1 133
订阅者
-224 小时
+17 天
+3530 天
帖子存档
የድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት መርሃ ግብርን ዛሬ በይፋ አስጀመረ ...!!
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት መርሃ ግብርን በይፋ አስጀመረ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመተባበር የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች ማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሂዷል።
በዚህ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የደም ልገሳ፣ የችግኝ ተከላ፣ የማዕድ ማጋራት እንዲሁም የአቅመ ደካሞች ቤት ግንባታና እድሳት ማስጀመሪያ ስራዎች በይፋ ተከናውነዋል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በአስተዳደሩ በርካታ የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።
ይህ የበጎ ፍቃድ ስራ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሀሳብ አመንጪነት ከተጀመረ በኋላ የበርካታ አቅመ ደካማ ዜጎችን ችግር መቅረፍ መቻሉን አቶ ኢብራሂም ጠቅሰው፣ መርሃ ግብሩ ወጣቶች በበጎ ፍቃድ ስራዎች ላይ በስፋት እንዲሳተፉ ትልቅ አቅም መፍጠሩን አብራርተዋል።
ስራና ክህሎት ቢሮ ከአቅመ ደካሞች ጎን በመቆም ላሳየው አለኝታነት ምስጋናቸውን ያቀረቡት አቶ ኢብራሂም፣ ይህ ተግባር ይበልጥ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትና ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በንቃት ሊሳተፍበት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው፣ በመደመር መንግስት በየክረምቱ የተለያዩ ሰው ተኮር ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
እነዚህ የበጎ ፍቃድ ስራዎች በተጨባጭ በዜጎች ህይወት ላይ ትርጉም ያለው ለውጥና ውጤት ማምጣታቸውንም አቶ ሮቤል አመላክተው፣ በዛሬው የቢሮው የበጎ ፍቃድ ስራዎች የማስጀመሪያ መርሃ ግብር 30 ለሚሆኑ ዜጎች ማዕድ ማጋራት የተከናወነ ሲሆን፣ በክረምቱ ወቅት በአጠቃላይ ለ100 ዜጎች ማዕድ ለማጋራት፣ በስፋት የችግኝ ተከላ ለማካሄድ እና 50 ዩኒት ደም ለማሰባሰብ መታቀዱን ተናግረዋል።
ከዚህም በተጨማሪ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እንደሚደረግና የ7 አቅመ ደካማዎችን ቤት ገንብቶ የማስረከብ ስራ እንደሚሰራ ኃላፊው አመላክተው፣ ይህ ተግባር የመደመር መንግስት ለህዝቡ ያለውን ቅርበት በተግባር የሚያሳይ መሆኑን ገልፀዋል።
በመርሃ ግብሩ ሲሳተፉ ያነጋገርናቸው የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች በበኩላቸው፥ በጎ ፍቃድ አገልግሎት የህሊና እርካታን ከመስጠቱም በላይ የወገንን ችግር በተግባር ለመቅረፍ ትልቅ እድል የሚፈጥር በመሆኑ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።
በክረምቱ ወቅት የታቀዱት የልማትና የድጋፍ ስራዎች ሙሉ በሙሉ ግባቸውን እንዲመቱ የጀመሩትን ንቁ ተሳትፎ አጠናክረው ለመቀጠልና የተጣለባቸውን አደራ በላቀ ቁርጠኝነት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
በድሬዳዋ ከተማ የሚገኙ ወጣቶች በሙያና ክህሎት የዳበሩ እና ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ በኮሌጁ የሚሰጡ ገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚሰጡ ተገለጸ፡፡
