ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
رفتن به کانال در Telegram
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
نمایش بیشتر3 306
مشترکین
-224 ساعت
-107 روز
-3830 روز
آرشیو پست ها
📖#አንቀጸ_ብርሃን_ትርጓሜ📖
#ቅዱስ_ኤፍሬም_ሶርያዊ ቅዱሳት መጻሕፍትን እንዲህ ገልጿቸው ነበር ✍️"ቅዱሳት መጻሕፍት ተቀድቶ እንደማያልቅ ጥልቅ የውኃ ጉድጓድ ናቸው፡፡ ማንም : ሰው : የፈለገውንና የቻለውን ያህል ጠጥቶ መርካትና ቀድቶ መውሰድ ይችላል፣ የውኃ ጉድጓዱን ግን አይጨርሰውም። ከእርሱ በኋላ የሚመጡ ሌሎችም እንዲሁ መጠጣትና መቅዳት ይችላሉ፡፡ የቀደመው ለኋለኛው፤ ያም ከእርሱ በኋላ ለሚመጣው አይጨርስበትም፡፡"
.. ይህም ማለት ቅዱሳት መጻሕፍትን ሊቃውንት በየዘመናቱ ይመሰጡባቸዋል፤ ይመገቧቸዋል፤ ይተረጕሟቸዋል፣ ያም ሆኖ ግን እነርሱ የተገለጠላቸውንና የቻሉትን ያህል ተረድተውና አስረድተው ያልፋሉ እንጂ ምሥጢሩን ግን አይጨርሱትም።
#መምህራችን መምህር ኃይለ ማርያም ዘውዱ እስከ ዛሬ ሐሳቡ ሳይፍታታና ሳይተረጐም በገጸ ንባብ ብቻ የነበረውን አንቀጸ ብርሃን የተባለውን የቅዱስ ያሬድን ድርሰት በአንድምታ ትርጓሜ ተርጉመው አቅርበውልናል።
#የኔታ ኃይለ ማርያም ዘውዱ በዚህ የጀመረው አስተማሪ የሆኑ ሌሎች መጻሕፍትንም ብዕራቸው ወደፊትም እንደሚያስነብበን ተስፋ በማድረግ፤ እርሳቸውን እንዲጠብቅልን እኛንም #አንብበን እንድንጠቀም #እግዚአብሔር ይርዳን እላለሁ፡፡
#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL ,በEMS እንዲሁም የ delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
https://t.me/GhionBookStore1623
❝እውነተኛ ፍቅር ማለት መቀበል ሳይሹ መስጠት መቻል ነው!❞
ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
#ስለ_እርሱ_አንብቡ
እግዚአብሔር በአሳባችሁ ውስጥ እንዲኖር ስለ እርሱ አብዝታችሁ #አንብቡ ።
እርሱን ለማወቅ ስለ እርሱ #አንብቡ ። እርሱን ካላወቃችሁት እንዴት እርሱን ልትወዱት ትችላላችሁ ?
ስለ እርሱ #አንብቡ ፤ ስታነቡ ግን በሳይንሳዊ ወይም በፍልስፍና ጠባይ አታንብቡ ወይም ደግሞ ስለ እርሱ ጥናታዊ ጽሑፍ ወይም ትምህርት ለመስጠት አታንብቡ ። ነገር ግን ወደ እርሱ ጥልቀት ለመግባት ወይም እርሱ ወደ እናንተ ጥልቀት እንዲገባ #አንብቡ። ለነፍሳችሁ ውድ የሆኑትን የእርሱን ባሕርያት ለማወቅ ስትሉ #አንብቡ ይህ እውቀት አሳባችሁ ከእርሱ ጋር እንዲጣበቅና ፍቅሩ ከእናንተ ልብ ጋር እንዲቀናጅ ያደርግላችኋልና ። ስለ ስምምነቱ ስትሉም #አንብቡ ። ከወደዱት ሰዎች ጋር ስላለው ግንኙነት በጠላቶቹ ላይ ስላለው አቋም ስትሉ #አንብቡ !
