fa
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

رفتن به کانال در Telegram
1 105
مشترکین
+424 ساعت
+67 روز
+3230 روز
آرشیو پست ها
Repost from E-LMIS - ብቁ
🎓🌍የስልጠና እድል 🚀Yokogawa Electric Corporation ከInternational Organization for Migration (IOM) እና የኢትዮጵያ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመ
🎓🌍የስልጠና እድል 🚀Yokogawa Electric CorporationInternational Organization for Migration (IOM) እና የኢትዮጵያ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለኢትዮጵያውያን ወጣቶች በነጻ የሚሰጥ ልዩ የአቅም ግንባታ ስልጠና አዘጋጅቷል። 📚የስልጠና ዘርፎች 🔹Business Ethics & Professional Conduct 🔹Logistics & Supply Chain Management 🔹Import/Export Regulations 🔹የAfCFTA ንግድ እድሎች 🔹የGCC አገራት የስራ ገበያ እና የቅጥር እድሎች 🔹Entrepreneurship 🔹 Workplace Readiness 🔹የጥራት ማረጋገጫና የጥራት ቁጥጥር 🔹የጤና፣ ደህንነት እና አካባቢ ጥበቃ 👥መስፈርቶች 🔹ዕድሜ፦ ከ30 በታች 🔹ትምህርት፦ በ2018 ዓ.ም. የሚመረቁ የባችለር ወይም የማስተርስ ምሩቃን፣ ወይም ባለፉት 2 ዓመታት ውስጥ የተመረቁ። 🔹የትምህርት መስኮች፦ • Supply Chain Management • Procurement • Logistics • Business Administration • Trade Studies • Sustainability • ወይም ሌሎች ተዛማጅ የትምህርት መስኮች። 📍 ቦታ Kaizen Excellence Centre (KEC)፣ አዲስ አበባ 📅የስልጠና ቀን- ከሐምሌ 6–8 ቀን 2018 🎁ከስልጠናው ተሳታፊዎች መካከል 1 ተሳታፊ ተመርጦ በYokogawa Internship Program2019 የልምምድ ፕሮግራም ይሳተፋል። ✅ከአዲስ አበባ ውጭ ለሚኖሩ የተመረጡ ተሳታፊዎች፦ 🔹የትራንስፖርት ወጪ 🔹በስልጠናው ቆይታ የማረፊያ ወጪ ይሸፈናል። 📝አመልካቾች በዚህ https://forms.lmis.gov.et/yokogawa_electric/ በመግባት ትክክለኛ መረጃዎችን ሞልተው ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

🚨 አስቸኳይ የጥንቃቄ መልዕክት   የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪትን በተመለከተ ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ወይም ከሌሎች የመንግስት ተቋማት ውክልና ተሰጥቶናል በማለት በግል ስልክ፣ በአጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፣ በቴሌግራም፣ በዋትስአፕ እና በሌሎች የማህበራዊ ትስስር ገፆች ገንዘብ በመጠየቅ ህብረተሰቡን የሚያጭበረብሩ ሕገ-ወጥ አካላት ተበራክተዋል።   የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት አገልግሎት በተመለከተ በስልክ፣ በአጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፣ በቴሌግራም፣ በዋትስአፕ ወይም በሌላ ማንኛውም የማህበራዊ ትስስር ገፆች ገንዘብ እንዲከፍሉ በፍጹም አይጠይቅም፡፡   በመሆኑም እንዲህ ዓይነት የስልክ ጥሪ፣ የጽሑፍ መልዕክት ወይም በማህበራዊ ሚዲያ በኩል የገንዘብ ጥያቄ ከደረሰዎት፣ ·       ምን አይነት ገንዘብ አንዳይልኩና ·       