዮጵያ የማጥፋት ፍኖተ ካርታ በይፋ መጀመሩን አስታውቀዋል። ወ/ሮ ሀና ተስፋዬ ፕሮጀክት ዜሮ ኮርዲኔተር ስለ ፕሮጀክቱ አጠቃላይ አላማና ግብ እንዲሁም እስካሁን በወረዳው የተሰሩ የአሰስመንት ስራዎች ለታዳሚዎች በማቅረብ አጠር ያለ ውይይት የተደረገ ሲሆን ለተነሱ ጥያቄና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶል። በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን የብልጽግና መንግስት በሽታ መከላከልንና አክሞ የማዳን ፖሊሲ በመቅረጽ ወደ ተግባር በመግባት የህዝቡን የጤና ችግር ለመቅረፍ ከመቼውም ጊዜ በላይ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን የአካባቢ ተወላጅ ባለሀብቶችና ህዝቡን በማቀናጀት በወረዳ ደረጃ በርካታ ተግባር እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸው የሀሚሊን ፌስቱላ ኢትዮጵያ ግብረ ሰናይ ድርጅት ወረዳችን ተማራጭ አድርጎ እንዲሰራ አስተዋጾ ላደረጉ በየደረጃው ለሚገኙ አካላት በወረዳው መንግስትና ህዝብ ስም ላቅ ያለ ምስጋናቸውን በማቅረብ ለበጎ አድራጊ ድርጅቱ አሰፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ አስገንዝበዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ ወ/ሮ ሚስጥር አለባቸው የሀሚሊን ፌስቱላ ኢትዮጵያ ኮርዲኔተር፣ ወ/ሮ ሀና ተስፋዬ  ፕሮጀክት ዜሮ ኮርዲኔተር፣አቶ ዱጉማ ጋሮምሳ ፌስቱላ ኢትዮጵያ ፋይናንስ፣የጉራጌ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አየለ ፈቀደ፣የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን ፣የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እና የጉራጌ ዞን ባለሙያዎች ፣ የወረዳው ሴቶች ህጻናት ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ፈትያ መህዲ፣የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም አብራር፣የጤና ጣቢያ ኃላፊዎችና የሃይማኖት አባቶችና ባለድርሽ አካላት ተገኝተዋል።

ሰኔ 23/2018 ዓ.ም የአየር ብክለትን በመቀነስ ለዜጎች ምቹና ማራኪ አከባቢ መፍጠር እንደሚገባ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ደንና አከባቢ ጥበቃ ልማት ፅ/ቤት አስታወቀ ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ይህ የተገለፀው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ደንና አከባቢ ጥበቃ  ልማት ፅህፈት ቤት "ብክለትን እንቀንስ እንቆጣጠር"በሚል መሪ ቃል ከባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ በተካሄደበት ወቅት ነው ። የዕለቱ የመወያያ ዕቅድ ሰነድ በጽ/ቤቱ ኃላፊ በአቶ አብዲ አ/ሀፊዝ ቀርቦ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጓል። ከተሳታፊዎች ከተነሱ ሀሳብ አስተያየቶች መካከል  ለተግባሩ መሳካት አዋጅና መመሪያ ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት ፣ምግብ ቤቶች ፣ሻይ ቡና ቤቶች ሽንት ቤት ማዘጋጀት እንደሚገባቸው አዲስ እየተሰራ ያለው መንገድ ላይ ቆሻሻ እየተጣለ መሆኑና የፈሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ዲች በቆሻሻ እየተዘጋ መሆኑ ፣ባለድርሻ ተቋማት ተጠያቂ ማድረግ እንደሚገባ፣ የግንዛቤ ስራዎች በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶችን በማቀናጀት የከተማ ንፅህና መጠበቅ የጋራ ዕቅድ መታቀድ እንዳለበት የሚሉት ናቸው ። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ደንና አከባቢ ጥበቃ  ልማት ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብዲ አ/ሀፊዝ እንደተናገሩት  የአካባቢያችን ውበትና ንፅህና ለመጠበቅ ተቋማት ተግባሮቻቸውን ማከናወን መቻል እንዳለባቸው ገልፀው አካባቢ ብክለትን ለመግታትና ህብረተሰቡን ያሳተፈ የአካባቢ ጥበቃ ስራን ለማጠናከር “ብክለት ይብቃ፣ ውበት ይንቃ!” በሚል መሪ ቃል የተፈጠረው የንቅናቄ መርሃ-ግብር ውጤታማ እንዲሆን አካባቢ ጥበቃ ስራ በልዩ ትኩት መስራት እንደሚገባ አስታውሰዋል። በከተሞች አካባቢ የሚታየውን የደረቅ፣ የፈሳሽ፣ የውሃ እና የድምፅ ብክለትን ለመቆጣጠር ቅንጅታዊ ስራ ማጠናከርና ባለድርሻ ተቋማት በጋራ በመስራት እንደ ተቋም ያሉብን ተግባራት ወስደን በመስራት ምቹና ማራኪ አከባቢ ለመፍጠር እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል። መድረኩን የመሩት የወረዳው መንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ሚፍታ አረቦ በበኩላቸው በመንገዶችና በተከለከሉ ቦታዎች የሚጣሉ የቆሻሻዎች ምንጭ በመለየት መመሪያ ለሚተላለፉ አካላት ተገቢው እርማት ማድረግ እንዳለባቸው የንግድ ድርጅቶች የሚሰሩበት ዘርፍ በመለየት ስራ መስራት እንደሚገባና ህግ መተግበር እንደሚገባ ተናግረዋል። የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ እና ለመከላከል ዋናው መፍትሔ የቆሻሻ አወጋገድ ስርዓትን ማሻሻል መሆኑ አስታውሰው የአረንጓዴ አሻራ ስራን በማጠናከር የአካባቢያችንን ጤና ለመጠበቅ የየዕለት ተግባሮቻችንን ማስተካከል እንደሚገባ ገልጸዋል።

ሰኔ 22/2018 ዓ.ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ 8.5 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን  የወረዳው ደንና አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ገለፀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በ2018/19 የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር 8.5 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል እቅድ መያዙንና እስካሁን ከ6.5 ሚሊዮን በላይ ጉድጓድ መዘጋጀቱን ጽ/ቤት አክሎ ገልጿል። የወረዳው ደንና አካባቢ ጥበቃ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብዲ አ/ሃፊዝ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት መገኙቱን አስታውቀዋል። አቶ አብዲ አያይዘውም በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ፤ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ነባርና ሀገር በቀል ችግኞ እንደሚተከሉ ጠቅሰው ለችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ፤ ከችግኝ ማፍላት ጀምሮ ሌሎች አስፈላጊ የቅድመ ዝግጅት ስራ መጠናቀቁንም አንስተዋል። በተለይም የአፈር ለምነትን የሚያሻሽሉ፣ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው፣ አግሮ ኢኮሎጂው ላይ ለውጥ የሚያመጡ ችግኞችን ለመትከል ስለመታቀዱ ተናግረዋል የዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለቸው 8.5 ሚሊዮን ችግኞች የተዘጋጁ ሲሆን ከነዚሁ የተዘሩት ችግኞች መካከልም ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለግንባታ እና ለማገዶ ዓላማ የሚውል ችግኞች ለመትከል መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል። በመንግስት ችግኝ ጣቢያ፤ በተቋማት፣ በአርሶ አደር ጓሮ፣ በግል፣ በማህበረሰብና በሌሎችም ችግኞቹ መዘጋጀታቸውን አቶ አብዲ አብራርተዋል። ከጉድጓድ ዝግጅት አፈፃፀም ጋር በተያያዘ ኃላፊው 8.5 ሚሊዮን በላይ ጉድጓድ ለማዘጋጀት በተያዘው ዕቅድ መሠረት እስካሁን ባለው ጊዜ ውስጥ 6.5 ሚሊየን በላይ ጉድጓድ የተዘጋጀ ሲሆን ቀሪው በቁፋሮ ሂደት ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በመጨረሻም አቶ አብዲ አ/ሃፊዝ ባስተላለፉት መልዕክት የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ለማሳካት የሚደረገውን ርብርብ  በየደረጃው የሚገኙ አካላት እገዛቸውን አጠናክረው ማስቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።