ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
رفتن به کانال در Telegram
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
نمایش بیشتر3 306
مشترکین
-224 ساعت
-107 روز
-3830 روز
آرشیو پست ها
✨አዲሱን #ብርህት_ዓይን የተሰኘውን መጽሐፍ አስገብተናል
ስለ መጽሐፉ የተሰጠ አስተያየት
#ብርህት_ዐይን ፡ የተሰኘው መጽሐፍ ጊዜ የማይገድበው የነገረ መለኮት ማስተዋሎችን በማቅረብ በቅዱስ ኤፍሬም አእምሮ /ልቡና/ እና በዚህ ዘመን በሚገኙ አማኞች መካከል እንዳለ ድልድይ ሆኖ ያገለግላል።
... ስከዚህ፡ የብርህት ዐይን፣ መጽሐፍ ወደ አማርኛ ቋኝቋ መተርጎሙ ፡ በአሁን ጊዜ በኢትዮጵያ ካሉት ምእመናን፡ የቤተ ክርስቲያ፣ አባቶች መፈሳዊ እይታ ለማስተዋወቅ የሚረዳ ፡ #በዲያቆን_ሕሊና_በለጠ የተበረከተ ጉልህ የኾነ አስተዋጽዖ ነው :: ለዚህ ድካሙም እውነተኛና ከልብ የመነጨ ምስጋና ይገባዋ ።
#ቀሲስ ዶክተር ጆሊ ኮብ
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
https://t.me/GhionBookStore1623
Facebook
https://www.facebook.com/share/12Jna5uDZaj/
የፍጥረት ሁሉ ደስታ - ልደታ ለማርያም
ግንቦት አንድ ቀን የእመቤታችን የንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ልደት ስለሆነ የደስታችን ቀን ነው፡፡ የቀደሙ አባቶቻችን ሁሉ በፍጹም ደስታ ያሳለፉት ቀን ነው፡፡
የልደቷ ቀን የሐና የደስታ ዕለት ነበር፤ "አንች ያልወለድሽ መካን ሆይ ደስ ይበልሸ የሚለውን ቃል ሰምታበታለችና" /ኢሳ 54፤1/፡፡ የልደቷ ቀን የኢያቄም የደስታ ዕለት ነበር፡፡ ከዕሴይ ግንደ በትር ይወጣል /ኢሳ 11፤1/ የሚለው ቃለ ነቢይ በውድ ልጁ ሲፈጸምና በበትሩ ሠራዊተ አጋንንትን ሲርቁ አይቷልና፡፡
በእርሷ ልደት ነቢያት ሁሉ ተደስተዋል፡፡ ትንቢታቸው ፍጻሜ ሲደርስ ፤ የንባባቸው መንፈሰ ሲገለጥ፣ ሕግ ለጸጋ፣ ኦሪት ለወንጌል ሊያስረክቡ፣ ነገደ ሌዊ ሊቀ ካህንነቱን ለነገደ ይሁዳ ሊያስረክብ ሲሰላለፉ አይተዋልና፡፡ የእርሷ ልደት የያዕቆብ ፍጹም ደስታ ነበረ፡፡ በሕልሙ ከመሬት እስከ ሰማይ ተዘርግታ ያያት መሰላል በእውን ከምድር ወደ ላይ በቅድስና ስትደርስ ለማየት በቅቷልና፡፡ ራስዋ ላይ እግዚአብሔር የተቀመጠባት እውነተኛዋ መሰላላችን በርግጥም ድንግል ማርያም ናት፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ የሴት ሁሉ ራስ ወንድ ነው/1ኛ ቆሮ 11፤1/ አለ፡፡ የእርሷ ራስ ግን ያዕቆብ እንዳየው እግዚአብሔር ነው፡፡ ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆንልኛል ያለችው ቅዱስ ጳውሎስ የሴት ሁሉ ራሰ ያለው ወንድ በእርሷ ዘንድ ስላልነበረ ነውና፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ይህን ልዩ መሆኗን ስለሚያውቅ አንቺ ከሴቶች ሁሉ ተለይተሸ የተባረክሽ ነሺ፤ ጸጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ፤ ጽንስሽም እንደ ሌሎቹ ሴቶች አይደለም እያለ ሲሰግድላትና ሲያመሰግናት እርሱን አልፋ ለእግዚአብሔር መቀመጫ ዙፋን ማደሪያ መቅደስ መሆኗን ያየው አባታችን ያዕቆብ በእውነት ደስ አለው፡፡
እንኳን አደረሰን!