ምንም ዓይነት የግል ወይም የባንክ መረጃ እንዳያጋሩ እያሳሰብን ረጃውን በአቅራቢያዎ ለሚገኙ የሕግ አስከባሪ አካላት ወይም ለሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና በየደረጃው ለሚገኙ መዋቅሮቹ በአስቸኳይ እንዲያሳውቁ እንጠይቃለን፡፡   ያስታውሱ ·       በስልክ፣ በቴሌግራም፣ በዋትስአፕ፣ በአጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS) ወይም በማንኛውም ሌላ መንገድ ገንዘብ እንዲልኩ የሚጠይቅ ማንኛውም ሰው ወይም ቡድን የመንግስት ተቋምን አይወክልም፤   ·       የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት አገልግሎትን ለማግኘት በአቅራቢያዎ ያሉ የመንግስት ተቋማትን ወይም ሕጋዊ ፈቃድ ካላቸው የሥራ ስምሪት ኤጀንሲዎችን ብቻ ያነጋግሩ፤   ·       ሚስጥራዊ የግል መረጃዎችዎን፣ የባንክ ሂሳብ ቁጥር፣ የይለፍ ቃል (Password) ወይም የOTP ኮድ ለማንም አያጋሩ፤   ·       የውች ሀገር ሥራ ስምሪትን የተመለከቱ መረጃዎች ሚኒስቴሩ የሚያወጣቸውን ይፋዊ መረጃዎች ከተቋሙ ይፋዊ የመገናኛ አውታሮች ብቻ ይከታተሉ፤     ሕጋዊ ስምሪት፣ ለደህንነትዎ ዋስትና ነው!

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ5 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ******* በኢትዮጵያ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የሥራ ስምሪት ከ5 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሕዝብ ተወካዮች በሰጡት ምላሽ እና ማብራሪያ ገልጸዋል። ከእነዚህ መካከል 4.9 ሚሊዮን የሚሆኑት በሀገር ውስጥ የሥራ ዕድል ያገኙ ሲሆኑ፣ ከ101 ሺህ በላይ የሚሆኑት ደግሞ በውጭ ሀገራት የሥራ ስምሪት ተጠቃሚ የሆኑ ናቸው። በተጨማሪም በልዩ የክህሎትና ሙያ ዘርፍ የተሰማሩ 40 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል ማግኘታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቅሰዋል። የየዘርፉን የሥራ ዕድል ፈጠራ ድርሻ በተመለከተም፥ ግብርና ከ2 ሚሊዮን በላይ፣ አገልግሎት፣ ንግድ እና ዲጂታላይዜሽን 1.8 ሚሊዮን እንዲሁም ኢንዱስትሪ ከ900 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን አብራርተዋል። የሥራ ዕድል ፈጠራ አፈጻጸም በሀገር ውስጥ የ13 በመቶ እንዲሁም በውጭ ሀገራት ስምሪት የ27 በመቶ ዕድገት ያሳየ መሆኑን አክለው ገልጸዋል። የፋይናንስ ዘርፉ በዲጂታላይዜሽን መታገዙ ያመጣውን ከፍተኛ ለውጥ ተከትሎ የሀገራችን አጠቃላይ ቁጠባ ከነበረበት 2.6 ትሪሊዮን ብር አሁን ላይ ወደ 4 ትሪሊዮን ብር ገደማ መድረሱን ተናግረዋል። አዲሱ የውጭ ምንዛሬ ፖሊሲ ተግባራዊ ከሆነ ወዲህ የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ባንክ ገበያውን ለማረጋጋት 2.7 ሚሊዮን ዶላር ለገበያ ማቅረቡንና የፋይናንስ ዘርፉ በአሁኑ ወቅት በትሪሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ የሚንቀሳቀስበት ግዙፍ ሴክተር መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።

Repost from E-LMIS - ብቁ
🚀 ሜድሮክ ኮንስትራክሽን ኢትዮጵያ ኃ.የተ.የግል ማህበር በሥራና ክህሎት ሚኒስትር በለማው የኢትዮጵያ ሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት E-LMIS በኩል ከታች በተዘረዘሩት የሥራ ዘርፎች አመልካቾችን አወዳድ