ክረምትን በክህሎት በቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በሚል መሪ ቃል የአካባቢውን ወጣቶች ቢያስ የአንድ ሙያ ባለቤት ለማድረግ ታልሞ የተዘጋጀው የክረምት የክህሎት ስልጠና በዛሬው እለት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዛሬው እለተ ተጀመረ፡፡
የአካባቢው ወጣቶች ክህሎት ያለውና አመለካከቱ የተለወጠ ወጣት ከራሱ አልፎ ሃገሩን መለወጥ ይችላል ያሉት እና የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ ይህንንም ለውጥ ለማምጣት ደግሞ ትክክለኛ ምርጫ የሚሆነው ሙያና ክህሎትን ወደሚያስጨብጠው የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች መምጣት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ደግሞ የአካባቢውን ወጣቶች በሙያ የዳበሩ እና ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ የተለያዩ ገበያ ተኮር ስልጠናዎችን በማዘጋጀት በክረምቱ እንዲሁም በበጋው የስልጠና ወቅት ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል የዘንድሮውን የክረምት ስልጠና ለመሳተፍ ኮሌጃችንን ስለመረጣችሁና የእረፍት ጊዜያችሁን በክህሎት ለማሳለፍ ስልመጣችሁ አመሰግናለሁ የስልጠና ጊዜያችሁ የተሳካ እንዲሆን መልእክቴን አስተላልፋለሁ ብለዋል፡፡
በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ዲን የውጤት ተኮር ት/ት ስልጠና ኃላፊ አቶ ቢቂላ ታደሰ እንዳሉት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ወጣቶችን ሙያና ክህሎት እንዲኖራቸው እንዲሁም አመለካከታቸው የተቀየረና ከራስ አልፈው ለሀገር የሚተርፉ ወጣቶችን በሚሰጠው ስልጠና እያፈራ ይገኛል፡፡ በዛሬው እለትም ገበያ ተኮር በሆኑ የክረምት አጫጭር ስልጠናዎችን ለመውሰድ ወደ ኮሌጁ ስለመጣችሁ እናመሰግናለን የስልጠና ጊዜያችሁም የተሳካ እንዲሆን አስፈላጊውን ነገር እናደርጋለን ብለዋል ፡፡
በዘንድሮ የክረምት ስልጠና በኮሌጁ ለመሳተፍ በርካታ የአካባቢው ወጣቶች በኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ፣በአውቶ ሞቲቭ ቴክኖሎጂ፣በማኑፋክቸሪንግ ቴክኖሎጂ፣በኤሌክትሪካል ቴክኖሎጂ፣በውድዎርክ ቴክኖሎጂ እና በሌዘርና ፋሽን ዲዛይን እንዲሁም በሆቴል ቱሪዝምና ICT ዘርፎች ስልጠናቸውን ለመውሰድ ተመዝግበዋል፡፡
ኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ሀምሌ 24/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የ2018 የክረምት የክህሎት ስልጠና በኮሌጁ ተጠናክሮ መካሄዱን ቀጥሏል::
#EIPC ሐምሌ 23. 2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 "የአንድ ሙያ ለአንድ ዜጋ" የክረምት ስልጠና ላይ በመሳተፍ ላይ የሚገኙ ወጣቶች ለሶስት ቀናት ሲከተታተሉ የቆየውን የህይወት ክህሎት(Life Skill) ስልጠና አጠናቀቁ::
ሰልጣኞቹ የህይወት ክህሎት ስልጠናቸውን እንዳጠናቀቁ በኮሌጁ የሚገኙ ዲፓርትመንቶች እና ስልጠና የሚሰጥባቸውን ወርክሾፖች ተዘዋውረ የተመለከቱ ሲሆን ስለ ሙያ ዘርፎችም ሰፊ ግንዛቤ ተፈጥሮላቸዋል::
የክረምት ክህሎት ሰልጣኞቹ በተፈጠረላቸው ግንዛቤ መነሻነት ሚፈልጉትን የሙያ ስልጠና አይነት የመረጡ ሲሆን ቀጣይ በተቀመጠላቸው መርሀ-ግብር መሰረትም ስልጠናቸውን የሚከታተሉ ይሆናል::
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት አማራጮች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/share/19wDiZAD7x/?mibextid=wwXIfr
በቴሌግራም -https://t.me/EIPC2001
በቲክቶክ -https://www.tiktok.com/@ethioitaly2001?_t=ZM-90MxIrBN8qe&_r=1