#ዜና ድጋሚ ኅትመት
📖የሐዋርያት ሲኖዶስ📖
ሐዋርያት በኢየሩሳሌም በጽርሓ ጽዮን ተሰብሰበው ሳሉ ለሚሰሟቸውና ለሚከተሏቸው ይህን ሥርዐት ሠሩ። ከአይሁድና ከአሕዛብም ሁሉ በእጃቸው በእግዚአብሔር አመኑ። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥራቸው ሁሉ በሰጣቸው ተስፋ መሠረክ በሃምሳኛው ቀን በጽርሐ ጽዮን በላያቸው ላይ የወረ መንፈስ ቅዱስ ጥበብ ሆኗቸዋልና የሚፈቀደውንም ሁሉ ልብ እንዲሉ አድርጓቸዋልና ዓለምን ሁሉ ሥርዐት አስያዙት።
(ግጽው ፶፫)
_አጲስ ቆጶስ ከክርስቶስ ወታደርነት ራሱን ይጥል ዘንድ ማዕርጉንም ያጎድል ዘንድ አይገባውም። ከመኰንንነት ሥራ በማንኛውም ላይ አይሾም። የሚሻለውና የሚያምረው ወደ ቤተክርስቲያን መግባቱ ነው እንጂ። ወደ መኳንንት ሥራ መግባትን ከመረጠና ወደ ምድራውያን ጭፍራዎች ከገባ እና የሰማያዊ ንጉሥ ወታደርነትን ከተወ ሹመቱን ይተዋት። እግዚአብሔር ለሁለት ጌታ መገዛት የሚችል ዓለም ይላልና። አንዱን ያስቆጣል፣ ሌላውንም ያስደስታል።
ቀኖና ፸፮ (ቀኖና በእንተ ኤጲስ ቆጶስ።)
ከምእመናን መካከል ዝሙት በማብዛት የወደቀ ካለ ይህም የዘወትር ልማድ ቢሆን ወይም ግብረ ሰዶም የሚፈጽም ሰው ቢኖር፣ ይህ ፍትወት የተዋረደ ተግባር ነው። ከሴቶችም ግብራቸው እንደዚህ የሆነ፣ ሌሎችም እንደዚሁ ዐይነት ግብር ያላቸው ካሉ፣ በሕግ መጽሐፍ ጣዖት አምልኮት ነው ከተባለው ከመዳራትና ከማመንዘር የተነሣ ስለ ነፍሱና ስለ ንስሓው ልቅሶ ያብዛ። ከክህነት መዓርግ በየትኛውም አይሾም። ይህን ካበዛ በመልካም ነገርም ንስሓ ከገባ ይቀበሉት።
(አብጥሊስ ፶፯)
አሑድ የዕረፍት ቀን የሆነችበት ምክንያት እግዚአብሔር ሥራውን የጀመረባት ቀን እንደ ሆነች እንድናውቅ ነው። በዚች ቀን ፍጥረቱን ፈጠረ። በችሎታውም ከፍ ከፍ አደረጋት፡ የዕላታት መጀመሪያና ጥንት አደረጋት: ለክርስቶስ ሥራም የመጀመሪያ አደረጋት። ኦሪት መርሕ ናት፣ ወንጌልም ለአዲስ ሕዝብ አዲስ መንፈሳዊ ዕለት ናት፣ ለዓለም ሕይወትም ቀዳሚና ጥንቱ ናት። ለከፍታው የተመረጠች ዕለት: ለቃሉ ሥልጣንም የብርሃን ዕለት አደረጋት። ለፍጥረቱ ሕይወትም የሕይወት ዕለት አደረጋት: የትንሣኤው ቀንም ዕለተ እሑድ ናት። የፍጥረት ዘመን የመጀመሪያ ዕለት እንደ ሆነች የኋለኛ ዘመን የመጀመሪያ ዕለት ናት የአዲሱ ሕግና ኪዳን የመጀመሪያዋ ዕለት ናት፡ ፍርድና ኩነኔ ያለባት የኋለኛው ዘመንም እንደዚሁ የመጀመሪያ ናት። እግዚአብሔር በሰማይ ብርሃንን ፈጠረባት፣ እርሱም የሚያበራ ፀሐይ ነው። በኋላም