🚀 ሜድሮክ ኮንስትራክሽን ኢትዮጵያ ኃ.የተ.የግል ማህበር በሥራና ክህሎት ሚኒስትር በለማው የኢትዮጵያ ሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት E-LMIS በኩል ከታች በተዘረዘሩት የሥራ ዘርፎች አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። 👷 ክፍት የስራ መደቦች 🔹 HR/Admin Officer2 ቦታ ትምህርት፡ BA Degree በManagement፣ Accounting ወይም ተዛማጅ ዘርፍ የስራ ልምድ፡ 3–4 ዓመት የቅጥር አይነት፡ ኮንትራት 🔹 Store Keeper2 ቦታ ትምህርት፡ Degree በSupply Chain Management፣ Accounting፣ Management ወይም ተዛማጅ ዘርፍ የስራ ልምድ፡ 3 ዓመት የቅጥር አይነት፡ ኮንትራት 🔹 Excavator Operator III15 ቦታ ትምህርት፡ 10ኛ ክፍል ያጠናቀቀ የስራ ልምድ፡ በExcavator Operator 8 ዓመት የቅጥር አይነት፡ ቋሚ 🏫 ስለሆነም በዚህ የሥራ እድል መወዳደር ለምትፈልጉ በመጀመሪያ lmis.gov.et ብላችሁ በመመዝገብ አቅራቢያችሁ ባለ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል (ወረዳ ወይም ቀበሌ) በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ በመስጠት የሰራተኛነት መለያ ቁጥር /Labor ID/ ከያዛችሁ በዚህ https://forms.lmis.gov.et/midroc-construction-ethiopia/ በመግባት ትክክለኛ መረጃዎትን ሞልተው ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን። 📆 አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ከ 29/10/2018 ዓ.ም ጀምሮ በ5 የስራ ቀናት ውስጥ ማመልከት ይችላሉ። ☎️አስተያየት እና ጥቆማዎን በ9138 የሥልክ መስመር ይደውሉ።

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥሪ ለኢትዮጵያ ልጆች ******* ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ላለፉት አምስት ዓመታት በፓርላማ ቆይታቸው ኢትዮጵያን ላገለገሉ የብልጽግና ፓርቲ
+1
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥሪ ለኢትዮጵያ ልጆች ******* ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ላለፉት አምስት ዓመታት በፓርላማ ቆይታቸው ኢትዮጵያን ላገለገሉ የብልጽግና ፓርቲ አባላት እና የሌሎች ፓርቲ አባላትን በከፍተኛ አክብሮት አመስግነዋል። በተለይም በዘንድሮ በሚመሠረተው መንግሥት አካል ለማይሆኑት የፓርላማ አባላት በሌላ የመንግሥት ኃላፊነት እንዲያገለግሉ የመንግሥታቸው ፍላጎት መሆኑን ጠቁመዋል። “አንዳንዶቻችሁ በሚቀጥለው ምክር ቤት ከእኛ ጋር የማትቀጥሉ መሆኑን የዘንድሮ ምርጫ ያሳየ ቢሆንም ክቡር አቶ ደሳለኝ ጫኔ የመጨረሻ ያሉት ንግግር የመጨረሻ ባይሆን የመንግሥትት ምኞት መሆኑን እና ከምክር ቤት ውጪ እነዚህ አባላት ከመንግሥታችን ጋር በጋራ ሆነን ኢትዮጵያን እንድናገለግል በተከበሩ ምክር ቤት ፊት ጥሪ ላቀርብላችሁ እፈልጋለሁ” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። “መንግሥትታችን እናንተን አካትቶ ኢትዮጵያን ማልማት ይፈልጋል። ኢትዮጵያ የጋራ ሀገራችን ናት። እኛም፣ እናንተም ልጆቿ በምክር ቤት ብቻ ሳይሆን በተለያየ ዘርፍ ተባብረን ኢትዮጵያን እንድናበለጽግ አብረን እንድንሠራ ጥሪ ላቀርብላችሁ እፈልጋለሁ” ብለዋል።