እግዚአብሔር ቸር እንደ ሆነ ቀምሳችሁ ታዩ ዘንድ ስለ እርሱ #አንብቡ ። ታዲያ ንባባችሁ ለልባችሁ ምግብ እንዲሆን እንጂ እንዲሁ ተራ ንባብ እንዲሆን አትፍቀዱ ።
ስለ እግዚአብሔር ብዙ ካነበባችሁ በእርሱ ዘንድ ያለውን ፍጹምነት በሙሉ ታገኛላችሁ ።
ከወደዳችሁት ስለ እርሱ ማንበባችሁን ትቀጥላላችሁ ። እግዚአብሔር ስለ እርሱ የሚያነቡትን ስለ እርሱ ዜና የሚጠይቁትን ከእርሱ ታሪኮች መካከል አንዱን ለማወቅ የሚናፍቁትንና እርሱን የሚያደንቁትን ሰዎች ይወዳቸዋል ። ስለ እርሱ ከመጽሐፍ ቅዱስ ወይም ከአባቶች ብሒሎች ወይም ከቤተክርስቲያንና ከቅዱሳን ታሪክ ልታነቡ ትችላላችሁ ። በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ የእግዚአብሔር እጅ ለመዳሰስ ስትሞክሩ በጥበቡ በኃይሉና በርኅራኄው ውስጥ እንደምትወዱት ታውቃላችሁ ።
#አቡነ_ሺኖዳ_ሳልሳዊ
✨📖 #ወንጌል_ቅዱስ ✨📖
.....፱/ ወእመኒ ዐይንከ ታስሕተከ ምልሓ ወግድፋ እምላዕሌከ፤
ዓይንህ ብታስትህ አውጥተህ ጣላት፡፡
እስመ ይኄይሰከ ነቋረከ ትባእ ውስተ ሕይወት እምእንዘ ክልኤ ዐይን ብከ ትትወደይ ውስተ እሳተ ገሃነም፡፡
➮ዛሬ በዚህ _ ዓለም ሁነህ ኑረህ፤ ኋላ ገሃነም ከምት ወርድ፤ ዛሬ በዚህ ዓለም አንድ ": ዓይን ሁነህ ኑረህ ኋላ መንግሥተ ሰማያት ብትገባ ይሻለሃልና፡፡
#አንድም ወእመኒ ዓይንከ ብለህ ሁሉ ንም አንብብ፡፡➮#የነቀፍከውን ኤጲስ
ቆጶስ ሹመህ ኑረህ ኋላ ገሃነም ከምትወርድ ፤
ዛሬ በዚህ ዓለምየነቀፍከውን ኤጲስ ቆጶስ ሽረህ ያልነቀፍከውን ኤጲስ ቆጶስ ሹመህ ኑረህ ኋላ መንግሥተ ሰማያት ብትገባ ይሻልሃልና፡፡
፲ ዑቁ ኢታስተሐቅርዎ ለአሐዱ እምእሉ ንዑሳን፤
➮#በእኔ ካመኑ ከምእመናን አንዱን አትናቁ አታቃሉ እንዳትንቁእንዳታቃልሉ አስተውሉ፡፡
#የማቴዎስ_ወንጌል_ከምዕራፍ_፲፰
✨ወንጌላችንን እንዲህ አንድ በአንድ እስከ ትርጓሜው ማወቅ ግድ ነው !ከቀድሞ አባቶች ሲተረጎም የመጣው ንባቡና ትርጓሜው በአንድምታ አድርገው ለአይን ጎላ ባለ ና ለንባብ ደግሞ በቀለም የተለየ ና በምቹ ኹኔታ ያቀረቡልልን #መጋቢ ሐዲስ ቃለ ሕይወትን እያመሰገንን እጅግ ወሳኝ በመኾኑ ባያመልጠን መልካም ነው እንላለን!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL ,በEMS እንዲሁም የ delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
https://t.me/GhionBookStore1623
በምድርም በሰማይም ሽማግሌ
በአካለ ሥጋ ሳሉ የወንድማማች ደም እንዳይፈስ ያስታረቁ ሽማግሌ
በሰማይም ከ፳፬ቱ ሽማግሌዎች ገብተው የተቆጠሩ ሽማግሌ
የአባታችን በረከት ትደርብን!