ብርሃንን ፈጠረባት። በዓለም ውስጥም ብርሃንን አሳየባት። አስቀድሞ በፈጠረው ማረፊያ አደረጋት። ዕለተ እሑድንም ከጨለማ በኋላ በፈጠረው በብርሃን ፋንታ አደረጋት። ቀን አደረጋት። ሕያዋን ለሆኑት ለንቁዎችም መኖሪያ አደረጋት። ይህች ዕለት ጌታችን ከሙታን ተለይቶ የነሣባት ዕለት ናት። በምድር ላይም ብርሃንን አሳየ። ለአዲስ ሕዝብም አዲስ ብርሃን አሳወቀ። ለክርስቲያኖችም ሕግንና ብርሃንን ገለጠ።
(ቀዳማይ ሲኖዶስ ዘስምዖን ቀነናዊ ቊ. ፲፬)
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
+ + +
ቅድስት ድንግል ማርያም፡ በምስጋናዋም ቤዛችን ናት።
ምንም እንኳ፡ እግዚአብሔር፡ እንደቸርነቱ፡ የጻድቃንን ምስጋና፡ በየዘመናቱ ሲቀበል የኖረ ቢኾንም፡ በሥጋም፥ በነፍስም፥ በልቦናም ከኃጢአት ንጹሕ ኾና፡ እግዚአብሔር ጥንቱንም ከፍጡር ሲፈልግ የነበረውን ዓይነት እንከን የለሽ የምስጋና መሥዋዕት ያቀረበች ግን፡ ቅድስት ድንግል ማርያም ናት።
"ነፍሴ እግዚአብሔርን ታላቅ ታደርገዋለች (ታከብረዋለች)፤ መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሓሴት ታደርጋለች" ያለችው (ሉቃ 1:46)፡ ይኽን ታላቅ እውነታ ስታመለክት እንጂ...
ዛሬ አፋቸውን የሚያላቅቁባት መ*ና*ፍ*ቃን በእባቡ መንፈስ እየተመሩ "በመንፈስ እንደሚገነደሱት"፥ ወይም ከዓለማዊ ዘፈኖች በተኮረጁ የዘፍሙር ዜማዎች አቅላቸውን ሲስቱ በሞቅታ እንደሚናገሩት፡ ድንገት በስሜት ተመርታ የተናገረችው አይደለም።
ቅድስት ድንግል ማርያም፡ በተፈጠርንበት ዋና ዓላማ (ምስጋና) በኩል፡ ለእኛ ምትክ (ቤዛ) ኾና የምስጋናን መሥዋዕት ባትሠዋ ኖሮ፡ የሰው ልጆች፡ ገና ፍጹም የኾነ ምሥጋና ለእግዚአብሔር በማቅረብ ረገድ፡ ባለዕዳዎች ኾነን እንቀር ነበር።
ስለዚህ፡ በምስጋናዋም ቤዛችን ናት። ሰዎች ቀርተው፡ መላእክት እንኳ በአዲስ ምስጋና እንዲያመሰግኑና ክብር እንዲጨመርላቸውም ምክንያት ናት።
"ድንግል ሆይ! የሱራፌል የዕጣናቸው ጽንሐሕ፥ የኪሩቤልም የምስጋና መቅጃ የወርቅ መጥለቂያ፥ የትጉሃን የሰማይ መላእክት ኹሉ የቅዳሴያቸው ነቅዕ፡፡ የማይተኙትም የውዳሴያቸው ፈልፈል ምንጭ" እንዳላት ሊቁ አባ ጊዮርጊስ (የኀሙስ አርጋኖን 8፥3)።
ከዚያም አልፎ፡ በምስጋና በኩል፡ ከፍጡራን ኹሉ ልዩ መብት አላት። አምላኳን "ልጄ" ብሎ ማመስገን፡ ለርሷ ብቻ እንጂ፡ ለሌላ አልተሰጠምና። ለወደፊትም አይሰጥም።
እንኳን ለ84ኛው የኢትዮጵያ አርበኞች ድል መታሰቢያ በዓል አደረሳችሁ!
