fa
Feedback
Addis Ababa Water & Sewerage Authority (AAWSA)

Addis Ababa Water & Sewerage Authority (AAWSA)

رفتن به کانال در Telegram

water is life

نمایش بیشتر
3 472
مشترکین
+124 ساعت
+217 روز
+5030 روز
آرشیو پست ها
----------------------------------- መረጃዎችን ለማግኘት ሊንኪን ይጫኑ https://linktr.ee/AAWSA_Social_media
+4
----------------------------------- መረጃዎችን ለማግኘት ሊንኪን ይጫኑ https://linktr.ee/AAWSA_Social_media

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የመሰረተ ልማትና ማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አመራርና አባላት በባለስልጣኑ እየተሰሩ ያሉ መሰረተ ልማቶችን እየጎበኙ ነው። AAWSA 05/10/2018ዓ.ም

አገልግሎት ለማሻሻል

የከርሰ ምድር ውሃ ልማት ትኩረቱ ወደ ጥልቅ ውሃ አዘል የመሬት ክፍል (Deep Aquifers) ሊዞር ይገባል ሲል አንድ ጥናት አመለከተ ፡፡ በአለም ባንክ ድጋፍ ባለስልጣኑ ሲያሰራ የቆየው በከርሰ ምድር ሀብት ላይ ያተኮሩ ጥናት ተጠናቀቀ፡፡   ሰኔ 2, 2018 ዓ.ም (AAWSA)   በአዲስ አበባና አካባቢዋ ያለውን የከርሰ ምድር ውሃ ሀብት በሳይንሳዊ መንገድ ለመለየትና ለማስተዳደር በቤልጂየምና በስዊዘርላንድ አማካሪ ድርጅቶች የተካሄደው ሰፊ ጥናት ተጠናቆ ውጤቱ ዛሬ ይፋ ሆኗል። የጥናቱ ውጤት እየጨመረ የሚሄደውን የከተማዋን የመጠጥ ውሃ ፍላጎት ለማሟላት አሁን የሚተገበረው የከርሰ ምድር ውሃ አጠቃቀም አሰራር መሻሻል እንደሚገባ አመልክቶ፣ የወደፊቱ ዋና የውሃ ልማት ትኩረት ወደ ጥልቅ የውሃ አዘል የመሬት ክፍል (Deep Aquifers) ሊዞር እንደሚገባ ጠቁሟል።   የባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ዘሪሁን አባተ ለጥናቱ የገንዘብ ድጋፍ ላደረገው የዓለም ባንክ ምስጋና አቅርበው፣ የጥናቱ ግኝቶች ወደ ተግባር ሲቀየሩ ለከተማዋ የውሃ ዋስትና ጠንካራ መሠረት እንደሚጥሉ ገልጸዋል። በቀጣይም የውሃ ደረጃን በቀጣይነት መከታተል፣ የጥልቅ ውሃ አዘል የመሬት ክፍልን ማልማት እና የውሃ ሀብቱን በሳይንሳዊ መረጃ ላይ ተመስርቶ ማስተዳደር የአዲስ አበባን የወደፊት የውሃ ዋስትና ለማረጋገጥ ወሳኝ እርምጃዎች መሆናቸውን አስገንዝበዋል።   በውይይቱ ላይ የተገኙት ባለስልጣኑ የውሃና ሳኒቴሽን መሰረተ ልማት ማስፋፊያ ዲቪዥን ቴክኒካል ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ደበበ ሙለታ በበኩላቸው ጥናቱ የአዲስ አበባና ዙሪያዋን የከርሰ ምድር ውሃ ሀብት ሙሉ ምስል የሚያሳይ ሁለገብ ሥራ መሆኑን ገልጸዋል። ጥናቱ ያለውን የውሃ መጠንና ጥራት በተሻለ ሁኔታ እንዲታወቅ ከማገዙም በላይ ለወደፊት የውሃ ልማት ውሳኔዎችን በዕውቀት ላይ ተመስርተው እንዲወሰኑ መሠረት እንደሚጥል ጠቁመዋል።   የጥናቱ ውጤቶች እንደሚያሳዩት ጥልቀት የሌላቸው አኳፈሮች (Shallow Aquifers) ከአቅማቸው በላይ ጫና ላይ ሲገኙ፣ በተለይ በአቃቂ የጉድጓድ መስክ የውሃ ደረጃ መቀነስና የሃይድሮሊክ ጣልቃገብነት (Hydraulic Interference) መጨመሩ ተረጋግጧል። በመሆኑም አዳዲስ ጉድጓዶች ከመቆፈራቸው በፊት በየከርሰ ምድር ውሃ ሞዴሎች (Groundwater Models) መገምገም፣ የጉድጓድ አቀማመጥን በሳይንሳዊ መንገድ ማቀድ እና የፓምፕ አሰራሮችን ማሻሻል አስፈላጊ መሆኑ ተመክሯል። በሌላ በኩል በለገዳዲ አካባቢ አዳዲስ ጉድጓዶችን በተገቢ የጂኦሎጂ (Geology) ክፍሎች ውስጥ በመቆፈር የውሃ ምርትን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ ዕድል እንዳለ ተገልጿል። ጥናቱ ለወደፊት የት ቦታ ላይ የከርሰ ምድር ውሃ መልማት አለበት የሚለውንም በሞዴሊንጉ አስቀምጧል።   ይህ ባለሙያዎቹ ያቀረቡት የተቀናጀ የከርሰ ምድር ውሃ አስተዳደር ማዕቀፍ ከጉድጓድ ቁፋሮ እስከ የውሃ ሀብት ውሳኔ አሰጣጥ ድረስ ያሉ ሂደቶች በተቀናጀ መንገድ መመራት እንዳለባቸው አሳይቷል። የፓምፕ ሙከራዎች (Pumping Tests)፣ የመረጃ ጥራት ቁጥጥር (QA/QC)፣ የከርሰ ምድር ውሃ ሞዴሊንግ (Groundwater Modeling) እና ቀጣይ ክትትል የዘላቂ አስተዳደር መሠረታዊ ክፍሎች መሆናቸው ተጠቁሟል።

የውሃ ክፍያ ለመፈጸም

የአውሮፓ ኅብረትና አጋር ሀገራት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሒደት አደነቁ የአውሮፓ ኅብረት እና አጋር ሀገራት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አድንቋል፡፡ ምርጫውን አስመል
የአውሮፓ ኅብረትና አጋር ሀገራት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሒደት አደነቁ የአውሮፓ ኅብረት እና አጋር ሀገራት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አድንቋል፡፡ ምርጫውን አስመልክቶ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ካደረጉ የኅብረቱ አባል ሀገራትና በኢትዮጵያ የካናዳ፣ የኖርዌይ እና ስዊዘርላንድ ኤምባሲዎች የጋራ መግለጫ አውጥተዋል፡፡ ሀገራቱ በመግለጫቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ እጩዎችና የሲቪል ተቋማት ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲካሄድ ያደረጉትን አስተዋጽኦ አድንቀዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) በምርጫው ላይ ለነበራቸው የታዛቢነት ሚና እውቅና እንደሚሰጡም ሀገራቱ አረጋግጠዋል፡፡

የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የቤተሰብ ጫወታ ማጠቃለያ በፎቶ ግንቦት 17/2018 ዓ.ም (AAWSA)
+2
የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የቤተሰብ ጫወታ ማጠቃለያ በፎቶ ግንቦት 17/2018 ዓ.ም (AAWSA)