በሕይወታችን ውስጥ ሁለቱ ወሳኝ ነገሮች ትእግስት እና ጊዜ ናቸው። እያንዳንዱ መጥፎ እድል በትእግስት ይረታል። ጊዜም የማይጠቅም የድንጋይ ከሰል ቅሪትን ወደ ዲያመንድ የመቀየር ኃይል እንዳለው ሁሉ የእኛንም ሕይወት መስመር ለማስያዝ ወሳኝ ነገር ነው።
ዛሬ ላይ የሚሰማን ህመም ነገ ላይ ለምንኖረው ሕይወት ጥንካሬ ነው። የሚያጋጥመንን እያንዳንዱ ፈተና በትክክል ከተጠቀምንበት ጥሩ የመለወጥ እድል ይፈጥርልናል።
ሰርድዮን
"ንባብ በሕይወታችን ውስጥ የሚመጡ ውጣ ውረዶችን እንደ አመጣጣቸው በትዕግስትና በፅናት እንድናልፍ የሚረዳን መሳሪያ ነው። ባነበብን ቁጥር ብዙ እናውቃለን። ብዙ ባወቅን ቁጥር የተሻሉ ነገሮች ወደ ሕይወታችን ይመጣሉ።......" ኅብር ከበረደድ ገዳሙ እሸቴ♥️😍
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL ,በEMS እንዲሁም የ delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
https://t.me/GhionBookStore1623
እመቤታችን በደብረ ምጥማቅ እንደተገለጠች እንዲሁ በጎደለ ነገራችን ሁሉ በመገለጥ ተዓምሯን ታድርግልን።
የሚፈርደው:- ዐረገ፣ በአብ ቀኝ ተቀመጠ።
✨#አሐቲ_ድንግል ✨
【ለ5ተኛ ጊዜ ታትማለች】
#ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን እመቤታችን ያስተበፅዑኒ ኩሉ ትውልድ" ብላ ከተናገረችላቸው አንዱ ናቸው። ይሄ መጽሐፍ በትውፊት የምናወርሰው፥ ነገር ግን እያየነው የተደረሰ አዲሱ አርጋኖን ነው። ከእኔ ጋራ የተወለደውን የመጻሕፍት ንጉሥ ታዩ ዘንድ ኑ!
#ሊቀ_ሊቃውንት_ስምዐ_ኮነ_መልአክ_የ፬ቱ_ጉባኤያተ_መጻሕፍት_ምስክር_መምህር
“#አሐቲ_ድንግል" የተባለው ይህ የርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን መጽሐፍ ቤተ ክርስቲያናችን ስለእመቤታችን ያላትን አስተምህሮ በሥርዓተ አምልኮዋ ውስጥ እመቤታችን ያላትን ቦታ እና ቅዱሳን ስለእርሷ እንዴት እንዳስተማሩ እና እንዴት እንዳመሰገኗት ማወቅ የሚፈልግ ሁሉ ይህ መጽሐፍ በእጂጉ ያስፈልገዋል።
#ዲያቆን_ብርሃኑ_አድማስ
#ይህች አሐቲ ድንግል የተሰኘችው መጽሐፍ ስለ ብቸኛዋ ድንግል የተጻፈች ብቸኛዋ የመጽሐፍት ንግስት ናት!#አንባቢን ከንባብ ጸሐፊን ከክታብ አያናውጽብን እያልን እጅግ አስፈላጊ መኾኑ እርግጥ ስለኾነ ይህች ብቸኛዋ መጽሐፍ #ለ5ተኛ ጊዜ ታትማለችና እነኾ ሳታልቅ እንቃመሳት።
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL ,በEMS እንዲሁም የ delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
https://t.me/GhionBookStore1623
📖#ሐተታ_ዘቅዱስ_አትናቴዎስ
#ያለሀሰት ቅዱስ አትናቴዎስ ለቤተክርስትያን አምድ ከምንላቸው ቅዱሳን አባቶቻችን አንዱና ዋነኛው መኾኑ አያጠያይቅም ታድድያ ከእርሱ ግሩማን አበርክቶዎች መካከል "ተስእሎተ አንትያኮስ" የተሰኘውን መጽሐፍ #መምህር_ቃለ ጽድቅ_ሕግነህ በተዋበ እና ለንባብ ምቹ አድርገው የተረጎሙት ሲኾን ➱ቅዱስ አትናቴዎስ በዚህ መጽሐፍ ከሚመልሳቸው ጥያቄዎች .....