✨🙏 ክብርና ምስጋና ውድ የሕይወት ዋጋ ከፍለው አገር ላቆዩልን አርበኞች!
"የክርስቶስ ቤዛነት ይህ ነው፦ እርሱ ስለተሸከማቸው ዘግናኝ ሕማሞች እና ኃጢኣቶች እስካሁን ድረስ ያለማቋረጥ ይናገራል። ኃጢኣት የማያውቀውን እርሱን እግዚአብሔር አብ ስለእኛ ሲል 'ኃጢኣት እንዲሆን' አደረገው። አመንዝራው፣ ስድ ሆኖ የሚበድለው፣ ቆሻሻ በሆኑ ተግባራት አረንቋ ውስጥ የሚዛቅጠው እና ኃፍረት አልባ በሆኑ ተግባራት የሚበላሸው ሁሉ ከክርስቶስ ሲሸሽ ድምጹ በኋላው ይከተለዋል። ይኸውም 'የተወደድህ ልጅ ሆይ፥ ና! ኃጢኣቶችህ ከእኔ ጋር ናቸው፤' እያለ የሚጣራ የእግዚአብሔር ልጅ ደም ነው! ገና የሠራሃቸው ዕለት ነው በምልዓት የተሸከምኳቸው። ካሣውን ከፍያለሁ፦ ሐፍረት ተጭኖብኛል፤ ተገርፌያለሁ፤ ደቅቄያለሁ፤ ተሰቅያለሁ፤ እንዲሁም መርገምን ተሸክሜያለሁ። ለአንተ የይቅርታ እና የንጽሕና ተግባራትን እንዲሁም ይገባኛል የምትልበትን ጸጋ አዘጋጅቼልሃለሁ። ና! ለአንተ መከራ የተቀበልኩትን ያህል በአንተ ደስ ይለኝ ዘንድ ና! የመዳንን ዘውድ እደፋልህ ዘንድ፣ ፍቅሬን እና መንፈስ ቅዱስን በአንተ ላይ አፈስስ ዘንድ፣ እንዲህ አድርጌ ወደ አባቴ አቀርብህ ዘንድ ና! አንተ ከበጎቼ ሁሉ እጅግ ውዱ ነህ፤ እኔ ደሜን እስከመክፈል ደርሼ ከፍ ያለ ዋጋ ሰጥቼሃለሁና።"
***
የክርስቶስ ስሞች፣ ገጽ 135-36።
ይህን ምሥጢር የሆነ መሐፍ እንድታነቡት ግብዣችን ነው።
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
ብፁዕ አቡነ እንድርያስ
በሊቃውንቱ የዝክረ ኒቅያ ጉባኤ መካተቻ ሲናገሩ "እመቤታችን ማርያም ቤዛዊተ ዓለም አትባልም ማለት ሕገ ወጥ ስብከት ነው። መስመር የሌለው፣ በቤተ ክርስቲያን በመላው ኢትዮጵያ ተነግሮ የማያውቅ ነው" ብለዋል።
ሲያጨበጭቡላቸውም ተግሣጻቸው ሥልጣን አለው።
📖#ነገረ_ማርያም_በአዲስ_ኪዳን
#ስለ መጽሐፉ የሊቃውንት አስተያየት
ደራስያንን አኽለኽ መስለኽ፡ ኹነኽ በመተርጉም ጸጋ መንፈስ ቅዱስ የተቸረኽ ወንድማችን መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ ይኽነን መጽሐፍኽን በሰከነ፣ በተሰበሰበ አእምሮ ተመልክቼዋለኍ። በእውነት ያለምንም ማጋነን እንደነ ቅዱስ ቄርሎስ፣ ቅዱስ ኤፍሬም፡ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ፡ አባ ሕርያቆስ _ወዘተርፈ መንፈስ ቅዱስ ስዉር ለኾነ ምስጢረ ሥጋዌ የጥበብ መሣሪያ አድርጉኻል እላለኍ። የመጻሕፍተ ብሉያት ወሐዲሳት መድኀኒቱ ምስጢር ለጠፋባቸው ሕሙማን መናፍቃን ስፔሻል ዶክተር(ሐኪም) ወይም የዘመናችን ሉቃስ ኾነኻቸዋል፡፡ ወንድማችን ሰይጣናዊ ቅናት ካሰከራቸው ፈተና ይጠብቅኽ፡፡ ድንቅ ነው!