Repost from E-LMIS - ብቁ
🔊🗣️አስደሳች ዜና ለስራ ፈላጊዎች! የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከE-LMIS ጋር በመተባበር ከዚህ በታች በተገለጹት ክፍት የስራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ ፣ በዝውውር; እና በኮንትራት መ
🔊🗣️አስደሳች ዜና ለስራ ፈላጊዎች! የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከE-LMIS ጋር በመተባበር ከዚህ በታች በተገለጹት ክፍት የስራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ ፣ በዝውውር; እና በኮንትራት መቅጠር ይፈልጋል። 🏫 ስለሆነም በዚህ የሥራ እድል መወዳደር ለምትፈልጉ በመጀመሪያ lmis.gov.et ብላችሁ በመመዝገብ አቅራቢያችሁ ባለ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል (ወረዳ ወይም ቀበሌ) በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ በመስጠት የሰራተኛነት መለያ ቁጥር /Labor ID/ ከያዛችሁ በዚህ https://forms.lmis.gov.et/federal_-civil_services_three/ በመግባት ትክክለኛ መረጃዎትን ሞልተው ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን። 📆 አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ከ 29/10/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 7ቀናት ማመልከት ይችላሉ። ☎️አስተያየት እና ጥቆማዎን በ9138 የሥልክ መስመር ይደውሉ።

በGermeny Development Bank/KFW እና AUDA-NEPAD አማካኝነት ተግባራዊ የሚደረገው የSIFA ፕሮጀክትን የህንጻ ግንባታ ክትትልና ግምገማ እንዲሁም ሙያዊ ድጋፍ ለድረግ ያለመ በዶ/ር
+8
በGermeny Development Bank/KFW እና AUDA-NEPAD አማካኝነት ተግባራዊ የሚደረገው የSIFA ፕሮጀክትን የህንጻ ግንባታ ክትትልና ግምገማ እንዲሁም ሙያዊ ድጋፍ ለድረግ ያለመ በዶ/ር ማውሪዚዮ ፒሮኒ የተመራ ከፍተኛ ባለሙያ ቡድን የመስክ የስራ ጉብኝት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አከናወነ፡፡ የከፍተኛ ልኡክ ቡድኑን የተቀበሉትና የኮሌጁን አጠቃላይ ስራ ያስጎበኙት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ እንዳሉት የSIFA ፕሮጀክት በኮሌጃችን ተግባራዊ መሆኑ የአካባቢውን ብሎም የቀጠናውን ወጣቶች በICT የዳበረና እውቀት ያለው ትውልድ ለመገንባት ያስችለናል ብለዋል።ይህንንም ለማድረግ ሁሉም በርብርብ እየሠራ እንዳለ አብራርተዋል። ከፍተኛ ልኡክ ቡድኑን የመሩት በAUDA-NEPAD የSIFA ፕሮጀክት ከፍተኛ የህንጻ አርክቴክት ባለሙያ የሆኑት ዶ/ር ማውሪዚዮ ፒሮኒ እንዳሉት የህንጻ ግንባታው ስራ በጥሩ ሁኔታ እና በጥራት መሰራቱን ያደነቁ ሲሆን ግንባታውን ለመጨረስ በቀረው 6 ወር ውሰጥ በጋራ መረባረብ ያሰፈልጋል ያሉ ሲሆን በእኛ በኩልም ስራውን ቶሎ ለመጨረስ ኃላፊነታችንን እነወጣለን ብለዋል። ልኡክ ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኘውንና ግንባታው እየተፋጠነ የሚገኘውን የICT ልህቀት ማእከልን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በኮሌጁ በነበራቸው ቆይታ እጅግ ደስተኛ እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ሰኔ 27/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በዚህ ክረምት እረፍትዎን ወደ ገቢ ምንጭነት ይቀይሩ! የዘመኑን ተፈላጊ ክህሎቶች በመማር እራስዎን ለስራ ገበያ ብቁ ማድረግ ይፈልጋሉ? እንግዲያውስ መልካም ዜና! የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከ