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
በአስተዳደሩ ለሚገኙ ወጣቶች የክረምት ወቅት የሙያ ስልጠና በኮሌጁ መስጠት ተጀመረ::
#EIPC ሐምሌ 21. 2018 ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 የክረምት ወቅት የክህሎት ስልጠና "አንድ ሙያ ለአንድ ዜጋ" በሚል በአስተዳደሩ ለሚገኙ ተማሪዎችና ወጣቶች በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ያዘጋጀውን የክህሎት ስልጠና ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር አካሂዷል::
በእለቱ ለወጣቶቹ በተዘጋጀው ኦረንቴሽን ላይ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ባስተላለፉት መልዕክት የዚህ የክረምት ወቅት ስልጠና የተዘጋጀበት ዋና አላማ ጊዜው የክህሎት በመሆኑ ወጣቶች የክረምት ጊዜያቸውን ቁምነገር ላይ በማዋል ቢያንስ የአንድ ሙያ ባለቤት እንዲሆኑ ለማስቻል መሆኑን ገልፀው በተለይም የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ክረምቱን በኮሌጃችን በሚኖራችሁ ቆይታ ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ በጥልቀት የምትገነዘቡ በመሆኑ በቀጣይ ምዕራፋችሁ ለሙያ ተኮር ስልጠናዎች ቅድሚያ እንድሰጡ ይረዳችኃልም ብለዋል::
ወጣቶች በትምህርት ያገኙትንም ሆነ ያላቸውን ሀሳብ ወደ ተግባር ለመቀየር ከየትኛውም ቦታ በተሻለ ቴክኒክና ሙያ ላይ ምቹ ሁኔታ መኖሩን የገለፁት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የትምህርትና ስልጠና ዋና ሀላፊ አቶ ኤሊያስ አህመድ ሲሆኑ አክለውም ወጣቶች በተመቻቸላቸው ወርቃማ እድል ስልጠናውን በአግባቡ በመውሰድ በቆይታቸው ተፈላጊውን ክህሎት ይዘው እንዲወጡ አሳስበዋል::
ቴክኒክና ሙያ ከሌሎች የትምህርት ተቋማት ልዩ የሚያደርገው ወጣቶች የተማሩትን በእጃቸው ነካክተው በተግባር የሚሰለጥኑበትና ሰርተው የሚያሳዩበት ተቋም በመሆኑ ነው ያሉት ደግሞ የኮሌጁ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንዱስትሪ ኤክስቴሽን አገልግሎት ዋና ሀላፊ እና ም/ል ዲን የሆኑት አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ አያይዘውም የክረምት ሰልጣኞች ከሚወስዷቸው ስልጠናዎች በተጨማሪ ወደ ቢዝነስ ሊቀይሩት የሚችሉት የቢዝነስ ሀሳብ ካላቸው ቢዝነስ ፕላናቸውን በኮሌጁ እንዲሰሩ ከማድረግ በተጨማሪ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትልም የሚደረግ መሆኑን በመድረኩ ገልፀዋል::
የ2018 የአንድ ሙያ ለአንድ ዜጋ የክረምት ስልጠና ላይ ለመሳተፍ ወደ ኮሌጁ የመጡ ወጣቶች በቅድሚያ የህይወት ክህሎት(Life Skill) ስልጠና የሚሰጣቸው ሲሆን የህይወት ክህሎት ስልጠናውም የቀጣይ ህይወታቸውን የመምራት ክህሎት፣ችግሮችን የመፍታት ክህሎት እንዲሁም የውሳኔ አሰጣጥ ክህሎቶችን የሚያዳብሩበት ስልጠና ሲሆን የህይወት ክህሎት ስልጠናውን እንዳጠናቀቁ በቀጣይ በመረጡት የሙያ ዘርፍ ላይ ስልጠናቸውን የሚወስዱ ይሆናል::
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት አማራጮች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/share/19wDiZAD7x/?mibextid=wwXIfr
በቴሌግራም -https://t.me/EIPC2001
በቲክቶክ -https://www.tiktok.com/@ethioitaly2001?_t=ZM-90MxIrBN8qe&_r=1
በዌብሳይት - https://ethioitalypolytechniccollege.com/
+8
ትልቅ ብሔራዊ የስራ ቅጥር ማስታወቂያ | በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የአገር መከላከያ ሚንስቴር!