#መጋቤ ሐዲስ ደጉ ዓለም ካሳ
[የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሐዲስ ኪዳን መምህር]
💦#ውድ_አንባብያን፦ ለተወሰነ ጊዜ ከአይናችን ቢሰወር በናፍቆቱ ተቃጥለን መድረሻ አጥተን የባዘንን እንዳለን አይዘነጌ ነው።ለምን ጉዳዩ፦ #የንግስቷ_የእናታችን_የእመቤታችን ነገር ስለኾነ ሊያውም እንዲህ የተመረመረ ብሎም እመቤታችን ላይ ለሚነሱ ለበዙ ጥያቄዎች አሳማኝ ምላሾችን ያጨቀ መኾኑ የማያከራክር መጽሐፍ መኾኑን አለመመስከር ስለማይቻል። እኛም ድጋሚ መታተሙን እያበሰርን በልዩ ቅናሽ አዘጋጅተንላችኋል ።
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
ታላቅ ምልክት በሰማይ!
ወዳጄ የታደልህ ከኾንህ ድንግል ማርያምን በምድርም በሰማይም በከበረው ክብሯ በታላቅ ግርማዋ ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች ባለ ሥልጣኗ ታያታለህ።
ፍቁረ እግዚእ ቅዱስ ዮሐንስን ተመልከት። ንግሥቲቱን በቀራንዮ ዐደባባይ በንጉሡ በስተቀኝ ቆማ ሳለች ተቀበላት። ለካ በመከራ ጊዜ ታጽናናው ዘንድ ነበረ።
ፍጥሞ በግዞት ላይ ሳለ በልዩ ግርማ እና ሥልጣን ፀሐይን ተጎናጽፋ ተገለጠችለት። "ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮቿ በታች ያላት በራሷም ላይ የዐሥራ ኹለት ከዋክብት አክሊል የተቀዳጀች አንዲት ሴት ነበረች" እንዲል። ራዕይ ፲፪: ፩።
ያ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት የወርቅ መጎናጸፊያ ተሸፋፍና ያያታል። መዝ ፵፬: ፱። ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ ፀሐይን ተጎናጽፋ። ነቢየ ልዑል ኢሳይያስ "እግዚአብሔር ምልክትን ይሰጣችኋል" ይልላታል። ወዲህም ፍቁረ እግዚእ ቅዱስ ዮሐንስ "ታላቅ ምልክት" ይላታል።
ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ "አንዲት ድንግል" እያለ ከፍ ያደርጋታል። ሉቃ ፩: ፳፮። የጌታ ወዳጅ ቅዱስ ዮሐንስም "አንዲት ሴት" እያለ ይተባበረዋል። ከኹሉም በላይ አምላኩ ኢየሱስ ክርስቶስ በቃና ዘገሊሊ "አንቺ ሴት" ማለቱን ተከትሎ የክብር አጠራር መኾኑን ተረድቶ ይኸው ቅዱስ ዮሐንስ በራዕዩ "አንዲት ሴት" ሲላት ታገኛታለህ።
አባታችን ቀዳማዊው አዳም እንደተረጎመልን ሴት ማለት አጥንትሽ ከአጥንቴ ሥጋሽ ከሥጋዬ ማለት ነውና (ዘፍ ፪: ፳፫።) - ዳግማዊ አዳም ኢየሱስ ክርስቶስ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ ኾኗልና ኦ ብእሲቶ አላት። (ዮሐ ፪: ፬።)
ቅዱሳት መጻሕፍት ብሉያትና ሐዲሳት እንዲህ ይተባበሩላታል። ታላቅ ምልክት ናትና። እኛም እንጅ ምልክታችንን አናስነካም።
ሠናይ ነው መቼስ!!!
