1 084
مشترکین
+524 ساعت
+107 روز
+530 روز
آرشیو پست ها
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በሚሰጠው የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው የውጭ ሀገር ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ዝርዝር።
ህጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ይሁኑ!
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ፡
ጥቅምት 16፤ 2017
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols
ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official
ሊንክዲን፡- https://www.linkedin.com/.../ministry-of-labor-skill-fdre/
"ማህበራዊ መስተጋብሩ ጠንካራ የሆነ ተቋም ተልዕኮውን ከግብ ለማድረስ የሚያደርገው ጉዞ ቀልጣፋና ውጤታማ ይሆናል"
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
በዛሬው ዕለት የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የመረዳጃ ዕድር ይፋዊ ምስረታ እና የሸራ ምርቃት መርሃግብር ተካሄደ።
በዚህ መርሃግብር ላይ የተገኙት የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው አመራሩ እና ሠራተኛው በደስታና በሃዘን የሚገጥማቸውን የህይወት ገጠመኞች በመረዳዳትና በመደጋገፍ የሚያደርጉት መተጋገዝ በቀጥታ በመንግስታዊ ተልዕኮ መፈጸም ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖ እንዳለው ገልጸው ቢሮውም ይህን መስተጋብር የሚያጠናክር ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የመረዳጃ ዕድር ኮሚቴ ተወካዮች በበኩላቸው የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና ማኔጅመንታቸው ዕድሩን የሚያጠናክሩ የተለያዩ ድጋፎችን ስላደረጉላቸው በተለይም ዋና ነገር የሆነውን ሸራ እንዲገዛ ከፍ ያለውን አስተዋጽኦ ስላበረከቱ አመሥግነዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 16/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በክረምት በጎ ፍቃድ ለአቅመ ደካሞች የተገነቡ ቤቶችን የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር መርቀው ቁልፉን ለባለቤቶቹ አስረክበዋል፡፡
በዚህም በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ እና በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በእያንዳንዳቸው ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ የወጣባቸው ሁለት ሁለት ቤቶች በድምሩ ከአንድ ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው አራት የተገነቡ ቤቶች ተመርቀዋል::
ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ቤቶቹን መርቀው ቁልፉን ለባለቤቶቹ ባስረከቡበት ወቅት ቤቶቹን ለገነቡ ሁሉም ተቋማት አመስግነው፤ እርስ በእርስ እንደ ቤተሰብ በመረዳዳት የተሰሩ ቤቶች መሆናቸውን ገልፀዋል፤ በቀጣይም ይህ የመረዳዳት ባህል ተጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል ሲሉ ከንቲባ ከድር መልእክታቸውን አስተላልፈዋል::
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው በዛሬው ዕለት እንደ ድሬዳዋ አስተዳደር በተቋማት የተሰሩ የበጎ ፈቃድ ስራዎችን በዚህ ልክ መመልከት የሚያስደስት መሆኑን ጠቅሰው ቢሮው ኮሌጆችን አስተባብሮ የድርሻውን አሻራ ማሳረፉ እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 16/2017
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት በኦፊስ ካይዘን ትግበራ ዙሪያ ለቢሮው ሰራተኞች ስልጠና አዘጋጀ።
በዚህም ስልጠናውን ከአስተዳደሩ የካይዘን ኢንስቲትዩት በመጡ ባለሙያ የተሰጠ ሲሆን በቢሮው የሚገኙ ዳይሬክቶሬቶችና ክፍሎች በቀጣይ የሚኖረውን ትግበራ ውጤት ሊያስገኝ በሚችል መልኩ እንዲከውኑ የሚያግዝ ይሆናል።
ቢሮው ለሪፎርም ስራዎች ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን እነዚህም ስራዎች የሆነ ጊዜ ብቻ ተግባር አለመሆኑ በሚያሳይ መልኩ የዚህ ትግበራ አካል የሆነው ኦፊስ ካይዘንን በሁሉም የቢሮው ዳይሬክቶሬቶችና ክፍሎች ላይ ተግባራዊ ማድረግ በተለየ መልኩ ቦታ ተሰጥቶታል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 16/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት መለቀቅን ተከትሎ በየዓመቱ ወደ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ገብተው መሰልጠን ለሚፈልጉ የመግቢያ ነጥብ ተዘጋጅቷል፤