➮አንትያኮስ፡ ርኩሳን መናፍስት የሆኑ አጋንንት ከቅዱሳት መጻሕፍት የሚፈሩት የጸሎት ዐይነት የቱ ነው?
➮ጥያቄ ፦ በውኑ ለኃጥአን ነፍሳት በዚህ ዓለም ዘመዶቻቸው የመታሰቢያ(ተዝካር) ቍርባን፣ ጸሎትና ምጽዋት ቢያደርጉላቸው በዚያኛው ዓለም ይጠቅማቸዋልን?
➮ጥያቄ ፦ ለሰው እጅ ሥራዎች እንዳንሰግድ እግዚአብሔር በነቢያቱ አዝዞናልና ለምን የሰው እጅ ለሠራው ለቅዱሳን ሥዕልና ለቅዱስ መስቀሉ እንሰግዳለን?
➮አንትያኮስ፡- ከኃጢአት ሁሉ የሚበልጠው ኃጢአት የቱ ነው?
➮አንትያኮስ፡- ብዙ በደልንና ኃጢአትን የሠራ ሰው ቢኖር ከዚያም በኋላ ንስሓ ቢገባ፤ እንደገና ተመልሶ ኃጢአት ቢሠራ እግዚአብሔር ንስሓውን ይቀበለዋልን ወይስ አይቀበለውም?
#ይህንና መሰል ጥያቄዎችን ከነ መልሶቻቸው የያዘ ልዩ መጽሐፍ በመኾኑ እንድታነቡት ግብዣችን ነው!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL ,በEMS እንዲሁም የ delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
https://t.me/GhionBookStore1623
📖#ሐተታ_ዘቅዱስ_አትናቴዎስ
#ያለሀሰት ቅዱስ አትናቴዎስ ለቤተክርስትያን አምድ ከምንላቸው ቅዱሳን አባቶቻችን አንዱና ዋነኛው መኾኑ አያጠያይቅም ታድድያ ከእርሱ ግሩማን አበርክቶዎች መካከል "ተስእሎተ አንትያኮስ" የተሰኘውን መጽሐፍ #መምህር_ቃለ ጽድቅ_ሕግነህ በተዋበ እና ለንባብ ምቹ አድርገው የተረጎሙት ሲኾን ➱ቅዱስ አትናቴዎስ በዚህ መጽሐፍ ከሚመልሳቸው ጥያቄዎች .....
➮አንትያኮስ፡ ርኩሳን መናፍስት የሆኑ አጋንንት ከቅዱሳት መጻሕፍት የሚፈሩት የጸሎት ዐይነት የቱ ነው?
➮ጥያቄ ፦ በውኑ ለኃጥአን ነፍሳት በዚህ ዓለም ዘመዶቻቸው የመታሰቢያ(ተዝካር) ቍርባን፣ ጸሎትና ምጽዋት ቢያደርጉላቸው በዚያኛው ዓለም ይጠቅማቸዋልን?
➮ጥያቄ ፦ ለሰው እጅ ሥራዎች እንዳንሰግድ እግዚአብሔር በነቢያቱ አዝዞናልና ለምን የሰው እጅ ለሠራው ለቅዱሳን ሥዕልና ለቅዱስ መስቀሉ እንሰግዳለን?
➮አንትያኮስ፡- ከኃጢአት ሁሉ የሚበልጠው ኃጢአት የቱ ነው?
➮አንትያኮስ፡- ብዙ በደልንና ኃጢአትን የሠራ ሰው ቢኖር ከዚያም በኋላ ንስሓ ቢገባ፤ እንደገና ተመልሶ ኃጢአት ቢሠራ እግዚአብሔር ንስሓውን ይቀበለዋልን ወይስ አይቀበለውም?