በዚህ ክረምት እረፍትዎን ወደ ገቢ ምንጭነት ይቀይሩ! የዘመኑን ተፈላጊ ክህሎቶች በመማር እራስዎን ለስራ ገበያ ብቁ ማድረግ ይፈልጋሉ? እንግዲያውስ መልካም ዜና! የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከ A2B Creatives ጋር በመተባበር ለሁለት ወራት የሚቆይ አጠቃላይ የቪዲዮ ኤዲቲንግ እና ግራፊክስ ዲዛይን ስልጠና አዘጋጅቶላችኋል። 👉 የግራፊክስ ዲዛይን (Graphics Design): ማራኪ የሆኑ የብራንዲንግ ስራዎችን፣ ፍላየሮችን እና የማህበራዊ ሚዲያ ፖስተሮችን ፣ ሎጎዎችን መስራት (Adobe Photoshop,Canva ...)። 👉 የቪዲዮ ኤዲቲንግ (Video Editing): ለዩቲዩብ፣ ለቲክቶክ፣ ለፊልሞች እና ለድርጅቶች ማስታወቂያ የሚሆኑ ፕሮፌሽናል ቪዲዮዎችን ማቀናበር (Adobe Premiere Pro ...)። ለመማር ምቹ እና ዘመናዊ የሆኑ መሰረተ-ልማቶች የተሟሉለት፦ 🖥 Professional Computer Lab: ዘመናዊ የኮምፒውተር ላብራቶሪ። 🌐 Internet Access: ማቴሪያሎችን በነፃነት ለማውረድ የሚያስችል ፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎት። 👨‍🏫 Experienced Instructor: በዘርፉ ሰፊ የገበያ እና የማስተማር ልምድ ባላቸው ባለሙያ አስተማሪዎች https://docs.google.com/forms/d/18NF9YM3GTqrA6aMYC9koNvyKaI8CvBLzr40JbBGUd6o/viewform የምዝገባ ቦታ:- በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የICT ዲፓርትመንት በአካል ተገኝተው መመዝገብ ይችላሉ:: 📞 ለበለጠ መረጃ እና ለምዝገባ በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች ያግኙን፦ 📱 0976315798 📱 0968377071

ድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አመራሮችና አባላትን ያካተተ ልዑካን ቡድን ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረ፡፡ #EIPC ሰኔ 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አመራሮችና አባላትን የያዘው ልዑካን ቡድን የኮሌጁን አጠቃላይ የስራ እቅስቃሴ መቃኘት ሚያስችለውን የመስክና ስራ ጉብኝት በዛሬው እለት በኮሌጁ ማካሄድ ችሏል:: ልዑካን ቡድኑን ተቀብለው ያስተናገዱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው.. ሰልጥነው የበቁና በሙያቸው ሀገር የሚያሻግሩ አምራች ዜጎች መፍለቂያ ወደሆነው ኮሌጃችን እንኳን በደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን ተቋማችን ከድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጋር በመቀናጀት አስተዳደሩ ላይ ለውጥ የሚያመጡ ተግባራትን የማከናወን ፍላጎት ያለው መሆኑን ገልፀው በቀጣይ በምጠይቁን ጉዳዮች በሙሉ ከተቋማችሁ ጋር በቅንጅት ለመስራት በኮሌጁ በኩል ሙሉ ዝግጁነት ያለ መሆኑንም ገልፀዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከምስረታው ጀምሮ አሁን እስከደረሰበት ደረጃ ያለውን አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ በኮሌጁ ዲን አማካኝነት ለቡድኑ ገለፃ የተደረ ሲሆን በዚህም የISO 9001:2015 የጥራት አስተዳደር ስርዓት አውቅና ከማግኘት ባሻገር በትምህርትና ስልጠናው፣ በቴክኖሎጂ ልማትን ጨምሮ በዲጂታላይዜሽን አተገባበር የተከናወኑ የለውጥ ስራዎችና የተመዘገቡ ውጤቶችን በዝርዝር ለልዑካን ቡድኑ ገለፃ አድርገዋል፡፡ ቀደም ሲል በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ በቅንጅት የተሰሩ የተወሰኑ ስራዎች መኖራቸውን ያስታወሱት በኮሌጁ የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ስራ ሂደት ሀላፊና የኮሌጁ ም/ል ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ በቀጣይም የሁለቱን ተቋማት ግንኙነቶችን በማጠናከርና የጋራ መግባቢያ ስምምነቶችን በማድረግ በአጫጭር ስልጠናዎች፣ በቴክኒካል ጉዳዮች እንዲሁም በቴክኖሎጂ ልማቶች ላይ በጋራ እንሰራለንም ብለዋል:: በተጨማሪም የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መመሪያ አባላትን የያዘው ልዑክ በኮሌጁ የሚገኙ የስልጠና ወርክሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በነበራቸው ጉብኝትም አጠቃላይ በኮሌጁ የስራ እንቅስቃሴ መደነቃቸውን ገልፀው በቀጣይ ስልጠናዎችን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከኮሌጁ ጋር ለመስራት ፅኑ ፍላጎት ያሳደረባቸው ጉብኝት እንደነበርም ገልፀዋል:: ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት አማራጮች ያግኙ፡- በፌስቡክ -https://www.facebook.com/share/19wDiZAD7x/?mibextid=wwXIfr በቴሌግራም -https://t.me/EIPC2001 በቲክቶክ -https://www.tiktok.com/@ethioitaly2001?_t=ZM-90MxIrBN8qe&_r=1 በዌብሳይት - https://ethioitalypolytechniccollege.com/

ለጣሊያን ሀገር የሥራ ዕድል የምዝገባ ጥሪ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በገባው የሁለትዮሽ ስምምነት መሰረት በህጋዊ የውጪ ሀገር ሥራ ስምሪት ፕሮግራም በጣሊያን ሀገር በሆቴልና መስተንግዶ (Hospitality) ዘርፍ የሰው ኃይል ይፈለጋል። የዜጎችን መብት፣ ደህንነት እና ጥቅም በማስጠበቅ ህጋዊ በሆነ መንገድ ወደ ጣሊያን ሄደው መስራት የሚፈልጉ አመልካቾች እንዲያመለክቱ እናሳውቃለን። 🏨 የሥራ መደቦች፦ 🔹ጸሐፊ(Commis de Rang / F&B Server) – 19 ቦታዎች 🔹 የፅዳት ሰራተኛ (Room Attendant / Housekeeping) – 20 ቦታዎች 🔹 ረዳት ሼፍ (Commis Chef) – 13 ቦታዎች 🔹 የእቃ አጣቢ (Kitchen Steward / Dishwasher) – 11 ቦታዎች 🔹 የወለል ረዳት (Floor Porter / Houseperson) – 3 ቦታዎች 🔹 የቢሮ አስተናጋጅ (Front Office Agent / Receptionist) – 4 ቦታዎች 🔹 የጥገና ቴክኒሺያን (Maintenance Technician) – 1 ቦታ 🔹 የስፓ ቴራፒስት / የማሳጅ ባለሙያ (Spa Therapist / Masseuse) – 1 ቦታ 📌 የማመልከቻ መስፈርቶች ✅ ከስራው ጋር ተያያዥ የስራ ልምድ ያላቸው ተመራጭ ናቸው። ✅ ለአብዛኛዎቹ የስራ መደቦች የእንግሊዝኛ እና/ወይም የጣሊያንኛ ቋንቋ እውቀት ያስፈልጋል። ✅ ለአንዳንድ የሙያ መደቦች ተዛማጅ የሙያ ማረጋገጫ ወይም የሆቴል እና መስተንግዶ ትምህርት ተመራጭ ነው። 