es
Feedback
Addis Ababa Water & Sewerage Authority (AAWSA)

Addis Ababa Water & Sewerage Authority (AAWSA)

Ir al canal en Telegram

water is life

Mostrar más
3 491
Suscriptores
+124 horas
+127 días
+4930 días
Archivo de publicaciones
በኢሰማኮ የበጋ ውድድር አንደኛ ዲቪዚዮን የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የእግር ኳስ ቡድን ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዋንጫ ውድድር ተጀምሯል

ለ5ኛ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ከ700 በላይ የልብ ህሙማንን በማከም ከስቃይ ያዳኑት Heart Attack Ethiopia (የኸርት አታክ ኢትዮጵያ) ፋውንዴሽን መስራቾችን እና የበጎ ፍቃድ ቡድኑን
+8
ለ5ኛ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ከ700 በላይ የልብ ህሙማንን በማከም ከስቃይ ያዳኑት Heart Attack Ethiopia (የኸርት አታክ ኢትዮጵያ) ፋውንዴሽን መስራቾችን እና የበጎ ፍቃድ ቡድኑን በጽ/ቤታችን ተቀብለናቸዋል። የኸርት አታክ ኢትዮጵያ ፋውንዴሽን እና የበጎ ፍቃድ ቡድኑ በፍቅር የምትሰጡት እጅግ የላቀ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ከልብ የሚደነቅ ነው ። በቀጣይም የህክምና ተራ እየጠበቁ ላሉ የልብ ህሙማን ፈጣን ምላሽ እንዲያገኙ በጋራ ተቀናጅተን የብዙዎችን ሕይወት ለመታደግ አብረን ለመስራት ተስማምተናል። እንደዚህ ትልቅ የህክምና ቡድን አቀናጅታችሁ ለወገኖቻችሁ ትልቅ ህይወትን የማዳን ስራ ለመተግበር የተጋችሁ መስራቾቹን እና የበጎ ፍቃድ የህክምና ቡድኑን አባላት በራሴ እና በታካሚዎች ስም ከልብ አመሰግናለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!

ተስፋችንን እንትከል!" የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በለገዳዲ አካሄደ ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም /AAWSA/ የአዲስ አበባ ውኃና ፍሳሽ ባለስልጣን አመራርና ሰራተኞች "ተስፋችንን እንትከል" በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በዛሬው ዕለት አካሂደዋል። ባለስልጣኑ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከ150 ሺህ በላይ ችግኞችን ለመትከል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ያጠናቀቀ ሲሆን፣ በዛሬው ዕለት ብቻ በለገዳዲ የውሃ መገኛ ስፍራ በተካሄደው ታላቅ ንቅናቄ ከ10,000 በላይ ችግኞች ተተክለዋል። የባለስልጣኑ የውሃ መገኛ ተፋሰሶች አስተዳደርና ጥበቃ የሥራ ሂደት መሪ አቶ ሙሉጌታ ታዬ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት፤ ቀጣይነት ያለው የውሃ አቅርቦትን ለማረጋገጥ የተፋሰስ ልማት ስራ የተቋሙ የህልውና ጉዳይ ነው በማለት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብርን የዚሁ የህልውና ጉዳይ ዋነኛ አካል በማድረግ በየዓመቱ የችግኝ ተከላና የተተከሉትን ችግኞች የመንከባከብ ስራዎች በልዩ ትኩረት እንደሚሰሩ አብራርተዋል። በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የኩራ ጅዳ ክፍለ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወንደሰን ታምሬ በበኩላቸው፤ የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ለክፍለ ከተማውና ለአካባቢው ነዋሪዎች የውሃ መሰረተ ልማትን ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ፣ በተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች፣ በትምህርት ቤቶች ግንባታና በትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ላይ በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። አቶ ወንደሰን አክለውም፣ ባለስልጣኑ በተለይም በአፈር እና ውሃ ጥበቃ ስራ ላይ የአካባቢውን ማህበረሰብ አመለካከትና ግንዛቤ በመቀየር ረገድ በርካታ የሚያስመሰግኑ የኢኒሼቲቭ ስራዎችን ማከናወኑን ጠቅሰዋል፡፡ የዛሬው የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብርም የዚሁ ጠንካራ የስራ ግንኙነት ማሳያ መሆኑን የገለጹት አቶ ወንደሰን በቀጣይም ተግባሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ባለስልጣኑ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እስካሁን 30 ሺህ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ 120 ሺህ ችግኞች በቀጣይ ቀናት በተለያዩ የውሃ መገኛ ስፍራዎች እና በፈሳሽ ማጣሪያ ጣቢያዎች ዙሪያ በዕቅዱ መሰረት የሚተከሉ ይሆናል።