#ይህንና መሰል ጥያቄዎችን ከነ መልሶቻቸው የያዘ ልዩ መጽሐፍ በመኾኑ እንድታነቡት ግብዣችን ነው!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL ,በEMS እንዲሁም የ delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
https://t.me/GhionBookStore1623
Facebook
https://www.facebook.com/share/12Jna5uDZaj/
ግልጸኝነት እና ክርስትና።
"የማይገለጥ የተከደነ የማይታወቅም የተሰወረ ምንም የለምና።በጨለማ የምነግራችሁን በብርሃን ተናገሩ፤ በጆሮም የምትሰሙትን በሰገነት ላይ ስበኩ።"ማቴ.፲፥፳፮ እንዳለ የማይገለጥ ሥውር የማይታወቅ ኅቡዕ የለም።
እግዚአብሔር በባሕርዩ ሥውር ረቂቅ ቢሆንም በሥራው ግን የተገለጸ ነው።
በሥውር ለሚጠይቁት ለሚለምኑትም በግልጽ ዋጋቸውን የሚከፍል አምላክ ነው።
’’አንተ ግን ምጽዋትን ስታደርግ ምጽዋትህ በስውር እንዲሆን ቀኝህ የምትሠራውን ግራህ አትወቅ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል።’’ ማቴ.፮፥፬ እንዲል
ግልጽነት እውነተኝት ነው።
የክርስትና ሕይወት የተገለጸ እውነት ነው።
በዚህ እውነት የሚኖሩ ሰዎቹም ግልጸኞች እውነተኞች ናቸው።
ብዙ ጊዜ ግልጽነት የጎደላቸው ነገሮች ለክፉ ነገር ይዳርጋሉ።
ለክፉ እየዳረጉ ያሉት
ይህ ሲባል ግን የንስሓ፣የሀገር ምስጢር የለም ማለት አይደለም።
ያ እንደተጠበቀ ሆኖ ሰው በሚገባው ነገር ግልጽ መሆን መቻል የመንፈሳዊነት መርህ ነው።
ሥውርነት ግን አርአያ ያለመሆን ምልክት ነው።
በእውነተኛት የምሠራው ትሩፋት ተሠውረን እንኳን ብንሠራው የተገለጸ እውነት ነው።
"እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ፤በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም።"ማቴ.፭፥፲፬ እንዲል።
📖#ትምህርት_በእንተ_ምክንያተ_ሐውልታት📖
.....ገብረ እግዚአብሔር ኪደን የማመሰግነው ይህን ሊቅ በራሳችን ቋንቋና ዘይቤ ዳግም እንዳውቀው ስላደረገኝ ነው፡፡ የትርጓሜው ወደረኛ ቋንቋና ውበት ሊቁን የራሳችን ትውፊትና የሕይወት ዘይቤ አካል አድርገን እንድንቈጥር ይጠቁመናል ሳይኾን ያስገድደናል፤ እኔ ተገድጄበታለሁ!
➮ይህን መጽሐፍ አንብቦ ትውፊቱን ከጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ለማነጻጸር፣ ሕይወቱን፣ ነባራዊውን የአገራችንን አኗኗር፣ የአገሩን ካህናት አገራዊ ሚና፣ ክርስቲያናዊ ምግባሩን ... ለመፈተሸ የማይገደድ አንባቢ ካለ ከሸንጎ ፊት ያቅርበኝ!በማለት የመጽሐፉን ግሩምነት የመሰከሩት #ደብተራና የሕግ ባለሞያ የኾኑት በአማን ነጸረ እኛም አንብበን ተጠቃሚዎች እነኾን ዘንድ ብሎም ራሳችንን እንድንፈትሽበት ያሳሰቡ ሲኾን #በግዮን_መጻሕፍት ደግሞ በልዩ ቅናሽ የተዘጋጀ ሲሆን ግዜ ሳንሰጥ መጽፏን ገዝተን ብንመገባት መልካም ነው እንላለን!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL ,በEMS እንዲሁም የ delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
https://t.me/GhionBookStore1623
Facebook
https://www.facebook.com/share/12Jna5uDZaj/
#ተክለ ሃይማኖት፦ ሊሰወር የማይችል የተራራ ላይ መብራት! ማቴ 5፤14
.
➮ተክለ ሃይማኖት የዓለም ብርሃን፤ ኢየሱስን ለዓለሙ ገልጦ ያሳየ!
.
➮ተክለ ሃይማኖት የዓለም ብርሃን፤ የኢየሱስን ወንጌል የሰበከ!
.
➮ተክለ ሃይማኖት የዓለም ብርሃን፤ በዙዎችን ወደ ክርስቶስና ወደ መንግሥቱ ያፈለሰ!
.