ሰላም ለከ
በእንተ ሃይማኖት ርትዕት ነፍሰ ዚአከ ትሜጡ፣
ጊዮርጊስ ዕፍረት ዘእጹብ ሴጡ፣
ገበርተ አፈው እምይጽዕጡ።
ሰላም ለከ
ሥነ ቆምከ በቀልት ጊዮርጊስ ሰማዕት፣
ታሕቴከ ያጸሉ አዕዋፈ ገነት፣
እለ ለብሱ ልብሰ ጥምቀት።
ሰላም ለከ
ያፈቅረከ ልብየ ወአኮ አፉየ፣
ኢታስትት አባ ማኅሌትየ፣
ተወኪፈከ ሀበኒ ዐስብየ፣
ለነዳይ ጊዮርጊስ ወርቅየ።
እንኳን አደረሳችሁ!!!
ቡርክት እና ቡሩክ
መንፈስ ቅዱስ ያደረባቸው የእግዚአብሔር ሰዎች በእመቤታችን እና በጌታችን መካከል ያለው ልዩነት በአንድ ቃል እያመሰገኑም ቢኾን መቼም አይምታታባቸውም።
ቅድስት ኤልሳቤጥን ምስክር እንጥራ። እመቤታችንን ቡርክት ባለችበት ጌታችንን ቡሩክ ብላዋለች። የሰው ስሕተት ነው ብለን እንዳንደነግጥ ይኽን ያናገራት መንፈስ ቅዱስ ነው።
"በታላቅ ድምፅም ጮኻ እንዲህ አለች፦ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፥ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው" እንዲል። ሉቃ ፩: ፵፪።
እንግዲህ በመንፈስ ቅዱስ የምትመራው ቤተ ክርስቲያን ቃላትን በየዐውዳቸው እንተርጉማቸው የምትለው ለዚህ ነው። መንፈስ ቅዱስን የሚከራከር (የሰደበ) ደግሞ ሥርየት የለውም ተብሏልና እየተጠነቀቅን። ማቴ ፲፪: ፴፩።
እመቤታችንን ቤዛዊተ ኲሉ ዓለም ስንል እና ኢየሱስ ክርስቶስን ቤዛ ኲሉ ዓለም ስንል አብነታችን መንፈስ ቅዱስ ነው!
መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችንን "ቡርክት" እያለ ነው ያመሰገናት። ሉቃ ፩: ፳፰። ለምን? የመጣው ከእግዚአብሔር ተልኮ ነዋ።
ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ "ቡሩክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር" እየተባለ ተመስግኗል። ማቴ ፳፩: ፱። እግዚአብሔር አብም ቡሩክ ተብሏል። "የቡሩክ ልጅ አንተ ነህን?" እንዲል። ማር ፲፬: ፷፩።
ልጇን በእግዚአብሔርነቱ እርሷን በወላዲተ አምላክነቷ እናመሰግናለን። መንፈስ ቅዱስ የወደደውን እንወድዳለን። የገለጠውንም እንቀበላለን።
ሠናይ ነው መቼስ!!!
📖#ታኦዶኮስ
©በመምህረ መምህራን በጽሐ ዓለሙ
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
❝.....በጎንደር መንበረ መንግሥት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን የዐራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት የትርጓሜ መምህር የሆኑት የሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ ደቀ መዝሙርና የጉባኤ ቤቱ ምክትል መምህር በሆኑት በመምህር በጽሐ ዐለሙ ታኦዶኮስ በሚል ርእስ የተዘጋጀው ይህ መጽሐፍ አማኞችን ሳይቀር ለሚያነታርከው እመቤታችን ጥንተ አብሶ አለባት የለባትም ለሚለው ጥያቄ ከቤተ ክርስቲያናችን ነባር ኣስተምህሮ አንጻር መልስ የሚሰጥ ግሩም መጽሐፍ ነው፡፡
.... ወደፊት በጽሑፍ ልትጠቅሙን የምትመኙ ሁሉ ወደፊት ለምትሠሩት ሥራ ቢያንስ እንደ አንድ መክፈቻ የሆነውንና ሌሎቹንም ጥያቄዎች በአስተማማኝነት ለመመለስ ብልሃትንና መንገድን የሚያሳየውን ይህን ድንቅ መጽሐፍ አንብባችሁ እንድትጠቀሙ በታላቅ ትሕትና ስጋብዛችሁ ከአነበባችሁ በኋላ በምታገኙት ትንሽ የማይባል ጥቅም የምትደሰቱት ደስታ እንደሚኖር በመተማመን ጭምር ነው፡፡
#ብርሃኑ አድማስ (ዲያቆን፣ በሥነ ድርሳን ሁለተኛ ዲግሪ)