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የአገር መከላከያ ሚንስቴር የመደበኛ ሠራዊት፣ ለዕጩ መኮንን እና ለልዩ ልዩ ሙያተኞች ስራ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሰራተኞችን ለመቅጠር ማስታወቂያ አውጥቷል።
📅 የማመልከቻ ጊዜ፡
⏲ የመደበኛ ሰራዊት እና የሙያተኛ ምዝገባ እስከ ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም ድረስ ይሆናል።
📍 ማመልከቻ ቦታ፡ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና የአንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት በአካል በመቅረብ መመዝገብ ይቻላል።
ኢትዮጵያ እንዴት ወደብ-አልባ ሆነች? ሴራ እና የሀገር ክህደት
*****
ኢትዮጵያ እንዴት ወደብ-አልባ ሆነች? የ1983 ዓ.ም የሥልጣን ሽግግር ኢትዮጵያን ከባሕር በር በማራቅ ሀገርን ለማያቋርጥ የደኅንነት ስጋት ያጋለጠበት ወቅት ነበር።
የኢትዮጵያ ወደብ-አልባ መሆን ድንገተኛ የታሪክ አጋጣሚ ሳይሆን፣ በወቅቱ ሥልጣን በያዙት የሕወሓት/ኢሕአዴግ መሪዎች ሆን ተብሎ የተፈጸመ፣ ሕጋዊ መሠረት የሌለው ውሳኔ ውጤት ነው።
የሥልጣን አልባነት እና የታሪክ ምጸት
የሴራው የመጀመሪያው ምዕራፍ የሚጀምረው በሽግግሩ ወቅት ነው። በወቅቱ የፖለቲካ ሥልጣኑን በኃይል የተቆጣጠሩት፣ በለንደን ጉባኤ እና በሌሎች መድረኮች ኤርትራ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንድትገነጠል ፈቃዳቸውን ሰጡ።
እዚህ ላይ መስተዋል ያለበት ትልቁ የታሪክ ምጸት እና የሕግ ስተት፣ የባሕር በር አሳልፎ የመስጠት ውሳኔ የወሰነው አካል (የሽግግር መንግሥቱ) እንዲህ ዓይነት ዘላቂ እና ብሔራዊ ውሳኔ ለማሳረፍ የሚያስችል ሕጋዊም ሆነ ሞራላዊ ውክልና (ሥልጣን) ያልነበረው መሆኑ ነው።
ያለ ሕዝበ ውሳኔ፣ ያለ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ተሳትፎ እና ያለ ጥልቅ ብሔራዊ ውይይት፣ በአንድ የታጠቀ ቡድን ፍላጎት ብቻ ኢትዮጵያ ለዘመናት ስትጠቀምባቸው የነበሩትን፣ በተለይም እንደ አሰብ ያሉ ስትራቴጂክ ወደቦችን አጣች። ይህንን ውሳኔ ያሳለፈ ተጠያቂ የሚሆን ተቋም አለመኖሩ ደግሞ ጉዳዩን እስካሁን ድረስ አስገራሚ አድርጎታል።
በዚህ ውሳኔ ኢትዮጵያ ለዘመናት የነበራትን ቀጥተኛ የባሕር ንግድ መስመር እና ዓለም አቀፍ ተደራሽነት አቋረጠች።
የታሪክ ጥያቄ እና የአክሱም ሥልጣኔ ላይ የተፈጸመው ክህደት
ይህ ውሳኔ ያለ ተቃውሞ አልቀጠለም። በርካታ ኢትዮጵያውያን ምሁራን፣ አንጋፋ ዐርበኞች እና የፖለቲካ ተንታኞች እና ዕድሉ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ሁሉ ይህንን በጽኑ በመቃወም፣ ሥርዓቱን ተጋፍጠውታል።
በተለይም ሻለቃ አድማሴ፣ ፕሮፌሰር ያዕቆብ ኃይለማርያም የመሳሰሉ ምሁራን ያሰሙት የነበረውን አቤቱታ እና ድምፅ ትውልድ የሚዘነጋው አይሆንም። በርካታ የዩኒቨርሲቲ ምሁራንም በይፋ አውግዘዋል።
የኢትዮጵያን ሕጋዊ እና ታሪካዊ የባሕር በር መብት መከበር እንዳለበት አጥብቀው ተከራክረዋል። የኤርትራ መገንጠል የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ፣ የጂኦ-ፖለቲካ እና የደኅንነት ጥቅም በጽኑ የሚጎዳ መሆኑን አስጠንቅቀዋል።
ይሁን እንጂ፣ የወቅቱ መሪዎች እነዚህን ተቺዎች ‘የፊውዳል ሥርዓት ርዝራዦች’፣ ‘የሰውን ሀገር ለመቀማት የሚቋምጡ ተስፋፊዎች’ በማለት በሶሻሊስታዊ ቀኖና አጣጥለውታል።