➮ተክለ ሃይማኖት የዓለም ብርሃን፤ ስለክርስቶስ ፍቅር ዓለሙንና በዓለሙ ያለውን ሁሉ ትቶ ክርስቶስን በመከተል አርዐያችንና ምሳሌያችን!
➱ተክለ ሃይማኖት የዓለም ብርሃን፤ በዙዎችን ከአምልኮተ ጣዖት ወደ አምልኮተ ክርስቶስ የመለሰ!
.
➮ተክለ ሃይማኖት የዓለም ብርሃን፤ መልካሙን ሥራውን አይተን የሰማዩን አባታችንን ያከበርንበትና የተከተልንበት የመቅረዝ ላይ መብራት!!!
.
🥀🥀🥀🥀🥀🥀#ዛሬ_ክርስቶሳዊ_የሚሆን_የተክለ_ሃይማኖት_ፍልሰተ_አፅሙ ነው!#እንደ_ተክለ_ሃይማኖት_ያለ_የመቅረዝ_ላይ_መብራት_እንሆን_ዘንድ_ቅድስት-ጸሎቱ_ትርዳን_ከበዓሉም_መንፈሳዊ_ሀብትና_በረከትን_ይክፈለን!!!
.
➱ተክለ ሃይማኖት በምግባርና በሃይማኖት ለወለዳችሁ ክርስቶሳውያን ሁሉ በመንፈሳዊነትና የክርስቶስን ፍቅር በማሰብ የሚደረግ በዓለ ፍልሰት ይሁንላችሁ!!!
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
እስኪ ንገሩኝ! ከእናንተ መካከል ከመዝሙረ ዳዊት ውስጥ አንዲትዋን ምዕራፍ ወይም ከሌላው የቅዱሳት መጻህፍት ክፍል ውስጥ ጥቂት በቃልህ ድገም ቢባል ይህን ማድረግ የሚችል ማን ነው? አንድ ሰውስ እንኳ አይገኝም።
የሚያሳዝነው ነገር ግን ይኼ ብቻ አይደለም። ከመንፈሳዊ ነገሮች አንፃር እንደዚህ አእምሮ የጎደላችሁ ኾናችሁ ሳለ ዲያቢሎሳዊ በኾኑ ነገሮች ላይ ግን ከእሳት በላይ ኀያላን ናችሁ። እንዲህም በመኾናችሁ አንድ ሰው መጥቶ ዲያቢሎሳዊ ዘፈኖችንና የዝሙት ዜማዎችን ንገሩኝ ቢላችሁ ከእናንተ መካከል እነዚህን የሚያውቁና ደስ ተሰኝተው የሚደግሟቸው ብዙ ሰዎችን ያገኛል።
ነገር ግን"ለምንድን ነው እንደዚህ የምትኾኑት?" ተብላችሁ ስትጠየቁ የምትመልሱትስ መልስ ምን የሚል ነው? "እኔ ከመነኮሳት አንዱ አይደለሁም። ሚስት አለቺኝ፣ልጆችም አሉኝ፣የቤተሰብ መሪ ነኝ" የሚል ምክንያት ታቀርባላችሁ። ለምን እንደዚህ ትላላችሁ? ከመነኮሳቱ ይልቅ ይበልጥ ማንበብ ያለባችሁ እናንተ ኾናችሁ ሳለ ብዙዎች እንዲጠፉ ያደረገው "ቅዱሳት መፃህፍትን ማንበብ ለመነኮሳት ብቻ ነው" የሚለው አመለካከታችሁ ነው። ይበልጥ ብዙ መድኃኒት የሚያስፈልጋቸው በማእከለ ዓለም የሚኖሩትና ዕለት ዕለትም መንፈሳዊ ቁስል የሚያገኛቸው ሰዎች ናቸውና። ስለዚህም ከለማንበባችሁም በላይ" የእኛ ማንበብ ትረፍ ነገር ነው" ብላችሁ ማሰባችሁ በራሱ የዲያብሎስ አሳብ ነው። ወይስ ንዑድ ክቡር የሚኾን ጳውሎስ "ዝንቱ ኵሉ ተጽሕፈ ለተግሣጸ ዚአነ - ይህም ኹሉ እኛን ሊገስጸን ተፃፈ"(1ኛ ቆሮ 10:11) ያለውን አላዳመጣችሁምን?