📅 የሥራ ቆይታ አብዛኛዎቹ የስራ መደቦች ለ2026/2027 የክረምት የቱሪዝም ወቅት የሚቀጠሩ ሲሆን፣ አንዳንድ የስራ መደቦች ዓመቱን ሙሉ ወይም በበጋና በክረምት ወቅት የሚሰሩ ናቸው። ✅ ለመመዝገብ 1.Labor ID ካሎት በተሰጠው የማመልከቻ ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ያመልክቱ። 2.Labor ID ከሌሎት የሚከተሉትን ሂደቶች ይከተሉ፦ 1. በ lmis.gov.et ይመዝገቡ። በአቅራቢያዎ ባለ የአንድ ማዕከል (ወረዳ ወይም ቀበሌ) በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ ይስጡ እና የሰራተኛነት መለያ ቁጥር (Labor ID) ይያዙ። 1. Labor ID ካገኙ በኋላ በተሰጠው የማመልከቻ ማስፈንጠሪያ https://forms.lmis.gov.et/italy-hotel/ገብተው መረጃዎትን በትክክል ሞልተው ያመልክቱ። ማሳሰቢያ • ምዝገባም ሆነ ስምሪቲ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ ብቻ የሚከናወን ሲሆን ሚኒስቴሩ ለየትኛውም አካል ውክልናም ሆነ ፈቃድ አለመስጠቱን እንገልፃለን። • ምንም አይነት ክፍያም የለውም

ለኮሌጁ ሰራተኞች በISO 9001:2015 QMS ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ:: #EIPC ሰኔ 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የISO 9001:2015 የጥራት አስተዳደር ስርዓት ትግበራን በተመለተ ለኮሌጁ አዲስ ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል:: በኮሌጁ የጥራት ደረጃን አስጠብቆ የአገልግሎት እርካታን በዘላቂነት የማረጋገጥ ሚናው የሁሉም ሰራተኛ እንደሆነ የገለፁት በኮሌጁ የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ሀላፊና የኮሌጁ ም/ል ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ በተቋሙ ከአመራር ጀምሮ በየደረጃው የሚገኝ ሁሉም ሰራተኛ በISO 9001:2015 QMS ትግበራ ተመሳሳይ ግንዛቤ እንዲኖረው ለማስቻል ታልሞ ስልጠናው መዘጋጀቱንም ገልፀዋል:: በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ የኮሌጁን የISO 9001:2015 QMS አተገባበር ሂደትና የሰራተኛው ሚናን አስመልክቶ በኮሌጁ የISO Task Force ባለሙያዎች አማካኝነት ስልጠናውን በተሳካ ሁኔታ መስጠትም ተችሏል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አለም አቅፍ ተወዳዳርነቱን ለማረጋገጥ በቁጠኝነት ባከናወናቸው ተግባራት የISO 9001:2015 የጥራት አስተዳደር ስርዓት እውቅና የተሰጠው በምስራቅ ኢትዮጵያ ብቸኛው የመንግስት ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ሲሆን ትምህርትና ስልጠናውን ጨምሮ አጠቃላይ የደንበኞች አገልግሎቱን በጥራት እየሰጠ የሚገኝ ተቋምም ነው:: ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት አማራጮች ያግኙ፡- በፌስቡክ -https://www.facebook.com/share/19wDiZAD7x/?mibextid=wwXIfr በቴሌግራም -https://t.me/EIPC2001 በቲክቶክ -https://www.tiktok.com/@ethioitaly2001?_t=ZM-90MxIrBN8qe&_r=1 በዌብሳይት - https://ethioitalypolytechniccollege.com/