ይባስ ብሎም፣ የጥንታዊቷ ኢትዮጵያ እና የአክሱም መንግሥት የነበራትን የቀይ ባሕር ተጋሪነት መብት የሚገልጹትን ጥንታዊ የታሪክ ማስረጃዎች ‘ተረት ተረት’ በማለት አዲሱ ትውልድ ስለ ታሪኩ እንዳያውቅ አደረጉ።
የአክሱም ሥልጣኔ የባሕር ንግድ መስመሮችን በመቆጣጠር የደረሰበትን ከፍታ የሚዘክሩትን የታሪክ ሰነዶች ችላ በማለት፣ “አክሱም እስከ ባሕር ደርሳ አታውቅም” የሚል ታሪካዊ ክህደት እንደ መርሕ ይዘው ቀጠሉ።
ከ1983 በኋላ ያመለጡ ዕድሎች እና የሠላሳ ዓመቱ ቸልተኝነት
ኢትዮጵያ ወደብ-አልባ እንድትሆን የተደረገው በ1983ቱ ውሳኔ ብቻ አይደለም፤ ከዚያ በኋላም መብቷን ለማስከበር የሚያስችሉ በርካታ ዕድሎች ሆን ተብሎ እንዲባክኑ ተደርገዋል።
የአሰብ ራስ-ገዝ መዋቅር ችላ መባል፦ ደርግ ከመውደቁ በፊት ለአሰብ ልዩ የራስ-ገዝ አስተዳደር መዋቅር ዘርግቶ ነበር። ይህ መዋቅር ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላም ቢሆን የአሰብን ወደብ ሕጋዊ ባለቤትነት ለመጠየቅ እንደ አንድ ጠንካራ መሠረት ሊያገለግል ይችል ነበር። ይሁን እንጂ፣ የኢሕአዴግ መንግሥት ይህንን ዕድል ሙሉ በሙሉ ችላ በማለት ወደቡን አሳልፎ ሰጠ።
የ1990-1992ቱ ጦርነት እና ታላቁ ክህደት
በሁለቱ ሀገራት መካከል የተነሣው የድንበር ጦርነት፣ ኢትዮጵያ በኃይልም ሆነ በዲፕሎማሲ የወደብ መብቷን የምታስከብርበት ታላቅ ዕድል ተፈጥሮ ነበር። የኢትዮጵያ ሠራዊት በውጊያ መስክ የበላይነት ይዞ በነበረበት ወቅት፣ የአሰብን መግቢያ በሮች መቆጣጠር ይቻል ነበር።
የዓለም አቀፍ ሕግ ዕድል እና የአሜሪካ ፍንጭ
በወቅቱ እንደ ዶክተር ያዕቆብ ኃይለ ማርያም ያሉ ታዋቂ ዓለም አቀፍ የሕግ ባለሙያዎች በዝርዝር እንደተነተኑት እና መጽሐፋቸው ላይ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት የባሕር በር የማግኘት መብት ነበራት።
እንዲያውም፣ በወቅቱ የአሜሪካ መንግሥት ዲፕሎማቶች ሳይቀሩ ኢትዮጵያ ይህንን ሕጋዊ መብቷን በዓለም አቀፍ መድረክ እንድትጠይቅ ፍንጭ እና ዕድል ሰጥተው ነበር። ይሁን እንጂ፣ የኢሕአዴግ መሪዎች ይህንን ዕድል ለመጠቀም ፈቃደኛ አልሆኑም።
የባድመ ማደናገሪያ እና የአልጀርስ ስምምነት
የኢትዮጵያ ሠራዊት በውጊያ መስክ የበላይነት ይዞ የአሰብን በር ባንኳኳበት ወቅት፣ የወቅቱ መንግሥት የሕዝቡን ቀልብ ወደ ባድመ (የድንበር) ጉዳይ ብቻ በማዞር፣ የወደቡን ወሳኝ ጥያቄ አጠፋው።
በመጨረሻም በአልጀርስ የተፈረመው ስምምነት የኢትዮጵያን የወደብ መብት ሙሉ በሙሉ ችላ ያለ፣ የወደብ ጉዳይ ሐሳቡም እንዳይነሣ በግልጽ የተከለከለበት ባድመንም ሆነ የወደብ ዕድልን ያጣችበት “የዲፕሎማሲ ክሥረት” ሆነ።
ውጤቱ እና ዋጋው
በዚህ ተከታታይ ክህደት እና ያመለጡ ዕድሎች ምክንያት ኢትዮጵያ ለ30 ዓመታት በባሕር ንግድ ለመሳተፍ ለጎረቤት ሀገሮች (በዋናነት ለጅቡቲ) በየዓመቱ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር ክፍያ ለመክፈል ተገድዳለች።
ይህ የኢኮኖሚ ደም-ፍሰት የሀገራችንን ዕድገት ገድቧል። ከዚህም በላይ፣ የባሕር በሯን ማጣቷ የጂኦ-ፖለቲካ ተፅዕኖዋን እና የብሔራዊ ደኅንነቷን አዳክሟል።
ይህ ብቻ ሳይሆን በኢሕአዴግ አገዛዝ ዘመን ስለ ወደብ መናገርም ሆነ መጠየቅ እንደ ወንጀል ተቆጥሮ በርካታ ኢትዮጵያውያን ለብዙ ችግር ተዳርገዋል። ወደብ ከማሳጣት በላይ ሐሳቡንም ማንሣት ወንጀለኛ የሚያስብልበት ሥርዓት መፈጠሩ የዘመን ውድቀት ያደርገዋል።