ቅዱስ ዮሀንስ አፈወርቅ
💦#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት
📖📖📖📖📖
#በእንተ_ክህነት
......መንጋው በደኅና ኹኔታ እያለና በጥሩ ምግብና ላይ ሳለ የጥበቃውን ኃላፊነት ብወስድና ከዚያ በኋላ ግን በእኔ【ካህን ኾኜ በራሴ 】 አላዋቂነትና ጥበብ የለሽነት ምክንያት ባጠፋቸው እነርሱን ለማዳንና ለመቤዠት ሲል ራሱን የሰጠላቸውን እግዚአብሔርን በራሌ ላይ አነሣሣዋለሁ ብዬ እፈራለሁ፡፡
➮ከመጽሐፉ የተወሰደ
#ስለመጋቢ /ስለ ካህን በጥልቀት የሚያትተው ይህ ግሩም መጽሐፍ በድጋሚ በውብ ኹኔታ ታትሟል!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL ,በEMS እንዲሁም የ delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
https://t.me/GhionBookStore1623
Facebook
https://www.facebook.com/share/12Jna5uDZaj/
💦#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት
📖📖📖
#ውዳሴ_ጳውሎስ
#መግቦተ_እግዚአብሔር
.......በእርግጥ የሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ መጽሐፍ የግድ ሊኖረን እንደሚገባ ግልጽ ነው። #ታድያ ለረጅም ጊዜ ገበያ ላይ ጠፍተው የነበሩ እነዚህ ግሩማን መጻሕፍት እነኾ በድጋሚ የታተሙ መኾናቸውን እያበሰርን ለእናንተ ለውድ አፍቃርያነ ንባብ ቤተሰቦቻችን በልዩ ቅናሽ አቅርበናልና ሳያልቅ ተቋደሷት እያልን እናሳስባለን ።
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL ,በEMS እንዲሁም የ delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
https://t.me/GhionBookStore1623
Facebook
https://www.facebook.com/share/12Jna5uDZaj/
📖ኆኅተ ስብከት ፩እና ፪
የግድ ሊኖረን የሚገባ መጽሐፍ‼
እስኪ በወፍ በረር ላስቃኛችኹ..
‹‹ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ›› ሲባል
➮አንድም ዐይነ ልቡናችሁን ወደ ወንጌል እግረ ነፍሳችሁን ወደ መንግሥተ ሰማያት አቅኑ ማለት ነው።
➮አንድም#ወደ_እመቤታችን_ተመለሱ_ሲል_ነው፦#እመቤታችን_አማናዊት ኢየሩሳሌም ትባላለች፤ አፈ በረከት ቅዱስ ኤፍሬም ‹‹ዛቲ ይእቲ ኢየሩሳሌም ሀገሮሙ ለነቢያት ወማኅደረ ፍሥሐሆሙ ለኵሎሙ ቅዱሳን᎓᎓ ደስ ብሏቸው የሚኖሩ የቅዱሳን የነቢያት የሐዋርያት የጻድቃን የሰማዕታት የመላእክት የማደሪያቸው ማደሪያ የኾነች የነቢያት ሀገረ ትንቢታቸው ይህቺ ኢየሩሳሌም እመቤታችን ናት::›› ሲል መስክሯል፡፡ ኢየሩሳሌም ማለት ሀገረ ሰላም ማለት ነው᎓᎓ ቅዱስ ያሬድ #እመቤታችንን ሀገረ ሰላም ይላታል ‹‹ይትፌሣሕ ልብኪ ኦ ድንግል ወይትሌዓል ቀርንኪ በክብር ሰማይ ዳግሚት ብኪ ድኅነ ዓለም ወበወልድኪ ኮነ ሰላም:: ድንግል ሆይ ልብሽ ደስ ይበለው፤ መንግሥትነትሽም በክብር ከፍ ከፍ ይበል፤ ሁለተኛ ሰማይ ሆይ ባንቺ ዓለም ዳነ በልጅሽም ሰላም ሆነ።›› በማለት የዓለም ድኅነት የሰላም መገኛ ምክንያት መሆኗን ሊቁ መስክሯል። ዳግመኛም ‹‹እምጽዮን ነበበ እምኢየሩሳሌም ቃሎ ወሀበ ከመ ይመጽእ ንጉሥ ዘስሙ አማኑኤል ዘውእቱ አምላክ ቡሩክ ለዓለም አስተርአየ ገሃደ በማኅበረ ቅዱሳን፡፡ ስሙ አማኑኤል የሆነ ንጉሥ እንደሚመጣ ከጽዮን ሆኖ ተናገረ፤ ከኢየሩሳሌምም ቃሉን ሰጠ፤ ይኸውም ለዘለዓለም የተመሰገነ አምላክ በቅዱሳን ማኅበር ተገለጠ ተመሰገነ፡፡›› ሲል ከአማናዊቷ ኢየሩሳሌም ከእመቤታችን አካላዊ ቃል እግዚአብሔር ተወልዶ ሰላምን እንደሰጠን ተናግሯል:: የሐዋ ፫ ፲ ፳
#ከመጽሐፉ_የተቀነጨበ
📚#ግዮን_መጻሕፍት
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
https://t.me/GhionBookStore1623
ውድ አንባብያን በጥያቄያችኩ መሰረት እነኾ.....