⩩እንደ እውነቱ የእናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ነገር የማይሸነቁጠው አማኝ [ኦርቶዶክሳዊ ] አለ ለማለት ያስቸግራል ለዚህም የልብን የሚያደርስ መጽሐፍ እነሆ ያሉንን የኔታ በጽሐ አለሙን ያኑርልንንን እያልን መጽሐፏን ሁላችንም አንብበን እናተርፍበት ዘንድ መጽሐፉን #በግዮን መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል ።
# ግዮን መጻሕፍት ለመላው ከሀገር ውጪ እና ሀገር ውስጥ ለምትገኙ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የ Delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623
📖#ታኦዶኮስ
©በመምህረ መምህራን በጽሐ ዓለሙ
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
❝.....በጎንደር መንበረ መንግሥት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን የዐራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት የትርጓሜ መምህር የሆኑት የሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ ደቀ መዝሙርና የጉባኤ ቤቱ ምክትል መምህር በሆኑት በመምህር በጽሐ ዐለሙ ታኦዶኮስ በሚል ርእስ የተዘጋጀው ይህ መጽሐፍ አማኞችን ሳይቀር ለሚያነታርከው እመቤታችን ጥንተ አብሶ አለባት የለባትም ለሚለው ጥያቄ ከቤተ ክርስቲያናችን ነባር ኣስተምህሮ አንጻር መልስ የሚሰጥ ግሩም መጽሐፍ ነው፡፡
.... ወደፊት በጽሑፍ ልትጠቅሙን የምትመኙ ሁሉ ወደፊት ለምትሠሩት ሥራ ቢያንስ እንደ አንድ መክፈቻ የሆነውንና ሌሎቹንም ጥያቄዎች በአስተማማኝነት ለመመለስ ብልሃትንና መንገድን የሚያሳየውን ይህን ድንቅ መጽሐፍ አንብባችሁ እንድትጠቀሙ በታላቅ ትሕትና ስጋብዛችሁ ከአነበባችሁ በኋላ በምታገኙት ትንሽ የማይባል ጥቅም የምትደሰቱት ደስታ እንደሚኖር በመተማመን ጭምር ነው፡፡
#ብርሃኑ አድማስ (ዲያቆን፣ በሥነ ድርሳን ሁለተኛ ዲግሪ)
⩩እንደ እውነቱ የእናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ነገር የማይሸነቁጠው አማኝ [ኦርቶዶክሳዊ ] አለ ለማለት ያስቸግራል ለዚህም የልብን የሚያደርስ መጽሐፍ እነሆ ያሉንን የኔታ በጽሐ አለሙን ያኑርልንንን እያልን መጽሐፏን ሁላችንም አንብበን እናተርፍበት ዘንድ መጽሐፉን #በግዮን መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል ።
# ግዮን መጻሕፍት ለመላው ከሀገር ውጪ እና ሀገር ውስጥ ለምትገኙ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የ Delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623
📖#ነገረ_ማርያም_በአዲስ_ኪዳን
#ስለ መጽሐፉ የሊቃውንት አስተያየት
ደራስያንን አኽለኽ መስለኽ፡ ኹነኽ በመተርጉም ጸጋ መንፈስ ቅዱስ የተቸረኽ ወንድማችን መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ ይኽነን መጽሐፍኽን በሰከነ፣ በተሰበሰበ አእምሮ ተመልክቼዋለኍ። በእውነት ያለምንም ማጋነን እንደነ ቅዱስ ቄርሎስ፣ ቅዱስ ኤፍሬም፡ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ፡ አባ ሕርያቆስ _ወዘተርፈ መንፈስ ቅዱስ ስዉር ለኾነ ምስጢረ ሥጋዌ የጥበብ መሣሪያ አድርጉኻል እላለኍ። የመጻሕፍተ ብሉያት ወሐዲሳት መድኀኒቱ ምስጢር ለጠፋባቸው ሕሙማን መናፍቃን ስፔሻል ዶክተር(ሐኪም) ወይም የዘመናችን ሉቃስ ኾነኻቸዋል፡፡ ወንድማችን ሰይጣናዊ ቅናት ካሰከራቸው ፈተና ይጠብቅኽ፡፡ ድንቅ ነው!