የአዲስ አበባ ዘመናዊ የፍሳሽ በመስመር የአገልግሎት ሽፋን 42 በመቶ ማድረስ ተችለዋል:: ሀምሌ 8/2018 ዓ.ም (AAWSA) የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን በ2018 በጀት ዓመት በፍሳሽ ዘር
+8
የአዲስ አበባ ዘመናዊ የፍሳሽ በመስመር የአገልግሎት ሽፋን 42 በመቶ ማድረስ ተችለዋል:: ሀምሌ 8/2018 ዓ.ም (AAWSA) የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን በ2018 በጀት ዓመት በፍሳሽ ዘርፍ ያከናወናቸው ሥራዎች የከተማዋን የፍሳሽ አገልግሎት በማስፋፋትና በማሻሻል ጉልህ ውጤት አስመዝግበዋል። በአጠቃላይ የከተማዋ የፍሳሽ ሽፋን 42 በመቶ በመድረሱ፣ የበለጠ ቁጥር ያላቸው ነዋሪዎች አስተማማኝ የፍሳሽ አገልግሎት እያገኙ መሆኑን ያሳያል። በበጀት ዓመቱ 42 ሺህ ኪዩቢክ ሜትር ፍሳሽ ተጣርቶ፣ ከዚህ ውስጥ 30.38 ሺህ ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ለዳግም ጥቅም ዝግጁ ተደርጓል። የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችም በስፋት ተከናውነዋል። ከ7,400 በላይ የተዘጉ የፍሳሽ መስመሮች ተከፍተዋል፣ ከ35 ሺህ በላይ ማንሆሎች ተጽድተውና ተጠግነው ለአገልግሎት ተዘጋጅተዋል። በተጨማሪም በሕገወጥ ግንኙነቶች ላይ የተደረገው ክትትል የፍሳሽ መስመሮችን ከጎርፍ፣ ከዝናብ ውሃ እና ከሌሎች ባዕድ ነገሮች በመጠበቅ የሥርዓቱን ቅልጥፍና አሻሽሏል። በደንበኞች አገልግሎትም 17,681 አዳዲስ ደንበኞች ወደ ቢል ሲስተም ሲካተቱ፣ ከ44 ሺህ በላይ ደንበኞችን በመድረስ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ ተከናውኗል። በማጣሪያ ጣቢያዎች የተጣራው ውሃም በተደረገ የላቦራቶሪ ምርመራ በታችኛው ተፋሰስ ላይ ምንም አይነት ጉዳት የማያደርስ እና ለግብርና እና አረንጓዴ ልማት መልሶ ለመጠቀም ምቹ መሆኑ ተመላክቷል። የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የፍሳሽ ዘርፍ ሀላፊ ኢንጂነር አለማየሁ መንግስቱ፣ የዘርፉ ሥራ ከፍተኛ ትጋትና መስዋዕትነት የሚጠይቅ በመሆኑ ለዘርፉ ሠራተኞች እውቅና ሰጥተው፣ በቀጣይም የመሠረተ ልማት ማስፋፋት፣ የአገልግሎት ጥራትን ማሻሻልና የደንበኞችን እርካታ ማሳደግ የዘርፉ ቀዳሚ ትኩረቶች እንደሚሆኑ ገልጸዋል

We had a discussion with the Project Manager about the micro tunneling technology works. Stay tuned for more updates.👇 AAWSA, July 8/2018 E.C

የውሃ መሰረተ ልማትን በተመለከተ በ2013 በጀት አመት ማብቂያ የውሃ ምርት አቅም 570,000 ሜትር ኪዩብ/በቀን የነበረ ሲሆን የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ እና ወደ ስርጭት በማስገባት የምርት
+4
የውሃ መሰረተ ልማትን በተመለከተ በ2013 በጀት አመት ማብቂያ የውሃ ምርት አቅም 570,000 ሜትር ኪዩብ/በቀን የነበረ ሲሆን የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ እና ወደ ስርጭት በማስገባት የምርት አቅማችንን ወደ 850,000 ሜትር ኪዩብ/በቀን ማድረስ ተችሏል። ከዚህም ተጨማሪ በቀን 280,000 ሜትር ኪዩብ ውሃ የማምርት አቅም ተፈጥሯል። የዘመናዊ ፍሳሽ ማስወገድ ስርአትን የማሻሻል ስራዎችን በተመለከተ ከዚህ ቀደም ከነበረበት 36 በሞቶ ወደ 42 በሞቶ ማድረስ ተችሏል። ከዚህ ቀደም በከተማችን የነበረው ፍሳሽ ማጣሪያ አንድ ብቻ ሲሆን፣ በአሁኑ ጊዜ ወደ 44 ማጣሪያዎች ማድረስ ተችሏል፡፡ የለገዳዲን የውሃ ግድብን በመጠገን እና በማሻሻል ግድቡ ለተጨማሪ 50 አመታት እንዲያገለግል የማስቻል ስራ ተሰርቷል። የከተማዋን የውኃ አቅርቦት ሽፋን በበጀት ዓመቱ ማብቂያ በቀን በ60 ሺህ ሜ.ኩብ ለማሳደግ በቁጥር እስከ 20 የሚደርሱ አዳዲስ ጉድጓዶች በመቆፈርና ወደ ስርጭት በማስገባት በቀን 60,000 ሜ.ኩብ ውሃ መጨመር ችለናል። በተመሳሳይ 100ሺህ ሜ.ኩብ ውኃ ማምረት ከሚያስችለው የጭቋላ ዌል ፊልድ የውሃ ልማት ፕሮጀክት ጋር ተያይዞ የተቆፈሩ ጉድጓዶችን ወደ ስርጭት ለማስገባት የግንባታ ሥራውን 30 በሞቶ ማድረስ ተችሏል። በሌላ በኩል ከገጸ ምደር ውሃ ልማት አንጻር በቀን እስከ 73 ሺህ ሜ.ኩብ ውሃ መስጠት የሚያስችለው የገርቢ መጠጥ ውሃ ግድብ ግንባታ ተጀምሯል፡፡ በአጠቃላይ ባለፉት አምስት አመታት አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትን ከ6ዐ በመቶ በላይ ያሳደግን ሲሆን፣ የዘመናዊ የፍሳሽ አወጋገድና የፍሳሽ ማጣራት ስርአትንም በከፍተኛ ደረጃ አድጓዋል፡፡ ከንቲባ አዳነች አቤቤ