📖 #888
✍️.......የ አ ፣ በ ፣ ገ ፣ ደ ቀመረ ፊደልን፣ በተመከተ ይኽ፣ መጽሐፍ ያዘጋጁ #መጋቢ_ሐዲስ_ዶክተር_ሮዳስ ታደሰ ፤ ጠለቅ ያለ ጥናት፣ መሠት ባደርገ ጽሑፋዊ ዝግጅታቸው መሮነት ፤ የአንባብያንን ሕዋስ አእምሮ እየፈለፈሉ፤ የጥናታዊ አጻጻፍ ጥበብ በኣት ለማድረግ አዘውትረው እየጣሩ እደኾነ ከዝግጅታቸው ምስጢራዊ ትንታኔ ለመገንዘብ ችያለኹ።
#መምህር_ዐምደወርቅ_እስጢፋኖስ
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL ,በEMS እንዲሁም የ delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
https://t.me/GhionBookStore1623
Facebook
https://www.facebook.com/share/12Jna5uDZaj/
አንዱ ለሌላው መትረፍ፦
በክርስትና ዓለም የምናስተምረው ትምህርት እና የምንኖረው ሕይወት ለራስ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም መትረፍ መቻል አለበት።
የአንዱ መኖር ለሌላዌ ሰው ክብሩ ጥቅሙ የመዳን ምክንያቱ ሊሆን ይገባዋል።
ብዙዎች የእግዚአብሔር ሕግጋቶች የሚፈጸሙት ለሌላ ሰው በሚደረግ ቸርነት ላይ ነው እንጂ ለራስ ብቻ በሚደረጉ ተግባሮች አይደለም።
ስለዚህ፦
፦ለሰው የሚተርፍ ትምህርት እና አኗኗራችን ሌላውነሰ በእውነተኛነቱ እና በአሳማኝነቱ መሳብ አለበት፣
፦በድካም ያሉትን ሌሎችን ማጽናት መቻል አለበት፣
፦በውስጣዊና በውጫዊ ችግራቸው መስቀል እንዲሸከሙ ማገዝ መቻል አለበት፣
፦ሌሎችን የሚያረክስ ሳይሆን ምክንያተ ቅድስና ሁኖ የሚቀደስ መሆን አለበት፣
፦በጎችን ከበረቱ የሚያጠፋ ሳይሆን መጠበቅ መቻል አለበት፣
፦ከጉባኤው የሚያወጣ የሚለያይ ሳይሆን አንድ ማድረግ መቻል አለበት፣
፦በጸጋ በክብር አድገው ወደ አምላካቸው ፊት በሞገሥ እንዲቀርቡ መሸኘት መቻል አለበት፣....
ለሌሎች የሚተርፍ ሕይወት የወንጌላዊ ሕይወት ነው።
ለሌሎች የማይተርፍ ግላዊ ሕይወት ግን የራስ ወዳድነት መገለጫ ነው።
የምንኖረው ሕይወት እና የማስተምረው ትምህርት ከየትኛው ይመደባል?
ግላዊ ነው? ኅብረታዊ ነው?
ትክክለኛውም የመዳን ጸጋ የሚገኘው ለሌሎች በምናደርገው የሕግ ፍጻሜ ሱታፌ ነው።
ከምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