በዚህ መሰረት ከጥቅምት 12/2017 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም ድረስ በድሬዳዋ አስተዳደር በሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የአዲስ ሰልጣኞችን ቅበላ(ምዝገባ) የሚያደርጉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 15/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና የማኔጅመንት አባላት በቢሮውና በኮሌጆች ቅንጅት የሚሰሩ የአቅመ ደካሞችን ቤቶችን ተዘዋውረው ጎበኙ፤
****
በዚህም አቶ ሮቤል ጌታቸው እና ማኔጅመንታቸው በድሬዳዋ አስተዳደር በወረዳ 02፣ 05 እና 08 የሚገኙ በአዲስ መልክ እየተሰሩ የሚገኙ እና ተጠናቀው ለርክክብ ዝግጁ የሆኑ የአቅመ ደካሞችን ቤት በአካል በመገኘት ተመልክተዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም በአስተዳደሩ የሚገኙ የመንግስት ኮሌጆች የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች በአጠቃላይ 7 የአቅመ ደካማ ቤቶችን በአዲስ ሰርተው ለማስረከብ በዚህም ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ቃል መግባታቸው የሚታወስ ነው፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 12/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና የማኔጅመንት አባላት በቢሮውና በኮሌጆች ቅንጅት የሚሰሩ የአቅመ ደካሞችን ቤቶችን ተዘዋውረው ጎበኙ፤
****
በዚህም አቶ ሮቤል ጌታቸው እና ማኔጅመንታቸው በድሬዳዋ አስተዳደር በወረዳ 02፣ 05 እና 08 የሚገኙ በአዲስ መልክ እየተሰሩ የሚገኙ እና ተጠናቀው ለርክክብ ዝግጁ የሆኑ የአቅመ ደካሞችን ቤት በአካል በመገኘት ተመልክተዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም በአስተዳደሩ የሚገኙ የመንግስት ኮሌጆች የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች በአጠቃላይ 7 የአቅመ ደካማ ቤቶችን በአዲስ ሰርተው ለማስረከብ በዚህም ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ቃል መግባታቸው የሚታወስ ነው፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 12/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና የማኔጅመንት አባላት በቢሮውና በኮሌጆች ቅንጅት የሚሰሩ የአቅመ ደካሞችን ቤቶችን ተዘዋውረው ጎበኙ፤
****
በዚህም አቶ ሮቤል ጌታቸው እና ማኔጅመንታቸው በድሬዳዋ አስተዳደር በወረዳ 02፣ 05 እና 08 የሚገኙ በአዲስ መልክ እየተሰሩ የሚገኙ እና ተጠናቀው ለርክክብ ዝግጁ የሆኑ የአቅመ ደካሞችን ቤት በአካል በመገኘት ተመልክተዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም በአስተዳደሩ የሚገኙ የመንግስት ኮሌጆች የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች በአጠቃላይ 7 የአቅመ ደካማ ቤቶችን በአዲስ ሰርተው ለማስረከብ በዚህም ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ቃል መግባታቸው የሚታወስ ነው፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 12/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
የሰልጣኞች ቅበላ በየደረጃው ሰፊ የንቅናቄ ሥራን የሚፈልግ መሆኑ ተጠቆ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እያካሄደ የሚገኘው የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ የክልሎች አፈፃፀም ግምገማ ቀጥሎ የሲዳማ ክልል አፈፃፀምን ተመልከቷል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ ባስተላለፉት መልዕክት፣ በዚህ ዓመት የሚደረገው የሰልጣኞች ቅበላ በየደረጃው ሰፊ የንቅናቄ ሥራን ይፈልጋል ብለዋል፡፡
ዜጎች በቂ መረጃ እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚያስፈልግ የጠቆሙት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ከመደበኛ እና አጫጭር ስልጠናው በተጨማሪ በልምድ የተገኘ ሙያ ላይ ግብ አስቀምጦ መስራት እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ፡
ጥቅምት 12፤ 2017
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols
ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official
ሊንክዲን፡- https://www.linkedin.com/.../ministry-of-labor-skill-fdre/
ኤክስ ፡- https://x.com/Jobs_FDRE
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