#መጋቤ ሐዲስ ደጉ ዓለም ካሳ
[የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሐዲስ ኪዳን መምህር]
💦#ውድ_አንባብያን፦ ለተወሰነ ጊዜ ከአይናችን ቢሰወር በናፍቆቱ ተቃጥለን መድረሻ አጥተን የባዘንን እንዳለን አይዘነጌ ነው።ለምን ጉዳዩ፦ #የንግስቷ_የእናታችን_የእመቤታችን ነገር ስለኾነ ሊያውም እንዲህ የተመረመረ ብሎም እመቤታችን ላይ ለሚነሱ ለበዙ ጥያቄዎች አሳማኝ ምላሾችን ያጨቀ መኾኑ የማያከራክር መጽሐፍ መኾኑን አለመመስከር ስለማይቻል። እኛም ድጋሚ መታተሙን እያበሰርን በልዩ ቅናሽ አዘጋጅተንላችኋል ።
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
"ማርያም ሆይ! ስለዚህ እንወድሻለን ከፍ ከፍም እናደርግሻለን፤ እውነተኛ የጽድቅ መብል እና እውነተኛ የሕይወት መጠጥ የሆነውን ወልደሽልናልና።"
***
ቅዳሴ ማርያም
📖#ምሥጢረ_ሥነ_ፍጥረት📖
እግዚአብሔር የሥራው ሁሉ መጀመሪያ ያደረገው ፍጥረትን መፍጠር ነው ስለዚህም የዕውቀት መጀመሪያው አምላክ በ፩ ቀን የፈጠረውን ፳፪ ፍጥረት ማወቅ ስለሚቀድም መ/ር ዲበኵሉ በዚህ መጽሐፍ አምላክ በከሀሊነቱ ፍጥረትን እንዴት እንደ ፈጠረ የፈጠረው ፍጥረትም ለያንዳንዱ የረቀቀ ምሥጢር እንዴት እንዳለው እንዲሁም ፬ ባሕርያትና ጠባያት አንድ የሚሆኑበትንና የሚለዩበትን እንዴት እንደተነተኑት አስደናቂ ምሥጢር ሁኖ አግኝቼዋለሁ።
፪ኛ በሌላ በኩል ይህ መጽሐፍ ለስነ ፈለክ ተመራማሪዎች ሳይንቲስቶች ለአዲስ ምርምር በር ከፋች ነው፤ የዓለም ሳይንቲስቶች ሁል ጊዜም ስለሚመራመሩት የፍጥረታት ምሥጢር ስለፀሐይና ጨረቃ ክዋክብት, ካልዕ ፍጥረት ስለሚባሉም ሥውራን ፍጡራን በሚገርም ሁኔታ ያስረዳል፣ በተለይ እንዳንድ የስነ ፈለክ ተመራማሪዎች ባለማወቅ ሳይንስ ቀዳማዊ ነው እምነት ደኅራዊ ነው እያሉ ለሚያስቡት መልሱ ይህ ነው:: ምክንያቱም አምላክ ዓለምን ካለመኖር አምጥቶ ከፈጠረ በኋላ ዓለም ላይ በተፈጠሩ ፍጥረታት ምርምር ተጀምሯልና፡፡
፫ኛ የዚህ መጽሐፍ ይዘቱ ሁሉንም አንባቢዎች ከመንፈሳውያን እስክዓለማውያን ለሳይንንቲስቶች ተመራማሪዎች ሁሉ ማዕከል ያደረገ በመሆኑ የፍጥረታትንም ረቂቅ ምሥጢር አጕልቶ አስፍቶ የያዘ በመሆኑ ሁሉም ሰው ቢያነበውና ቢማርበት ትውልድን የሚቀርፅ እጅግ በጣም ጥሩ መጽሐፍ ነው ብዬ አምናለሁ
መ/ር ቸሬ ሲሳይ መኰንን
የወልድያ የዩንቨርስቲ መምህርና ተመራማሪ
📚ግዮን መጻሕፍት መደብር ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
ለበለጠ መረጃ፦በ0913083816 ይደውሉ።
t.me/GhionBookStore1623
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