የትውልዱ መነሳት እና የማይቀረው ጥያቄ
የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የሕልውና፣ የኢኮኖሚ ነጻነት እና የብሔራዊ ክብር ጉዳይ ነው። ያለፈው ትውልድ በሴራ ያሳጣውን መብት፣ የዛሬው እና የቀጣዩ ትውልድ በሰላማዊ፣ በሕጋዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ማስመለሱ የማይቀር ነው።
ኢትዮጵያውያን መብታቸውን ለማስከበር ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩ ነው። ስለሆነም፣ የኢትዮጵያ የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ መፍትሔ እስካላገኘ ድረስ፣ ትውልዱ እንቅልፉን ሊተኛ አይችልም። ይህ የትውልድ አደራ እና የሀገር ጥሪ ነው።
©️ EBC
በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ።
ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ መሰረት፣ ከሐምሌ 14 እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት አስር ቀናት ውስጥ የዝናብ ሁኔታን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች የበለጠ እየተጠናከሩ እንደሚሄዱ አሰታወቋል።
በዚህም መሰረት በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን፣ መካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ እና ምስራቅ የሀገሪቷ ክፍሎች የተሻለ የዝናብ ሥርጭት መጠን ይኖራቸዋል።
በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብና ሰሜን የሀገራችን አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል።
በተጨማሪም በመካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ፣ ምስራቅ እና ደቡብ የሀገሪቷ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያመለክታሉ ብሏል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አብዛኛዎቹ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም ነው ኢንስቲትዩቱ የጠቆመው።
በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን እና በመካከለኛው የሀገሪቷ አካባቢዎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል።
በተጨማሪም በኤሊ ዳር፣ ዱብቲ፣ ሰመራ፣ ቡሬ፣ አሳይታ፣ ሁንዱፎ፣ ገዋኔ፣ ሚሌ፣ ዳሊፋጊ፣ አይሻ፣ ጉሊና፣ አዋሽ አርባ፣ ባቲ፣ ዶሎ አዶ፣ ዳዋ፣ አሶሶ፣ ጎዴ፣ ቋራ፣ አዋሽ ፈንታሌ፣ ጭፍራ፣ ላሬ፣ መተሀራ እና፣ ላሬ፣ ፉኙዶ አካባቢዎች ከሚኖረው የቀን ከፍተኛ የፀሀይ ሀይል ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ሙቀት ይኖራቸዋል።
ኢንስቲትዩቱ በቀጣይ ቀናት የሚኖረውን መልካም አጋጣሚዎችን ለመጠቀም እና የሚጠበቁ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ለመከላከል የግብርና ሚቲዎሮሎጂ ምክር ሀሳብን ከወዲሁ መተግበር እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
©️ ኢዜአ
